ሀቅን ፍለጋ ከቁርዐንና ከሀዲስ አርባ ምንጭ ዪኒቨርስቲ AMU chamo Campus


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


ዳዕዋ ሰለፍያ በአርባ ምንጭ AMUጫሞ ካምፓስ
ሃቅን ፍለጋ ከቁርዓንንና ከትክክለኛ ሃድስ በነዚያ ደጋግ ቀደምቶች ( በሰለፉነ–ሷሊሂን) አረዳድ !
"ከሃቅ በሗላ ጥሜት እንጅ ምን አለ! ? "
ስለዚህ ሃቅን ብቻ ተከተል !
ማሳሰቢያ: –ለማንኛውም አስተያየትዎ ከታች ባለው ቦት ያስቀምጡልን ጀዛኩሙላህ ኸይር
@JemalEndroAbuMeryem

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


♨️ለአህባሾች ብዥታ የተሰጠ መልስ

ትላንት ማታ በሀይቅ ከተማ በአባ ሀጂ መስጂድ ከተራዊህ በፊት የተደረገ

🎤በሙርሰል ሰይድ ጨፌ

👉https://t.me/murselseid


🎙 በወንድማችን አህመድ አሰን ሃፊዘሁላህ

🕌 በወረኢሉ ከተማ ፉርቃን መስጅድ (በተለምዶ ላይኛው መስጅድ )

ከፈጅር ሶላት የተወሰዴ

ረመዿን 13/1446
መጋቢት 4/2017


በሃፊዞች መስገድ ምንኛ መታደል ነው አልሃምዱሊላህ ወረኢሉ ሆናችሁ በሃፊዞች ለመስገድ ያልታደላችሁ ከዛሬ ጀምራችሁ እነዚህ ወንድሞች እያሉ ለምን ትዘናጋላችሁ


ተጋብዛችሗል
በቀድሞው የሰመራ ዩኒቨርስቲ 2015 GC ተማሪ


https://t.me/YeZemzemMesjidJemea/23808


Репост из: Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ከዩሱፍ ታሪክ ከምንማራቸው ቁም ነገሮች ውስጥ አንዱ እነሆ
~
የዩሱፍ ወንድሞች ዩሱፍን ለመገላገል ብዙ በደል አድርሰውባቸዋል። ይሁን እንጂ የአላህ ድንቅ ስራ ሆኖ ከዘመናት በኋላ የደረሰው ደርሶ፣ ያለፈው አልፎ ዩሱፍን አንግሶ እነሱን ደግሞ በችግር ፈተኖ አገናኛቸው። ዩሱፍ ለይተዋቸዋል። እነሱ ግን አላወቁም። የንጉሱ መስፈሪያ ዋንጫ በ"ቢኒያሚን" ጓዝ ውስጥ ሲገኝ ዩሱፍን በነገር የሚወጋ እንዲህ የሚል ቃል ተናገሩ:-
{إِن یَسۡرِقۡ فَقَدۡ سَرَقَ أَخࣱ لَّهُۥ مِن قَبۡلُۚ}
"ቢሰርቅ ከአሁን በፊት የርሱው ወንድም በእርግጥ ሰርቋል።"

ዩሱፍን ማለታቸው ነው። ዩሱፍ ዛሬ ስልጣን ላይ፣ ሃብት ላይ ናቸው። እርምጃ መውሰድ፣ እሱ ቢቀር የሚወስዱት እህል ላይ ማእቀብ መጣል ይችላሉ። ቢሆንም እዚያ ሊደርሱ ቀርቶ ለውንጀላቸው ግልፅ ምላሽ እንኳን አልሰጧቸውም። ዋጥ አደረጉት።

{ فَأَسَرَّهَا یُوسُفُ فِی نَفۡسِهِۦ وَلَمۡ یُبۡدِهَا لَهُمۡۚ قَالَ أَنتُمۡ شَرࣱّ مَّكَانࣰاۖ وَٱللَّهُ أَعۡلَمُ بِمَا تَصِفُونَ }
"ዩሱፍም (ይህችን ንግግር) በነፍሱ ውስጥ ደበቃት፡፡ ለእነሱም አልገለጣትም፡፡ 'እናንተ ሥራችሁ የከፋ ነው፡፡ አላህም የምትሉትን ሁሉ ይበልጥ ዐዋቂ ነው' አለ" በምላስ ሳይሆን በልብ። [ዩሱፍ: 77]

