EOTC TV


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия



Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций




• የሥራ ልምድ፡- ለሰርተፊኬት (10+1) 1 ዓመት ከሙያው ጋር የተያያዘ ቀጥተኛ የሥራ ልምድ፤ለመጀመሪያ ዲግሪና ተጨማሪ ሰርተፊኬት (10+1) 0 ዓመት የሥራ ልምድ ፤ ከግል ቀጣሪ ተቋማት የሚርቡ የሥራ ልምድ ማስረጃዎች ከመንግሥታዊ የግብር ሰብሳቢ መሥሪያ ቤት ግብር ስለመከፈሉ ተጨማሪ ማረጋገጫ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
• መሠረታዊ የኮምፒውተርና ማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃም ክህሎት ያለው/ ያላት
• በኦሮምኛ እና አማርኛ ቋንቋዎች መናገር ማዳመጥ ማንበብ እና መጻፍ የሚችል /የምትችል
• የቅጥር ሁኔታ፡- ለስድሰት ወር ኮንትራት ሆኖ እንደ አስፈላጊነቱ በቋሚነት የሚቀጠሩ ይሆናል
• ደመወዝ በድርጅቱ ስኬል መሠረት

2.3 የሥራ መደቡ መጠሪያ ፡- የካሜራ ባለሙያ
• ብዛት ፡- 2
• ፆታ ፡- አይለይም
• ዕድሜ፡- ከ40 ያልበለጠ (ያልበለጠች)
• የትምህርት ደረጃ ፡- ከታወቀ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ በቪዲዮና ፎቶግራፍ ትምህርት ለአንድ ዓመት የሚሰጠውን ትምህርት ተከታትሎ በሰርተፊኬት (10+1) የተመረቀ ወይም የተመረቀች፡፡
• የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታይ የሆነ ወይም የሆነች መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን ዕውቀት ያለው ወይም ያላት (በሰንበት ትምህርት ቤት ወይም በግቢ ጉባኤ የተማረ/የተማረች ማስረጃ ማቅረብ የሚችል/ የምትችል)
• የሥራ ልምድ፡- ለሰርተፊኬት (10+1) 1 ዓመት ከሙያው ጋር የተያያዘ ቀጥተኛ የሥራ ልምድ ፤ ከግል ቀጣሪ ተቋማት የሚርቡ የሥራ ልምድ ማስረጃዎች ከመንግሥታዊ የግብር ሰብሳቢ መሥሪያ ቤት ግብር ስለመከፈሉ ተጨማሪ ማረጋገጫ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
• መሠረታዊ የኮምፒውተርና ማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃም ክህሎት ያለው/ ያላት
• የቅጥር ሁኔታ፡- ለስድሰት ወር ኮንትራት ሆኖ እንደ አስፈላጊነቱ በቋሚነት የሚቀጠሩ ይሆናል
• ደመወዝ በድርጅቱ ስኬል መሠረት
ተጨማሪ መስፈርቶች ለሁሉም አመልካቾች
አመልካቾች የትምህርትና የሥራ ልምድ ማስረጃዎቻቻን እና ሲቪ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉ 5 ተከታታይ የሥራ ቀናት 5 ኪሎ ቅድስተ ማርያም ቤተክርስቲያን አጠገብ በሚገኘው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት የሰው ኃይል አስተዳደር ዋና ክፍል ቢሮ ቁጥር 16 በሥራ ሰዓት ኦሪጅናሉን ለማመሳከሪያ በማቅረብ የማይመለስ ኮፒ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
በአካል በመቅረብ ከሚመጡ ማመልከቻዎች ውጪ በማናቸውም መንገድ መመዝገብ አይቻልም፡፡
ለተጨማሪ መረጃ
Tell + 251- 11 8 12 12 24
+251-111 274 847
FAX +251-111 275 531
E-mail office@eotctv.et
POBOX 30730 ኮድ/Code 1000
Addis Ababa, Ethiopia


