ATC NEWS


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Образование


#ADDIS_ABABA : ETHIOPIA
ለመልዕክት 👇🏻
@mujaabot
For Advertisement👇🏿
@atcads

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Образование
Статистика
Фильтр публикаций


#Reminder

የፋይዳ መታወቂያ አውጥተዋል?

በሰኔ 2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና ለመውሰድ ተፈታኞች የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ሊያወጡ እንደሚገባ ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል።

የመንግሥት እና የግል ዩኒቨርሲቲዎች የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ በማድረግ ላይ ይገኛሉ።

የመውጫ ፈተናውን ለመውሰድ ምዝገባውን በጊዜ በማድረግ የፋይዳ መታወቂያዎን ይያዙ።


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


7 ሳይቶችን ሰርተን አስረክበናል !!!

ሳር ቤት  ዘመናዊ አፓርትመንት እንደገና !!

የ40% ቅናሽ ከቴምር ፕሮፐርቲስ !!
60% እናንተ !! እኛ 40% 

ይሄ የበዓል ስጦታችሁ ነው !!  በካሬ 64,200 !!

ባለሁለት መኝታ 5,649,600 ሚሊየን
ባለሦስት መኝታ 8,346,000 ሚሊየን ይፍጠኑ !!

ለበለጠ መረጃ በ0943155542 ይደውሉ።


ወራቤ ዩኒቨርሲቲ ለወራቤ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ከ1 ሚሊየን 2 መቶ ሺ ብር በላይ የሚገመት የመማሪያ ክፍል እደሳት እና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

ወራቤ ዩኒቨርሲቲ በወራቤ ከተማ አስተዳደር ለሚገኘው ወራቤ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት የቅድመ አንደኛ ተማሪዎች መማሪያ ክፍል እድሳት እና የህጻናት መጫወቻ እና የመማሪያ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርጓል።

150 ወንበር እና ጠረጴዛዎች፣ 30 ፍራሾችን፣ መጽሃፍት፣ የውሃ ማጠራቀሚያ ሮቶ፣ ለመምህራን የማስተማሪያ ቁሳቁስ እና የመማሪያ ክፍል የግንባታ እደሳቱን ጨምሮ በአጠቃላይ ከ1 ሚሊየን 2 መቶ ሺ ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ አድርጓል ።

በስፍራው ተገኝተው ድጋፉን ያበረከቱት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኢንጂነር ተውፊቅ ጀማል አሁን የተደረገው ድጋፍ ጊዜያዊ መሆኑንና በቀጣይ ህፃናት የትምህርት ጊዜያቸውን በአግባቡ የሚከታተሉበትን ሁኔታ የማመቻቸት ስራ በተለይ በግንባታ በኩል ተጨማሪ ክፍሎችን ዩኒቨርሲቲው እንደሚገነባ ገልጸዋል።

ህጻናት ላይ በትኩረት መስራት ለሀገራችን ዘላቂ ዕድገትና ለውጥ መሠረት መጣል ስለሆነ ወራቤ ዩኒቨርሲቲ መሠል ስራዎችን በተጠናከረ መልኩ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ፣ ምርምር፣ ቴክኖሎጂ ሽግግር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዚዳንት ረ/ፕ አንዋር አህመድ ወራቤ ዩኒቨርሲቲ ከሚያከናውናቸው ዋና ዋና ተግባራት አንዱ የማህበረሰብ አገልግሎት ስራ ትምህርት ቤቶችን የመደገፍ ተግባር እንደሆነ ጠቁመው ህፃናት ትምህርታቸውን በአግባቡ እንዲከታተሉ የማድረጉን ስራ እንደተቋም ኮሌጆች ተከፋፍለው በየዘርፋቸው የመደገፍ ስራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል ።

የስልጤ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሹክራላ አወል በበኩላቸው ወራቤ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ በሚያደርጉ ተግባራት ላይ ሁሌም ግንባር ቀደም መሆኑን አውስተው በተለይ ለትምህርት ቤቶች ከመማሪያ ቁሳቁስም ሆነ አቅም ግንባታ ስልጠናዎችን በመስጠት በርካታ አበረታች ስራዎችን እየሰራ ያለ ተቋም ነው ብለዋል።

