Фильтр публикаций


ክፉ ግዜ!

ነፍስ ይማር!

@EliasMeseret


የጉልበት ስራ ሰርቼ ይቺን ቀን ሳይርበኝ ባሳልፍ ብሎ በየመንገዱ የሚንከራተት የሀገሬ ወጣት እየታፈሰ የሚደርስበት የግፍ ፅዋ ሞልቶ እየፈሰሰ ነው

@EliasMeseret


500 ሺህ የፌስቡክ ወዳጅ 🙏🏽

@EliasMeseret


የተፈጠረ ብዥታ የለም፣ ህዝቡ ሊደረግ የታሰበው ገብቶት ነው

እንደ አንድ የመንግስት የመረጃ ምንጭ፣ በሚቀጥሉት 5 አመታት ብቻ ይህን ህግ በመጠቀም እስከ 60 ቢልዮን ብር ለመሰብሰብ (ለመዝረፍ) ታቅዷል።

@EliasMeseret


ከሁለት ኢትዮጵያዊ አንዱ፣ ወይም 60 ሚልዮን ገደማው ኤሌክትሪክ አያገኝም

መንግስት 13 ሀገራትን በኤሌክትሪክ ለማስተሳሰር እየሰራ ነው።

@EliasMeseret


#FactCheck የኢትዮጵያ ሰብዐዊ መብቶች ኮሚሽን በርካታ ታዳጊዎች ከመንገድ እየታፈሱ ወደ እርሻ ጣቢዎች በግድ እየተወሰዱ እንደሆነ መግለፁ ይታወቃል

"እርሻዎቹ የት ይሆኑ?" ብላችሁ ለጠየቃችሁ እና ማጣራት ለምትፈልጉ፣ ዋና መዳረሻው በሚድሮክ ሆራይዘን ፕላንቴሽን ስር የሚተዳደረው የበበቃ ቡና እርሻ ልማት ነው። "ሚድሮክ ፈቅዶ ነው ወይ ተገዶ ነው?" ለሚለው ምላሽ ቢሰጥበት ጥሩ ነው።

ሚድሮክ በዚህ ዙርያ አስተያየት እንዲሰጥ ደጋግሜ ብጠይቅም ምላሽ ከመስጠት ተቆጥቧል፣ ህዝብ ግን ልጆቹ የት እየተወሰዱ እንደሆነ የማወቅ መብት አለው።

በነገራችን ላይ ታፍሰው እየተወሰዱ ያሉት የጎዳና ላይ ልጆች ብቻ ሳይሆኑ እንደ ሊስትሮ፣ ፍራፍሬ መሸጥ፣ የጉልበት ስራ በመስራት፣ መኪና በማጠብ ወዘተ የሚተዳደሩ እና ቤተሰብ ያላቸው ልጆች ጭምር ናቸው።

@EliasMeseret


በጅማ ከተማ በትንሹ 15 ሺህ ቤቶች መፍረሳቸውን እና  ህዝቡ ካሳ ከመጠየቅ ይልቅ “እስቲ ሃሳባችሁን አፍሱት፤ ልየው ነው’ ያለው” በማለት ጠ/ሚሩ ያሰፈሩትን ሀሳብ አየሁ።

የጅማ ህዝብ ደግሞ ባለፈት ሶስት ወራት በግሌም፣ በመሠረት ሚድያ በኩልም ሲያሰማ የነበረውን ጩኸት ከታች በምስሉ ላይ ተመልከቱ ⤵️

መሠረት ሚድያ በዚህ ዙርያ የሰራቸው ዜናዎች:

1. https://t.me/meseretmedia/282

2. https://t.me/meseretmedia/516

@EliasMeseret


ተደጋግሞ ሲነገር ውሸት እንደሆነ ያሳብቅ ካልሆነ ህዝቡ በቀን ተቀን ህይወቱ ምን ያህል ፍዳውን እየበላ እንደሆነ ያውቃል።

@EliasMeseret


#መሠረትሚድያ

በጀት= 0 ብር

የሰራተኛ ብዛት= 1

በጎ ፈቃደኞች= 3

ተፅእኖ= 100 ፐርሰንት

ሁሌ እኮራለሁ!