ዩሱፍ ከራሳቸው ለመከላከል አልቸኮሉም። ባይሆን የኋላ ኋላ ምን አሏቸው?
{ قَالَ هَلۡ عَلِمۡتُم مَّا فَعَلۡتُم بِیُوسُفَ وَأَخِیهِ إِذۡ أَنتُمۡ جَـٰهِلُونَ }
"እናንተ የማታውቁ በነበራችሁ ጊዜ በዩሱፍና በወንድሙ ላይ የሰራችሁትን ግፍ ዐወቃችሁን?' አላቸው፡፡'' [ዩሱፍ: 89]

በዚህን ጊዜ ነበር የሚመላለሱት ከዩሱፍ ጋር እንደሆነ የገባቸው።
{ قَالُوۤا۟ أَءِنَّكَ لَأَنتَ یُوسُفُۖ قَالَ أَنَا۠ یُوسُفُ وَهَـٰذَاۤ أَخِیۖ قَدۡ مَنَّ ٱللَّهُ عَلَیۡنَاۤۖ إِنَّهُۥ مَن یَتَّقِ وَیَصۡبِرۡ فَإِنَّ ٱللَّهَ لَا یُضِیعُ أَجۡرَ ٱلۡمُحۡسِنِینَ }
" 'አንተ በእርግጥም ዩሱፍ ነህንዴ?' አሉት። 'እኔ ዩሱፍ ነኝ፡፡ ይህም ወንድሜ ነው። አላህ በኛ ላይ በእርግጥ ለገሰልን። እነሆ! የሚጠነቀቅና የሚታገስ ሰው (አላህ ይክሰዋል)። አላህ የበጎ አድራጊዎችን ዋጋ አያጠፋምና' አለ።" [ዩሱፍ: 90]

እዚህ ላይ የሚያሳቅቅ ነገር እንደገጠማቸው ገባቸው። "በአላህ እንምላለን፡፡ አላህ በኛ ላይ በእርግጥ አበለጠህ፡፡ እኛም በእርግጥ አጥፊዎች ነበርን አሉ።"
ዩሱፍ ግን በበደል ላይ በደል ቢደራረብባቸውም ጥፋታቸውን ባመኑት ወንድሞቻቸው ላይ ሆደ ሰፊ ነበር የሆኑት። እንዲህ ሲሉ ያለፈውን ሁሉ አለፉት:-
{ قَالَ لَا تَثۡرِیبَ عَلَیۡكُمُ ٱلۡیَوۡمَۖ یَغۡفِرُ ٱللَّهُ لَكُمۡۖ وَهُوَ أَرۡحَمُ ٱلرَّ ٰ⁠حِمِینَ }
«ዛሬ በናንተ ላይ ወቀሳ የለባችሁም፡፡ አላህ ለእናንተ ይምራል፡፡ እርሱም ከአዛኞች ሁሉ ይበልጥ አዛኝ ነው» አላቸው፡፤
[ዩሱፍ: 92]

ይህን ትምህርት ያዙና የበደሏችሁን ሰዎች እና ይቅር ለማለት የሚተናነቃችሁን ስሜት አስቡት። የምንማረው ለመለወጥ ነው አይደል? ስሜታችንን ረግጠን፣ እልሃችንን ውጠን ስለ አላህ ሁሉን ይቅር እንበል። ከዩሱፍ ታሪክ እንማር።
~
የቴሌግራም ቻናል:-
https://t.me/IbnuMunewor


ለሐጅ 600,000 ሺ ብር   ?!

