የአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን የመማማሪያ መድረክ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


نفهم الكتاب والسنة بفهم سلفنا الصالح
ቁርአንና ሐዲስን በሰለፎች ግንዛቤ እንገንዘብ

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


ለመላ ሙስሊም ማህብረሰብ በሙሉ እንኳን ለ1446 ዓ·ሂ ለተከበረው ለረመዷን ወር አሏህ በሰላም አደረሳችሁ።
ይህ የረመዷን ወር በውስጡ የያዘውን ኸይር ሁሉ የምንቋደስበት በህይወታችን ላይ ትልቅ ለውጥ የምናስገኝበት በዓለም ላይ ያሉ ተበዳይ ሙስሊሞች ከበደላቸው የሚገላገሉበት የተባረከ ወር አሏህ ያድርግልን ።


የፆም  መደንገግ ጥበቦችና ጥቅሞቹ

   ከአላህ ስሞች መካከል አንዱ “አል-ሐኪም” የሚለው ነው። “አል-ሐኪም” በመባል የሚጠራው በጥበብ የሚገልጽ አካል ነው። ጥበብ (ሒክማ) ማለት ደግሞ ነገሮችን አሳምሮና አስተካክሎ በየቦታቸው ማኖር ነው። ይህ የአላህ ስም የሚያስገነዝበን እርሱ የፈጠረው ማንኛውም ፍጥረትም ይሁን የደነገገው ድንጋጌ ሁሉ እጅግ ለላቀ ጥበብ እንደሆነ ነው። ያወቀ ቢያውቅውም ያላወቀ ባያውቀውም!
   አላህ በባሮቹ ላይ የደነገገው እና ግዴታ ያደረገው ፆም  በውስጡ ታላላቅ ጥበቦችን እና  እጅግ በጣም ብዙ ጥቅሞችን አካቷል::
ከፆም መደንገግ ጥበቦች መካከል፦ አንድ ባሪያ በተፈጥሮ እንዲወዳቸው ተደርጎ የተፈጠረባቸውን እንደ ምግብ፣ መጠጥ እና የግብረ ስጋ ግንኙነት ያሉ (ስጋዊ) ፍላጎቶቹን ወደጐን በመተው የጌታውን ውዴታ ለማግኘት እና የተከበረውን አገር ጀነትን ለመታደል ወደርሱ የሚቃረብበት የአምልኮ ተግባር መሆኑ ነው:: በዚህ ተግባሩም ነፍሱ ከምትወዳቸው ነገሮች ይልቅ ጌታው የሚወደውን ከቅርቢቱ አለም (ዱንያ) ይልቅ የወዲያውኛውን ዓለም (አኼራን) ማስበለጡ ግልፅ ይሆናል::
ከፆም መደንገግ ጥበቦች መካከል፦ አንድ ባሪያ የፆም ግዴታውን በሚገባ ከተወጣ የጌታውን ፍራቻ (ተቅዋ) የሚያገኝበት ምክንያት መሆኑ ነው:: አላህ እንዲህ ይላል፦
(( يَاأَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا كُتِبَ عَلَيْكُمُ الصِّيَامُ كَمَا كُتِبَ عَلَى الَّذِينَ مِنْ قَبْلِكُمْ لَعَلَّكُمْ تَتَّقُونَ)) [البقرة:183]
ትርጉሙም፦«እናንተ ያመናችሁ ሆይ ፆም በነዚያ ከናንተ በፊት በነበሩት (ሕዝቦች) ላይ እንደ ተጻፈ በናንተም ላይ ተጻፈ (ተደነገገ) ልትጠነቀቁ ይከጀላልና፡፡»(አል-በቀራ፡ 183)
   ፆመኛ አላህን እንዲፈራ ታዟል። እሱም የአላህን ትዕዛዛት መታዘዝ እና ክልከላውን መራቅ ነው። ከፆሙም በዋነኝነት የሚፈለገው ትልቁ ዓላማ እርሱ ሲሆን በአንፃሩ ፆመኛው ምግብን፣ መጠጥን እና የግብረ ስጋ ግንኙነትን በመተዉ የተፈለገው እንዲሰቃይ አይደለም። ነብዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፡- «የሀሰት ንግግርን፣ በሀሰት መስራትን እንዲሁም የመሀይማንን ተግባር ያልተወ ሰው ምግቡንና መጠጡን  ከመተዉ አላህ  ጉዳይ የለውም። (ቡኻሪ ዘግበውታል)