@EliasMeseret

@MeseretMedia


የትራንስፖርት ዋጋ መጨመር ያስከተለው ምስቅልቅል እና ምሬት

(መሠረት ሚድያ)- ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ፣ በተለይ ደግሞ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻ ከተደረገ ወዲህ የኑሮ ውድነት ተባብሶ ቀጥሏል።

የመገበያያ ዋጋቸው እጅግ እየጨመሩ ከመጡ ምርቶች አንዱ ነዳጅ ነው። የዛሬ ሁለት አመት በዚህ ወቅት ቤንዚን በሊትር 61 ብር ነበር፣ ነጭ ናፍጣ በሊትር 67 ይሸጥ ነበር፣ ኬሮሲንም በሊትር 67 ብር ነበር።

አሁን ላይ ቤንዚን 101 ብር ከ47 ሳንቲም ገብቷል፣ ናፍጣ ደግሞ በሊትር 98 ብር ከ98 ሳንቲም ሆኗል፣ በሌሎች የነዳጅ ምርቶች ላይም በትንሹ ከ8 ብር በላይ ተጨምሯል።

ታድያ የዚህ የነዳጅ ዋጋ ማሻቀብ የህዝብ ትራንስፖርቱ ዋጋም በእጅጉ እንዲያሻቅብ ምክንያት ሆኗል። በተለይ በተለይ በአዲስ አበባ ዳርቻ አካባቢዎች በሰፈሮችና በኮንዶሚኒየምዎች የሚኖሩ ዜጎች ለትራንስፖርት የሚያወጡት ወጪ እጅግ በጣም ጨምሮ ኑሮን እንዳከበደባቸው ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።

ለምሳሌ በኮዬ ፈጬ፣ በአራብሳ፣ በቂሊንጦ፣ በቱሉዲምቱ ወዘተ... የሚኖሩ ዜጎች ከነዚህ መኖሪያ መንደሮች እስከ መገናኛ እንኳን ለመድረስ በአውቶብስ 20 ብር፣ በታክሲ ደግሞ 50 ብር መክፈል ይጠበቅባቸዋል።

"ወቅታዊ ታሪፉ ደርሶ መልስ በአውቶቡስ 40 ብር፣ በታክሲ 100 ብር ነው መገናኛ ድረስ ብቻ። እኛ ግን አልፈን ሄደን መሀል ከተማ ነው የምንሰራው፣ ለትራንስፖርት ብቻ በቀን እስከ 130 ብር በትሹ እናወጣለን" በሚል አስተያየት የሰጡት እነዚህ ዜጎች ይህንንም ለማግኘት ብዙ ተሰልፈው እና ተንገላተው እንደሆነ ያስረዳሉ።

"ይሄ እጅግ በጣም ኑሮአችንን አክብዶብናል፣ ከአቅማችን በላይ ሆኖብናል። አቤቱታችንን በሚዲያችሁ አስተላልፉልን፣ የሚመለከተው አካል መፍትሔ ሊሰጠን ይገባል" የሚሉት እነዚህ ዜጎች የነዳጅ ድጎማ ቀስ በቀስ መነሳት ላልተጠበቀ እና እጅግ አቅምን ለሚፈታተን ከባድ ወጪ እንደዳረጋቸው በምሬት ይናገራሉ።

"በአንድ ቤት ውስጥ ብቻ ስራ ለመሄድ፣ ልጆችን ት/ቤት ለማድረስ እንዲሁም ሌሎች የቤተሰብ አባላትን እንቅስቃሴ ሳይጨምር ለአንድ ሰው  ይሄን ያህል ወጪ በቀን እያወጡ እንዴት መኖር ይቻላል?" በማለት አስተያየታቸውን በጥያቄ ቋጭተዋል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia




ከእዳ ወደ ምንዳ ወይስ ከእዳ ወደ እዳ?

የተቃርኖ ዘመን!

@EliasMeseret


የትብብር ጥያቄ!

አቶ ገብረማርያም መለስ እድሜያቸው 85 ሲሆን ጥር 9/2017 ዓ/ም ከሰአት ላይ ጠፍተዋል፣ መጨረሻ የታዩበት ቦታ ወሰን 02 አካባቢ ነው። በሰአቱ ለብሰውት የነበረ ልብስ ጥቁር ጃኬት ነው፣ ከዘራም ይዘው ነበር።

አቶ ገብረማርያምን ያየ ሰው በዚህ ስልክ ቁጥር ቢጠቁመን ብለው ቤተሰብ ተማፅኖ አቅርበዋል:

0920581054


እንኳን ለደማቁ የጥምቀት በአል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!

መልካም በዓል!

@EliasMeseret


ኦሮሚያ ውስጥ ወታደሮች አንድ የሲቪል ልብስ የለበሰ ወጣትን እጁን ወደኋላ አስረው በጭካኔ ሲረሽኑ የሚያሳይ ቪድዮ ማህበራዊ ሚድያ ላይ ተለቋል

ቆይ፣ ይህ በቪድዮ የተቀረፀ ነው። እንዲህ ተቀርፆ ለህዝብ ያልደረሰ ምን ያህል ግፍ በየቀኑ ይፈፀማል?