ቀን 11/08/2016 ዓ.ም
በድጋሚ የወጣ ክፍት የሥራ ማስታወቂያ

1.1 ለትግርኛ ቋንቋ መርሐግብር ክፍል የሠራተኛ ቅጥርን በተመለከተ
ዝርዝር የቅጥር ማስታወቂያ ፡-
• የሥራ መደብ መጠሪያ፡- ለትግርኛ ቋንቋ መርሐ ግብር ሪፖርተር
• ብዛት፡- 2
• ፆታ፡- አይለይም
• ዕድሜ፡- ከ40 ያልበለጠ (ያልበለጠች)
• ተፈላጊ የት/ት ደረጃ ከታወቀ ዩኒቨርስቲ በጋዜጠኝነት፣በቋንቋና ሥነ ጽሑፍ፣በፎክሎር፣ ቲያትሪካል አርት በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቀ/የተመረቀች፤ ወይም በሥነ መለኮት የመጀመሪያ ዲግሪና ተጨማሪ የጋዜጠኝነት ሥልጠና የወሰደ ወይም የወሰደች ለዚህም ማስረጃ ማቅረብ የሚችል የምትችል፡፡፡
• የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታይ የሆነ ወይም የሆነች መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን ዕውቀት ያለው ወይም ያላት (በሰንበት ትምህርት ቤት ወይም በግቢ ጉባኤ የተማረ/የተማረች ማስረጃ ማቅረብ የሚችል/ የምትችል)
• በትግርኛ ቋንቋ መናገር ፣ማዳመጥ ማንበብ እና መጻፍ የሚችል /የምትችል
• የሥራ ልምድ፡- 1 ዓመት ከሙያው ጋር የተያያዘ ቀጥተኛ የሥራ ልምድ፤ከግል ቀጣሪ ተቋማት የሚርቡ የሥራ ልምድ ማስረጃዎች ከመንግሥታዊ የግብር ሰብሳቢ መሥሪያ ቤት ግብር ስለመከፈሉ ተጨማሪ ማረጋገጫ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
• መሠረታዊ የኮምፒውተርና ማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃም ክህሎት ያለው/ ያላት
• የቅጥር ሁኔታ፡- ለስድሰት ወር ኮንትራት ሆኖ እንደ አስፈላጊነቱ በቋሚነት የሚቀጠሩ ይሆናል
• ደመወዝ በድርጅቱ ስኬል መሠረት
1.2 ለአፋን ኦሮሞ መርሐ ግብር ሪፖርተር ቅጥርን በተመለከተ
• የሥራ መደብ መጠሪያ፡- የኦሮምኛ ቋንቋ መርሐ ግብር ሪፖርተር
• ብዛት፡- 1
• ፆታ፡- አይለይም
• ዕድሜ፡- ከ40 ያልበለጠ (ያልበለጠች)
• ተፈላጊ የት/ት ደረጃ ከታወቀ ዩኒቨርስቲ በጋዜጠኝነት፣በቋንቋና ሥነ ጽሑፍ፣በፎክሎር፣ ቲያትሪካል አርት በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቀ/የተመረቀች፤ ወይም በሥነ መለኮት የመጀመሪያ ዲግሪና ተጨማሪ የጋዜጠኝነት ሥልጠና የወሰደ ወይም የወሰደች ለዚህም ማስረጃ ማቅረብ የሚችል የምትችል፡፡፡
• የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታይ የሆነ ወይም የሆነች መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን ዕውቀት ያለው ወይም ያላት (በሰንበት ትምህርት ቤት ወይም በግቢ ጉባኤ የተማረ/የተማረች ማስረጃ ማቅረብ የሚችል/ የምትችል)
• በኦሮምኛ ቋንቋ መናገር ፣ማዳመጥ፣ ማንበብ እና መጻፍ የሚችል /የምትችል
• የሥራ ልምድ፡- አንድ ዓመት ከሙያው ጋር የተያያዘ ቀጥተኛ የሥራ ልምድ፤ከግል ቀጣሪ ተቋማት የሚርቡ የሥራ ልምድ ማስረጃዎች ከመንግሥታዊ የግብር ሰብሳቢ መሥሪያ ቤት ግብር ስለመከፈሉ ተጨማሪ ማረጋገጫ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
• መሠረታዊ የኮምፒውተርና ማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃም ክህሎት ያለው/ ያላት
• የቅጥር ሁኔታ፡- ለስድሰት ወር ኮንትራት ሆኖ እንደ አስፈላጊነቱ በቋሚነት የሚቀጠሩ ይሆናል
• ደመወዝ በድርጅቱ ስኬል መሠረት
1.3 የአማርኛ ቋንቋ ከፍተኛ ሪፖርት
የሥራ መደብ መጠሪያ - የአማርኛ ቋንቋ ከፍተኛ ሪፖርት
• ብዛት፡- 1
• ፆታ፡- አይለይም
• ዕድሜ፡- ከ40 ያልበለጠ (ያልበለጠች)
• ተፈላጊ የት/ት ደረጃ ከታወቀ ዩኒቨርስቲ በጋዜጠኝነት፣በቋንቋና ሥነ ጽሑፍ፣በፎክሎር፣ ቲያትሪካል አርት በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቀ/የተመረቀች፤ ወይም በሥነ መለኮት የመጀመሪያ ዲግሪና ተጨማሪ የጋዜጠኝነት ሥልጠና የወሰደ ወይም የወሰደች ለዚህም ማስረጃ ማቅረብ የሚችል የምትችል፡፡፡
• የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታይ የሆነ ወይም የሆነች መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን ዕውቀት ያለው ወይም ያላት (በሰንበት ትምህርት ቤት ወይም በግቢ ጉባኤ የተማረ/የተማረች ማስረጃ ማቅረብ የሚችል/ የምትችል)
• የሥራ ልምድ፡- ለመጀመሪያ ዲግሪ 2 ዓመት ከሙያው ጋር የተያያዘ ቀጥተኛ የሥራ ልምድ፤ከግል ቀጣሪ ተቋማት የሚርቡ የሥራ ልምድ ማስረጃዎች ከመንግሥታዊ የግብር ሰብሳቢ መሥሪያ ቤት ግብር ስለመከፈሉ ተጨማሪ ማረጋገጫ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
• መሠረታዊ የኮምፒውተርና ማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃም ክህሎት ያለው/ ያላት
• የቅጥር ሁኔታ፡- ለስድሰት ወር ኮንትራት ሆኖ እንደ አስፈላጊነቱ በቋሚነት የሚቀጠሩ ይሆናል
• ደመወዝ በድርጅቱ ስኬል መሠረት