   የሀሰት ንግግር (قول الزور) የሚለው ሀራም የሆኑ እንደ ውሸት፣ ሀሜት፣ ስድብና ሌሎችም በሸሪዓ የተከለከሉ ነገሮችን መፈጸምን የሚያጠቃልል ነው። በሀሰት መስራት (العمل بالزور) የሚለው ደግሞ ማንኛውንም በሰዎች ላይ ድንበር ማለፍ ያለበትን እንደ መክዳት፣ ማታለል፣ ሰዎችን መደብደብ፣ ገንዘባቸውን መቀማት እና የመሳሰሉትን ይመለከታል በተጨማሪም በሸሪዓ መስማት የተከለከሉ እንደ “አል-አጋኒ'' ዘፈንና መሰል (በሙዚቃ መሳሪያ የተቀነባበሩ ነገሮችን) መስማትም እዚህ ውስጥ ያካትታል። አልመዓዚፍ (المعازف) ማለት የሙዚቃ መሳሪያዎች ማለት ነው። ጀህል (الجهل) ማለት ደግሞ መሀይምነት (ድንቁርና) ሲሆን በንግግርም ይሁን በተግባር ከትክክለኛው አቋም መራቅን የሚያመለክት ቃል ነው።
   አንድ ፆመኛ ከላይ በተጠቀሰው የቁርአን አንቀፅና ሐዲስ መስረት ከተጎዘ ፆሙ ነፍስን ማስተካከያና መኮትኮቻ፣ እንዲሁም ስነ-ምግባሩን የሚገራበት፣ አካሄዱን የሚያቀናበት ይሆናል። እንዲህ ከሆነ ደግሞ ከረመዷን በኃላ በስነ-ምግባሩ ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ (መሻሻል) ይታይበታል ማለት ነው።
ከፆም መደንገግ ጥበቦች መካከል፦ የሃብት ባለቤት የሆነ ግለሰብ በርሱ ላይ አላህ የዋለው ፀጋና ስጦታ ምን ያህል ታልቅ እንደሆነ ይረዳበታል። ይህም የሚሆነው ግለሰቡ የፈለገውን እና የተፈቀድልትን መብላት እና መጠጣት እንዲሁም ከተፈቀደለት አካል ጋር የግብረ ስጋ ግንኙነትን ማድረግ በፈለገ ሰአት እንዲያገኝ አላህ ያገራለት መሆኑን ስለሚያስተውልበት ነው። ስለሆነም ጌታውን ያመሰግናል፣ ይህንን ማግኘት ያልቻለውን ድሃ ወንድሙን ያስታውሳል በዚህም የተነሳ ለሱ ምፅዋትን (ሰደቃን) ይሰጣል እንዲሁም መልካም ተግባራትን በመፈፀም የቸርነትን ባህሪ ይላበሳል።
ከፆም መደንገግ ጥበቦች መካከል፦ የሰው ልጅ እንዴት አድርጎ ነፍሱን (ስሜቱን) መቆጣጠር እና ሙሉ ለሙሉ በርሱ የበላይነት ስር በማዋል ለርሶ በቅርቢቱ ዓለምም (ዱንያ)ም ይሁን በወዲያኛው ዓለም (አኼራ) መልካም እንዲሁም ስኬታማ ወደ ሆነው አቅጣጫ መምራት እንደሚችል የሚለማመድበት መድረክ መሆኑ ነው። በዚህም ነፍሱን ከፍላጎቶቿ መከልከል የማይችል እንስሳዊነት የተጠናወተው ሰብአዊ ፍጡር ከመሆን ይልቅ ለርሷ ጠቃሚ የሆነውን ወደ ማሟላቱ ያዘነብላል።
ከፆም መደንገግ ጥበቦች መካከል፦ ፆመኛ ምግብን በመቀነሱ የተነሳ ጨጓራ እና መሰል የምግብ መፈጨት ሂደት የሚከናወንባቸው የሰውነት ክፍሎች ለተወሰነ ግዜ እረፍት ያገኛሉ በተጨማሪም አንዳንድ ለሰውነት አላስፈላጊ የሆኑ በሰውነት ውስጥ የሚገኙ እንደ ስብ እና መሰል ትርፍ ጎጂ ነገሮች መወገድ ከጤና ጋር ተያያዥነት ካላቸው የፆም ጥቅሞች መካከል ጥቂቶቹ ናቸው።

