Temari Podcast - ተማሪ ፖድካስት


Гео и язык канала: Эфиопия, Английский
Категория: Образование


የዩቲዩብ ቻናላችን መቀላቀል አትርሱ 👇👇👇
https://youtube.com/@temari_podcast?si=--vADFvenliwbocx

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Английский
Категория
Образование
Статистика
Фильтр публикаций


#ASTU

አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን አስመርቋል።

የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ትምህርት ቤት፣ ቅድመ-መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ የአካሚክ ሠረተኞች መኖሪያ ህንጻ፣ ባለ አራት ወለል የታደሰ የንግድ ማዕከል ህንጻ እና የሠረተኞች መዝናኛ ላውንጅ የተመረቁ ፕሮጀክቶች መሆናቸው ተገልጿል።

ዕድሳት ተደርጎባቸውና ተገንብተው የተመረቁት ፕሮጀክቶች፥ የትምህርት ጥራትን ለማምጣት እንዲሁም የተቋሙን ሠራተኞች እርካታ ለማምጣት ያግዛሉ ተብሏል።

ዩኒቨርሲቲው የዳታ ማዕከል፣ የምርምር ፓርክ እና ዘርፈ-ብዙ አገልግሎት የሚሰጥ አዳራሽ ግንባታዎች እያከናወነ መሆኑ ተጠቁሟል።

@Temari_podcast


#MoE

በሰኔ 2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ዕጩ ተመራቂዎች የፋይዳ መታወቂያ ሊያወጡ ይገባል። - ትምህርት ሚኒስቴር

የካቲት 21/2017 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተፈርሞ ለሁሉም የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተላከ ሰርኩላር፤ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪ እና የሠራተኞችን መረጃ በተደራጀ መልኩ ለመያዝ ጠቀሜታ እንዳለው ይገልጻል።

የሀገር አቀፍ ፈተናዎችን ደህንነት ለማስጠበቅ አስፈላጊ መሆኑንም ያትታል።

በዚህም በሰኔ 2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ዕጩ ተመራቂዎች ፈተናውን ለመውሰድ የፋይዳ መታወቂያ ሊያወጡ እንደሚገባ አሳስቧል።

@Temari_podcast




በ2017 Entrance ፈተና ላይ ከ 10ኛ እና 11ኛ ክፍል የሚካተቱ ምዕራፎች / Common Units for grade 10 and 11 for entrance👇👇👇

https://youtu.be/qqOW0KAFVyI


"የ2017 የት/ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሁሉም ተማሪዎች በተማሩበት ስርዓተ ትምህርት ይዘት ይዘጋጃል፡፡" - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

የ2017 የት/ዘመን ተፈታኝ ተማሪዎች ከ9ኛ-10ኛ በነባሩ ስርዓተ ትምህርት፣ ከ11ኛ-12ኛ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት እንዲሁም ለስርዓተ ትምህርት የሙከራ ትግበራ በናሙናነት ተመርጠው የተሳተፉ ትምህርት ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች 10ኛ ከፍልን በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት የተማሩ መሆናቸውን አገልግሎቱ ገልጿል፡፡

በአማራ ክልል በፀጥታ ችግር ምክንያት በ2016 የት/ዘመን ሳይፈተኑ የቀሩና የ11ኛ ክፍልን በነባሩ ስርዓተ ትምህርት የተማሩ ትምህርት ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች በ2017 የት/ዘመን የሚፈተኑም አሉ፡፡

በመሆኑም በ2017 የት/ዘመን የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና "ከላይ የተገለፁትን ነባራዊ ሁኔታዎች ከግምት ውስጥ ባስገባና ሁሉንም ተፈታኝ ተማሪዎች በማከለ መንገድ በመዘጋጀት ላይ ይገኛል" ብሏል አገልግሎቱ።


የፈተና ዝግጅቱ:
1. ከ9ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከነባሩ ስርዓተ ትምህርት፣

2. ከ10ኛ ክፍል በነባሩ እና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ተመሳሳይ ይዘቶች፣

3. ከ11ኛ ከፍል በነባሩ እና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ተመሳሳይ ይዘቶች፣

4. ከ12ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት የሚዘጋጅ ይሆናል።

የኢኮኖሚክስ ትምህርት በአዲሱ ስራአተ ትምህርት የተጀመረ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በ12ኛ ክፍል ይዘት ላይ ብቻ ተመስርቶ ይዘጋጃል ተብሏል።