2 ለቴክኒክ ዋና ክፍል የሠራተኛ ቅጥር
2.1 የሥራ መደቡ መጠሪያ ፡- ለትግርኛና አማርኛ ቋንቋ የምስልና ድምጽ ቅንብር (ኤዲቲንግ) ባለሙያ
• ብዛት ፡- 1
• ፆታ ፡- አይለይም
• ዕድሜ፡- ከ40 ያልበለጠ (ያልበለጠች)
• የትምህርት ደረጃ ፡- ከታወቀ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ በምስልና ድምጽ ቅንብር (በቪዲዮ ኤዲቲንግ) ትምህርት ለአንድ ዓመት የሚሰጠውን ትምህርት ተከታትሎ በሰርተፊኬት (10+1) የተመረቀ ወይም የተመረቀች፡፡
• ወይም በኮምፒዩተር ሳይንስ፣አይቲ እና ተዛማጅ መስኮች ከታወቀ ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ዲግሪ ያለው ወይም ያላት እና ከታወቀ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ በምስልና ድምጽ ቅንብር (በቪዲዮ ኤዲቲንግ) በሰርተፊኬት (10+1) የተመረቀች ወይም የተመረቀ፡፡
• የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታይ የሆነ ወይም የሆነች መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን ዕውቀት ያለው ወይም ያላት (በሰንበት ትምህርት ቤት ወይም በግቢ ጉባኤ የተማረ/የተማረች ማስረጃ ማቅረብ የሚችል/ የምትችል)
• የሥራ ልምድ፡- ለሰርተፊኬት (10+1) 1 ዓመት ከሙያው ጋር የተያያዘ ቀጥተኛ የሥራ ልምድ፤ለመጀመሪያ ዲግሪና ተጨማሪ ሰርተፊኬት (10+1) 0 ዓመት የሥራ ልምድ ፤ ከግል ቀጣሪ ተቋማት የሚርቡ የሥራ ልምድ ማስረጃዎች ከመንግሥታዊ የግብር ሰብሳቢ መሥሪያ ቤት ግብር ስለመከፈሉ ተጨማሪ ማረጋገጫ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
• መሠረታዊ የኮምፒውተርና ማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃም ክህሎት ያለው/ ያላት
• በትግርኛ እና አማርኛ ቋንቋዎች መናገር ማዳመጥ ማንበብ እና መጻፍ የሚችል /የምትችል
• የቅጥር ሁኔታ፡- ለስድሰት ወር ኮንትራት ሆኖ እንደ አስፈላጊነቱ በቋሚነት የሚቀጠሩ ይሆናል
• ደመወዝ በድርጅቱ ስኬል መሠረት
2.2 የሥራ መደቡ መጠሪያ ፡- ለኦሮምኛና አማርኛ ቋንቋ የምስልና ድምጽ ቅንብር (ኤዲቲንግ) ባለሙያ
• ብዛት ፡- 1
• ፆታ ፡- አይለይም
• ዕድሜ፡- ከ40 ያልበለጠ (ያልበለጠች)
• የትምህርት ደረጃ ፡- ከታወቀ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ በምስልና ድምጽ ቅንብር (በቪዲዮ ኤዲቲንግ) ትምህርት ለአንድ ዓመት የሚሰጠውን ትምህርት ተከታትሎ በሰርተፊኬት (10+1) የተመረቀ ወይም የተመረቀች፡፡
• ወይም በኮምፒዩተር ሳይንስ፣አይቲ እና ተዛማጅ መስኮች ከታወቀ ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ዲግሪ ያለው ወይም ያላት እና ከታወቀ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ በምስልና ድምጽ ቅንብር (በቪዲዮ ኤዲቲንግ) በሰርተፊኬት (10+1) የተመረቀች ወይም የተመረቀ፡፡
• የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታይ የሆነ ወይም የሆነች መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን ዕውቀት ያለው ወይም ያላት (በሰንበት ትምህርት ቤት ወይም በግቢ ጉባኤ የተማረ/የተማረች ማስረጃ ማቅረብ የሚችል/ የምትችል)










EOTC TV
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
              https://youtu.be/Wqgq1KebrOo
     🇪🇹   "የቤተክርስቲያን የሆነውን ብቻ"  🇪🇹
        📡  የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት 🎥
                       📱 የዲጂታል ሚዲያ ገጾች💻
ለመረጃ  📞 +251985585858
➽ የዩቲዮብ ገጻችን
http://www.youtube.com/c/eotctv
➽ የፌስ ቡክ ገጻችንን
https://www.facebook.com/eotctvchannel
➽የቴሌግራም ገጻችን
https://t.me/eotctvchannel
➽ የቲክ ቶክ ገጻችን
https://vm.tiktok.com/ZMFSxXdUf/
➽ የዩቲዮብ ገጻችን Eotc tv 2
https://youtu.be/Wqgq1KebrOo
➽የትዊተር ገጻችን
https://twitter.com/EotcT/
➽የኢንስታግራም ገጻችን
https://www.instagram.com/p/CknRF0MtB77/?igshid=MDJmNzVkMjY


የአዲስ አበባ ሀገረ ስበከት ሥራ አስኪያጀ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ በበኩላቸው የሐመረ ብርሃን የብራና መጻሕፍት ሥራ ድርጅት የሚያከናውናቸውን ተግባራት ለመደገፍ ሀገረ ስበከቱ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል።
ዘገባው የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ነው።