በበሸታ እና በመንገድ ላይ ስላሉ ሰዎች የጾም ህግጋት በተመለከተ ይሆናል። 

አላህ በተሞላ ጤንነት እና እሱ በሚወደው መልኩ ረመዷንን ከሚጾሙት ያድርገን። በተለያየ የጤና እክል ላይ ላሉትም አላህ ጤንነትን ይስጣቸው!!

ከኡስታዝ ጠሃ አህመድ

🌐
https://t.me/dawudyassin


🔹ልዩ የሙሀደራ ፕሮግራም በረመዳን ዋዜማ

🎤  በወጣት ዳዒ ኢንጅነር ጅብሪል አክምል

📚  ረመዳን እና ተውበት

በሚል ወሳኝ እና ወቅታዊ ርእስ ይዞላቹ ይቀርባል
አዘጋጅ∞
የቢላል/ኮካ መስጂድና መድረሳ ወጣቶች ጀመአ


🕌 በቢላል/ኮካ መስጂድ ውስጥ
የፊታችን ጁምአ  ማለትም የካቲት 21/ 2017

🌃 ከመግሪብ እስከ ዒሻ
ሁላቹም ተጋብዛቹዋል ጥሪው ሴቶችንም ይመለከታል
መቅረት አይታሰብም!!!


T.me/dawudyassin


((الَّذِينَ يَحْمِلُونَ الْعَرْشَ وَمَنْ حَوْلَهُ يُسَبِّحُونَ بِحَمْدِ رَبِّهِمْ وَيُؤْمِنُونَ بِهِ وَيَسْتَغْفِرُونَ لِلَّذِينَ آمَنُوا رَبَّنَا وَسِعْتَ كُلَّ شَيْءٍ رَحْمَةً وَعِلْمًا فَاغْفِرْ لِلَّذِينَ تَابُوا وَاتَّبَعُوا سَبِيلَكَ وَقِهِمْ عَذَابَ الْجَحِيمِ))
قال خلف بن هشام :
أتيت سليم بن عيسى لأقرأ عليه ، فكنت أقرأ عليه حتى بلغت يوماً سورة غافر فلما بلغت إلى قوله تعالى ﴿ وَيَسْتَغْفِرُ‌ونَ لِلَّذِينَ ءآمَنُوا ﴾ بكى بكاءً شديداً ، ثم قال لي : يا خلف ألا ترى ما أعظم حق المؤمن ؟ تراه نائماً على فراشه والملائكة يستغفرون له .