🎙በኡስታዝ ሳዳት ከማል ሓፊዘሁላህ

   ~¤   t.me/Darutewhide


ይህ የኢትዮጲያ ሙስሊም ተማሪዎች ለጠቅላይ ሚኒስተሩ ፅህፈት ቤት የቀረበ ጥያቄ ነው !
①)
ክቡር የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት እንደገለጻችሁት ጥያቄዎችን ለመቀበል ዝግጁ መሆናችሁን ስላሳወቃችሁን እናመሰግናለን።
እኛ ሙስሊሞች በትምህርትና በመንግስት ተቋማት በተለይም ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በሒጃብና ኒቃብ አለባበስ ምክንያት እንዲሁም በሶላት አፈጻጸም ላይ እምነት ነጻነታችን እየተገደበ መሆኑን ልናሳውቃችሁ እንወዳለን።

√ በትምህርት እና በተለያዩ የስራ መስኮች የሙስሊም ሴቶችን መብት በተመለከተ፤ በኢትዮጵያ ሕገ መንግስት አንቀፅ 27 ላይ በግልጽ እንደሰፈረው እያንዳንዱ ሰው የመረጠውን ሃይማኖት የመከተል፣ የማምለክ እና የመግለጽ መብት አለው።
ሆኖም በተጨባጭ፦

1) • በትምህርት ዘርፍ፡ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች (ለምሳሌ ጉራጌ ዞን ጉንችሬ፣ አክሱም፣ ዲላ ዩኒቨርስቲ፣ ጅማ ዩኒቨርስቲ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ…) ያሉ ሙስሊም ተማሪዎች (ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ ዩኒቨርሲቲ) ኒቃብ፣ ሒጃብ እና ሌሎች ኢስላማዊ አለባበሶችን በመልበሳቸው ምክንያት፡

ከትምህርት ገበታቸው እየተባረሩ ነው። (ለምሳሌ በጉራጌ ዞን ጉንችሬ ከ3 አመት በላይ ሆኗቸዋል)

በብሔራዊ ፈተናዎች ወቅት በአለባበሳቸው ምክንያት ፈተና እንዳይፈተኑ እየተደረጉ ነው። (ለምሳሌ፦ በአክሱም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፎርም አልሞሉም፣ እስከዛሬ በበርካታ የትምህርት ተቋማት ላይ ልክ ፈተና ሲቀመጡ ኢስላማዊ ልብሳችሁን አውልቁ የሚባሉባቸው አጋጣሚዎች ነበሩ።)

ትንኮሳ እና መድልዎ እየደረሰባቸው ነው።

ከሶላት ጋር በተያያዘም የእምነት ነፃነታቸው እየተገደበ ነው።

ጥያቄያችን፡ መንግስት ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሕገ-መንግስታዊ መብታቸው ተጠብቆ፣ ያለምንም ሥጋትና መድልዎ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ምን አይነት ተጨባጭ እርምጃዎችን እየወሰደ ነው? መቼስ መፍትሄ ይሰጣል?

2)• በመንግስት ተቋማት (ለምሳሌ በኢትዮጵያ አየር መንገድ)፡

ሙስሊም ወንዶች እምነታቸው ስለሚያዛቸው ፂማቸውን በማስረዘማቸው እና ሱሪያቸውን በማሳጠራቸው ምክንያት የመቀጠር እድል እየተነፈጋቸው ነው።

ሒጃብ የሚለብሱ ሙስሊም ሴቶች የመስራት መብታቸው እየተገደበ ነው።

ጥያቄያችን፡ እነዚህ ተቋማት ከሕገ መንግስቱ ጋር የሚቃረኑ አሰራሮችን እንዲያስተካክሉ እና ኃይማኖታዊ ነፃነትን እንዲያከብሩ መንግስት ምን አይነት ቁጥጥር እና የማስተካከያ እርምጃዎችን እየወሰደ ነው?

  ለዚህ አንገብጋቢ ጉዳይ በዝርዝር እንድታብራሩልን እና ተገቢውን ትኩረት በመስጠት አፋጣኝ እና ዘላቂ መፍትሄ እንዲሰጡን በአክብሮት እንጠይቃለን።

እናመሰግናለን

https://t.me/daewaselefiyaArbaminch/15587?single


Репост из: Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union
ይህ የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄ ነው ••• ለኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር አብይ አህመድ!

