ስለ ነገ ጨዋታ🗣: "ባለፈው በሊጉ ካደረግነው የተለየ ጨዋታ ነው፤ ከሜዳ ውጪ ነው የምንጫወተው። ጫና ውስጥ ሊያስወድቁን ይሞክራሉ እና የሚኖረው ድባቡ በጣም የተለየ ይሆናል።"
🗣: "ነገ ዋንጫውን ማሸነፍ አንችልም ግን ልናጣው እንችላለን፤ እኛ ደግሞ ያንን አንፈልግም።"
ኦልሞ እና ጋቪ በነገው ጨዋታ ላይ ስለመገኘት?
🗣: "ዳኒ ለነገው ጨዋታ ዝግጁ ነው፤ እና ለሁለተኛው አጋማሽ አማራጭ ነው፤ ለጋቪ የቀመጠለት ፕሮቶኮል አለ እና በነገው ጨዋታ ላይ አይኖርም። ዛሬ ከቡድኑ ውጪ ልምምዱን ማድረጉ ጥሩ ነው ምክንያቱም ግጭቱ በጣም ሀይለኛ ነበር፤ ጉዳቱ ላጋጠመው የተጋጣሚው ቡድን ተጫዋችም ከባድ ስለነበር ነው።"
🎙
ስለ ፍሬንኪ?🗣: "ሁልጊዜ ተጫዋቾችን በሚጫወቱበት ያወዳድራሉ፣ ግን እንደዛ አይደለም የሚሰራው። ነገ እና እሁድ ሌላ ጨዋታ ይኖረናል። ሁሉንም ተጫዋቾች እፈልጋለሁ፤ አማራጮች በማግኘቴ ደስተኛ ነኝ። ፍሬንኪ በጣም ጥሩ ተጫዋች ነው ግን ካሳዶም እንዲሁ። እኔ ማንንም ልምረጥ ለውጥ አያመጣም ዋናው ነገር ቡድኑ ነው።"
ስለ ኦልሞ?🗣: "ዳኒ ለእኛ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ በብዙ ጨዋታዎች አሳይቷል። ጎሎችን አስቆጥሯል፣ ኳሱን እንዴት እንደሚይዝ ያውቃል። እንደ እሱ ያሉ ተጫዋቾች በቡድኑ ውስጥ መኖራቸው አስፈላጊ ነው ነገርግን እሱን መንከባከብ አለብን። ብዙ ተጎድቷል ነገርግን እንዲጫወት ማድረግ አለብን። ለመላመድ ምን እንደሚሰማው በማወቅ ጥንቃቄ ማድረግ አለብን። እሱ ለእኛ በጣም አስፈላጊ ነው።"
🎙
ሪያል ማድሪድ ስለ ዳኞች ስላወጣው መግለጫ?🗣: "እውነት ለመናገር ስለሱ ማውራት አልፈልግም። እነሱ በእንደዛ መልክ አደረጉት ግን ያ የእኛ ስታይል አይደለም። ሰበብ አንሰጥም፤ እያንዳንዱ ክለብ የራሱ መንገድ አለው። ሰው ነን እንሳሳታለን። ዳኞች ከባድ ስራ ስላለባቸው ልንከባከባቸው ይገባል፤ ለእነሱ ቀላል አይደለም።"
ተጨማሪ ስለመግለጫ የተናገረው...
🗣: "ሁሉንም ነገር የተናገርኩት ይመስለኛል። እዚህ ክለብ ስመጣ ሰበብ ወይም ቅሬታ አልፈልግም ብያለው:: ጨዋታዎቻችንን ማሸነፍ አለብን እና ጥቂት ነጥቦችን እንደጣልን እናውቃለን፤ ይህ የእኛ ጥፋት ነው፤ ወደፊት ምን ማድረግ እንደምንችል ማየት አለብን። እሁድ ሌላ አስፈላጊ ጨዋታ አለን, ነገር ግን የመጀመሪያው ነገር ቫሌንሲያ ማሸነፍ ነው።"
@BARCAFANSETHIOPIA @BARCAFANSETHIOPIA