[ وفيات الأعيان ] (2/242)


👉የመክተበተ ሻሚላ አጠቃቀም ሙሉ መማሪያ (Tutorial) የያዘ አዲስ የቴሌግራም ቻናል ከ☀ሁዳ መልቲሚዲያ

📣🔅አንዳንድ ወንድሞች በጠቆሙት መሰረት ከዩትዩብ የሻሚላን ቪዲዮ ማውረድ ባለመቻላቸው ከዚህ የቴሌግረሰም ቻናል በቀላል አውርደው ማየት እንዲችሉ አዘጋጅተነዋል።

✍መክተበተ ሻሚላን በደንብ መጠቀም ይፈልጋሉን?
🖌ሻሚላ ማለት እጅግ ብዙ መፅሀፍትን በውስጡ የያዘ ላይብረሪ ነው። የሀገራችን ትልቁ ላይብረሪ ገብተው መደርደሪያው ላይ ከተደረደሩት መፅሀፍቶች የሚፈልጉትን መምረጥ ምን ያህል ያስቸግራል? ነገር ግን የላይብረሪውን ሰራተኛ ቢያማክሩት በምን ያህል ደቂቃ ያቀርብልዎታል?

📚መክተበተ ሻሚላም ልክ እንደዚሁ ትልቅ ላይብረሪ ነው! አጠቃቀሙን በደንብ ላወቀበት ሰው እጅግ ይጠቀምበታል፣ ኪታቦችን ይቀራበታል፣ ያመሳክርበታል፣ ትንተናዎችን፣ የቁርአን ተፍሲሮችን፣ ሀዲስ እና የሀዲስ ትንታኔዎችን ማንበብ፣ ማመሳከር፣ መማር፣ ማስተማር የሚቻልበት ትልቅ የኮምፒተር ላይበረሪ ነው።
በደንብ ይወቁት ይጠቀሙበት!

ወደ አዲሱ የሻሚላ ቻናል ለመቀላቀል
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
t.me/ShamelaAmharic


አንዳንድ እህቶች ኒካሕ ሲቃረብ አባቶቻቸው ሺርክ ላይ እንደሆኑ በመጥቀስ ምን ማድረግ እንዳለባቸው ይጠይቃሉ።
1- በመጀመሪያ የእውነት ሺርክ መኖሩን በተጨባጭ ማረጋገጥ ይገባል። ኹራፋት፣ ቢድዐዎች፣ ተወሱላት ጥፋት ከመሆናቸው ጋር ብቻቸውን ሺርክ ላይ ላይደርሱ ይችላሉ። ችግሩ እዚያ የሚደርስ መሆን አለመሆኑን በትክክል መለየት ይገባል።
2- በተጨባጭ አባት ሺርክ ላይ መሆኑ ከተረጋገጠ ተስፋ ሳይቆርጡ የሚችሉትን ሁሉ ጥረት በማድረግ ለመመለስ መጣር ይገባል። ይሄ የኒካሕ ሰሞን ሳይሆን ቀድሞ ነው ሊሰራበት የሚገባው። ከኒካሑ የበለጠ የሚያሳስበው ይሄ ነው። "ክፉ ደግ አይቶ፣ ለፍቶ ያሳደገኝ አባቴ ኒካሕ አታስርም ሲባል በጣም አዘንኩኝ፣ ከፋኝ፣ ..." የሚል የዓጢፋ (ስሜት) ንግግር ዋጋ የለውም። ሺርክ ከኢስላም የሚያስወጣ፣ ዘላለማዊ ክስረትን የሚያስከትል፣ እስከወዲያኛው ከሚወዱት የሚለያይ ከባድ ጥፋት ነው። ከኒካሑ በፊት ሺርክ ውስጥ ሲኖሩ ያልተሰማን ስሜት "ወሊይ አይሆኑም" ሲባሉ ከተሰማን ችግሩ ከራሳችን ነው። ገና ያልጠራ ነገር አለ ማለት ነው። እናጥራ።
3- በተረፈ ከኢስላም የሚያስወጣው ትልቁ ሺርክ መኖሩ በተጨባጭ ተረጋግጦ፣ ተመክረው ተዘክረው ከተቀበሉ ወሊይ ሆነው ኒካሑን ያስራሉ። ከኢስላም የሚያስወጣው ትልቁ ሺርክ መኖሩ በተጨባጭ ተረጋግጦ፣ ተመክረው ተዘክረው ለመቀበል አሻፈረኝ ካሉ ግን ወሊይ ሆነው ኒካሕ ሊያስሩ አይፈቀድም። ከዚህ ዝቅ ባለ ጉዳይ ሶላት የማይሰግዱ ሆነው እንዲሰግዱ ቢመከሩም ፈቃደኛ ካልሆኑ ግን ለኒካሕ አይሆኑም። የሶላት ጉዳይ በንፅፅር ከተውሒድ ያነሰ ከመሆኑ ጋር ማለት ነው።
4- እንዲህ አይነት ሁኔታ ከገጠመ ወሊይነቱ ወደሌላ ቅርብ ቤተሰብ ይሻገራል። ኒካሑ በነሱ በኩል ይታሰራል። ለኒካሕ የሚሆን ቤተሰብ ከሌለ በቃዲ ይታሰራል።