ነፍስ ይማር ወንድሜ!

@EliasMeseret


የዘርፉ ባለሙያዎች አስረዱን!

ታሪካዊ ቅርስ ሲታደስ በዚህ መልኩ የቀድሞ መልኩን እስኪቀይር እንዲህ ይደረጋል? ወይስ አለም አቀፍ ተሞክሮዎችም ይህንኑ ያሳያሉ?

@EliasMeseret


ከጥቂት ሳምንታት በፊት መሠረት ሚድያ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የመንግስት ሰራተኞች ከስራቸው ሊቀነሱ እንደሆነ መረጃ አቅርቦ ነበር

መረጃው በወጣ በነጋታው የመንግስት ሀላፊዎች ተሯሩጠው "ውሸት ነው፣ አዲስ የፀደቀው የሰራተኞች አዋጅ ተቋማት ተልዕኳቸውን በብቃት እንዲፈፅሙ የሚያስችል ብቻ ነው" ብለው ነበር።

ዛሬስ?

እንደ አንበሳ አውቶቡስ አገልግሎት፣ ፖስታ አገልግሎት፣ የተለያዩ የክፍለ ከተማ ፅህፈት ቤቶች... ወዘተ በመቶዎች እና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ማሰናበት ጀምረዋል።

በዚህ ሳምንት ብቻ 450 የፖስታ አገልግሎት ሰራተኞች "በሪፎርም ምክንያት" በሚል ከስራቸው ተነስተው በሌሎች ተተክተዋል፣ ድርጊቱ በዘመድ፣ በእውቅ እና በብሄር ተለይቶ እንደሆነ ሰራተኞቹ ነግረውኛል።

አሁን በዚህ የኑሮ ውድነት የእነዚህ ሰራተኞች እና ቤተሰብ እጣ ምንድን ነው? ጎዳና ላይ መውጣት?

@EliasMeseret


ኢሚግሬሽን አላማው ለህዝብ አገልግሎት መስጠት ነው ወይስ ለትርፍ መስራት?

ኧረ የህዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ሚና እንኳን እየለየን?!

@EliasMeseret


አንዳንድ ግዜ እነዚህ እኔ ላይ ሲደረጉ የነበሩ ዘመቻዎችን መለስ ብዬ ሳስብ ይገርመኛል!

መንግስት በወቅቱ 'ታጋሽ' ሆኖ ይሁን እነዚህ የ 'እሰሩት' ጥሪዎች ውሸት እንደሆኑ ተገንዝቦ ባላውቅም እኔ ላይ አልደረሱም። የሚገርመው ደግሞ እነዚህ የውጭ ጋዜጠኞችን በአካልም፣ በኢሜይልም፣ ወይም በሌላ መንገድ አናግሬያቸው የማላውቅ ናቸው። አግኝቼ አስተርጓሚ ብጠቁማቸውም ምንም ችግር የሌለበት ትብብር ነበር።

ግዜ ደጉ፣ ይህን ለእኔ ሲመኙ የነበሩት አሁን የት ናቸው?

አንዱ ሳውዲ ለእስር ተዳርጎ፣ በቅርቡም ተላልፎ ተሰጥቶ ሀገር ቤት እስር ላይ ይገኛል። አንደኛው የጦርነት አራራው ወጥቶለት ይመስለኛል የስፖርት ተንታኝ ሆኗል።

ለሱሌማን አብደላ ሳይታሰር በፊት በአንድ ጉዳይ ሊያናግረኝ ደውሎ ስህተት እንደሰራ ነግሬ ለውሸቱ ወቅሼዋለሁ፣ አሁንም ትክክለኛ ፍትህ እንዲያገኝ እና ለቤተሰቡ እንዲበቃ እመኛለሁ።

#Karma

@EliasMeseret


ተቀጣሪ ወይም ነጋዴ ሆነህ ቤት ብትገነባ
- ከገቢህ 35% የገቢ ግብር
- የመሬቱ ሊዝ
- የጣራና ግድግዳ ግብር
- ለግንባታው የባንክ ብድር ወለድ
- በምትከፍለው እያንዳንዱ ትራንዛክሽን ባንክ ቻርጅና ቫት
- አሁን የንብረት ግብር
- በሁሉም ክፍያ ላይ ቫት
- ከሆነ ባለሥልጣን ጋር ከተነጃጀስክ ውርስ
- 30% ግሽበት
- ያለምክንያት መዋጮ
- ያለዕድሜህ ሽበት
- የማይቆም ጦርነት

=> መፍትሔ:- ባገኘኸው የትኛውንም safe መንገድ ስደት

Via Abdulkadir Hajj Nureddin

@EliasMeseret

Показано 20 последних публикаций.