ትራምፕ ወደ መካከለኛው ምስራቅ
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሚቀጥለው ወር ወደ መካከለኛው ምስርቅ ብቅ ሊሉ ነው ተባለ፡፡
ሪፐብሊካኑ ትራምፕ ሳውዲ አረቢያን፣ ኳታርን እና አረብ ኤሚሬቶችን ግንቢት ላይ ይጎበኛሉ፡፡
ወደ ቀጠናው ከፈረንጆቹ ግንቦት 13 እስከ 16 ሲመጡ በርካታ ጉዳዮችን ግምት ውስጥ አስገብተው ነው ተብሏል፡፡
በመጀመሪያው ዙር የፕሬዚዳንትነት ዘመናቸው ትተውት የሄዱትን የመካከለኛው ምስራቅ ፖለቲካ በአሁኑ ጉብኝታቸው እንደማያገኙትም ተነግሯል፡፡
ኢራን እና ሳውዲ አረቢያ በቻይና አማካኝነት መታረቃቸው እንዲሁም እስራኤል እና ሃማስ የገቡበት ጦርነት እንግዳ ጉዳይ ይሆንባቸዋል ተብሏል፡፡
ትራምፕ ወደ መካከለኛው ምስራቅ የሚጓዙት ፖለቲካዊ መፍትሄ ለማምጣት ነው የተባለ ሲሆን እስከዛው ግን ከኢራን ጋር ያለው ውጥረት ወይ ይረግባል አሊያም ይለይለታል የሚል መረጃ ወቷል፡፡
በየመን ከሁቲዎች ጋር ያለው ውጥረትም አብሮ ፖለቲካዊ ግምት ውስጥ የሚገባ ጉዳይ ነው ብሏል የፕሬዚዳንቱ ቢሮ ዖቫል ኦፊስ፡፡
ፕሬዚዳንቱ እስከዛው የጋዛውን ጦርነት መቋጨት ካልቻሉም በመካከለኛው ምስራቅ መልካም አቀባበል አይጠብቃቸውም እየተባለ ነው።
የዶናልድ ትራምፕ ጉዞ ከፍተኛ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ትርጓሜ እንደሚኖረው ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡
አልጀዚራ እንዳስነበበው፡፡
@ZenaAdis_Ethiopia