IbnuMunewor

T.me/dawudyassin


በቢላል ኮካ መስጅድ የተደረገ የጁመአ ኹጥባ

ረመዷንን በምን መልኩ እንቀበለው

በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን

T.me/dawudyassin




🔹ኢማሙ ማሊክ ቢን አነስ ረሒመሁሏህ እንዲህ ብለዋል፦

❝ስኬታማ ደስተኛ  ሰው ማለት የሰለፍ መሪዎች በነበሩበት ተግባር ላይ የጸና "ኸለፎች" ካስተዋወቁት አዲስ ነገር የራቀው ነው።❞

📚【 فتح الباري (٢٥٣/١٣) 】

T.me/dawudyassin


ልዩ የሙሀደራ ፕሮግራም በቢላል/ኮካ መስጂድ

👌 የወረዳው መጅሊስ ከቢላል/ኮካ መስጂድ ጋር

በመተባባር የፊታችን ጁምአ ከመግሪብ ጀምሮ

🕰 ልዩና ወቅተዊ ፕሮግራም አዘጋጅቷል
አቅራቢ ወጣት ዳዒ ቶፊቅ በደዊ


ርእስ ረመዳንን እንዴት እንጠቀም..⁉
ሁላቹም ተጋብዛቹዋል !! ሴቶችንም ያካትታል

የፕሮገራሙ እለት እና ሰአት=>  የካቲት 14 /2017
ከመግሪብ እስከ ዒሻ


አንተ ሃብት ስለሌለኝ አላገባም ትላለህ።
ማግባት በራሱ የሃብት ማግኛ ሰበብ መሆኑን ረስተኸዋል! ኢማጅን 4 ስታገባበትና ከሁሉም ስትወልድ → ሪዝቁ በሴቶቹም፣ በልጆቹም ልክ ነው…።


👉 ታላቅ የደዕዋና የመድረሳ መዝጊያ ፖሮግራም ጥሪ  ለሙስሊም ሴቶች በሙሉ

አሰላሙ ዐለይኩም ወረህመቱሏሂ ወበረካቱህ
እነሆ ኡስማን መስጂድ በየወሩ ሲካሄድ የነበረዉ የሴቶች የደዕዋ ፖሮግራምና ኡስማን የሴቶች ለሴቶች መድረሳ በጋራ በመሆን ደማቅ የመዝጊያ ፖሮግራም አዘጋጅተዉ ጥሪ ስያደርጉላቹ በታላቅ ደስታነዉ
ፖሮግራሙን ሊዩ ከሚያደርጉት ነገሮች ዉስጥ
👌በቀኑ ኡስማን መድረሳ እስካሁን ሲያቀራቸዉ የነበሩ የሒፍዝ ተማሪዎቹን በአምስት ጁዝእ መረሀ ግብር ያስመርቃል
👌 የተለያዩ ልጆች የሚያቀርቧቸዉ ትምህርቶችም ሊዩ ያደርጉታል
መቅረት አይታሰብም ማርፈድ ያስቆጫል!!!
ሰኣትና ቦታ ኡስማን መስጂድ  የፊታችን ቅዳሜ ከቀኑ 8:00ፖሮግራም ይጀመራል እንሻአሏህ

