የአዲስ አበባ ሀገረ ስበከት ሥራ አስኪያጀ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ በበኩላቸው የሐመረ ብርሃን የብራና መጻሕፍት ሥራ ድርጅት የሚያከናውናቸውን ተግባራት ለመደገፍ ሀገረ ስበከቱ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል።
ዘገባው የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ነው።
ቅዱስ ፓትርያርኩ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ አባቶች በሰንሻይን ፊላንትሮፊ ፋውንዴሽን የአረጋውያን መጦሪያና መንከባከቢያ ማዕከል ጉብኝት አደረጉ።
(#EOTCTV ሚያዝያ ፭ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም አዲስ አበባ)
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ አባቶች የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉሐን ቀሲስ ታጋይ ታደለ፥ የሰንሻይን ፊላንትሮፊ ፋውንዴሽን የአረጋውያን መጦሪያና መንከባከቢያ ማዕከልን ጎብኝተዋል።
በአቶ ሳሙኤል ታፈሰና ባለቤታቸው ወይዘሮ ፈትለወርቅ ከእነ ልጆቻቸው ባሠሩት
በዚህ መጠለያ 400 አረጋውያን ለመርዳት እንዲሠጣቸው የሃይማኖት አባቶችን ጠይቀዋል።
በመርሐ-ግብሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፣ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ ሱራፌል፣ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ጽህፈት ቤት ኃላፊ መጋቤ ጌትነት ለማና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ቅዱስነታቸውና የበላይ ጠባቂ አባቶች ተዘዋውረው በተመለከቷቸው በጎ ስራዎች መደሰታቸውን እንዲሁም ለሌሎች አካላት ትምህርት የሚሰጡ መሆናቸውን ገልጸው በበጎ ተግባራት የተሳተፉ አካላትን አመስግነዋል።
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉሐን ቀሲስ ታጋይ ታደለ፥ በበጎ አድራጊ ባለሃብቶች የተሰሩ በጎ ስራዎች የሚያስደስቱ መሆናቸውን ገለጸዋል።
ምንም ገቢ የሌላቸው አቅመ ደካሞችን ከማገዝ አኳያ ሌሎች ባለሀብቶችን ለመሰል ዓላማ የሚያነሳሳ መሆኑንም ጠቁመዋል። እርስ በእርስ መረዳዳትን እና አቅመ ደካሞችን ማገዝን በተግባር የምናሳይባቸው ተጨማሪ ማዕከሎች እንደሚያስፈልጉ ከጉብኝቱ መረዳታቸውን ጠቅሰዋል።
የሰንሻይን ፊላንትሮፊ ፋውንዴሽን መስራችና የሰንሻይን ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሳሙኤል ታፈሰ፥ ሰንሻይን ከኢንቨስትመንት ስራው ጎን ለጎን ማህበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል።
የሰንሻይን ፊላንትሮፊ ፋውንዴሽን የአረጋውያን መጦሪያና መንከባከቢያ ማዕከል
በ650 ሚሊየን ብር ወጪ የወጣበት የአረጋውያን መንደር ነው።
ይኸው ማዕከል በአዲስ አበባ ከተማ በ30 ሺ ካሬ ላይ ያረፈ ራሱን በራሱ የሚያሥተዳድር ግዙፍ የአረጋውያን መጦሪያ እና መንከባከቢያ ማዕከል በአሁኑ ወቅት ከ1000 በላይ አረጋውያንን እየኖሩ ይገኛሉ።
አቶ ሳሙኤል ታፈሰ እና ባለቤታቸው ወይዘሮ ፈትለወርቅ ከእነ ልጆቻቸው በሀገራችን ኢትዮጵያ ካሉ ባለሀብቶች ተርታ የሚሠለፉ በጎ እና ደግ ብሎም ፈሪሐ እግዚያብሄር ያደረባቸው ኢትዮጵያዊ ናቸው።
በተለያዩ የኢትዮጵያ ከፍሎችም በርካታ ትምህርት ቤቶችን ገንብተው አቅም የሌላቸውን ተማሪዎች በየወሩ የኪስ ገንዘብ እየሰጡ እና የመምህር ደሞዝ እየከፈሉ በርካታ ተማሪዎች እንዲማሩ እያደረጉ ይገኛሉ።
አቶ ሳሙኤል ታፈሰ እና ባለቤታቸው ወይዘሮ ፈትለወርቅ ከእነ ልጆቻቸው ገንዘባቸውን እና ሀሳባቸውን በመስጠት በርካታ ቤተክርስቲያናትንም አንጸዋል ገንብተዋል።
EOTC TV
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
