Brook News ብሩክ ኒዉስ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


Breaking News from all over the world about our beloved country Ethiopia.

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


ሁሉን በአንድ ቦታ የምታገኙበት አማዚያ ኮስሞቲክስ‼️

በታዋቂው ቲክቶከር ባቢ (Yohanis Teshome) በመሀል ቦሌ የተከፈተው አማዚያ ኮስሞቲክስ የተለያዪ Skin Care ፕሮዳክቶችን በተመጣጣኝ እና በማከፋፈያ ዋጋ ይዞ ቀርቧል።

Contact- +251933513324
@Babi_1916
📍ቦሌ አደይ አበባ ስታዲየም ፊት ለፊት mmk ህንጻ ጎን እቱ የገበያ ማዕከል #19


ይሄን ቻናል ይቀላቀሉ።
https://t.me/socailmidea


#የጥንቃቄ #መልክት

የተለያዩ የገበታ ጨው ምርት ዓይነቶች በሚመለከተው አካል የደረጃ ምልክት የመጠቀም ፈቃድ ሳይሰጣቸውና ጥራትና ደረጃቸው ሳይረጋገጥ ገበያ ላይ በመገኘታቸው ህብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው ባለስልጣኑ አሳሰበ፡፡

አዲስ አበባ፡ መጋቢት 4፣2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በቅርቡ ገበያ ላይ ባደረገው ቁጥጥር አምስት የተለያዩ የገበታ ጨው ምርቶች የብሔራዊ የደረጃ ምልክት የመጠቀም ፈቃድ ሳያገኙ ምልክቱን ለጥፈው ገበያ ላይ ውለው ተገኝተዋል፤በመሆኑም እነዚህ ምርቶች ጥራታቸውና ደህንነታቸው ያልተረጋገጡ በመሆናቸው ህብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው ባለሰልጣኑ ያሳስባል፡፡

ምስላቸው እና ዝርዝራቸው ከዚህ በታች የተቀመጡ የተለያዩ የገበታ ጨው ምርቶች የብሔራዊ ደረጃ ምልክቱን የመጠቀም ፈቃድ ያላገኙና ጥራት እና ደህንነታቸው ያልተረጋገጠ በመሆናቸው ያሳውቃል፡፡

1. ሊኑ የገበታ ጨው /LINU IODIZED SALT /፣

2. ታሪክ የገበታ ጨው /TARIK TABLE SALT /፣

3. SALT BAY፣

4. ሺማ አዮዳይዝድ ጨው /SHIMA IODIZED SALT/

5. እና ጂ.ኤም ኤዳይዝድ ጨው /G.M Iodized salt/ በሚባል የምርት ስም የሚጠሩ ናቸው።
Via- #EFDA


የ104.4 የመቐለ ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያ በደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በሚመራው ህወሓት በተመደቡ የመቐለ ከተማ አመራሮች አባላት ቁጥጥር ስር መዋሉ ተሰምቷል።

አመራሮቹ በሰራዊት ታጅበው ሬድዮ ጣቢያውን እንደተቆጣጠሩት ተነግሯል።

ምናልባትም በቀጣይ ደግሞ የድምፂ ወያነ እና ትግራይ ቴሌቪዥን ሚድያዎችን ሊያዙ እንደሚችሉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ከታማኝ ምንጮች ለመስማት ችሏል።

መገናኛ ብዙሃኑ ዛሬ ከአዲስ አበባ የተሰጠውን የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳን መግለጫ እስካሁን አላስተላለፉም።