✍️ የወራቤ ሙስሊም ሴቶች ጀምዓ ደዕዋና እርሻድና ኡስማን የሴቶች መድረሳ በጋራ በመሆን

T.me/dawudyassin


🔹ኢብኑ መስዑድ ረዲየአሏሁ ዐንሁ እንዲህ አለ፡-

❝ከናንተ አንዳችሁ፦ ከፈተናዎች በአላህ እጠበቃለሁ አይበል! ነገር ግን "ከፈተናዎች ጥመት በአላህ እጠበቃለሁ"ይበል። ከዚያም እንዲህ የሚለውን የአላህን ቃል አነበበ፡-

" إِنَّمَا أَمْوَالُكُمْ وَأَوْلَادُكُمْ فِتْنَةٌ ۚ وَاللَّهُ عِندَهُ أَجْرٌ عَظِيمٌ"

"ገንዘቦቻችሁና ልጆቻችሁ ለናንተ መፈተኛ ብቻ ናቸው፤ አላህም እርሱ ዘንድ ታላቅ ምንዳ አልለና፡፡(አል-ተጋቡን፤15)።❞

ኢማም ኢብኑ ረጀብ ረሒመሁላህ እንዲህ አሉ፦

❝ይህ የሚያመለክተው ገንዘብም ሆነ ልጆች ፈተና ናቸው ከእነሱም  መሸሸጊያ አይጠየቅምና።❞

📚الجامع المنتخب / 104

منقول
T.me/dawudyassin


🔹ሸቂቅ ቢን ኢብራሂም አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ ብለዋል፡-


🗞የተውበትን በር ለመዝጋት ምክንያት የሚሆኑ ነገሮች ስድስት  ናቸው፦


❶ የአላህን ፀጋ  አለማመስገን በሌላ ነገር ላይ መጠመድ።

❷ ለእውቀት እና ለተግባር ያላቸውን ፍላጎት መተው።

❸ ወደ ኃጢአት መቻኮል እና ተውበትን ማዘግየት

❹ በሷሊሆች  መታለል ተግባራቸውን ከመከተል መቆጠብ።

❺ ዱኒያ ከእነሱ እየሸሸች ሳለ እነርሱ እሷን መከተላቸው።

❻ አኼራ ወደ እነርሱ እየመጣች ሳለ እነርሱ ከእርሷ መሸሻቸው።

📚( من كتاب الفوائد لإبن القيّم رحمه الله ج١ ص١٧٧)

منقول
T.me/dawudyassin


📚بلوغ المرام
📚ቡሉጉል መራም

√ዘውትር ሰኞና ማክሰኞ

√ከመግሪብ እስከ ኢሻ

√በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን

√ክፍል 69

√በቢላል ኮካ መስጅድ ከአብነት ዝቅ ብሎ ከአሚን አጠቃላይ ሆስፒታል ጀርባ

T.me/dawudyassin


📚بلوغ المرام
📚ቡሉጉል መራም

√ዘውትር ሰኞና ማክሰኞ

√ከመግሪብ እስከ ኢሻ

√በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን

√ክፍል 68

√በቢላል ኮካ መስጅድ ከአብነት ዝቅ ብሎ ከአሚን አጠቃላይ ሆስፒታል ጀርባ

T.me/dawudyassin


🔹ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያህ አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ አሉ፡-

