🎙Zena Adis Ethiopia🎙


Гео и язык канала: Эфиопия, Английский
Категория: Новости и СМИ


ይህ ዜና አዲስ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ_ትቅደም!!

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Английский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ዛሬ 125% አዲስ የታክስ ታሪፍ  ቻይና ላይ ጥሏል። ከቻይና ውጪ የጣሉት ሁሉም ታሪፎች ለ 90 ቀናት እንዲዘገዩ አዘዋል።

@Zena_Adis_Ethiopia


ቻይና አሜሪካ ላይ የ84 በመቶ ታሪፍ መጣሏን አስታወቀች

ቻይና በአሜሪካ ላይ ጥላው የነበረውን የ34 በመቶ ታሪፍ ወደ 84 በመቶ ማሳደጓን ገልጻላች።

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይና ወደ አሜሪካ የሚገቡ ምርቶች ላይ የ104 በመቶ ታሪፍ መጣላቸውን ተከትሎ ነው ሀገሪቱ ማሻሻያውን ያደረገችው።

“በኢኮኖሚ ረገድ ለሚደረግ ጦርነት እስከመጨረሻው ለመታገል ዝግጁ ነኝ” ያለችው ቻይና፣ አሁንም ወደ ኋላ እንደማታፈገፍግ ነው ያስረገጠችው።

በሌላ በኩል የአውሮፓ ኅብረት በአንድ አንድ የአሜሪካ ምርቶች ላይ ታሪፍ ለመጨመር ድምፅ መስጠቱ ተጠቁሟል።

የታሪፍ እርምጃው የአውሮፓ እና እስያ ሀገራት አክሲዮን ገበያ እንዲያሽቆለቁል ከማድረጉ ባሻገር የአሜሪካ እና የዓለም አቀፍ ኢኮኖሚ 60 በመቶ እንዲወድቅ ያደርጋል ሲል ቢቢሲ በዘገባው አመላክቷል።

@Zena_Adis_Ethiopia


ከአራት ኪሎ እስከ ሽሮ ሜዳ የዩኒቨርሲቲ መንደር እንዲሆን ተወሰነ‼️

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በ4ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ስብሰባው አራት አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ በዛሬዉ እለት ውሳኔዎችን አስተላልፏል።

በዚህም መሰረት:-

1ኛ.በፕላንና ልማት ቢሮ እና በትምህርት ሚኒስቴር በጋራ ተጠንቶ የቀረበዉን ከአራት ኪሎ እስከ ሽሮ ሜዳ ያለዉ አካባቢ የዩኒቨርሲቲ መንደር በመሆን በአካባቢዉ ያሉትን አገልግሎቶች አካቶ የትምህርት ፣ የምርምር ፣ የእውቀት እና የባህል ልህቀትን በከተማዋ ለማሳደግ በሚያስችል አግባብ የቀረበ በመሆኑ ፤  ካቢኔዉ ተወያይቶ የመንደር ምስረታውን ዉሳኔ አፅድቋል፡፡

2ኛ.የምግብ ስርዓትና ኒዉትሪሽን ምክር ቤት ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ ዉሳኔ አስተላልፏል::

3ኛ.የአደጋ ስጋት አመራር ምክር ቤትና ፤የአደጋ ዝግጁነት ፈንድ ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ካቢኔዉ ተወያይቶ ዉሳኔ አስተላልፏል፡፡

4ኛ.በመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ የቀረበዉን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸዉ ፕሮጀክቶች፤የመሬት ምደባ ጥያቄዎች አስመልክቶ ካቢኔዉ ተወያይቶ ዉሳኔ አስተላልፏል፡፡

@Zena_Adis_Ethiopia


የጋዛ መፃኢ እድል በቀጣይ ወር የሚደረገውን የአወስትራሊያ ምርጫ ውጤት የመወሰን አቅም አለው ተባለ

እስራኤል በጋዛ ላይ እየፈፀመቻቸው ያሉት የማያባሩ ጥቃቶች እንዲሁም የአወስትራልያ መንግስት ለጉዳዩ የሚሰጠው ትኩረትና ግብረመልስ ቀጣይ ወር የሚደረገው ሀገራዊ ምርጫ ውጤት ላይ የራሱ የሆነ ከፍተኛ ተፅእኖ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል። በተለይም ገዢው የሰራተኞች ፓርቲ በፓርላማው የበላይ የምታደርገውን አንድ ወንበር አስጠብቆ ለማስቀጠል ይሻል።

