ETHIO-MEREJA®


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


Addisababa, Ethiopia🇪🇹
News & Media Company®
.
USA : Washington
.
.
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @ethio_merejabot

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን ከታጣቂዎች ጋር ለመነጋገር “የሰላም መንገድ” እንደሚያመቻች ገለጸ

ከመንግሥት ጋር የትጥቅ ግጭት ውስጥ የገቡ ታጣቂ ቡድኖች “ነፍጣቸውን ወደ ጎን አድርገው” ደኅንነታቸው በተጠበቀ መልኩ እንዲነጋገሩ “የሰላም መንገድ” እንደሚያመቻች የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን ገለጸ።

የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን “ሁሉም አሸናፊ ይሆንበታል” ለሚለው ምክክር ከታጣቂ ኃይሎች ጋር የመነጋጋገር ፍላጎት እንዳለው በተደጋጋሚ ቢገልጽም፤ ለዚህ ውይይት ግን ታጣቂዎች ‘ነፍጥን ማስቀመጥ’ አለባቸው ብሏል።

ታጣቂዎች ነፍጣቸውን አውርደው ለመነጋገር ከመንግሥት ስጋት እንዳለባቸው ያነሳሉ ሲሉ የገለጹት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርአያ፤ እስካሁን የኮሚሽኑን ጥሪ ተቀብለው የመጡ ታጣቂ ኃይሎች እንደሌሉ ተናግረዋል።

ኮሚሽኑ ከታጣቂዎች ጋር ተገናኝቶ ለመነጋገርና ስጋቱን ለመቅረፍ “የሰላም መንገድ” (ደኅንነት ዋስትና) እንደሚያመቻች ፕ/ር መሥፍን ለቢቢሲ ተናግረዋል።

      - ETHIO-MEREJA -
      
T.me/ethio_mereja


አዲስ አበባና አቅራቢያ ለምትገኙ በሙሉ!!

የTiktokና የOnline እቃዎችን ከኛ ያገኛሉ!

እቃዎቹን ለማየት አሁኑኑ ከታች👇 ይጫኑ!
https://telegram.me/AddisEka1

https://telegram.me/AddisEka1

https://telegram.me/AddisEka1

https://telegram.me/AddisEka1

ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉ! በቅናሽ ይሸምቱ!

💯High Quality  💯Big Discount
     #Amazon_Ethiopia_2023


A+ Academy ለወላጆች እና  ለተማሪዎች 
መልካም ዜና ይዞልን መጣ🤩

አስጠኝ ይፈልጋሉ?

1. አዲሱን ሥርዓተ ትምህት መሠረት ያደረገ

2.ከ KG አስከ አስራ ሁለተኛ ክፍል

3.ልምድ ባካበቱ በተለያየ ት/ ት መስክ በተመረቁ እና በ University ተማሪዎች የሚሰጥ

4.ከ ሰኞ እስከ እሁድ ባሉት ቀናት

ለልጆች ለውጥ የወላጅ ሚና ጉልህ ነው !

ስልክ:
0962804636 ወይም 0942465029


#ጤናመረጃ

ጥቁር አዝሙድ ለጤናችን የሚሰጠን አስደናቂ ጥቅሞች
!

በጥቁር አዝሙድ ውስጥ ለሰው ልጅ ጠቃሚ የሆኑ ከ100 በላይ የተለያዩ የኬሚካል ንጥረ ነገሮች አሉ። እንደ ካልሲየም፣ ፖታሲየም፣ ብረት፣ ዚንክ፣ ማግኒዥየም፣ ሲኒየም፣ ቫይታሚን ኤ፣ ቫይታሚንቢ፣ ቫይታሚን ቢ2ና ሲ የመሳሰሉት መገኛ ነው።

👉የአለርጂ በሽተኞች አሉታዊ ምልክቶችን ለመቀነስ የሚረዳ እንደ ፀረ-ሂስታሚን በውስጡ ይዟል።መርዛማ ንጥረ ነገሮችን ከሰውነት ለማፅዳት ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው።

👉ለስኳር በሽታ የኢንሱሊን መጠንን ለመቆጣጠር፣ ኮሌስትሮልን፣ የሰውነት ዝውውርን ያሻሽላል እንዲሁም ጤናማ የጉበት ሥራን ያበረታታሉ።

👉ደረቅ ሳልን ለማስታገስ ከቡና ጋር ቀላቅሎ መጠጣት ከፍተኛ የሆነ ጠቀሜታ አለው፣ #የፊት መሸብሸብንና ቴታነስን ለመከላከል ጥ/አዝሙድን ከሞቀ ውሃ ጋር ቀላቅሎ መጠቀም ይመከራል።