tikvahethiopia


"አሁን ባለዉ ሁኔታ መፈንቅለ መንግስት እየተፈጸመ ነዉ"‼️- አቶ ጌታቸዉ ረዳ

https://www.youtube.com/watch?v=VX4nf8eldtE


ፈጣን መረጃ 👇👇
የሚሸጥ 2 active የTiktok Account ለ content crእጅግ በቅናሽ ዋጋ አሁኑኑ ይግዙ

ሻጩን በቀጥታ ለማግኘት
@mikolas43
0701290257


በሟች ወ/ሮ ቀነኒ አዱኛ ዋቆ አሟሟት ዙሪያ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ!
***
በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 3 ልዩ ቦታው ሰንሻይን ቤቶች ፊት ለፊት ከሚገኘው ውዳሴ ህንፃ ላይ ነዋሪ የነበረችው ሟች ወ/ሮ ቀነኒ አዱኛ ዋቆ መጋቢት 01 ቀን 2017 ዓ/ም ከሌሊቱ 10፡00 ሠዓት አካባቢ ከቤቷ የማብሰያ ክፍል በኩል ካለው በረንዳ 5ኛ ፎቅ ላይ ለጊዜው ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ወድቃ ለህክምና እርዳታ ወደ ያኔት ሆስፒታል እየተወሰደች ባለበት ወቅት ህይወቷ አልፏል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ መረጃው ከደረሰው በኋላ የምርመራ ቡድን በማዋቀርና ቦታው ድረስ በመሄድ ተገቢውን የቴክኒክና የታክቲክ መረጃዎችን ያሰባሰበ ሲሆን የሟችንም አስከሬን ወደ ዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል ለተጨማሪ ለምርመራ እንዲሄድ አድርጓል፡፡

ሟች ወ/ሮ ቀነኒ አዱኛ በወቅቱ ከበረዳ ላይ በወደቀችበት ሰዓት ፖሊስ በቤቱ ውስጥ የነበረውን ባለቤቷን ድምፃዊ አንዷለም ጎሳን በቁጥጥር ስር በማዋልም ምርመራ እያጣራ ሲሆን በቀጣይ የመጨረሻውን የምርመራ ውጤትም ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ እያስታወቀ በተለያዩ ማህበራዊ ድረ ገጾች ላይ ከፖሊስ የወንጀል ምርመራ ውጤት በፊት የሚናፈሱ መረጃዎች ተገቢነት የሌላቸው ከመሆኑም ባሻገር በምርምራ ሒደቱ ላይ የሚያሳድረውን አሉታዊ ተፅህኖ በመገንዘብ የተሳሳተ መረጃ የሚያስተላልፉ እና የሚያሰራጩ ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳስቧል፡፡


መቀሌ ውጥረት ነግሷል‼️
ዛሬ ለሊቱን ጀምሮ ብዛት ያለው  ሰራዊትና መትረየስ የጫኑ ፓትሮል መኪኖች በመቀሌ ከተማ በከፍተኛ ሁኔታ  እንቅስቃሴ እያደሩጉ እንደሚገኙ ታውቋል‼️
በደብረፂዮን የሚመራው የህወሓት ቡድን በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከሌሊቱ 8:00 ሰዓት መግለጫ ያወጣ ሲሆን ህዝባዊ ሰራዊታችን በከሃዲ ቡድን ሴራ አይፈርስም ብሏል።
ህወሓት በመግለጫው የግዚአዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንትን ጨምሮ ብሄራዊ ክህደት የፈጸሙ እና እየሰሩ ያሉ አመራሮችን በማባረር በጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ ያላቸውን ውክልና አንስቻለሁ ያለ ሲሆን ነገር ግን ጊዚያዊ ፕሬዝዳንቱ እና ሌሎች የቡድኑ አባላት ከህግና ስርዓት ውጪ ፀረ ህዝብ ተግባራቸውን ቀጥለዋል ብለዋል።