ይህ ይሆን ዘንድና ደጋፊዎቹን ለማስከተል እንዲችል የአወስትራልያ መንግስት ከእስራኤል ጎን መሆኑን በማስታወቅ የጋዛውን ሰቆቃ በተኩስ አቁም እንዲገታ በተደጋጋሚ ጥሪውን ሲያቀርብ ቆይቷል።

ነገር ግን የአወስትራልያ መንግስት የጋዛን ሰቆቃ ለማስቆም በበቂ ሁኔታ ጫና አላደረገም የሚሉ የግል ተፎካካሪዎች በምርጫው ላይ ይሳተፋሉና ከነሱ ጠበቅ ያለ ፉክክር ይጠብቀዋል ተብሎ ተገምቷል። በተለይ ደግሞ ምስራቅ ሲድኒ የምርጫ ቀጠና ወሳኝ ድምፆችን ሊያጣ እንደሚችል ከወዲሁ የተገመተ ሲሆን የአከባቢው ነዋሪዎች አንድ ሶስተኛ የእስልማና እምነት ተከታዮችና የጋዛን ሰቆቃ በአፋጠኝ እንዲቆም የሚሹ ከመሆናቸው አንፃር የእስራኤል ደጋፊ የሆነው ገዚው ፓርቲ በዛ አከባቢ የመመረጡ ነገር ጥያቄ ውስጥ ገብቷል።

@Zena_Adis_Ethiopia


የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ዛሬ ከሰዓት ቡኃላ 104% አዲስ የታክስ ታሪፍ  ቻይና ላይ ጥሏል።

@Zena_Adis_Ethiopia


የትግራይ ህዝብ ላሳየኝ ክብር እና ድጋፍ ላቅ ያለ ምስጋና አለኝ - አቶ ጌታቸው ረዳ
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
የትግራይ ህዝብ ላሳየኝ ክብር እና ድጋፍ ላቅ ያለ ምስጋና አለኝ ሲሉ የቀድሞው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ገለጹ።

አቶ ጌታቸው በኤክስ ማህበራዊ ትስስር ገጻቸው በትግሪኛ ቋንቋ ባሰፈሩት መልዕክት የሁለት ዓመት የጊዜያዊ መስተዳድር ሀላፊነቴን በይፋ አስረክቤያለሁ ብለዋል።

የትግራይ ህዝብ ላሳየኝ ክብር እና ድጋፍ ላቅ ያለ ምስጋና አለኝ ያሉት አቶ ጌታቸው ህዝባችን ወደ ተሻለ ሁኔታ እንዲመለሰ ሁለንተናዊ ፍላጎቱ እንዲሟላለት የተቻለኝን ሁሉ አደርጋለሁ ሲሉም ገልጸዋል።

የሰላም እና የለውጥ ፍላጎት እንዳይሰናከል ትግላችንን እናጠናክር በማለትም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

@Zena_Adis_Ethiopia


ሌተናል ጄኔራል ታደሰ ወረደ የትግራይ ጊዚያው አስተዳደር ፕሬዚደንት ሆነው ሲሾሙ በስልጣን ቆይታቸው ከላይ የተያያዙትን ነጥቦች ለማስፈጸም ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና አቶ ጌታቸው ረዳ በተገኙበት በፊርማቸው ቃል ገብተዋል።

1. የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀያቸው የመመለስ ሂደት፣ በጅምር ያለው እንዲጠናቀቅ እና በቀሪ አካባቢዎችም በፍጥነት እንዲተገበር ማድረግ፤

2. በፕሪቶሪያ ስምምነት መሠረት ትጥቅ የመፍታት እና የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ የማቋቋም ተግባር በአፋጣኝ እንዲጠናቀቅ ማድረግ፤