ጠይቁን ብለዋልን ጥያቄዎቻችንን በጨዋ ደንብ አሰናድተን እንጠይቅ:: መልስ እንሰጣለን ብለዋልና መልሳቸውን እናውቅ ዘንድ ጥያቄዎቻችንን እናቅርብ::

ሁላችንም እንጠይቅ ••• ለጥያቄያችን ትኩረት እስኪሰጡ ድረስ ••• ድምፃችንን ሰምተው መልስ እስኪሰጡ ድረስ!

ቅሬታ ማቅረቢያው https://www.facebook.com/share/p/1LNAiWkmeA/ ነው::

መብት በትግል እንጅ በልመና አይገኝም!

@EHEMSU


Репост из: Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ንፅፅር ላይ ለተሰማራችሁ ወገኖች አጭር ጥቆማ
~
1- በቀዳሚነት የማነሳው ስራችሁን አጠናክራችሁ ቀጥሉ የሚል ነው። የግርግር ፈጣሪዎች ዋና አላማ ይህን ማሰናከል ስለሆነ ይበልጥ ትጋታችሁን ጨምሩ።
2- አቅማችሁን ይበልጥ አዳብሩ። በተለይም በቀዳሚነት የራሳችሁን ኢስላማዊ ግንዛቤ ከዐቂዳ ጀምራችሁ አጥሩ። እንደ አጠቃላይ ጥልቅ የሆነ ንባብና ጥናት ይኑራችሁ። ዘርፉ በደከመ አቅም የሚገባበት አይደለም። ወይ ባጭር ታጥቃችሁ ግቡ። ካልሆነ ይቅርባችሁ። ቦታውን ባግባቡ ለሚሰሩት ተውት።
3- የሚቻል ከሆነ የጋራ መድረክ ቢኖራችሁ መልካም ነው። አካሄዱ ላይ የሚታዩ ጠንካራ እና ደካማ ጎኖችን ነቅሳችሁ የምትነጋገሩበት፣ ተግዳሮቶች እና መፍተሄዎቻቸው ላይ የምትወያዩበት፣ ልምድ የምትቀሳሰሙበትና የምትተራረሙበት፣ መረጃዎችን የምትለዋወጡበት፣ ... የጋራ መድረክ ቢኖር መልካም ነው። የሚቻል ከሆነ ማለቴ ነው። በሆነ ምክንያት በተናጠል መስራቱ ከተሻለም እሰየው።
4- በውይይት ጊዜ፣ በአቀራረብ ላይ፣ ... ሊኖራችሁ የሚገባን አደብና አነጋገር ድባቡ የሚወስነው ሳይሆን ቀድሞ የተጠና፣ ጠንካራ መሰረት ላይ የቆመ፣ ትንኮሳ የማይወዘውዘው እንዲሆን አድርጎ መቅረፅና ማነፅ ይገባል። ደግሞም አጀንዳ ተቀባይ አትሁኑ። መስመራችሁን አትልቀቁ፣ አታስለቅቁም። ካልሆነ ፍሬያማነታችሁን ሊቀንሰው ይችላል።
5- በተቻለ መጠን ከደዕዋው መስክ አትጥፉ። ሰዎች ናችሁና ሁሌ አይደላችሁም። የማይመች ሁኔታ ሊገጥም ይቻላል። በተቻለ መጠን ግን ከደዕዋው ዘርፍ አትራቁ። በመሀል እልም ማለት ሞራላችሁንም፣ አቅማችሁንም፣ ተፅእኗችሁንም ያቀዘቅዘዋል። ብዙ ቆይታችሁ ስትመለሱ ነገሮች እንዳሰባችኋቸው ላይሆኑ ይችላሉና በየመሀል ረጃጅም ቆይታዎች እንዳይኖሩ ጣሩ።
አላህ ያበርታችሁ።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor


Репост из: 🌺JU Muslim Students Jema'a Kito Campus
Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
በተራዊህ እና በተሃጁድ ሶላት ላይ ስለሚያጋጥም ይህችን ማስታወሻ ያዟት!!