የህዝባችንን አንድነት በማደፍረስ የትግራይን ሁለንተናዊ አቅም በማዳከም ብሄራዊ ክህደት እየፈፀመ ያለው የቀድሞ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አሁን በትግራይ ህዝብ ላይ የታወጀውን የዘር ማጥፋት ለመፋለም የተደራጀውን የትግራይ ሰራዊት ለመበተን ድርጊቱን አጠናክሮ ቀጥሏል"ብሏል።
የቀድሞ ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከስልጣናቸው እና ከኃላፊነታቸው ውጪ የትግራይ ጦር ግንባር አመራሮችን እና ጄኔራሎችን  አግደዋል ያለው ህወሃት፣ይህ ማዕቀብ መሠረተ ቢስ እና ተግባራዊ ሊሆን የማይችል ቢሆንም ህዝባዊ ትግሉን ከህግ እና ከስርዓት ውጭ ለማድረግ ቡድኑ ሌት ተቀን እየሰራ መሆኑን ያሳያል ማለቱን አዩዘሀበሻ ከመግለጫው ተመልክቷል።
አዩዘሀበሻ


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ሃዲድ ላይ ተኝቶ ባቡር በላዩ ላይ ከሄደበት በኋላ በተአምራዊ ሁኔታ የተረፈው ግለሰብ።

በፔሩ ዋና ከተማ ሊማ ውስጥ አንድ ግለሰብ ሰክሮ በከተማዋ ውስጥ በሚያቋርጥ የባቡር ሃዲድ ላይ ተኝቶ ሳለ ባቡሩ በላዩ ላይ ሄዶበታል። ነገር ግን ግለሰቡ ከባድ ጉዳት ሳይደርስበት ከአሰቃቂው አደጋ ለመትረፍ ችሏል። የአካባቢው አስተዳደር ግለሰቡ በተአምራዊ ሁኔታ የተረፈበትን አሰቃቂ አደጋ የሚያሳይ ቪዲዮን አጋርቷል።

Brook News


የመከላከያ አቅሞችን የምናጎለብተው “ለመዋጋት አይደለም” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ

ኢትዮጵያ የመከላከያ አቅሟን የምታገጎለብተው “ትናንሽ አቅም ይዘው ለሚሳሳቱ ኃይሎች ብዙ ጊዜ እንዲያስቡ ለማስቻል” እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ “እነዚህን አቅሞች የምናጎለብተው ለመዋጋት አይደለም። ውጊያን ለማስቀረት ነው” ብለዋል።

አብይ ይህን ያሉት “ስካይ ዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪ” የተባለ የሰው አልባ አውሮፕላኖች (ድሮኖች) ማምረቻ ትላንት ቅዳሜ የካቲት 29፤ 2017 በመረቁበት ወቅት በሰጡት ገለጻ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለወታደራዊ አገልግሎት የሚውሉ ምርቶችን በሚያመርቱ ፋብሪካዎች ተገኝተው ማብራሪያ ሲሰጡ፤ የትላንቱ በአንድ ሳምንት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜያቸው ነው።

ባለፈው ረቡዕ በኦሮሚያ ክልል አምቦ ከተማ አቅራቢያ የሚገኘውን የሆሚቾ ጥይት ፋብሪካ የጎበኙት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ፤ ኢትዮጵያ ከወታደራዊ ግብዓት አንጻር የነበረባትን “ውስንነት ከሞላ ጎደል ፈትታለች” ብለው ነበር። የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፋብሪካ ጉብኝትም ሆነ ያቀረቡት ገለጻ፤ ኢትዮጵያ “ከኤርትራ ጋር ወደ ሌላ ዙር ጦርነት ለመግባት በዝግጅት ላይ ለመሆኗ ማሳያ” አድርገው የቆጠሩ ወገኖች አሉ።

ይህን አመለካከት የተረዱ የሚመስሉት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በትላንቱ ገለጻቸው፤ “እነዚህን አቅሞች የምናጎለብተው ለመዋጋት አይደለም። ውጊያን ለማስቀረት ነው። ትናንሽ አቅም ይዘው ለሚሳሳቱ ኃይሎች፤ ብዙ ጊዜ [ሰጥተው] እንዲያስቡ ለማስቻል ነው። ውጊያን ለማስቀረት (deter) ለማድረግ ከፍተኛ አቅም ስላለው ነው” ሲሉ ተደምጠዋል።

Via ኢትዮጵያ ኢንሳይደር
Via ዳጉ_ጆርናል


ዛሬ የሴቶች ቀን ነው !