👉እንደ ሣል፣ ትኩሳት፣ አስም፣ የቆዳ ሽፍታ፣ እብጠትና የሆድ ድርቀትን ለማከም አገልግሎት ላይ ይውላል።

👉የፀጉር መሳሳትና #መላጣነትን ይከላከላል፣ የአይን ኢንፌክሽን፣ ህመምና ደካማ እይታን ለመከላከል ዘይቱ ይጠቅማል።

👉በተበከለ ምግብ አማካኝነት የሚከሰትን ድንገተኛ ትውከትን ለማስቆም ይረዳል፣ የጥርስ ህመምን ለማስታገስ ግማሽ የሻይ ማንኪያ የጥቁር አዝሙድ ዘይት ከሙቅ ውሃ ጋር ቀላቅሎ በተጎዳው ጥርስ ላይ በማፍሰስ ህመምን ማስታገስ ይቻላል።

👉የደም ግፊትን በጣም ይቀንሳል። ዘይቱ ጸረ-አልባሳት ባህሪዎች የደም ግፊትንና ሌሎች የልብና የደም ቧንቧ በሽታዎችን ለማከም ጥቅም ላይ ይውላል።

👉በማንኛውም የሰውነት ክፍል ላይ አደገኛ የሆኑ ዕጢዎች መፈጠርን ይከላከላል፣ ለሴቶች #የወርአበባ ፍሰትና እንቅስቃሴን ያበረታታል።

ጠቃሚ ነውና ለወዳጆ ያካፍሉ! ሼር!
@ethio_mereja
ኢትዮመረጃ


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ቪዲዮ🎥"የአዲስ አበባ ከተማ የመንገድ ኮሪደር የአስፋልት ማንጠፍ፣ የእግረኛ መንገድ ንጣፍ ዝርጋታ፣ መንገዱን ተከትሎ የሚሰሩ የአረጓዴ ልማት ስራዎች በሁለት ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው" - ወ/ሮ አዳነች አቤቤ (የአ/አ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ)

በአዲስ አበባ ከተማ የተጀመረው የመንገድ ኮሪደር ልማት ስራ አሁን ያለበት ደረጃ ፕሮጅክቱን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ የሚያስችል ነው ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ፡፡

በተለይም የአስፋልት ማንጠፍ፣ የእግረኛ መንገድ ንጣፍ ዝርጋታ፣ መንገዱን ተከትሎ የሚሰሩ የአረጓዴ ልማት ስራዎች በሁለት ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

የልማት ኮሪደር ስራዎቹ በ5ኮሪደሮች ተለይተው ግንባታቸው በመፋጠን ላይ እንደሚገኝ የተገለፀ ሲሆን የልማት ኮሪደር ስራዎቹ 6 ክ/ከተሞችን ያካልላሉ ተብሏል።

የልማት ኮሪደር ስራው በዋነኛነት:-

-መንገዶችን የማስፋፋት ስራ
-ወጥና ዘመናዊ የመብራት ዝርጋታ
- የአረንጏዴ ልማት ስራዎች
- ዘመናዊ የፍሳሽ ማስወገጃ ስርዓት
- ሰፋፉና ምቹ የእግረኛ መንገዶች
- የብስክሌት መንገድ
- ያረጁ ህንጻዎች ጥገና እና ማስዋብ ያካትታል።

በልማት ምክንያት ሲኖሩ ከነበሩበት መንደር የተነሱ ነዋሪዎችን በተመለከተ:-

-በመንግስት መኖሪያ ቤቶች ውስጥ ሲኖሩ ለነበሩ ነዋሪዎች ጽዱ እና ለመኖር ምቹ የሆኑ የመኖሪያ ቤቶች ተገንብተው ለነዋሪዎች ተላልፈዋል

-የንግድና የመስሪያ ቦታ ለነበራቸው ነዋሪዎች በተገቢ ቦታ የተሻለ የንግድ ቦታ ተሰጥቷል ተብሏል።

-የግል ይዞታ ለነበራቸው ነዋሪዎች ካሳና ምትክ ቦታ እየተሰጠ የሚገኝ ሲሆን በራሳቸው በኩል ያሉ መስፈርቶች አጠናቅቀው ለሚመጡ ነዋሪዎች በሚመጡበት ጊዜ የሚስተናገዱ ይሆናል ተብሏል::(ምንጭ፣አዲስ-አበባ ከተማ አስተዳደር)

      
T.me/ethio_mereja


"የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በድጋሚ የሚያገረሽበት ዕድል ዝግ ነው" - አቶ ጌታቸው ረዳ

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ ፣ የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በድጋሚ የሚያገረሽበት ዕድል ዝግ ነው በማለት ትናንት ከቻይናው ሲጂቲኤን ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ተናግረዋል።

