የድጋፍ ጥሪ ለቄስ ፈይሳ ቶለሳ
በአንድ ቀን 100,000 ዶላር ለወንድማችን ኤርሚያስ መሰብሰብ ተችሏል ለረዳችሁት ሰዎች እግዚአብሔር ዋጋችሁን በሰማይ ይክፈላችሁ 🙌🏾
40 አመት ላገለገሉ አባታችንም በአንድ ቀን 20,000 ዶላር መሰብሰብ አያቅተንም, ያላችሁ በገንዘባችሁ የሌላችሁ ሼር በማድረግ ሌሎች እንዲረዱ እናድርግ 🙏
➡️
https://gofund.me/93491becቄስ ፈይሳ ቶለሳ ይባላሉ። ላለፉት 40 ዓመታት በወንጌል ስራ እና የእግዚአብሔርን መንግሥት የማስፋፋት ሥራ ውስጥ በትጋት ሲሳተፉ ቆይተዋል። ለብዙ አመታት ባገለገሉት አገልግሎት ብዙ ዋጋ ከፍለዋል፣ ብዙ እንግልትና መከራ ደርሶባቸዋል። በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ፣ የማዕከላዊ ጊቤ ሲኖዶስ እና በሰበካ ደረጃ በኢጃጂ እና አካባቢው፣ እንዲሁም በተለያዩ የወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያናት አገልግለዋል።
በትምህርት እና በአገልግሎት ልምዳቸው ያገኙትን ለህዝቡ ለማካፈል "በቤተክርስቲያን ላይ የሚነሱ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው" በሚል ርዕስ መጽሐፍ ጽፈው አሳትመዋል። ሌላ መጽሐፍ ለማሳተምም በዝግጅት ላይ ነበሩ።
በመገናኛ ብዙኃን እግዚአብሔር የሰጣቸውን የወንጌል መልእክት በ ቲቪ፣ እንዲሁም በወንጌል ሬዲዮ በማቅረብ አገልግለዋል። በ 2015 ዓ.ም ፣ በዚህ የወንጌል ሥራ እያገለገሉ ሳሉ ድንገት በ'Stroke' በሽታ ተያዙና መላ አካላቸው ፓራላይዝድ ሆነ:: ህመሙ በጣም በረታባቸው፣ መላ ሰውነታቸው ተያዘ፣ እጃቸውና እግራቸው መንቀሳቀስ አልቻለም። ከበሽታው ለመዳን በሆስፒታል ውስጥ ለወራት ሲታከሙ ቆይቷል።
አሁንም በአዲስ አበባ ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል። ቤተሰቦቹ ያላቸውን ገንዘብ በሆስፒታል ጨረሱ 🥲 አሁን የህክምናው ወጪ ከቤተሰብ አቅም በላይ ሆኖ ሳይወዱ የህዝብ ድጋፍ ፈለጉ። እጆቻቸውና እግሮቻቸው አገልግሎት አይንቀሳቀሱም በሰው ድጋፍ ነው መንቀሳቀስ የሚችሉት በከፍተኛ ችግር ውስጥ ናቸው።
☄️ስለዚህ በአገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ ያላችሁ እንድትጸልዩላቸውና ባላችሁ ነገር በገንዘብ እንድትረዷቸው በጌታ ፍቅር እንጠይቃለን።
ድጋፋችሁን ለመለገስ ከቄስ ፈይሳ ቤተሰብ ጋራ በመነጋገር በወንድማችን ዘማሪ Official Samuel T Michael የተከፈተውን የGoFundme አካውንት ሊንክ እንድትጠቀሙ በጌታ ፍቅር እንጠይቃችኋለን!
https://gofund.me/93491bec#Share በማድረግ ለሌሎችም እንዲደርስ ተባበሩ ተባረኩ!
©️Samuel T Michael
@christian_mezmur💎