#Gambella
በጋምቤላ መምህራን ትምህርትና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሚፈተኑ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ተፈታኝ ተማሪዎች " የጤና እክል " ገጥሟቸው እንደነበር የክልሉ የመንግስት አሳውቋል።
ተፈታኞቹ ትላንት ምሽት ከ1:30 ጀምሮ ወደ ጋምቤላ አጠቃላይ ሆስፒታል አቅንተው ተገቢው ህክምና እየተደረገላቸው ነው ተብሏል።
ተፈታኞቹ የገጠማቸው የጤና እክል መነሻው " የምግብ መመረዝ " አልያም " የተበላሸ ምግብ መብላት " መሆን አለመሆኑን በማጣራት ላይ ክልሉ አሳውቋል።
ሆስፒታል ከገቡ ተማሪዎች መካከል ለህይወት የሚያሰጋ የጤና እክል የደረሰባቸው እንደሌሉ የገለፀው ክልሉ አብዛኞቹ አገግመው ወደ ፈተና ማዕከላቸው መመለሳቸውን አመልክቷል።
በአሁኑ ሰዓትም ህክምና በመከታተል ላይ ያሉ ተፈታኞች እንደሚገኙ የተጠቆመ ሲሆን በህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለ ክልሉ አሳውቋል።
" የተፈታኝ ወላጆች ልጆቻቸው በመልካም ጤንነት ላይ የሚገኙ በመሆናቸው እንዳይደናገጡ " ያለው የጋምቤላ ክልል " ምክንያቱ ምን እንደሆነ የህክምና ባለሙያዎች የሚሰጡትን መረጃ ለህዝብ ይፋ እናደርጋለን " ብሏል።
በጋምቤላ ክልል በተከሰተው የፀጥታ ችግር ምክንያት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ እና በጋምቤላ መምህራን ትምህርትና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እንዲሰጥ መወሰኑ አይዘነጋም።
https://t.me/+-4xFxbBrBfIzNmE0
በጋምቤላ መምህራን ትምህርትና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሚፈተኑ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ተፈታኝ ተማሪዎች " የጤና እክል " ገጥሟቸው እንደነበር የክልሉ የመንግስት አሳውቋል።
ተፈታኞቹ ትላንት ምሽት ከ1:30 ጀምሮ ወደ ጋምቤላ አጠቃላይ ሆስፒታል አቅንተው ተገቢው ህክምና እየተደረገላቸው ነው ተብሏል።
ተፈታኞቹ የገጠማቸው የጤና እክል መነሻው " የምግብ መመረዝ " አልያም " የተበላሸ ምግብ መብላት " መሆን አለመሆኑን በማጣራት ላይ ክልሉ አሳውቋል።
ሆስፒታል ከገቡ ተማሪዎች መካከል ለህይወት የሚያሰጋ የጤና እክል የደረሰባቸው እንደሌሉ የገለፀው ክልሉ አብዛኞቹ አገግመው ወደ ፈተና ማዕከላቸው መመለሳቸውን አመልክቷል።
በአሁኑ ሰዓትም ህክምና በመከታተል ላይ ያሉ ተፈታኞች እንደሚገኙ የተጠቆመ ሲሆን በህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለ ክልሉ አሳውቋል።
" የተፈታኝ ወላጆች ልጆቻቸው በመልካም ጤንነት ላይ የሚገኙ በመሆናቸው እንዳይደናገጡ " ያለው የጋምቤላ ክልል " ምክንያቱ ምን እንደሆነ የህክምና ባለሙያዎች የሚሰጡትን መረጃ ለህዝብ ይፋ እናደርጋለን " ብሏል።
በጋምቤላ ክልል በተከሰተው የፀጥታ ችግር ምክንያት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ እና በጋምቤላ መምህራን ትምህርትና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እንዲሰጥ መወሰኑ አይዘነጋም።
https://t.me/+-4xFxbBrBfIzNmE0