🎙 በወንድማችን አቡ ማሂር ሙሀመድ አወል ሃፊዘሁላህ

🕌 በወረኢሉ ከተማ ፉርቃን መስጅድ (በተለምዶ ላይኛው መስጅድ )

ከማታ ተረሃዊ ሶላት የተወሰዴ

ረመዿን 10/1446


በሃፊዞች መስገድ ምንኛ መታደል ነው አልሃምዱሊላህ ወረኢሉ ሆናችሁ በሃፊዞች ለመስገድ ያልታደላችሁ ከዛሬ ጀምራችሁ እነዚህ ወንድሞች እያሉ ለምን ትዘናጋላችሁ



ተጋብዛችሗል የወረኢሉው ሹረይም

https://t.me/YeZemzemMesjidJemea/23800?single


Репост из: AMU- Muslim Students Union
አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱህ!

  የተወደዳችሁ ሙስሊም እህት ወንድሞች:-

   በመጀመሪያ የታላቁ የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት እንደ አድስ ተደራጅቶ፡ ተዋቅሮ በ መመስረቱ እንድሁም የህብረቱ የስራ አስፈፃሚ ተደርጌን በመመረጣችን የ ተሰማንን ክብር ለ መግለፅ እንወዳለን:: ይህ ሀላፊነት ማዕረግ ብቻ ሳይሆን ለ ሁላችንም ተመራጮች ለእናንተም እንደ ማህበረሰብ ከአምላካችን አላህ (ሱብሃነሁ ወተዓላ) በኩል የተሰጠን ቅዱስ አደራ ነው:: የህብረታችን ዋና አላማ ስም መያዝ ብቻ ሳይሆን ራዕያችንንና ተልዕኳችንን ለማሳካት በዩኒቨርሲቲያችን ውስጥ ለሚገኙ ሙስሊም ተማሪዎች ተገቢ የሆነውን አገልግሎት መስጠት ነው:: በዚህ ውስጥ የምንሰራቸው ስራዎች ሁሉ ለሀይማኖታችንና ለ ማህበረሰባችን የ ሚኖረንን ቀናዒነት እንድናን ፀባርቅ ማድረጋቸው ልዩ የሆነ ስሜት ይሰጠናል::

    በመቀጠል መንገዳችንን ስንጀምር መንገዳችን የኢስላም ነውና መሰረታችንን ከቁርዓንና ከሐዲስ ማድረግ እንዳለብን ለማሳሰብ እንወዳለን:: አላህ (ሱብሃነሁ ወተዓላ) በቁርዓኑ:- "በላቸውም ሥሩ አላህ በእርግጥ ስራችሁን ያያልና:: መልዕክተኛውና ምዕምናንም (እንደዚሁ ያያሉ)" ሲል ስራችንን በትክክል እንድንሰራ ያዛል:: ሁሉን ተመልካች አዋቂ ነውና ከእርሱ ምንም እንደማይደበቅ ያስጠነቅቃል:: በዚህ ውስጥ በስራችን ውስጥ አላህ ዘንድም ሆነ አማኞች ዘንድ ተጠያቂነት እንደሚኖር ልብ እንድንል ያደርጋል:: የእኛ ዘላለማዊ አርዓያ የሆኑት ነብይም (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም):- "አማኞች እርስ በዕርስ ባላቸው መልካምነት መተዛዘንና አንዱ የሌላውን ሀዘን በመካፈል ልክ እንደ አንድ አካል ናቸው:: ከእርሱ አንዱ ክፍል ሲታመም ሌላው እንቅልፍ በማጣትና በትኩሳት እንደሚጣራው::" ሲሉ ሙስሊሞች እርስ በዕርስ በመተዛዘንና አንድ በመሆን ምን ያክል መጓዝ እንዳለባቸው ያሳስባሉ:: ጥንካሬያችን የሚታየው አንዱ ለሌላው ባስፈለገው ሰዓት በሚያሳየው ድጋፍ እንደሆነ ያመላክታሉ::