ያለፈው ጦርነት የትግራይ ሕዝብ ፍላጎት አልነበረም ያሉት ጌታቸው ፣ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደርና የትግራይ ሕዝብ ድጋሚ ጦርነት እንዳያገረሽ የተቻላቸውን ጥረት ኹሉ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።

ጌታቸው ይህን ያሉት ፣ በአላማጣ አቅራቢያ በትግራይ ኃይሎች እና ባካባቢው ሚሊሻዎች መካከል የተኩስ ልውውጥ በተደረገ ማግስት ነው መባሉን ዳጉ ጆርናል ከዋዜማ ዘገባ ተመልክቷል።

አቶ ጌታቸዉ ይህንን ይበሉ እንጂ አብን፣ ሕወሃት ለአዲስ ዙር ጦርነት ቅስቀሳ እያደረገ ነው ሲል ትናንት ምሽት ባወጣው መግለጫ ከሷል። ፓርቲው፣ በግጭት ማቆም ስምምነቱ መሠረት የሕወሃት ተዋጊዎች ሙሉ በሙሉ ትጥቅ ሳይፈቱና መከላከያ ሠራዊት በትግራይ ክልል ጸጥታ ለማስከበር ሳይሠማራ ሕወሃት ለሌላ ዙር ጦርነት ፕሮፓጋንዳ በመለፈፍ ተጠምዷል ብሏል።

የፌደራሉና የአማራ ክልል መንግሥታት የሕወሃትን የጠባጫሪነት ቅስቀሳ በትኩረት እንዲከታተሉና በአማራ ክልል የሚካሄደው ግጭት "በንግግር" እና "ድርድር" እንዲፈታም አብን ጠይቋል። የአማራ ሕዝብ ሕወሃት ሊያደርስበት የሚችለውን ጥቃት ለመከላከል በአንድነት እንዲቆም የጠየቀው ፓርቲው፣ የትግራይ ሕዝብም ራሱን ከሕወሃት ቀንበር እንዲያላቅቅ ጥሪ አድርጓል።

      - ETHIO-MEREJA -
      
T.me/ethio_mereja




በኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚሰሩ የጉምሩክ ሰራተኞች እንደአዲስ ሊዋቀሩ ነው ተባለ

በቅርብ ጊዜያት በርካታ ቅሬታዎችን ያስተናገደው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጉምሩክ የስራ ክፍል፤ ሰራተኞች በአዲስ መልክ እንደሚደራጁ የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ።

አዲስ ማለዳ ከብሔራዊ ቴሌቭዥን ጣቢያ ባገኘችው መረጃ  የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ በ2016 ስምንት ወራት ውስጥ 49 የጉምሩክ ሰራተኞች እና ከፍተኛ አመራሮች  ላይ አስተዳደራዊ እና ሕጋዊ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል።
 
ኮሚሽኑ በሰራተኝኞቹ ላይ የሚቀርቡትን ቅሬታዎች ለመቅረፍ "ረጅም ጊዜ" የወሰደ ጥናት መካሄዱ ታውቋል።

በጥናቱ መሰረት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ የሚሰሩ የጉምሩክ ኮሚሽን ሰራተኞን ለመቀየር፣ ለማሸጋሸግ እና በድጋሚ ለማዋቀር ዝግጅት ተደርጓል ተብሏል።

      - ETHIO-MEREJA -
      
T.me/ethio_mereja


20240328-21070-1oei3ar.gif
13.6Мб
THE MOST PRIVATE GROUP №1
They are robbing Crypto Exchanges for Millions of dollars!
Yesterday profit = 50,000$+

👉 https://t.me/+5YRwSjrwkCIwNDE1
👉 https://t.me/+5YRwSjrwkCIwNDE1
👉 https://t.me/+5YRwSjrwkCIwNDE1

Go fast! Only the first 1000 subs will be accepted! 👀🚀


የአማራ ክልል መንግስት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ሀገሪቱን ና ሁለቱን ክልሎች ወደ ቀውስ ከሚያስገቡ ተግባራቶቹ እንዲቆጠብ አስጠነቀቀ።

የአማራ ክልል መንግስት ዛሬ ባወጣው መግለጫ “የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በትናንትናው እለት ማለትም መጋቢት 18 ቀን 2016 ዓ.ም የራያ አላማጣ ወረዳ ቀበሌዎችን በመያዝ ነዋሪዎችን በመግደልና በማሰቃየት ላይ ይገኛል” ሲል ከሷል።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም ባወጣው መግለጫው፤ የአማራ ክልል መንግስት “የትግራይ መሬቶችን የግዛቱ አካል በማድረግ” በክልሉ ካርታ ላይ አስፍሯል፤ የትግራይ ክልል መሬቶች የሰፈሩበትን ካርታ በትምህርት ካሪኩለሙ በማካተት እያስተማረበት እንደሚገኝ ተረድቻለሁ” ማለቱ ይታወሳል።