@Temari_podcast


ከዚህ ቀደም 10ኛ ክፍልን በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ተማሪዎች ፈተናዉ የሚዘጋጀዉ በሁለቱ ሥርዓተ ትምህርት ውስጥ ከሚገኙ የጋራ የሆኑ ጥያቄዎች ይዘጋጃል👇👇👇

https://youtu.be/H9Y51G_7dxw


ያነበብነውን አየረሳን ለተቸገርን ተማሪዎች መፍትሔ

https://youtu.be/SGtHq2Q6OCo




#Exit_Exam_Result

ሀገር አቀፍ የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት ተለቋል።

https//:result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት ExitExam የሚለውን በመምረጥና የራስዎን User Name በማስገባት ውጤትዎን መመልከት ይችላሉ።

በ2017 ዓ.ም አጋማሽ ዓመት የመውጫ ፈተና ከጥር 26-30/2017 ዓ.ም መሠጠቱ ይታወቃል።

@Temari_podcast


የመውጫ ፈተና ውጤት መቼ ይፋ ይደረጋል?

በርካታ የመውጫ ፈተና ተፈታኞች የፈተና ውጤት መቼ ይፋ ይደረጋል የሚል ጥያቄ አድርሰውናል።

👉እስካሁን ባገኘነው መረጃ መሰረት የመውጫ ፈተና ውጤት #ከሁለት ቀን በኋላ ይፋ ይደረጋል የሚል መረጃ ሰምተናል።

(በተጨማሪ መረጃ እንመለሳለን)

@Temari_podcast


የ2017 ኢንትራንስ ፈተና ዝግጅት ምን ይመስላል❓

https://youtu.be/7hSs-PTJyvs


የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የስፖርት ፌስቲቫል በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አሸናፊነት ተጠናቀቀ

ላለፉት 10 ቀናት በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ሲካሄድ የቆየው የተማሪዎች የስፖርት ፌስቲቫል በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አሸናፊነት ተጠናቅቋል፡፡

በተጨማሪም በምስጉን ዋንጫ የአዲግራት ዩኒቨርሲቲ ተሸላሚ ሆኗል።

በማጠቃለያ መርሐግብሩ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስቴር ዴኤታ ኮራ ጡሹኔ (ዶ/ር)÷ የውድድሩ ጠቀሜታ የጎላ በመሆኑ ሊቋረጥ እንደማይገባ ተናግረዋል፡፡

ለውድድሩ መሳካት የበኩላቸውን ድርሻ ለተወጡ አካላትም ሚኒስቴር ዴኤታው ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በአምስት የተለያዩ የውድድር አይነቶች በ49 ዩኒቨርሲቲ መካከል በተካሄደው ውድድር 2 ሺህ 500 ተማሪዎች ተሳታፊ ሆነውበታል ።

https://t.me/Temari_podcast


ዛሬ መሠጠት የተጀመረውን የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ዕጩ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና በጥብቅ የፈተና ዲሲፕሊን እንዲሰጥ እያደረጉ መሆኑን ዩኒቨርሲቲዎች ገለፁ።

ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ተፈታኞች ወደፈተና ማዕከላት ይዘው እንዳይገቡ የተከለከሉ ነገሮችን ፍተሻ በማድረግ መያዙን ገልጿል።

በዚህም ዩኒቨርሲቲው ኩረጃ እና ስርቆት የሚያግዙ ክልክል የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ይዘው የተገኙ ተማሪዎችን ወደ መፈተኛ ክፍሎች እንዳይገቡ አድርጓል።

ምስል፦ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ

@Temari_podcast


#EXITEXAM #Note

ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ተግባራዊ ማድረግ ከጀመራቸው ስራዎች አንዱ የሆነ የተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ከጥር 26 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ ይሰጣል።

⚡️በፈተና ወቅት ከተፈታኝ ተማሪዎች ምን ይጠበቃል ?


👉🏾 ተፈታኞች ወደ መፈተኛ ክፍል ሲመጡ ማንኛውም አይነት ስልክ፣ ስማርት ሰዓት ፣ ታብሌት ፣ ላፕቶፕና ... ወዘተ ተመሳሳይ ኤክትሮኒክ ቁሳቁስ መያዝ በፍፁም የተከለከለ ነው።  (ይዞ የተገኘ ፈተናው /ውጤቱ ተሰርዞበት በቀጣይ ጊዜ እንዲቀመጥ ይደርጋል)

👉🏾 ፈተና ከመጀመሩ ከ30 ደቂቃ በፊት መፈተኛ ክፍል መገኘት አለባቸው ይህም ማለት ከጥዋቱ 2፡00 በፊት ፤ ከሰዓት ደግሞ ከ8፡00 በፊት ተፈታኞች መገኘት አለባቸው።

👉🏾 ተፈታኞች ለፈተና ሲመጡ ID መያዝ ያለባቸው ሲሆን User Name እና Password lower-case and upper-case ፊደላትን ለይተው በጥንቃቄ መያዝ አለባቸው።