ቅዱስ ፓትርያርኩ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ አባቶች  በሰንሻይን ፊላንትሮፊ ፋውንዴሽን የአረጋውያን መጦሪያና መንከባከቢያ ማዕከል ጉብኝት አደረጉ።
(#EOTCTV ሚያዝያ ፭ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም አዲስ አበባ)
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት  ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ አባቶች የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉሐን ቀሲስ ታጋይ ታደለ፥ የሰንሻይን ፊላንትሮፊ ፋውንዴሽን የአረጋውያን መጦሪያና መንከባከቢያ ማዕከልን ጎብኝተዋል።
በአቶ ሳሙኤል ታፈሰና ባለቤታቸው ወይዘሮ ፈትለወርቅ ከእነ ልጆቻቸው ባሠሩት
በዚህ መጠለያ 400 አረጋውያን ለመርዳት እንዲሠጣቸው የሃይማኖት አባቶችን ጠይቀዋል።

በመርሐ-ግብሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፣ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ ሱራፌል፣ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት  ጽህፈት ቤት ኃላፊ መጋቤ ጌትነት ለማና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ቅዱስነታቸውና የበላይ ጠባቂ አባቶች ተዘዋውረው በተመለከቷቸው በጎ ስራዎች መደሰታቸውን እንዲሁም ለሌሎች አካላት ትምህርት የሚሰጡ መሆናቸውን ገልጸው በበጎ ተግባራት የተሳተፉ አካላትን አመስግነዋል።
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉሐን ቀሲስ ታጋይ ታደለ፥ በበጎ አድራጊ ባለሃብቶች የተሰሩ በጎ ስራዎች  የሚያስደስቱ መሆናቸውን ገለጸዋል።
ምንም ገቢ የሌላቸው አቅመ ደካሞችን ከማገዝ አኳያ ሌሎች ባለሀብቶችን ለመሰል ዓላማ የሚያነሳሳ መሆኑንም ጠቁመዋል። እርስ በእርስ መረዳዳትን እና አቅመ ደካሞችን ማገዝን በተግባር የምናሳይባቸው ተጨማሪ ማዕከሎች እንደሚያስፈልጉ ከጉብኝቱ መረዳታቸውን ጠቅሰዋል።
የሰንሻይን ፊላንትሮፊ ፋውንዴሽን መስራችና የሰንሻይን ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሳሙኤል ታፈሰ፥ ሰንሻይን ከኢንቨስትመንት ስራው ጎን ለጎን ማህበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል።
የሰንሻይን ፊላንትሮፊ ፋውንዴሽን የአረጋውያን መጦሪያና መንከባከቢያ ማዕከል
በ650 ሚሊየን ብር ወጪ የወጣበት የአረጋውያን መንደር ነው።
ይኸው ማዕከል  በአዲስ አበባ ከተማ በ30 ሺ ካሬ ላይ ያረፈ ራሱን በራሱ የሚያሥተዳድር ግዙፍ የአረጋውያን መጦሪያ እና መንከባከቢያ ማዕከል በአሁኑ ወቅት ከ1000 በላይ አረጋውያንን  እየኖሩ ይገኛሉ።
አቶ ሳሙኤል ታፈሰ እና ባለቤታቸው ወይዘሮ ፈትለወርቅ ከእነ ልጆቻቸው በሀገራችን ኢትዮጵያ ካሉ ባለሀብቶች ተርታ የሚሠለፉ በጎ እና ደግ ብሎም ፈሪሐ እግዚያብሄር ያደረባቸው ኢትዮጵያዊ ናቸው።
በተለያዩ የኢትዮጵያ ከፍሎችም በርካታ ትምህርት ቤቶችን ገንብተው አቅም የሌላቸውን ተማሪዎች በየወሩ የኪስ ገንዘብ እየሰጡ እና የመምህር ደሞዝ እየከፈሉ በርካታ ተማሪዎች እንዲማሩ እያደረጉ ይገኛሉ።
አቶ ሳሙኤል ታፈሰ እና ባለቤታቸው ወይዘሮ ፈትለወርቅ ከእነ ልጆቻቸው ገንዘባቸውን እና ሀሳባቸውን በመስጠት በርካታ ቤተክርስቲያናትንም አንጸዋል ገንብተዋል።

EOTC TV
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
              https://youtu.be/Wqgq1KebrOo
     🇪🇹   "የቤተክርስቲያን የሆነውን ብቻ"  🇪🇹
        📡  የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት 🎥
                       📱 የዲጂታል ሚዲያ ገጾች💻
ለመረጃ  📞 +251985585858
➽ የዩቲዮብ ገጻችን
http://www.youtube.com/c/eotctv
➽ የፌስ ቡክ ገጻችንን
https://www.facebook.com/eotctvchannel
➽የቴሌግራም ገጻችን
https://t.me/eotctvchannel
➽ የቲክ ቶክ ገጻችን
https://vm.tiktok.com/ZMFSxXdUf/
➽ የዩቲዮብ ገጻችን Eotc tv 2
https://youtu.be/Wqgq1KebrOo
➽የትዊተር ገጻችን
https://twitter.com/EotcT/
➽የኢንስታግራም ገጻችን
https://www.instagram.com/p/CknRF0MtB77/?igshid=MDJmNzVkMjY