https://youtu.be/Wqgq1KebrOo 🇪🇹 "የቤተክርስቲያን የሆነውን ብቻ" 🇪🇹
📡 የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት 🎥
📱 የዲጂታል ሚዲያ ገጾች💻
ለመረጃ 📞 +251985585858
➽ የዩቲዮብ ገጻችን
http://www.youtube.com/c/eotctv➽ የፌስ ቡክ ገጻችንን
https://www.facebook.com/eotctvchannel➽የቴሌግራም ገጻችን
https://t.me/eotctvchannel➽ የቲክ ቶክ ገጻችን
https://vm.tiktok.com/ZMFSxXdUf/➽ የዩቲዮብ ገጻችን Eotc tv 2
https://youtu.be/Wqgq1KebrOo➽የትዊተር ገጻችን
https://twitter.com/EotcT/➽የኢንስታግራም ገጻችን
https://www.instagram.com/p/CknRF0MtB77/?igshid=MDJmNzVkMjY"ኦርቶዶክሳውያን ብዙኃን መገናኛ ለኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን" በሚል ርዕስ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ያዘጋጀው ሥልጠና ውይይት እና ምክክር መርሐ ግብር በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ዘጋቢ መ/ር አቤል አስፋ
(#EOTCTV ሚያዝያ ፭ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም አዲስ አበባ)
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብዙኃን መገናኛ ተቋማትና የማኅበራዊ ሚዲያ ባለድርሻዎች በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሁሉም ክፍላተ ከተሞች የሚገኙ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የመምሪያ ኃላፊዎች በተገኙበት በጁፒተር ሆቴል በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ሊቀ ሥዩማን እስክንድር ገብረ ክርስቶስ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በንግግራቸውም የሕዝብ ግንኙት መምሪያ በቅዱስ ሲኖዶስ ውሣኔ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ እያከናወነ የሚገኘውን ዋና ዋና ሥራዎችን አብራርተዋል።
ሊቀ ሥዩማን እስክንድር የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ቤተክርስቲያናችንን የሚመጥን የሕዝብ ግንኙነት ተግባራት ለማከናወን ከፍተኛ የበጀት እጥረት ያለበት ቢሆንም ባለው ውስን አቅም በሕትመት ዘርፍ አመርቂ ሥራ እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል:: ለዚህም ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መምሪያውን ለመደገፍ እያደረጉ ላለው ጥረት በማመስገን ; በቀጣይ መምሪያው ራሱን በቴክኖሎጂ በማደራጀት ዘመናዊ መረጃ የስብሰቢያና የመተንተኛ ቴክኖሎጂና አሠራር በመጠቀም ቤተክርስቲያንን የሚመጥን የሕዝብ ግንኙነት ሥራ ለማከናወን ጥረት በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ሥልጠና ውይይትና ምክክር መርሐ ግብሩን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክትም የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብዙኃን መገናኛ ተቋማትና የማኅበራዊ ሚዲያ ባለድርሻዎች የቤተክርስቲያንን ተቋማዊ ውግንና መሠረት ያደረገ ተመጋጋቢ ሥራ ለማከናወን እንዲያስችል የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል::
በመድረኩ ዶክተር አካለ ወልድ ተሰማ "የማኅበራዊ ሚዲያ አዎንታዊ ተጽዕኖ የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን " በሚል ርዕስ ጥናታዊ ጽሑፍ አቅርበዋል።
በመርሐ ግብሩ ሌሎችም ሥልጦታዎች የሚሰጡ ሲሆን