ለሚስቴ ምን ልስጥ ብለህ ተጨንቀሃል::
በዚህ ስልክ ደዉል እና ያለህበት ቦታ እናደርሳለን::
ሁሉንም አይነት የስጦታ ዕቃ እኛ ጋር ያገኛሉ::
ግሩም ስጦታዎች ነን::

ይደውሉ 0952798480

ይሄን ቻናል ይቀላቀሉ::
https://t.me/Girumgifts


🔥 ጀማሪዎችን ለማበረታታት ብርፎሬክስ ለ11ኛ ዙር የዲሞ አካውንት ውድድር ይዞላችሁ መቷል።

🔥11ኛዙር የፎሬክስ ዲሞ አካውንት ውድድር
(ከመጋቢት 1 እስክ መጋቢት 13)

1️⃣ 1ኛ ሽልማት🥇 ፡ 60,000 ብር
2️⃣ 2ኛ ሽልማት🥈 ፡ 40,000 ብር
3️⃣ 3ኛ ሽልማት🥉 ፡ 15,000 ብር

🧡በዚውድድር ለመሳትፍ ከእናንተ ምንም አይነት ወጪ አያስፈልግም፤ በዲሞ አካውንት ብቻ ሰርታችሁ ጥሩ ልምድ ታካብታልችሁ ተሽላሚም ትሆናላችሁ።

📌ስለውድድሩ ሙሉ መረጃ ከታች የተቀመጠው የብርፎሬክስ ቴሌግራም አካውንት ላይ ታገኛላችሁ
👉👉👉@birrforex  👈👈👈

⭐️ውድድሩ የፊታችን መጋቢት 1 ይጀምራል፣ አሁኑኑ ወደ ብርፎሬክስ ቴሌግራም አካውንት በመሄድ ቦታችሁን ያዙ⭐️


#የሚዘጉ መንገዶች ስለማሳወቅ

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ከቢሊግርሃም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን ጋር በመተባበር የካቲት 29 እና 30 ቀን 2017 ዓ/ም በመስቀል አደባባይ የሚያደረገው የስብከተ ወንጌል አገልግሎት መርሀ ግብር ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።
***
በዚህም መሠረት በሁለቱም ቀናት ከቀኑ 5:00 ሠዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስኪጠናቀቅ ድረስ፦
. ከኦሎምፒያ ወደ መስቀል አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ)
. ከጥላሁን አደባባይ ወደ ሳንጆሴፍ መብራት (ጥላሁን አደባባይ ላይ)
. ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ (ለገሃር መብራት)
. ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድየም (ቴሌ ማቋረጫ ላይ)
. ከሀራምቤ መብራት ወደ መስቀል አደባባይ (ሀራምቤ መብራት ላይ )
. ከብሔራዊ ቤተ መንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ (ብሔራዊ ቤተመንግሥት ላይ)
. ከቅዱስ ዑራኤል አደባባይ ወደ መስቀል (ባምቢስ መቅረዝ ሆስፒታል መታጠፊያ) ላይ የሚዘጋ ሲሆን አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳስቧል።


በፕሬዚዳንት ትራምፕ የፖሊስ ኦፊሰርነት ሹመት የተሰጠው የካንሰር ታማሚ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለ13 ዓመቱ የካንስር ታማሚ ታዳጊ የፖሊስ ኦፊሰርነት ሹመት በመስጠት የልጅነት ህልሙ እውን እንዲሆን ማድረጋቸው የዓለምን ትኩረት ስቧል፡፡

ዲጄ ዳንኤል የተባለው የ13 ዓመት ታዳጊ ህልሙ የፖሊስ ባለሙያነት ቢሆንም፤ ከ2018 ጀምሮ ባጋጠመው የብሬን ካንሰር ህመም ምከንያት ሰባት ዓመታትን ከህመሙ ጋር በመታገል አሳልፏል፡፡