    ወንድም እህቶች:- ጀመዓችን ለሙስሊሙ ማህበረሰብም ሆነ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ባደረገው አበርክቶ ትልቅ የሆነ ታሪክ እንዳለው ይታወቃል:: እኛም በትላንት አባቶቻችን ጠንካራ ትከሻ ላይ ሆነን ታሪክ የማይሽረው መልካም አሻራ አሳርፈን ማለፍ አለብን:: በዚህ ውስጥ አንዱ ለሌላው እውቅና በመስጠት ሊያበረክተው የሚችለው አስተዋፅዖ እንዳለ ልብ ሊባል ይገባል:: በህብረት ክንዳችንን በአንድ ላይ አድርገን  በትምህርት ዘርፉም ሆነ ሀይማኖታችንን በመማርና በማስተማር ውስጥ የኢስላም አምባሳደር እንደመሆናችን ጥንካሬያችንን ልናሳይ ግድ ይለናል:: ያለንበትም አከባቢ እንደምታውቁት ብዙ ዳዕዋ የሚያስፈልግበት፡ ብዙ ልንሰራቸው የሚገቡ የቤት ስራዎችም አሉብን። ሁላችሁም ተሳተፉ:: እንተባበር:: እንተጋገዝ:: ፕሮግራሞቻችንን እውን እናድርግ:: የህብረታችንን ፍሬ ዘመን በማይሽራቸው ተፅዕኖዎች ውስጥ እንመልከት::

  አላህ በጥረቶቻችን ላይ በረካን ይጨምር:: ወደ ቀጥተኛው መንገድ ሁሌም ይምራን:: ለመልካም ነገር ምንጭ ያድርገን:: ጀዛኩሙላሁ ኸይረን!!

https://t.me/amumsu1


Репост из: Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የመግሪብ በዕዲያ
~
ተምርና ውሃ አግኝተህ ካፈጠርክ "ጫማ ተራ" ያለው ግርግር እስከሚቀንስ ሁለት ረከዐ ቀለል ያለች ሱና ስገድ፣ የመግሪብ በዕዲያ። በር ላይ ያለውን ግርግር ካስተዋልከው በመቸኮልህና በመረጋጋትህ መካከል ያለው የቆይታ ርዝማኔ ኢምንት ነው። ጊዜው ረመዳን ነው፣ እያንዳንዱ ዒባዳ በተለየ የሚታሰብበት የተከበረ ወቅት። እያንዳንዱ ቀን ዳግም ላይገኝ እያለፈ ነው። ተጠቀምበት።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor


"ተራዊህ ሰላት ላይ: ብዙ ሰው ጥሎ ይወጣል። ምነው ስትለው? መስጂዱ ይሞቃል ይልሃል። ቢሞቅስ? በረሃ አቋርጠው የሚሄዱ ነጋዴዎች! ሞቀን ብለው የተመለሱ አሉ? እንዴ? ለንግድና ለዱንያ ጥቅም መቼ በሙቀት ተገድቦ ያውቅና!! እንግዲያውስ መስጂዱ ሳይሆን ሾርባውና አክሰሰሪዎቹ ናቸው የሞቁህ። ቀንስ። እንግዲህ አላህ ለበረካው ካደለህ? ወይም አልታደልክም ይሆናል እንጂ በእንዲህ አይነት ተልካሻ ሰበብ ጥለህ አትወጣም።"

ከወንድማችን ኢሊያስ ናስር
https://t.me/daewaselefiyaArbaminch/15575


Репост из: ARBA MINCH UNIVERSITY
ሁላቹህም ሃላፊነት አለባቹህ ስለ ሃላፊነታቹህም ትጠየቃላቹህ

ዲናዊ በሆነ ጉዳይ ላይ ሀላፊነቱ የጋራ ነው። ፉላን የሆነ ድርሻ ተሰጠው ማለት ከዚያ ውጭ ያለው ሰው አይመለከተውም ማለት አይደለም። አንተም ወንድሜ በሆነ ዘርፍ ላይ የሆነ ነገር ሀላፊነት ሲሰጥህ የእስልምናና የሙስሊሞች ተወካይ የሆንክ መስሎህ ያለኔ እውቅና፣ያለኔ ፈቃድ የመሳሰሉ ስሜቶችን እንዳይጠናወቱህ ተጠንቀቅ።

በአጭሩ በዲን ጉዳይ መስራት ያለብህን በኢኽላስ ከወንድሞችህ ጋር ተባብረህ ስራ!