👉🏾 ተፈታኞች ፈተና ከተጀመረ በኃላ ከ30 ደቂቃ በፊት ከፈተናው ክፍል መውጣት የለባቸውም።

👉🏾 ተፈታኞች ፤ ፈተናውን የሚያስፈትኑ መምህራን በሚያሳዩት ቦታ ብቻ መቀመጥ አለባቸው።

👉🏾 ሁሉም ተፈታኝ እንዲቀመጥ የተመደበበት የራሱ ኮምፒውተር ላይ ብቻ ተቀምጦ መክፈትና መጠቀም አለበት።

👉🏾 በፈተና ክፍል ውስጥ መነጋገር እና ከቦታ ቦታ መዘዋወር በፍፁም የተከለከለ ነው። እንዲሁም ማንኛውም ተፈታኝ ከጎኑ ያለውን ተማሪ ኮምፒውተር በፍፁም ማየት የለበትም።

👉🏾 ምንም ዓይነት ወረቀት ወደ መፈተኛ ክፍል ይዞ መምጣት አይቻልም።

👉🏾 ተፈታኞች በምንም ሁኔታ መኮርጅም ሆነ ማስኮርጅ ተግባር ላይ ቢሳተፉ እርምጃ ይወሰድባቸዋል።

👉🏾 ሁሉም ተፈታኞሽ ለፈታኝ መምህራንና ለአስተባባሪዎች  መታዘዝ ያለባቸው ሲሆን የፈተናው ደንብ እና ስርዓት ተገዢ መሆን ይጠበቅባቸዋል።

👉🏾 በድጋሚ ተፈታኞች የፈተና መግቢያ ትኬት (Exit Exam Entry Ticket) መያዝ ይጠበቅባቸዋል።

NB.  ሁሉም ተፈታኞች ወደ መፈኛ ክፍል ተፈትሸው እንዲገቡ የሚደረግ ሲሆን ማንኛውም ተፈታኝ ከፀጥታ ኃይሉ ጋር በፍተሻ ወቅት ይሁን ሥርዓት ለማስያዝ በሚደረግ እንቅስቃሴ እንቅፋት ሆኖ ከተገኘ ከመፈተኛ አከባቢ እንዲገለል ተደርጎ በቀጣዩ የመውጫ ፈተና መስጫ ወቅት እንዲቀመጥ ይፈቀድለታል።

⚡️ከፈታኝ መምህራን የሚጠበቅ

👉🏾 የተፈታኝ ተማሪዎችን ID በአግባቡ በማረጋገጥ ወደ ክፍል እንዲገቡ ማደረግ ይጠበቅባቸዋል።

👉🏾 ተፈታኝ ተማሪዎችን በሥም ዝርዝራቸው መሠረት ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል።

👉🏾 ፈታኝ መምራህን የተማሪዎችን አቴንዳንሰ ይወስዳሉ ፤ ተማሪዎችን ፊርማ ያስፈርማሉ።

👉🏾 በፈተና ክፍል ውስጥ ደምጽ እንዳይሰማ፣ ተማሪዎች ከቦታ ቦታ እንዳይዘዋወሩ ተገቢውን ቁጥጥር ማድረግ አለባቸው።

👉🏾 የፈተናው አጠቃለይ ሂደት በትኩረት መከታተል አለባቸው።

👉🏾 በህመም ምክንያት ተማሪዎች ከክፍል መውጣት ቢፈልጉ ከሱፐርቨዘር ጋር በመነጋገር አስፈላጊውን እርዳታ ያደርጋሉ።

👉🏾 ተማሪዎች በጎናቸው ያለውን ሌላ ኮምፒውተር እንዳይመለከቱ መቆጣጠር አለባቸው።

👉🏾 ተማሪዎች ፈተናው ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በፊት እንዳይወጡ መቆጣጠር ይጠበቅባቸዋል።

👉🏾 ሲኮርጂ ወይንም ሲያስኮርጅ የተገኘ ተማሪ ከመፈተኛ ክፍል እንዲወጣ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።

👉🏾 ፈተናው ከጀመረ 15 ደቂቃ በኃላ የሚመጣ ተማሪ እንዲገባ ማድረግ የላባቸውም።

👉🏾 የፈተና አፈጻጸም ሪፖርት ለሱፐርቨዘር ማቅረብ

🍀 መልካም ፈተና 🍀

@Temari_podcast


Репост из: Freshman Tricks
የ ጤና እና የ ኢንጂነሪንግ ዲፓርትመንቶች ንፅፅር / Health Bs Engineering Departments comparison 👇👇👇

https://youtu.be/JQRlyHMGJpM

Показано 15 последних публикаций.