በተለይ የዛሬው ድጋፍ የትምህርት ጥራትን ከታች ጀምሮ ለማምጣት የሚያግዝ በመሆኑ የቀጣይ ትውልድንም የሚያነቃቃ ተግባር እንደሆነ ገልፀው ስለተደረገው ድጋፍ ዩኒቨርሲቲውን በማህበረሰቡ ስም አመስግነዋል ።

ቁሳቁሱን የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት አካላት ለስልጤ ዞን እና የወራቤ ከተማ አስተዳደር አመራር አካላት አስረክበዋል።


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


#BahirDarUniversity

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በአሁኑ ወቅት የሚሰጠው ምንም ምንም ዓይነት ነጻ የትምህርት ዕድል እንደሌለ ገልጿል፡፡

"ነጻ የትምህርት ዕድል እንሰጣለን በማለት በሐሰተኛ መረጃ ገንዘብ የሚሰበስቡ እንዳሉ ለማወቅ ችለናል" ያለው ዩኒቨርሲቲው፤ ከሐሰተኛ መረጃ እንድትጠነቀቁና በተሳሳተ መረጃ ገንዘባችሁን እንዳታባክኑ በጥብቅ አሳስቧል፡፡

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


#TigrayEducationBureau

በትግራይ ክልል የ2017 ዓ.ም ሁለተኛ ዙር የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ከሰኔ 4-6/2017 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

የክልሉ አጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማረጋገጫ ኤጀንሲ የትምህርት ምዘናና ሀገር አቀፍ ፈተናዎች ዳይሬክቶሬት ለወረዳ ትምህርት ጽ/ቤቶች በላከው ሰርኩላር፥ ጽ/ቤቶቹ አስፈላጊውን ዝግጅት እነዲያደርጉ አሳስቧል።

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


በሶስቱም ቅርንጫፎቻችን ( መገናኛ፣ ሜክሲኮና ጀሞ) እንዲሁም በኦንላይን በምንሰጣቸዉ  ስልጠናዎች በ Advanced level እና 90% practical በሆነ ካሪኩለም እንዲሁም ዘመኑ ያፈራቸዉን ሙሉ የላብራቶሪና የስቱዲዮ እቃዎችን በማሟላት ከሁሉም ስልጠናዎቻችን ላይ ታላቅ የዋጋ ቅናሽ አድርገናል! አሁኑኑ ይመዝገቡና ትልቅ ለዉጥ ወደሚያመጡበት ተቋም ይቀላቀሉ!

ከትምህርትና ስልጠና ጥራትና ቁጥጥር ባለስልጣን ሙሉ ዕዉቅና ካለዉ ሰርተፊኬት ጋር!

እኛጋ ለመሰልጠን ኮምፕዩተር መግዛት አያስፈልግዎትም!

የብዙ አመት ልምድ እና ብቃት ባላቸዉ አሰልጣኞች!

🎯 Graphics Design
🎯 Video Editing
🎯 Digital Marketing
🎯 Photography
🎯 Videography
🎯 Cinematography
🎯 Adobe photoshop
🎯 Fullstack Web app development 
🎯 Programming Language
🎯 Interior Design
🎯 English Language
🎯 Database
🎯 Basic Computer
🎯 Accounting Softwares
🎯 Engineering Softwares
🎯 SPSS & STATA
🎯 MS-Project
🎯  Foreign & Local Languages

አድራሻ:-
1. መገናኛ መተባበር ህንፃ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 419 (ሊፍት ይጠቀሙ)  ☎️ 0991929303

2. ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 639 (ሊፍት ይጠቀሙ ሁለተኛዉን ሊፍት) ☎️ 0991929304

 3. ጀሞ 1 አንደኛ በር ካኩ ቢዝነስ ሴንተር 3ኛ ፎቅ ☎️ 0991926707

Join telegram https://t.me/topinstitutes

tiktok https://Tiktok.com/@topinstitute

Facebook https://www.facebook.com/Topinstitutes


Репост из: In Africa Together
🌏IAT & IAIC INTERNATIONAL STUDENT FAIR🌎

✨Ready to study abroad and change your life?

🎓This is your chance to meet top university representatives from:

USA 🇺🇸 Canada 🇨🇦 Sweden 🇸🇪
Germany 🇩🇪 France 🇫🇷 Finland 🇫🇮 Denmark 🇩🇰 and more!