3. በክልሉ የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን ማድረግ፤ ለሕዝብ ደኅንነት፣ ለሰላም እና ለጸጥታ ጠንቅ የሆኑ ጉልህ ሕገ ወጥ እንቅስቃሴዎች እንዲቆሙ ማድረግ፤ ለዚህም ተገቢውን የቁጥጥር እና የሕግ ማስከበር ሥራ መሥራት፤

4. መደበኛ የልማት ሥራዎች፣ መንግሥታዊ እና ማኅበራዊ አገልግሎቶች፣ እንዲሁም የመልሶ ግንባታ ሥራዎች እንዲሣለጡ ማድረግ፤

5. ከሕገ መንግሥታዊ እና ከሕጋዊ ሥርዓት፣ ከሀገር_ሉዓላዊነት እና ከፕሪቶርያ ስምምነት ያፈነገጡ ግንኙነቶች እና እንቅስቃሴዎች እንዲቆሙ ማድረግ፤

6. ክልሉ ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ዝግጁ እንዲሆን ማድረግ፤ በክልሉ የሲቪክ እና የፖለቲካ መብቶች ተግባራዊ የሆኑበት፣ የፖለቲካ ብዝኃነትን የሚያስተናግድ ደሞክራሲያዊ ዐውድ እንዲፈጠር መሥራት፤

7. የክልሉ ሕዝብ፣ የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች እና የፖለቲካ ተዋንያን በሀገራዊ_የምክክር_ሂደት እንዲሳተፉ ሁኔታዎችን ማመቻቸት፤

8. የክልሉ መንግሥታዊ የሚዲያ እና የኮሙኒኬሽን እንቅስቃሴዎች የሀገሪቱን ሕዝቦች ትሥሥር እና መልካም ግንኙነት የሚያጠናከሩ፣ ሕግ እና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓትን የሚያስከብሩ መሆናቸውን ማረጋገጥ፤

ሌተናል ጄኔራል ታደሰ ወረደ የትግራይ ጊዚያው አስተዳደር ፕሬዚደንት ሆነው ሲሾሙ በስልጣን ቆይታቸው ከላይ የተያያዙትን ነጥቦች ለማስፈጸም ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና አቶ ጌታቸው ረዳ በተገኙበት በፊርማቸው ቃል ገብተዋል።

@Zena_Adis_Ethiopia


የዩክሬን ወታደሮች እንቅስቃሴ በሩሲያ ቤልጎሮድ ድንበር
።።።።።።።።።።።።።

የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ወታደሮቻቸው በሩሲያ ቤልጎሮድ አካባቢ እንደሚንቀሳቀሱ ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋ አምነዋል።

በሁለቱ ወገኖች ከተጀመረው ጦርነት ወዲህ ዘለንስኪ 1.5 ሚሊዮን ህዝብ በሚኖርበት የድንበር ክልል ቤልጎሮድ ውስጥ የዩክሬን ወታደሮች መኖራቸውን ነው ለመጀመሪያ ጊዜ ያመኑት።

"በጠላት ግዛት ድንበር አከባቢዎች ላይ ንቁ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ማካሄዳችንን እንቀጥላለን፣ ይህ ፍጹም ፍትሃዊ ነው - ጦርነቱ ወደ መጣበት መመለስ አለበት" ብለዋል ዘለንስኪ።

የሩስያ ጦር ባለፈው ወር የዩክሬን ወታደሮች ወደ ቤልጎሮድ ክልል በመዝለቅ ጥቃት መሰንዘራቸው አስታውቆ የነበር ሲሆን ዩክሬን በበኩሏ ማስተባበሏ ይታወሳል ።

ዘለንስኪ ዋናው አላማ የዩክሬንን ሱሚ እና ካርኪቭ የድንበር ክልሎችን መጠበቅ ነው ፣ በተለይም በምስራቅ ዶኔትስክ ክልል ላይ ያለውን ጫና ማቃለል ነው ብለዋል።