❝አንድ ሰው ሙንከር  በሚታይበት ቦታ ላይ መሳተፍ የለበትም ለመቃወምም አይመቸውምና ሸሪዓዊ ምክንያት ያለው ሲቀር፡-

ለሃይማኖቱ ወይም ለዓለማዊው ጉዳይ የሚጠቅም "መስላሃ" ካለውና  መገኘቱ የግድ አስፈላጊ ከሆነበት ወይም የተገደደ ካልሆነ በስተቀር ቦታው ላይ መገኘት የለበትም።

ያለ ሸሪዓዊ ምክንያት ለማየት ለመዝናናት ለመሰል ነገሮች  ብቻ ብሎ መገኘቱ ይህ  ፍትሃዊነቱን እና ጨዋነቱን በፅኑ የሚያጎድፍ ነገር ነውና ይጠንቀቅ።❞

📚مجموع الفتاوى (٢٨/٢٣٩)

T.me/dawudyassin


📚بلوغ المرام
📚ቡሉጉል መራም

√ዘውትር ሰኞና ማክሰኞ

√ከመግሪብ እስከ ኢሻ

√በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን

√ክፍል 67

√በቢላል ኮካ መስጅድ ከአብነት ዝቅ ብሎ ከአሚን አጠቃላይ ሆስፒታል ጀርባ

T.me/dawudyassin


📚بلوغ المرام
📚ቡሉጉል መራም

√ዘውትር ሰኞና ማክሰኞ

√ከመግሪብ እስከ ኢሻ

√በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን

√ክፍል 66

√በቢላል ኮካ መስጅድ ከአብነት ዝቅ ብሎ ከአሚን አጠቃላይ ሆስፒታል ጀርባ

T.me/dawudyassin


السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
ኡስታዝ ዳውድ ያሲን ከታች በወንድማችን "sami aljeberti/facebook page" አማካኝነት የቀረበው ጥያቄ ድሮ "Nesiha audio" ከነበረበት ጀምሮ የ መርከዝ ኡስታዞችንም ሆነ ለመርከዙ ቅርብ የሆኑ ሰዎችን ግልፅ አቋምና ዳእዋ የሚያውቁና የሚከታተሉ የሆኑ የበርካታ ወንድም እህቶች ጥያቄ ነውና ቢላሂ አለይክ ይህንን ጥያቄ ለሚመለከተው አካል አድርሳችሁ ማብራሪያ ቢሰጥበት ባረከሏሁ ፊኩም።
አሁን ላይ በአደባባይና በየመድረኩ እየታየ ያለውን አካሄድ ስናይ ማን እንደሆነ የተሳሳተው ግራ ገብቶናል:–
①– ድሮ [በመርከዙና ለመርከዙ ቅርብ በሆኑ ኡስታዞች]ሲደረጉልን የነበረውን ዳእዋቸውን እኛ የተረዳንበት መንገድ ስህተት ነበር?!
②– እነርሱ የዛኔ የሚያደርጉት ዳእዋና የያዙት አቋም ስህተት ሁኖ አግኝተውት ከዛ ተመልሰው ነው?! ያ ከሆነ ዳእዋቸውንና አካሄዳቸውን ተከትሎ ሰው ስለተሳሳተ (ለሰው በግልፅ እንዲመለስ) ሊያሳውቁ አይገባም?
③– የዛኔ ተህዚር ሲደረጉ የነበሩት አካላት ከአቋማቸው በግልፅ መመለሳቸውን አውጀው ነው?! ከ ሶስቱ አንዱ ምክንያቱ የቱ ይሆን?!
               ↓↓↓
ለመርከዝ ኢብኑ መስዑድ እና ለነሲሓ ቲቪ አመራሮችና አባሎቻቸው