Репост из: ARBA MINCH UNIVERSITY
የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪወች ህብረት ተመሰረተ

በካምፓሶች መካከል የነበረው ትስስር መላላትና መድከም የአምስቱም ካምፓስ ተወካዮች ለረዥም ጊዜ ውይይት በማድረግ አምስቱንም ካምፓስ ያካተተ ህብረት በአዲስ መልክ በ9/9/1446ሂ ተመስርቷል።

ህብረቱ
-ፕሬዝዳንት~ኡሳማ አሊ(main)
-ምክትል ፕሬዝዳንት~ነቢል ሙሐመድ(nechsar)
-ፀሀፊ~ኸይሩ ጀማልን(chamo) በአመራርነት መርጧል።

መልካም የስራ ዘመን


ወንድም እና እህቶች ተባበሩን!

ይህ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት የሞተር ታርጋ መንገድ ላይ ወድቆ ጠፍቷል የሞተሩ ባለቤት ቤተሰቡን የሚያስተዳድረዉ የእለት እንጀራዉን የሚያገኝዉ በዚሁ ስለሆነ በዚህ ኑሮ ዉድነት ስራ ከፈታ ቀናቶች ስለተቆጠረ እባካችሁ ይህን ታርጋ ያገኘ ከስር በተገለጽዉ ቁጥር ያሳዉቀን

SHARE ....SHARE .....SHARE ....SHARE

0973096262
        or
0907136729


Репост из: ከ ደጋጎቹ ዓለም
መስጂድ ስትገባ ብዙ ሰዎች መስጂድ በመግባት ቀድመውህ እየሰገዱ ስታይ፤ እነሱ ካንተ ያነሰ ቢዚ የሚያደርጋቸው ነገር ኖሮ ወይም አንተ ከነሱ የባሰ ቢዚ የሚያደርግህ ነገር ኖሮህ አይደለም። ጉዳዩ የመታደል(የተውፊቅ) ጉዳይ እንደሆነ እወቅ።

አላህ ሆይ ከታደሉቱ አድርገን!


መንገደኛ ሰው መፆሙ ነው ማፍጠሩ በላጩ ?

🎙በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር ሀፊዘሁላህ

https://t.me/Darutewhide


Репост из: SadatKemal Abu Meryem
🛑🛑🛑ኢንሻ አላህ 30 የነብዩ ﷺ ሐዲሶች በአንድ ቀን ይማሩ።

ዛሬ
🕓ከ ጠዋቱ 3:00 እስከ ዙሁር።

📖📚ኪታቡ ቦታው ላይ በነፃ ይሰጣል።

ትምህርቱ ለሁሉም እድሜ ክልል የተዘጋጀ ነው።

ለሴቶች በቂ ቦታ አለ።

መልክቱን በማሰራጨት የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ።

🚘🚘🚘🚘🚘🚘🚘🚘
አድራሻ ሑዘይፋ መስጂድ ሸገር ሲቲ ከየሺ ደበሌ ከፍ ብሎ።

የሑዘይፋ መስጂድ አድራሻ
https://maps.app.goo.gl/sXLNJJKViVc3xFcu8


الله أكبر
الله أكبر
الله أكبر

ኒቃቢስቷ ዛኪራ ሰዒድ በወርቅ ተመርቃለች!


በወሎ ዩኒቨርሲቲ የሳይኮሎጂ ተማሪ የነበረችው ዛኪራ ሰዒድ 3.99 በማምጣት በሁለት ዋንጫ እና የወርቅ ሜዳልያ ተመርቃለች።
Congratulations 🎉🎉🎉 Our sister!

Once again ኒቃብ ከመማር ከመመረቅ ከመሸለም አያግድም፣ተምራለች፣ተመርቃለች: ተሸልማለች።

ትለብሳለች
ትማራለች!

ሙተነቂብን ከትምህርት ማገድ ሃገርን ማውደም ነው።

https://t.me/daewaselefiyaArbaminch/15568


Репост из: Abul Abas Nasir mohamed (bako)
🆕🔴የመልካም ስራ ጥሪ
አሰላሙ ዐለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱ

بسم الله الرحمن الرحيم

⭐️እንደሚታወቀው መረከዝ አቡ ሙሳ አልአሽዐሪ ላለፉት 4 አመታት ገደማ የቁርአን ሂፍዝና ተያያዥ የተረቢያ ትምህርቶችን በተለያዩ መርሀግብሮች ማለትም በአዳሪ፣ በተመላላሽና በርቀት በርካታ ተማሪዎችን አስተምሮ ለውጤት በማብቃት ኡማውን በዲኑ የሚያገለግሉ ተተኪዎችን በማፍራት የበኩሉን አሰተዋፆ ሲያበረክት ቆይቷል ።

📸እነሆ አሁን ላይ መርከዙ ተደራሽነቱን በማስፋት በ3ቱም ቅርንጫፎች በበይነ መረብ የሚማሩትንም ጨምሮ ቁጥራቸው ወድ 400 ገደማ የሚደርሱ ተማሪዎችን እያስተማረ ይገኛል ።

✅አንዱ ቅርንጫፍ 30 አከባቢ የሚሆኑ ተማሪዎችን ያለ ምንም ክፍያ የምናስተምር ሲሆን በ2ቱ ቅርንጫፎች ላይ መክፈል ለማይችሉ የግድ መማር ያለባቸው 10ራ ምናምን ተማሪዎችን እና በ ኦንላይን በርከት ያሉ ተማሪዎች በነፃ ተቀብለን እያስተማርን እንገኛለን ።
አጠቃላይ በነፃ የምናስተምራቸው ተማሪዎች አሁን ላይ ቁጥራቸው ወድ 45 አከባቢ ደርሷል ።

☑️እኛ አቅማችን በሚችለው አላህ በረካ አድርጎልን  ይሄን ያክል ርቀት ተጉዘናልና እናንተስ ለቀጣዩ ፕሮጄክታችን ልታግዙን ዝግጁ አይደላችሁም ?  ዛሬ ስለሱ ይሆናል የምናወራው።

🥳ይሄንን ሁሉ ስናድርግ ሁሉም ነገር አልጋ በአልጋ ሆኖልን ሳይሆ በጣም ብዙ ቻሌንጆችን በመቋቋም መሆኑን እንድትረዱልን እንፈልጋለን ። በጣም ብዙ ውጣ ውረዶች ..
አሁን ላይ ግን አንዱንና ዋነኛውን ነው የምንነግራቹህ ። እሱም ቋሚ የሆነ ቦታ አለማግኘታችን እና በቤት ኪራይ መሰቃየታችን ትልቁ ተግዳሮታችን ነው ።

📣ስለሆነም እነሆ ዛሬ ላይ የሙስሊሙን ማህበረሰብ እገዛ ፈልገን የመጣነው በዚሁ ጉዳይ ላይ ነውና በአላህ ፍቃድ በህይውት እስካለን ድረስ ኢስላማዊ ሀለሰፊነታችንን የምንወጣበት እና ለልጆቻችንና ለቀጣዩ ትውልድ መልካምን ነገር ያስቀጥል ዘንድ ይሄንን መርከዝ ገንብተን ለማስረከብ ሁላችንም የበኩላችንን አሰተዋፆ እንድናበረክት በአለሰህ ስም እንጠይቃለን ።

ይሄንን በማስመልከት ታላቅ የዳዕዋና የኒያ ፕሮግራም አዘጋጀተናል። እርሶም እንዳይቀሩ በክብር ተገሰብዘዋል።

😬የእለቱ ተጋባዥ እንግዱች ▶️

✅ ኡስታዝ  ሳዳት ከማል
✅ ኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር
✅ ኡስታዝ ሙሐመድ ሲራጅ
✅ ሸይኽ   አወል ኬሚሴ
✅ ኡስታዝ ኸድር ኬሚሴ
✅ ኡስታዝ አቡ ሙሰሊም

😓እሁድ ማታ ከተረዊህ ሰላት በሇላ
4️⃣🔤1️⃣5️⃣


💎ፕሮግራሙ የሚካሄድበት የተሌግራም ግሩፕ⤵️
https://t.me/merkezabumussa1
https://t.me/merkezabumussa1

ውድና የተከበራቹህ ሙስሊም ወንድምና እህቶች፣ የቁርአንና ሱና ወዳጆች ይሄንን ፕሮግራም ሼር በማድረግ የአጅር ተካፋይ እንድትሆኑ ለማስታወስ እንወዳለን ።

Показано 20 последних публикаций.