እ.ኤ.አ. በ 2022 በዩክሬንና ሩሲያ መካከል ከተጀመረው ጦርነት ወዲህ ሞስኮ በአሁኑ ጊዜ 20 በመቶ የሚሆነውን የዩክሬን ግዛት ተቆጣጥራ ትገኛለች ።

ዘገባው የቢቢሲ ነው

@Zena_Adis_Ethiopia


ቻይና የትራምፕ ታሪፍ ጭማሪ ዛቻን እንደማትቀበል ተናግራለች።

@Zena_Adis_Ethiopia


ቻይና አሜሪካ ላይ የጣለችውን የ 34 በመቶ አዲስ የታክስ ታሪፍ በነገው እለት ማታነሳ ከሆነ ትራምፕ ተጨማሪ 50 በመቶ (April 9) ቻይና ላይ እንደሚጥሉ አሳወቁ ።

@Zena_Adis_Ethiopia


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግርኛ ቋንቋ ያስተላለፉት መልዕክት

ብመሰረት ሕገ መንግስቲ  ፌዴሪኢ 62 (9) ፣ ብኣወጅ 359/1995 ኣንቀጽ 15(3) ን ደንቢ ቁጥር 533/2015 ከምኡ ድማ ስምምዕ እማመ ሰላም ፕሪቶርያን፣ ኣይተ ጌታቸው ረዳ ንዝሓለፉ ኽልተ ዓመታት ፕረዚደንት ጊዝያዊ ምምሕዳር ክልል ትግራይ ኮይኖም ንዘበርከትዎ፣  ብፍላይ ድማ ዝተረኽበ ሰላም ክዕቀብ ንዝነበሮም ልዑል ጥንቃቐን ኣመራርሓን መንግስቲ ፌደራል ኣፍልጦ ከምዘለዎን፤ ኣብ ቀፃሊ ስራሕቲ እውን ብሓባር ተቐራሪብና ከምእንስራሕን እናረጋገፅኩ፣  ንዝነበሮም ፃንሒት ኣመስግን።

@Zena_Adis_Ethiopia


በሲስተም ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት አገልግሎት ተቋርጧል

🗣የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

ሲስተም ላይ ባጋጠም ብልሽት ምክንያት 905 እና 904 ነፃ የጥሪ ማዕከሎች እንዲሁም የዲጂታል የክፍያ አማራጮችን ጨምሮ ከኢንተርኔት አገልግሎት ጋር ተያያዥነት ያላቸው የድህረ ክፍያ አገልግሎቶች አገልግሎት መስጠት ማቆማቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል፡፡ 

ችግሩ ተፈትቶ የተቋረጠው አገልግሎት እስኪመለስ ድረስ ደንበኞች በአቅራቢያዎቻቸው በሚገኙ ዲስትሪክቶች ወይም አገልግሎት መስጫ ማዕከሎች በአካል ወይም በቀጥታ ስልክ በመደወል ተገቢውን አገልግሎት ማግኘት የሚችሉ መሆኑን የአገልግሎቱ መረጃ ያመለክታል፡፡

@Zena_Adis_Ethiopia


ፈረንሳይ አይሲሲ የእስር ማዘዣ ያወጣባቸውን ኔታንያሁን ይዛ ስትጓዝ የነበረች አውሮፕላን በአየር ክልላ እንድታልፍ ማድረጓ እያነጋገረ ነው

ፍላይት ራዳር 24 የተሰኘው ድህረገፅ ይዞት የወጣ መረጃ እንደሚያሳየው ከሆነ ንብረትነቷ የእስራኤል መንግስት የሆነችና ጠቅላይ ሚኒስተር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ያሳፈረች አውሮፕላን ከሀንጋራ በመነሳት ወደ አሜሪካ በምታደርገው ጉዞ ወቅት በፈረንሳይ የአየር ክልል ማለፏ በርካቶች እንዴት ፈረንሳይ አባል የሆነችበት ተቋም የእስር ማዘዣ ያወጣባቸውን ኔታንያሁ ዝም ብላ ታሳልፋለች የሚሉ ጥያቄዎች ይነሱ ዘንድ አስገድዷል።