ምላሹንም የምፈልገው ከጠቀስኳቸው አካላት ነው።

በአደባባይ ያመጣሁትም በአደባባይ የሰሩት ነገር ስለሆነ እና ለዳዕዋው በመቆርቆርም ጭምር ነው።

በተረጋጋ መንፈስ ምላሽ ቢሰጥ መልካም ነው። ከነፍሲያ ወጥተን በመሃል ለታዩ ችግሮች ምላሽ አለመሰጣጠት እንዲሁም በእውቀት እና በስርዓት ምላሽ አለመሰጣጠት በመሃል ያለውን ልዩነት ከማጥበብ ይልቅ ልዩነቱን ወደ ማስፋት ያመራል እና በተረጋጋ መንፈስ መተራረሙ መልካም ነው።

ከነቢያችን ﷺ ወዲህ ከስሕተት የተጠበቀ ሼይኽ፣ ኡስታዝ፣ ጣሊበል-ዒልም እንደሌለ መዘንጋት የለብንም። "ሼይኼ ለምን ተነካ?" ሳይሆን "ምን አድርጎ ነው?" ብለን ማጤን አለብን። ስሕተት ካለ ማረም ከሌለ ደግሞ መመከት።

የመጨረሻው ቅድመ-ጥያቄዬ "ለምን ቀርባችሁ አልተመካከራችሁም?" እንዳይባል ቀርበን ሂደን አውርተናል ግን ከመሻሻል ይልቅ እየባሰ የመጣ ችግር ሁኗል።

-------ጥያቄዬ-------

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በ"መስለሓ" ስም ድሮ ስትኮንኗቸው ከነበሩ ሰዎች ጋር መቀራረብን መመስራታችሁ አደባባይ የወጣ እውነታ ነው፤ በተለይም ከዳዕዋ ቲቪ አባላት (እነ ሼይኽ ሙሓመድ ሓሚዲን እና ባልደረቦቻቸው) ጋር።

አሁን ደግሞ ከአፍሪካ ቲቪ አባላት ጋር ለመስራት እየተቀራረባችሁ እንደሆነም እያየን ነው። "መጥተውባችሁ ነው" እንዳይባል ሄዳችሁባቸው ነው። ማስረጃውንም ኮሜንት ላይ አስፍሬዋለሁ።

ጥያቄዬ:
1- ድሮ ለምን እና በምን ጉዳይ ኮነናችኋቸው?

2- አሁን ላይ ከነሱ ጋር መስራት የጀመራችሁት ድሮ ከነበረባቸው ችግር ተመልሰው ነው ወይስ ድሮ ስትኮንኗቸው የነበረው እናንተው ተሳስታችሁ ነው?

3- ከነበረባቸው ችግሮች ተመልሰው ከሆነ የተመለሱበትን መግለጫ በድምፅም ሆነ በፅሑፍ ያቅርቡ ወይም አቅርቡላቸው።

4- "መጀመሪያም ችግር አልነበረባቸውም" ካላችሁ ለስከዛሬው እናንተው መግለጫ አውጡና ጥፋታችሁን አምናችሁ እኛም እነዚህን መሻኢኾች እንጠቀምባቸው፣ አብረናቸውም እንስራ።

አላህ በሚያውቀው አንድነትን አንጠላም፣ አንድነትን የሚጠላ ልቡ ላይ ችግር ያለበት ሰው ነው፣ አሊያም ስለ አንድነት ያለው ግንዛቤ የተዛባ ነው።

👉 አንድነት ሲባል ግን በዓቂዳም በመንሃጅም አንድ ሲኮን ነው፣ ይሄን ነው ያስተማራችሁን። የሰለፎቻችንን ዓቂዳ ይዞ መንሃጁ ከሰለፎቻችን መንሃጅ ውጪ ከሆነ የአካሄድ ችግር አለበት።

እነዚህ እና መሰል ጥያቄዎች የኔ ብቻ ሳይሆኑ ለናንተ የሚወግኑ ወንድም እህቶች ጥያቄዎች ናቸው።

መልሳችሁን 1- 2- 3- 4- ብላችሁ መልሱልን።

እጠብቃለሁ።
✍ sami al-jeberti

Показано 20 последних публикаций.