በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜን።
. #እንኳን አደረሳችሁ።
👇አጭር ታሪክ ስለ ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ👇
አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ግብጻዊ ሲሆኑ እስከ 300 ዓመታቸው ድረስ በጾም
ጸሎት ሲያገለግሉ ከቅዩ በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ
ያዛቸዋል፥ በቅዱስ ገብርኤል አማካኝነት በንፋስ ሰረገላ ከሶስት አንበሶች እና ነብሮች ጋር
አድርጎ በ11ኛው መቶ ክ/ዘመን በንጉስ ላሊበላ ወቅት ወደ ኢትዮጵያ ያመጣቸዋል።
አባታችን ኢትዮጵያ ከመጡ በኋላም በጾምና ጸሎት ስለ ኢትዮጵያ ሕዝቦች አጥብቀው
ይጸልዩ ነበር፤
በዚህም ጸሎታቸው ምክንያት ጌታ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል፥ ሆኖም አባታችን የሚፈልጉት
ሙሉ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲማርላቸው ነበር፥ በዚህም በጸሎት እየተጉ ሳለ ሰይጣን ውኃ
በተጠማ ቁራ ተመስሎ ጸሎታቸውን ለማስታጎል ከአይናቸው ውስጥ ያለውን ውኃ ቢጠጣም
ጸሎታቸውን አላቋረጡም ነበር።
አባታችን በአጠቃላይ ለ562 ዘመን የኖሩ ሲሆን ዕረፍታቸውም እንዲህ ነበር፦
መጋቢት ፩ በዕለተ ዕረቡ ብሔረ ሕያዋን በመሄድ በዚያ ከሚኖሩ ቅዱሳን ጋር ቆይተዋል።
መጋቢት ፪ ሐሙስ ዕለት ከብሔረ ሕያዋን በመመለስ ገድላቸውን አጽፈዋል።
መጋቢት ፫ አርብ ይታመማሉ።
መጋቢት ፬ ቅዳሜ በጸና ቢታመሙም ከጸሎታቸው አልተስተጓጎሉም ነበር።
ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ በጸና በመታመማቸው መሬት ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ይቀመጣሉ፥
በዚህን ጊዜ ከሰማይ ወደ ምድር እንደሚዘረጋ መሠላልን የመሠለ ነገር ቁልቁል ይወርዳል፤
በዚህም ጌታችንና እናቱን ጨምሮ ቅዱሳን ሰዎችና መላዕክት አባታችን ወዳሉበት ይመጣሉ፥
በዚህ ጊዜ መሬት የጌታዋን መምጣት ስትመለከት ወደ ኋላዋ ትሸሻለች፥ ጌታችንም መሬትን
ምነው ሸሸሽ ቢላት እነሆ በቃል ብቻ አዝዞ የፈጠረኝ ጌታ ወደ እኔ ሲመጣ ከበደኝ ብላ
ትመልስለታለች፥ ጌታችንም በዚያ ያለችውን ሥፍራ ምድረ ከብድ ብሎ ሰየማት።
ጌታችን ለጻዲቁ እነሆ እኔ ምን እንዳደርግልህ ትፈልጋለህ? ሲላቸው ጻድቁም እነሆ
ስለሁሉም ነገር ስምህ የሚመሠገን ጌታ ሆይ የኢትዮጵያን ምድር ማርልኝ ብለው
ይማጸኑታል፤ ጌታም እነሆ ያልከው ይፈፀማል፥ ስምህን ለጠራ ዝክርህንም ለዘከረ እስከ 15
ትውልድ ድረስ እምርልሀለው፥ ኢትዮጵያንም የአስራት ሀገር አድርጌ ሰጥቼሀለው ብሎ ቃል
ይገባላቸዋል።
አባታችንም በ562 ዘመናቸው አረፉ፥
የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው። መዝ᎐፻፲፪፥፮ ምሳ᎐፲፥፯
አሜን አሜን አሜን።
እንኳን አደረሳችሁ
Join For More👇