ዓለም አቀፊ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ባለፈው ዓመት ነበር የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስተር በቁጥጥር ስር ለማዋሎ የእስር ማዘዣ ያወጣባቸው። ፍርድ ቤቱ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ በተጨማሪ የቀድሞ የእስራኤል መከላከያ ሚኒስተር በዮቭ ጋላንት ላይም የጦር ወንጀል፣ እንዲሁም በሰብአዊነት ላይ በሚፈፀሙ ወንጀሎች ላይ ተሳትፎ አላቸው በሚል የእስር ማዘዣ አውጥቶባቸዋል።

ፈረንሳይ የአይሲሲ አባል እንደመሆኗ ፍርድ ቤቱ የሚፈልጋቸውን አካላት አሳልፋ የመስጠት ግዴታ ያለባት ቢሆንም ያላትን ድምፅን በድምፅ የመሻር ቬቶ ፓወር በመጠቀም ግን የፍርድ ቤቱን ውሳኔዎች አለመቀበል ወይንም ውድቅ ማድረግ ትችላለች።

ታዲያ ፈረንሳይ ይህንን መብቷ በመጠቀም በአይሲሲ የእስር ማዘዣ የወጣባቸውን ኔታንያሁ ያሳፈረውን አውሮፕላን ዛሬን ጨምሮ ለሶስተኛ ጊዜ በአየር ክልሏ እንዲያልፍ የፈቀደች ሲሆን እንደ ፍላይት ራደር 24 መረጃ ከሆነ ፈረንሳይ ከዚህ ቀደም የካቲት 2ና 9 ኔታንያሁ ወደ አሜሪካ ሄደው ሲመለሱ የፈረሳይን የአየር ክልል መጠቀማቸው ይፋ አድርጓል። ይህ መረጃ የወጣው ሀነጋሪ ኔታንያሁን ወደ ሀገራ በመጋበዝ ራሷን ከአይሲሲ አባልነት ባገለለች ማግስት ነው።



@Zena_Adis_Ethiopia


አዲስ  ጥቃት በዩክሬን ላይ

። ። ። ። ። ። ። ። ። ።
ዛሬ ጠዋት ጀምሮ  የዩክሬን ዋና ከተማ ኬይቭ በሩሲያ ሚሳኤል እየተደበደበች መሆኑ ተሰምቷል፤

ከባድ ፍንዳታ በኬይቭ ከደረሰ በኋላ ሶስት ሰዎች ቆስለዋል ሲሉ የኬቭ ከንቲቫ ቫታሊ ኪልቲሽኮ ተናግረዋል፡፡

ቫታሊ ኪልቲሽኮ የህክምና አገልግሎት የሚሰጡ የነፍስ አድን ሰራተኞች ጥቃቱ በደረሰበት  አካባቢ እርዳታ እየሰጡ እንደሚገኙም ገልጸዋል፡፡

በከተማዋ ፍንዳታ እንደደረሰ አየር ሀይላችን በመከላከል ላይ ነው ሲሉም በቴሌግራም ገጻቸው ላይ ከንቲባው አስፈረዋል፡፡

በኬይቭ  የሚፈጸመው የሚሳኤል ጥቃት ቀጣይ ስለሆነ  ነዋሪዎች በመጠለያዎች እንዲቆዩ የዩክሬን ባለስልጣናት ማሳሰቢያ ሰጥተዋል  ተብሏል ፡፡

ሩሲያ ከሁለት ቀን በፊት በዩክሬን ላይ በፈጸመችው የሚሳኤል ጥቃት 18 ሰዎች መሞታቸውን እና ከ 50 በላይ  ደግሞ መቁሰላቸውን መዘገባችን ይታወሳል ፡፡