"ኦርቶዶክሳውያን ብዙኃን መገናኛ ለኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን" በሚል ርዕስ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ  ግንኙነት መምሪያ ያዘጋጀው ሥልጠና ውይይት እና ምክክር መርሐ ግብር በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ዘጋቢ መ/ር አቤል አስፋ
(#EOTCTV ሚያዝያ ፭ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም አዲስ አበባ)
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብዙኃን መገናኛ ተቋማትና የማኅበራዊ ሚዲያ ባለድርሻዎች በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሁሉም ክፍላተ ከተሞች የሚገኙ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የመምሪያ ኃላፊዎች በተገኙበት በጁፒተር ሆቴል በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ሊቀ ሥዩማን እስክንድር ገብረ ክርስቶስ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ  ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በንግግራቸውም የሕዝብ ግንኙት መምሪያ በቅዱስ ሲኖዶስ ውሣኔ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ እያከናወነ የሚገኘውን ዋና ዋና ሥራዎችን አብራርተዋል።
ሊቀ ሥዩማን እስክንድር  የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ቤተክርስቲያናችንን የሚመጥን የሕዝብ ግንኙነት ተግባራት ለማከናወን ከፍተኛ የበጀት እጥረት ያለበት ቢሆንም ባለው ውስን አቅም በሕትመት  ዘርፍ አመርቂ ሥራ እያከናወነ  መሆኑን ገልጸዋል:: ለዚህም ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መምሪያውን ለመደገፍ እያደረጉ ላለው ጥረት በማመስገን ; በቀጣይ መምሪያው ራሱን በቴክኖሎጂ በማደራጀት  ዘመናዊ መረጃ የስብሰቢያና የመተንተኛ ቴክኖሎጂና አሠራር በመጠቀም ቤተክርስቲያንን የሚመጥን የሕዝብ ግንኙነት ሥራ ለማከናወን  ጥረት በማድረግ ላይ እንደሚገኝ  ገልጸዋል።
ሥልጠና ውይይትና   ምክክር መርሐ ግብሩን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክትም የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብዙኃን መገናኛ ተቋማትና የማኅበራዊ ሚዲያ ባለድርሻዎች የቤተክርስቲያንን ተቋማዊ ውግንና መሠረት ያደረገ ተመጋጋቢ ሥራ ለማከናወን  እንዲያስችል የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል::
በመድረኩ ዶክተር አካለ ወልድ ተሰማ "የማኅበራዊ ሚዲያ አዎንታዊ ተጽዕኖ የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን " በሚል ርዕስ ጥናታዊ ጽሑፍ አቅርበዋል።
በመርሐ ግብሩ ሌሎችም ሥልጦታዎች የሚሰጡ  ሲሆን


እንደ መንበረ ፓትርያርክ ከዲጂታል ሚዲያዎች ጋር ተቀራርቦ ለመሥራት የተጀመሩ ሥራዎች እንደሚቀጥሉ የገለጹት ብፁዕነታቸው ; በዲጂታል ሚዲያ እና ማኅበራዊ ሚዲያ የሚገለገሉ እና የሚያገለግሉ  የቤተክርስቲያን ልጆች ለቤተክርስቲያን ከማይጠቅሙ አጀንዳዎች ራሳቸውን እንዲያርቁ መክረዋል። 
በዲጂታል ሚዲያና ማኅበራዊ ሚዲያውን በመጠቀም በሕሙማን እና በቤተክርስቲያን ስም የሚከናወኑ ልመናዎች ለተባለው ዓላማ ስለመዋላቸው ማረጋገጥ ከእያንዳንዱ እርዳታ ሰጪ ይጠበቃል ብለዋል ብፁዕ አቡነ አብርሃም።
ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን በጣስ መልኩ ምስጢራተ ቤተክርስቲያን እና ሥርዓተ አምልኮ  በዲጂታል ሚዲያ የሚያስተላልፉ አገልጋዮች እና ሌሎች የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ከድርጊታቸው መቆጠብ እንዳለባቸው ገልጸዋል። ብፁዕነታቸው ቤተ ክርስቲያን በቀጣይ ለዲጀታል ሚዲያና ማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን በተመለከተ የራሷን ሕግና መመሪያ እንዲዘጋጅ ይደረጋል ብለዋል።
ብፁዕነታቸው መርሐ ግብሩን ላሰናዳው በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ  ግንኙነት መምሪያ ምስጋና አቅርበዋል።
መርሐ ግብሩ ሚያዝያ ፯ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
#EOTC TV
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
              https://youtu.be/Wqgq1KebrOo
     🇪🇹   "የቤተክርስቲያን የሆነውን ብቻ"  🇪🇹
        📡  የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት 🎥
                       📱 የዲጂታል ሚዲያ ገጾች💻
ለመረጃ  📞 +251985585858
➽ የዩቲዮብ ገጻችን
http://www.youtube.com/c/eotctv
➽ የፌስ ቡክ ገጻችንን
https://www.facebook.com/eotctvchannel
➽የቴሌግራም ገጻችን
https://t.me/eotctvchannel
➽ የቲክ ቶክ ገጻችን
https://vm.tiktok.com/ZMFSxXdUf/
➽ የዩቲዮብ ገጻችን Eotc tv 2
https://youtu.be/Wqgq1KebrOo
➽የትዊተር ገጻችን
https://twitter.com/EotcT/
➽የኢንስታግራም ገጻችን
https://www.instagram.com/p/CknRF0MtB77/?igshid=MDJmNzVkMjY