📆 May 3 & 4
🕐 3:00 - 10:00 (LT)
📍Ghion Hotel

Don’t forget to bring:
🪪Passport or Birth certificate
📚Transcripts or Student copy

✅Entrance Fee: FREE!!

💡Opportunities:
- Study loan options
- Learn about the scholarships offered

🏆Don’t miss this golden opportunity to take your future global!

🆓No entrance fee — just register now!

Click the link below to book your spot: 🔗
https://forms.gle/81ZueGK5d9R9Cg9P6


#AmharaEducationBureau

በአማራ ክልል የ2017 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል የመጀመሪያ ዙር ክልል አቀፍ ፈተና ሰኔ 3 እና 4/2017 ዓ.ም እንዲሁም የ6ኛ ክፍል የመጀመሪያ ዙር ክልል አቀፍ ፈተና ሰኔ 5 እና 6/2017 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ለሁሉም የዞን፣ የከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያዎች በላከው ሰርኩላር፥ የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ደረጃ (6ኛ ክፍል) እና የመካከለኛ ደረጃ (8ኛ ክፍል) ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና በሁለት ዙር ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጿል፡፡


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ 10ኛዉን ከተማ አቀፍ የሳይንስ የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ ከሚያዚያ 16-18/2017 ዓ.ም ድረስ “በፈጠራ ስራ የተካነ ትጉህ ትውልድ ለሀገር ብልጽግና!” በሚል መሪ ሀሳብ ከፍተኛ የመንግስት የሰራ ሀላፊዎች ፣ የትምህርት አመራሮች ፣ የትምህርት ባለድርሻ አካላት ፣ የትምህርት ባለሙያዎች ፣ መምህራንና ተማሪዎች በተገኙበት በወዳጅነት ፓርክ በዛሬው እለት ይካሂዳል፡፡

የሶስት ቀናት ቆይታ የሚያደርገው 10ኛው ከተማ አቀፍ የሳይንስ የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ የመክፈቻ መርሀ ግብሩም በዛሬው እለት በድምቀት የሚካሄድ ይሆናል፡፡

በ2017 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን ከትምህርት ቤት ጀምሮ እስከ ከተማ በተካሄደው የተማሪዎች የሳይንስና የፈጠራ ሥራ ዐውደ ርእይ በ 5000 የቡድንና የግል ተወዳዳሪዎች 3100 የፈጠራ ሥራዎች ተሠርተው ለዕይታ ቀርበዋል፡፡


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ የማጣራት ሥራ በይፋ አስጀምረናል- አቶ አረጋ ከበደ

የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም አካል የሆነውን ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ የማጣራት ሥራ በይፋ አስጀምረናል ሲሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ አስታወቁ፡፡

ርዕሰ መሥተዳድሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ ፤ ዛሬ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ማስፈጸሚያ ዕቅድን ከአሥተዳደር ምክር ቤት አባላት ጋር ገምግመናል ብለዋል።

የሪፎርም ሂደቱ በጥሩ ሁኔታ ላይ የሚገኝ መሆኑን አረጋግጠናል ያሉት አቶ አረጋ፤ የሪፎሩሙ አካል የሆነውን ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ የማጣራት ሥራም በይፋ አስጀምረናል ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ለሕዝባችን ዘላቂ ልማት እና ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚተጋ ሲቪል ሰርቫንት ለመገንባት የሪፎርም ሥራውን ከፍ ባለ ቁርጠኝነት ለመፈፀም እንሠራለን ብለዋል፡፡

#FMC
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


የአሜሪካ ኤምባሲ ማስጠንቀቂያ

በቪዛዎ ከተፈቀደሎት ጊዜ በላይ ከቆዩ ወደፊት ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ለመጓዝ ቋሚ እገዳ ሊጣልቦትና በህግ ሊያስጠይቅ ይችላል ብሏል።

የቆንስላ ኦፊሰሮች የኢሚግሬሽን ሙሉ ታሪክዎን ማግኘት ይችላሉ።  በተጨማሪም ከዚህ በፊት የተላለፉት የኢሚግሬሽን ሕግ ጥሰቶች ካሉም የቆንስላ ኦፊሰሮች ያውቃሉ።  ቪዛዎን በትክክል መጠቀም የእርስዎ ኃላፊነት ነው"ብሏል።


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news

Показано 11 последних публикаций.