አልጀዚራ፣ ሮይተርስ ፣ ኤቢሲ ኒውስ፣ ዘ ጋርዲያን እና ፍራንስ 24 አስነብበዋል፡፡

@Zena_Adis_Ethiopia


🚨 " አሁንም በርካታ የታመሙ ተማሪዎች ወደ ህክምና ተቋሙ እየሄዱ ነው "- ተማሪዎች

➡️ " በሽታው የተከሰተው ከምግብ ወይም ከውሃ ጋር የተያያዘ መሆኑን ገና እየተጣራ ነው " - አብርሃም ዘገየ የተማሪዎች ዲን

በጎንደር ዩንቨርስቲ የፋሲል ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ፋክሊቲ ያሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች መታመማቸውን ተገልጾዋል።

ከባለፈው እሮብ ጀምሮ በግቢው " በውሃና በምግብ ብክለት ነው " ብለው በጠረጠሩት ምክንያት በርካታ ተማሪዎች መታመማቸውን ህክምና ላይ ያሉ ተማሪዎች አመልክተዋል።

ስማቸውን እንዳንጠቅስ የጠየቁን በግቢው ተማሪ መሆናቸውን እና አሁን በህክምና ላይ መሆናቸውን የገለፁልን ተማሪዎች ግቢው ውስጥ ባለው የህክምና ተቋም በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች እየታከሙ መሆኑን ገልፀዋል።

ለተሻለ ህክምናም ወደ ጎንደር ዩንቨርስቲ ሪፈራል ሆስፒታል የተላኩ እንዳሉም ተማሪዎች ተናግረዋል።

የሁለተኛ አመት የኬሚካል እንጂነሪንግ የሆነ አንድ ተማሪ ባለፈው እሮብ ምሳ ላይ የተመገቡት ፓስታ እርሱን ጨምሮ በርካቶችን ለህመም እንደዳረጋቸው ይጠረጥራል።

የትኩሳት፣ የተቅማጥ እና እጅና እግር የመቆረጣጠም ምልክት እንዳለው የሚናገሩት ታማሚዎች ወደ ህክምና ተቋም የሄዱ ተማሪዎች በሙሉ " ታይፎድ " ነው እንደተባሉ ተማሪው ተናግሯል።

ሌላው የሶስተኛ አመት የኤሌክትሪካል እንጂነሪንግ ተማሪ መሆኑን የነገረንና ስሙ እንዳይጠቀስ የጠየቀን ተማሪ ደግሞ ምግቡ፤ የሚጠጣው ውኃም ተበርዟል ይላል። ህክምና ተደርጎለት መድሃኒት እየወሰደ እንደሆነ የሚናገረው ይህ ተማሪ የውሃ እጥረት በግቢው ስር የሰደደ ችግር ነው ብሏል።

ከየት እንደሚመጣ የማይታውቅ ውኃ በቦቴ ተጭኖ ይመጣል በጥራቱ ሁሌ እንጠራጠር ነበር። በተለይ ሰሞኑን ከተማሪዎች መታመም ጋር በተያያዘ አብዛኛው ተማሪ የታሸገ ውሃ ገዝቶ እየጠጣ ይገኛል ብሏል።

ተማሪዎቹ ለተማሪዎች ህብረት ተወካይ ችግሩን ማሳወቃቸውን ተናግረዋል።

የኢንጅነሪግ ተማሪዎች ብቻ በሚማሩበት በጎንደር ዩንቨርስቲ የፋሲል ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ፋክልቲ የተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳት የሆነውን ተማሪ ተመስገን ችግሩ መከሰቱንና እርሱን ጨምሮ በርከት ያሉ ተማሪዎች መታመማቸውን ገልጾ፥ ችግሩ ከውሃው ነው በመባሉ ትላንት በታንከሩ ያለው ውሃ ተቀይሮ በኬሚካል በታከመ ውሃ መቀየሩን ተናግሯል።

በጎንደር ዩንቨርስቲ የፋሲል ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ፋክልቲ የተማሪዎች ዲን አብርሃም ዘገየ በግቢው ከመቶ በላይ ተማሪዎች ወደ ክሊኒክ ታመው መሄዳቸውን ጠቅሰው ከመጡት ውስጥ 84 ተማሪዎች ብቻ " ባክቴሪያ " ተገኝቶባቸው መድሃኒት ተሰጥቶቸው እያገገሙ ነው ብለዋል።