በመልአከ ሰላም ዶክተር አባ ቃለ ጽድቅ ሙሉጌታ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ ኃላፊ " ማኅበራዊ ሚዲያን መረዳት ከኦርቶዶክሳዊ ማንነት አንጻር" በሚል ርዕስ በመጽሐፍ ቅዱስ መረጃ ላይ የተመሠረተ ጥናትና ማብራሪያ አቅርበዋል፡፡
በቀጠልም በአቶ ነጻነት ተስፋዬ  "ሙያዊ ሐላፊነት በማኅበራዊ ሚድያ"
በሚል ርእስ ጥናታዊ ጽሑፍ  አቅርበዋል ። በጥናታቸውም ማኅበራዊ ሚዲያ ለቤተ ክርስቲያን የፈጠረውን ዕድል በተመለከተ ማሳያዎች  አቅርበዋል፡፡የፌስቡክን፣ የቲዩተር፣ የሊንክዲን፣የኢንስታግራም፣ የዩቲዮብ፣የቲክቶክ፣ የቴሌግራም፣የፓድካት ዝርዝር ሁኔታዎችን እና የዓለም አቀፍ ድርጅቶችና ተቋማት እንዲሁም  የኅብረተሰቡ ዝንባሌ ከየት ላይ እንደሚያመዝን ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ቤተክርስቲያን በሀገር አቀፍ ደረጃ ያላት ድርሻ ወደፊት በዲጂታል ሚዲያ በፋክት ቼክ እንዲሁም አሊጎሪዝሙን ተረድቶ መሥራትን በተመለከጥቆማ የተሰጠበት መድረክ ነበር።
በመቀጠል በተለያዩ ፬ ቡድኖች በተደረጉ ውይይቶች ተጠቃለው በመድረኩ ቀርቧል።
#EOTC TV
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
              https://youtu.be/Wqgq1KebrOo
     🇪🇹   "የቤተክርስቲያን የሆነውን ብቻ"  🇪🇹
        📡  የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት 🎥
                       📱 የዲጂታል ሚዲያ ገጾች💻
ለመረጃ  📞 +251985585858
➽ የዩቲዮብ ገጻችን
http://www.youtube.com/c/eotctv
➽ የፌስ ቡክ ገጻችንን
https://www.facebook.com/eotctvchannel
➽የቴሌግራም ገጻችን
https://t.me/eotctvchannel
➽ የቲክ ቶክ ገጻችን
https://vm.tiktok.com/ZMFSxXdUf/
➽ የዩቲዮብ ገጻችን Eotc tv 2
https://youtu.be/Wqgq1KebrOo
➽የትዊተር ገጻችን
https://twitter.com/EotcT/
➽የኢንስታግራም ገጻችን
https://www.instagram.com/p/CknRF0MtB77/?igshid=MDJmNzVkMjY



ሊቀ ሥዩማን እስክንድር  የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ቤተክርስቲያናችንን የሚመጥን የሕዝብ ግንኙነት ተግባራት ለማከናወን ከፍተኛ የበጀት እጥረት ያለበት ቢሆንም ባለው ውስን አቅም በሕትመት  ዘርፍ አመርቂ ሥራ እያከናወነ  መሆኑን ገልጸዋል:: ለዚህም ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መምሪያውን ለመደገፍ እያደረጉ ላለው ጥረት በማመስገን ; በቀጣይ መምሪያው ራሱን በቴክኖሎጂ በማደረጀት  ዘመናዊ መረጃ የስብሰቢያና የመተንተኛ ቴክኖሎጂና አሠራር በመጠቀም ቤተክርስቲያንን የሚመጥን የሕዝብ ግንኙነት ሥራ ለማከናወን  ጥረት በማድረግ ላይ እንደሚገኝ  ገልጸዋል።
ሥልጠና ውይይትና   ምክክር መርሐ ግብሩን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክትም የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብዙኃን መገናኛ ተቋማትና የማኅበራዊ ሚዲያ ባለድርሻዎች የቤተክርስቲያንን ተቋማዊ ውግንና መሠረት ያደረገ ተመጋጋቢ ሥራ ለማከናወን  እንዲያስችል የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል::
በመድረኩ ዶክተር አካለ ወልድ ተሰማ "የማኅበራዊ ሚዲያ አዎንታዊ ተጽዕኖ የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን " በሚል ርዕስ ጥናታዊ ጽሑፍ አቅርበዋል
ሌሎችም ሥልጦታዎች የሚሰጡ  ሲሆን
በመርሐ ግብሩ ማጠናቀቂያ  አባታዊ  ቃለ ምእዳንና መልዕክት ያስተላልፍሉ ተብሎ ይጠበቃል።








ሐመረ ብርሃን የብራና መጻሕፍት ሥራ ድርጅት የብራና ሥራዎች አዘገጃጀትን ለአሁኑ ትውልድ ማሳየትን ዓላማ ያደርገ ዓውደ ርዕይ አዘጋጀ።
(#EOTCTV ሚያዝያ ፭ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም አዲስ አበባ)
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ሐመረ ብርሃን የብራና መጻሕፍት ሥራ ድርጅት “ንጹህ ምንጭ ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል ባዘጋጀው ዐውደ ርእይ የአባቶቻችን የብራና ስራዎች በዘመናችን መኖራቸውን ለአሁኑ ትውልድ ለማሳየት ታስቢ ያደርግ ለ፲ ተከታታይ ቀናት የሚቆይ አውድ ርእይ በግዮን ሆቴል እያካሄደ ይገኛል።