ለመሞት አምስት ወራት ብቻ እንደቀረው በዶክተሮቹ የተነገረው ታዳጊው፤ በመጨረሻዎቹ ሰዓታት የልጀነት ህልሙ እውን የሚሆንበት የፖሊስ ባሉሙያነት ሥራ በፕሬዚዳንት ትራምፕ ተሳክቷል፡፡
Via-FBC


ሰደድ እሳት

የእሳቱ መነሻ እየተጣራ ነው፣ከከምባታ ዞን ወደ ሀላባ ዞን ተደርሷል በአሁን ወቅት በሀላባ ምስራቅና ምዕራብ ጎርጣንቾ ቀበሌ ደን ውስጥ ነው እሳቱ እየነደደ የሚገኘው፣

እሳቱ እየነደደ የሚገኘው አከባቢ መኪና እንዲገባ ምቹ ስፍራ አይደለም ስምጠት ያለው ጉርጓድ በመኖሩ አስቸጋሪ አድርጎታል የዞኑ የአደጋ ስጋት አመራር ጽ/ቤት ከዌራ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ጉዳዩን በማጠራት ላይ እንደሚገኙ ተረድቻለሁ።

በስፍራው የምትገኙ ነዋሪዎች ብርቱ ጥንቃቄ አድርጉ!!

Mizhabe nejibe


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
#OMEGA_COMPUTER_TRADING

ሁሉንም አይነት ላፕቶፖች ከእኛ ጋር ያገኛሉ

ድርጅቶች, ለ ቢሮ ሰራተኛዎች እና ለ ተማሪዎች

ከ አስተማማኝ የ 1 አመት ዋስትና እንዲሁም ከ በቂ መስተንግዶው ጋር ይዘን እንጠብቆታለን።

እኛ ጋር መሸጥም ሆነ መግዛት ይችላሉ !!

የቴሌግራም ቻናል ሊንክ
https://t.me/Omegacomputer2

አድራሻ : - መገናኛ ማራቶን የ ገበያ ማእከል በ ዋናው መግቢያ መሬት ላይ ወይንም ግራውንድ: ቁጥር 15 OMEGA COMPUTER

Inbox @teddyjo1 Call 0911539252 : 0913667240


🔥 ጀማሪዎችን ለማበረታታት ብርፎሬክስ ለ11ኛ ዙር የዲሞ አካውንት ውድድር ይዞላችሁ መቷል።

🔥11ኛዙር የፎሬክስ ዲሞ አካውንት ውድድር
(ከመጋቢት 1 እስክ መጋቢት 13)

1️⃣ 1ኛ ሽልማት🥇 ፡ 60,000 ብር
2️⃣ 2ኛ ሽልማት🥈 ፡ 40,000 ብር
3️⃣ 3ኛ ሽልማት🥉 ፡ 15,000 ብር

🧡በዚውድድር ለመሳትፍ ከእናንተ ምንም አይነት ወጪ አያስፈልግም፤ በዲሞ አካውንት ብቻ ሰርታችሁ ጥሩ ልምድ ታካብታልችሁ ተሽላሚም ትሆናላችሁ።

📌ስለውድድሩ ሙሉ መረጃ ከታች የተቀመጠው የብርፎሬክስ ቴሌግራም አካውንት ላይ ታገኛላችሁ
👉👉👉@birrforex  👈👈👈

⭐️ውድድሩ የፊታችን መጋቢት 1 ይጀምራል፣ አሁኑኑ ወደ ብርፎሬክስ ቴሌግራም አካውንት በመሄድ ቦታችሁን ያዙ⭐️


ጥቆማ‼️

በሀገራችን ታማኝ የዜና ምንጮችን የሚያገኙበት የቴሌግራም ቻናል ነው!

ሊንክ👇
https://t.me/+gPveFwjiiXdiMDE0
https://t.me/+gPveFwjiiXdiMDE0

Показано 17 последних публикаций.