ከዚህ ህመም ጋር በተያያዘ ለከፍተኛ ህክምና ወደ ጎንደር ዩንቨርስቲ ሪፈራል ሆስፒታል የሄዱት ከ5 እንደማይበልጡና ከእነዚህ ውስጥ ተጏዳኝ የጨጏራና ሌሎች ችግሮች ያለባቸው ናቸው ተብለው ታክመው የተመለሱ ናቸው ሲሉ አስረድተዋል።

ቀለል ያለ ስሜት ላላቸው ተማሪዎችም ኦ አር ኤስ እየተሰጣቸው ነው፤ ከዩንቨርስቲው አመራር ጋር በመሆን የመድሃኒት ችግር እንዳያጋጥምም ወደ ክሊንኩ አስገብተናል ያሉት አብርሃም የውሃና የምግብ ችግር ነው የሚለውን ምክንያት እየተጣራ መኦኑን ተናግረዋል።

@Zena_Adis_Ethiopia


ቻይና በአሜሪካ ለተጣለባት ታክስ ተመሳሳይ አጸፋዊ እርምጃ ወሰደችች።
።።።።።።።።።።።።።።።

ቻይና ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ የ34 በመቶ ቀረጥ  በሁሉም የአሜሪካ ምርቶች ላይ ለመጣል መወሰኗን አስታውቃለች ። ይህ የቻይና እርምጃ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይና ወደ አሜሪካ በሚገቡ ምርቶች ይፋ ያደረጉት የ 34 በመቶ አዲስ የታክስ ታሪፍ ተከትሎ የሰጠችው ጠንካራ የበቀል እርምጃ አካል ነው ተብሏል።

ቀደም ሲል አሜሪካ በየካቲት እና መጋቢት ወር  በቻይና ምርቶች ላይ የ 10 በመቶ እና የ20 በመቶ ታክስ ጥላ የነበር ሲሆን ቤጂንግም ውሳኔው የንግድ ጦርነት የሚቀሰቅስ ድርጊት በማለት ስትቃወም ቆይታለች። እንዲሁም ሀገሪቱ ለተጣለባት ቀረጥ 15 በመቶ ታክስ መጣሏም የሚታወስ ነው።

ቻይና በተጨማሪ ቁልፍ በሆኑ የማዕድናት ንግድ ላይ ቁጥጥር እንደምታደርግ አስታውቃለች። ይህም  ከአሜርካን ጋር የሚደረገውን ግብይት ሊገድበው እንደሚችል ተጠቁሟል።

የቻይናን የበቀል እርምጃ ተከትሎ የአሜሪካ የአክሲዮን ገበያ ከኮቪድ ወረርሽኝ ወዲህ በእጅጉ መቀነሱ ተነግሯል።

የቻይና ውሳኔ ተከትሎ ትራምፕ " ቻይና በድንጋጤ የማይሆን ጨዋታ ተጫውታለች " ሲሉ ትሩዝ በተባለው በማህበራዊ ድህረ ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት መልእክት ተናግረዋል ።

በሎላ በኩል  ቬትናም፣ ህንድ እና እስራኤል በአሜሪካ የተጣለባቸው ቀረጥ ተከትሎ የሚደርስባቸውን ጫና ለመቀነስ  ከፕሬዚዳንት ትራምፕ ጋር እየተነጋገሩ ነው ተብሏል።

ዘገባው የአሶሺየትድ ፕሬስ ነው

በሰላማዊት ወልደገሪማ

@Zena_Adis_Ethiopia


የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር በዲጂታል ማንነት ዙሪያ ባሳዩት የአመራርነት ብቃት ዓለም አቀፍ እውቅና አገኙ

ዋና መቀመጫውን በአሜሪካ ሳን ፍራንሲስኮ ያደረገው ኦክታ ኩባንያ የብሔራዊ መታወቂያ ዋና ዳይሬክተር ዮዳሔ አርአያስላሴን በዲጂታል ማንነት የአመራርነት ሚና ካላቸው 25 ሰዎች አንዱ አድርጎ እውቅና ሰጥቷቸዋል።

በኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም መርሐግብር ከ13 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ተመዝግበዋል። የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም እ.ኤ.አ በ2025 70 ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያንን ለመመዝገብ አቅዷል ሲል ስፑትኒክ ኢትዮጵያ ዘግቧል፡፡

@Zena_Adis_Ethiopia


በአገራችን አንድ የድንገተኛ ህክምና ሀኪም ከግማሽ ሚሊየን እስከ 1 ሚሊየን ለሚደርስ ታካሚ አገልግሎት ይሰጣል።

በድንገተኛ ህክምና የማስተርስ ነርስ ያለው ባለሙያ ደግሞ ለግማሽ ሚሊየን ህዝብ አገልግሎት ለመስጠት ይገደዳል።

በአገራችን ያለው የድንገተኛ ህክምና ባለሙያዎች ቁጥር ከማህበረሰቡ ጋር የተጣጣመ አይደለም ተብሏል።

ከጣቢያችን ጋር ቆይታ ያደረጉት የኢትዮጵያ ድንገተኛ እና ፅኑ ህክምና ባለሙያዎች ማህበር ፕሬዝዳንት ዶክተር ወልደሰንበት ዋጋኖ፤በዓለም ጤና ድርጅት መስፈርት 1 ነርስ ወይም ሀኪም ለ50ሺህ እና ከዛ በታች ላለ ታካሚ መድረስ አለበት።

በእኛ አገር ያለው ሁኔታ ግን ከዚህ በተቃራኒ መሆኑን ይገልፃሉ።

በድንገተኛ ህክምና ዘርፍ 2መቶ1 ስፔሻሊስት ሀኪሞች እና 2መቶ50 ማስተርስ እና ፒኤችዲ ያላቸው ነርሶች መኖራቸውን ነግረውናል።

በጎ ፍቃደኞችን ጨምሮ 500 ፓራሜዲክ አሉ ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ በአጠቃላይ ወደ 7መቶ50 ባለሙያዎች አሉን ብለዋል።

ድንገተኛ ህክምና በአገራችን እውቅና ከተሰጠው 10 ዓመት ሆኖታል የሚሉት ዶ/ር ወልደሰንበት፤ በ10 ዓመት ዕድሜ አሁን ያለበት ደረጃ እንደ አገር መልካም ውጤት ነው ይላሉ።

ነገርግን ማህበረሰቡ ከሚፈልገው፣ካሉት አደጋዎች ብዛት እና ከአገሪቱ ዕድገት አንፃር እንደ አገር ብዙ የሰው ሀይል ያስፈልገናል ብለዋል።

ይህን ችግር ለመቅረፍ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በጋራ በመሆን በተለያዩ የህክምና ዘርፍ ለተማሩ እና ለሚሰሩ ባለሙያዎች አጫጭር ስልጠናዎችን እየሰጠን እንገኛለን ብለውናል።

እስከዳር ግርማ

@Zena_Adis_Ethiopia


ትምህርት ሚኒስቴር

"10ኛ ክፍል ላይ ሀገር አቀፍ ፈተና ሳይወስዱ ወደ 11 የተዘዋወሩ ተማሪዎች ልዩ የማካካሻ ትምህርት ሊሰጣቸው ይገባል፣ ካልሆነ ግን መውደቅ ይቀጥላል።"

@Zena_Adis_Ethiopia


በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ ምዝገባ ያጠናቀቃችሁ የጤና ባለሙያዎች ፈተና ከሚያዚያ 1-3/ 2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ ጤና ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል፡፡

ሚኒስቴሩ የመፈተኛ ጣቢያዎች ዝርዝርን ይፋ አድርጓል። ተፈታኞች የመፈተኛ ጣቢያችሁን መመልከት ትችላላችሁ። (ከላይ ተያይዟል)

ምንሊክ ጤና ሳይንስ ኮሌጂ የመረጣችሁ ተመዛኞች፥ የመፈተኛ ማዕከላችሁ ወደ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተቀየረ መሆኑ ተገልጿል።

@Zena_Adis_Ethiopia

Показано 20 последних публикаций.