በመክፈቻ መርሐ ግብር ላይ የጠቅላይ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ የባህርዳር እና ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም፤ የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅድስት ሥላሴ  ዩኒቨርስቲ ፕሬዘዳንት ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስበከት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ ፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን እና በርካታ ምእመናን ተገኝተዋል።

ብጹዕ አቡነ አብርሃም የተዘጋጀውን ዐውደ ርእይ ጎብኘተው ባስተላለፉት መልእክት የብራና ጽሑፍ ቤተክርስቲያን ትኩረት ሰጥታ ልትሠራው  የሚገባው ጉዳይ ቢሆንም አስካሁን ምንም  አለማድረጉዋ ቢያሳዝነኝም ታሪኩዋን የሚያስቀጥሉ ልጆች እንዳሉዋት በማየቴ ኩራት ተሰምቶኛል ብለዋል።

ብፁዕ አቡነ ፊልጶስም ከጉብኝቱ በኋላ አባቶቻችን ያውረሱን የብራና ውጤቶች እና ልዩ ልዩ የእደ ጥበብ ሥራዎች በዚህ መልኩ መዘጋጀታቸው ለቀጣይ ትውልድ ታሪኩን ለማሻገር ይረዳል በማለት ገልጸዋል።


ቅዱስ ፓትርያርኩ ለበጎ አድራጊው አቶ አባተ የሥጋት እና   ለባለቤታቸው ለወይዘሮ   በላይነሽ  ተገኔ  የምስክር  ወረቀት እና  የማስታወሻ  ስጦታ አበረከቱ።
መምህርነት   ኑኀሚን  ዋቅጅራ
(#EOTCTV ሚያዝያ ፯ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም አዲስ አበባ)
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
በብፁዕ  አቡነ  ማቲያስ  ቀዳማዊ ፖትርያርክ   ርዕሰ   ሊቃነ ጳጳሳት  ዘኢትዮጵያ  ሊቀ  ጳጳስ  ዘአክሱም  ወእጨጌ  ዘመንበረ   ተክለ ሃይማኖት ለበጎ አድራጊው አቶ አባተ የሥጋት እና   ለባለቤታቸው ለወይዘሮ   በላይነሽ  ተገኔ  የምስክር  ወረቀት እና  የማስታወሻ  ስጦታ አበረከቱ።
ለሀገር  እና  ለቅድስት  ቤተ  ክርስቲያን   በብዙ አቅጣጫ  በጎ ሥራዎችን  የሰሠሩት እና  ከ10, 000 (አሥር  ሺህ  )   በላይ  ብርድ  ልብሶችን  ለገዳማት  ለአብነት  ትምህርት ቤቶች  እና  ለመንፈሳዊ  ተቋማት   በመስጠት   ከፍተኛ አስተዋጽዖ ላበረከቱት ግለሰቦች ስጦታው ሲበረከት ብፁዕ አቡነ   አብርሃም የጠቅላይ  ቤተ ክህነት   ዋና  ሥራ   አስኪያጅ እና የባህር  ዳር  እና  የሰሜን  ጎጃም    አኅጉረ  ሰብከት ሊቀ ጳጳስ እና ብፁዕ   አቡነ  ፊልጶስ  የቅድስት  ሥላሴ    ዩኒቨርስቲ   ፕሬዚዳንት   የደቡብ  ኦሞ  እና  የአሪ ዞኖች አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ  በተኙበት ነው የተከናወነው ።
 በቅዱስነታቸው ስለ በጎ አድራጎት ሥራቸው አቶ  አባተ  የሥጋትና ቤተሰቦቻቸውን  አመስግነዋቸዋል  ።
 በዕለቱ   የአቶ  አባተ  የሥጋትን  የበጎ  ተግባር  አርአያነትን በመከተል  ልጆቻቸው  እና  የልጅ  ልጆቻቸው  ሁሉ  የመልካም  ተግባር   ምሳሌዎች  ናቸው  በማለት በቅርብ  በአገልግሎታቸው   የሚያውቋቸው ብፁዓን  አበው  ሊቃነ   ጳጳሳት ምስክርነትና  አባታዊ  መልእክታቸውን  አስተላልፈዋል።
#EOTC TV
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
              https://youtu.be/Wqgq1KebrOo
     🇪🇹   "የቤተክርስቲያን የሆነውን ብቻ"  🇪🇹
        📡  የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት 🎥
                       📱 የዲጂታል ሚዲያ ገጾች💻
ለመረጃ  📞 +251985585858
➽ የዩቲዮብ ገጻችን
http://www.youtube.com/c/eotctv
➽ የፌስ ቡክ ገጻችንን
https://www.facebook.com/eotctvchannel
➽የቴሌግራም ገጻችን
https://t.me/eotctvchannel
➽ የቲክ ቶክ ገጻችን
https://vm.tiktok.com/ZMFSxXdUf/
➽ የዩቲዮብ ገጻችን Eotc tv 2
https://youtu.be/Wqgq1KebrOo
➽የትዊተር ገጻችን
https://twitter.com/EotcT/
➽የኢንስታግራም ገጻችን
https://www.instagram.com/p/CknRF0MtB77/?igshid=MDJmNzVkMjY