@amde_haymanot
@amde_haymanot
. #እንኳን አደረሳችሁ።
👇አጭር ታሪክ ስለ ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ👇
አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ግብጻዊ ሲሆኑ እስከ 300 ዓመታቸው ድረስ በጾም
ጸሎት ሲያገለግሉ ከቅዩ በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ
ያዛቸዋል፥ በቅዱስ ገብርኤል አማካኝነት በንፋስ ሰረገላ ከሶስት አንበሶች እና ነብሮች ጋር
አድርጎ በ11ኛው መቶ ክ/ዘመን በንጉስ ላሊበላ ወቅት ወደ ኢትዮጵያ ያመጣቸዋል።
አባታችን ኢትዮጵያ ከመጡ በኋላም በጾምና ጸሎት ስለ ኢትዮጵያ ሕዝቦች አጥብቀው
ይጸልዩ ነበር፤
በዚህም ጸሎታቸው ምክንያት ጌታ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል፥ ሆኖም አባታችን የሚፈልጉት
ሙሉ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲማርላቸው ነበር፥ በዚህም በጸሎት እየተጉ ሳለ ሰይጣን ውኃ
በተጠማ ቁራ ተመስሎ ጸሎታቸውን ለማስታጎል ከአይናቸው ውስጥ ያለውን ውኃ ቢጠጣም
ጸሎታቸውን አላቋረጡም ነበር።
አባታችን በአጠቃላይ ለ562 ዘመን የኖሩ ሲሆን ዕረፍታቸውም እንዲህ ነበር፦
መጋቢት ፩ በዕለተ ዕረቡ ብሔረ ሕያዋን በመሄድ በዚያ ከሚኖሩ ቅዱሳን ጋር ቆይተዋል።
መጋቢት ፪ ሐሙስ ዕለት ከብሔረ ሕያዋን በመመለስ ገድላቸውን አጽፈዋል።
መጋቢት ፫ አርብ ይታመማሉ።
መጋቢት ፬ ቅዳሜ በጸና ቢታመሙም ከጸሎታቸው አልተስተጓጎሉም ነበር።
ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ በጸና በመታመማቸው መሬት ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ይቀመጣሉ፥
በዚህን ጊዜ ከሰማይ ወደ ምድር እንደሚዘረጋ መሠላልን የመሠለ ነገር ቁልቁል ይወርዳል፤
በዚህም ጌታችንና እናቱን ጨምሮ ቅዱሳን ሰዎችና መላዕክት አባታችን ወዳሉበት ይመጣሉ፥
በዚህ ጊዜ መሬት የጌታዋን መምጣት ስትመለከት ወደ ኋላዋ ትሸሻለች፥ ጌታችንም መሬትን
ምነው ሸሸሽ ቢላት እነሆ በቃል ብቻ አዝዞ የፈጠረኝ ጌታ ወደ እኔ ሲመጣ ከበደኝ ብላ
ትመልስለታለች፥ ጌታችንም በዚያ ያለችውን ሥፍራ ምድረ ከብድ ብሎ ሰየማት።
ጌታችን ለጻዲቁ እነሆ እኔ ምን እንዳደርግልህ ትፈልጋለህ? ሲላቸው ጻድቁም እነሆ
ስለሁሉም ነገር ስምህ የሚመሠገን ጌታ ሆይ የኢትዮጵያን ምድር ማርልኝ ብለው
ይማጸኑታል፤ ጌታም እነሆ ያልከው ይፈፀማል፥ ስምህን ለጠራ ዝክርህንም ለዘከረ እስከ 15
ትውልድ ድረስ እምርልሀለው፥ ኢትዮጵያንም የአስራት ሀገር አድርጌ ሰጥቼሀለው ብሎ ቃል
ይገባላቸዋል።
አባታችንም በ562 ዘመናቸው አረፉ፥
የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው። መዝ᎐፻፲፪፥፮ ምሳ᎐፲፥፯
አሜን አሜን አሜን።
እንኳን አደረሳችሁ
Join For More👇
@amde_haymanot
@amde_haymanot