ቅዱስ ፓትርያርኩ ለኦርቶዶክሳውያን ብዙኃን መገናኛና ዲጂታል ሚዲያ ባለሙያዎች ያዘጋጀው ሥልጠና ማጠናቀቂያ ላይ ቃለ ምእዳንና የሥራ መመሪያ ሰጡ።
ዘጋቢ መ/ር አቤል አሰፋ
(#EOTCTV ሚያዝያ ፯ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም አዲስ አበባ)
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
በሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተዘጋጀው " ኦርቶዶክሳውያን ብዙኃን መገናኛ ለኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን " በሚል ርዕስ ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና  ማጠናቀቂያ   ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት አባታዊ  ቃለ ምእዳንና መልዕክት አስተላልፉ።
በመድረኩ  ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ የኮንታ ዳውሮ አህጉረ ስብከት ጳጳስ ፤ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የሥራ ኃላፊዎች የሥልጠናው ተሳታፊዎች በተገኙበት ነው የተከናወነው ።
በመድረኩ ተሳታፊዎች በሥልጠናው በደረሱበት ስምምነት መሠረት የአቋም መግለጫ አቅርበዋል።
በማስከተልም ብፁዕ አቡነ አብርሃም ኦርቶዶክሳውያን ብዙኃን መገናኛ ተቋማትና ማኅበራዊ ሚዲያዎች ሐሰተኛ ወሬ ባለመቀበል እና ለማስተላለፍ የቤተክርስቲያን አጋር በመሆን ለመሥራት  ቤተክርስቲያንን ከማይጠቅሙ አጀንዳዎች ራሳቸውን ለማራቅና ሌሎች በአቋም መግለጫቸው በንባብ ያሰሟቸውን    ቃል ኪዳኖች መተግበር እንደሚገባቸው ገልጸዋል።
ቅዱስ ፓትርያርኩ በሥልጠናው ለተሳተፉ አሰልጣኞችና አሰልጣኞች የምስክር ወረቀት ሰጥተዋል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በመድረኩ መዝጊያ  ባስተላለፉት መልዕክት የቤተክርስቲያናችን በሚዲያው ዘርፍ ያለውን ክፍተት በማየት የሕዝብ ግንኙነት  መምሪያ ተፈላጊ የሆነውን ሥራ መሥራቱን በመግለጽ  ምስጋና አቅርበዋል።
ቅዱስነታቸው እግዚአብሔር  ምድርን የሰጠን እርስ በእርስ ተዋደን በሰላም አንድንኖርባት ነው ያሉ ሲሆን  ሚዲያዎች እንደሚያስተላልፉት መልዕክት ጎጂም ጠቃሚም ተግባራት እንደሚከናወንባቸው ገልጸዋል። ሚዲያ ከቀና ሁሉም ይቀናል በእዉነት የሚሠሩ ሚዲያዎች ለሀገር ይጠቅማሉ ያሉት ቅዱስነታቸው  ሕግና ሥነ ሥርዓትን ከልተከተለው ካልሠሩ ሚዲያዎች ጎጂ  ስለሚሆኑ  በጥንቃቄ መሥራት አለባቸው ብለዋል።
#EOTC TV
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
              https://youtu.be/Wqgq1KebrOo
     🇪🇹   "የቤተክርስቲያን የሆነውን ብቻ"  🇪🇹
        📡  የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት 🎥
                       📱 የዲጂታል ሚዲያ ገጾች💻
ለመረጃ  📞 +251985585858
➽ የዩቲዮብ ገጻችን
http://www.youtube.com/c/eotctv
➽ የፌስ ቡክ ገጻችንን
https://www.facebook.com/eotctvchannel
➽የቴሌግራም ገጻችን
https://t.me/eotctvchannel
➽ የቲክ ቶክ ገጻችን
https://vm.tiktok.com/ZMFSxXdUf/
➽ የዩቲዮብ ገጻችን Eotc tv 2
https://youtu.be/Wqgq1KebrOo
➽የትዊተር ገጻችን
https://twitter.com/EotcT/
➽የኢንስታግራም ገጻችን
https://www.instagram.com/p/CknRF0MtB77/?igshid=MDJmNzVkMjY


ቤተክርስቲያኒቱን ሳያውቁ ተገቢው ሙያና እውቀት ሳይኖራቸው  የሃይማኖት አስተምህሮ ለማስተላለፍ እና በየማኅበራዊ ሚዲያው እና ዲጂታል ሚዲያው  ለመንቀሳቀስ  የሚሞክሩ እንዳሉ በውይይት መነሳቱን የጠቆሙት ብፁዕነታቸው እውቀቱ ሳይኖራቸው ቤተክርስቲያንን ወክሎ ሃይማኖታዊ አስተምህሮ ማስተላለፍ እንደማይገባ ገልጸዋል ::
ማኅበራዊ ሚዲያውና ዲጀታል ሚዲያው  ከቤተክርስቲያን ይልቅ ለግለሰቦች እና ለቡድን ፍላጎቶች የመቆም ዝንባሌ በሰፊው ይታያል ሆኖም ቅድሚያ ለቤተክርስቲያን መስጠት ይገባል ያሉት ብፁዕነታቸው ገንዘብ መስብሰብን ዒላማ ያደረገ የዲጂታል ሚዲያ እና ማኅበራዊ ሚዲያ ሥራ በመንፈሳዊ ቅኝት ያልተቃኘ  በመሆኑ እርምት የሚሻ መሆኑን ገልጸዋል።



















Показано 20 последних публикаций.