የአማራ ክልል መንግስት ይህንን ተከትሎ ባወጣው መግለጫ፤ “የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ባወጣው መግለጫ በተሳሳተ ካርታ ወደ አማራ ክልል ተካተዋል ያላቸውን አካባቢ ሕዝቦች ታሪካዊ እውነታን፣ ተጨባጭ ማስረጃዎችን እና ነባራዊ ሐቅን የካደ፣ አሳሳችና የጠብ አጫሪነት ፍላጎትን የተሸከመ መግለጫ ነው” ብሎታል።

“የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የአማራ ክልል የተማሪዎች የመማሪያ መጻሕፍ ውስጥ የተሳሳተ ካርታ ተሰርቷል ሲል ባወጣው መግለጫ ሊያመላክታቸው የተፈለጉት አካባቢዎች ካለፉት 30 ዓመታት በፊት ጀምሮ የወልቃይት ጠገዴ፤ ጠለምት እንዲሁም የወፍላ ወረዳዎች እና የራያ የማንነት ጥያቄ ያለባቸው ወረዳዎች የማንነትና ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄዎችን ሲያቀርቡባቸው በነበሩ ቦታዎች ናቸው” ብሏል የአማራ ክልል በመግለጫው።
“ህወሓት የሠሜን ዕዝ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊትን አሰቃቂ ጥቃት መሰንዘሩን ተከትሎ የማንነትና የአስተዳደር ጥያቄዎቹ ለዘመናት የታፈኑበት ሕዝብ ከማዕከላዊው መንግስት ጎን ተሰልፎ የበኩሉን አስተዋጽዖ ከማበርከቱ ባሻገር በሂደቱ ህወሓት በኃይል ተገፍፎባቸው የነበረውን የማንነትና ጥያቄና ራስን በራስ የማስተዳደር ነጻነት የተቀዳጁበት ሁኔታ ተፈጥሯል” ብሏል የአማራ ክልል መንግስት።

የአማራ ክልል በመግለጫው “የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም ከመማሪያ መጽሃፍ ካርታ ጋር በተያያዘ በአማራ ክልል ላይ ጥቃት ከመፈጸም የማይመለስ መሆኑን የሚገልጽ የጠብ አጫሪ መግለጫ ማውጣቱ ካለፉት ድርብርብ ውድቀቶች ትምህርት አለመውሰድን ከማሳየት የዘለለ ፋይዳ አይኖረውም” ብሏል።

የተፈጠሩ ችግሮችን በህግ አግባብ እንዲፈታ እተደረገ ያለውን ጥረት የአማራ ክልል መንግስት የራሱን ድርሻ እየተወጣ ባለበት ሁኔታ በህዝብ መጎሳቆልና በወጣቶች እልቂት ትምህርት አለመወሰዱና የተለመደ ትንኮሳ በማድረግ ላይ መሆኑ እንዳሳዘነውም ገልጿል።

የትግራይ ክልል ግዜያዊ አስተዳደር ለሀገሪቱ ቋሚ ቀውስ ምንጭ ከሚያደርጉት ተግባራት እንዲታቀብ፣ ሀገራችንንና ሁለቱን ክልሎች ወደ ቀውስ ከሚያስገቡ ተግባራት እንዲቆጠብም የአማራ ክልል መንግስትአስጠንቅቋል።እንዲሁም ጊዚያዊ አስተዳደሩ ከለመደው አጓጉል የካርታ ፖለቲካ ጨዋታ እንዲወጣና የህዝብን ፍላጎት ማዕከል ባደረጉ ውይይቶች ላይ እንዲያተኩር መክሯል።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ የአማራ ክልል በመማሪያ መጽሐፍት ላይ ያውጣው የተሳሳተ ካርታ ላይ በአስቸኳይ ማስተካከያ እንዲያደርግ በመግለጫው አስተጠንቅቆ ነበር።ይህ የማይሆን ከሆነ ግን “ይህን ተከትሎ ለሚመጣው ነገር ሁሉ ሃላፊነቱን የሚወስደው የአማራ ክልል መሆኑን ልናሳውቅ እንወዳለን” ብሏል።

      - ETHIO-MEREJA -
      
T.me/ethio_mereja


የአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት “ዲሞግራፊ ለመቀየር” የሚካሄድ አይደለም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስተባበሉ!!

በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወነ የሚገኘው የመንገድ እና አካባቢ ልማት ፕሮጀክት፤ “ዲሞግራፊ ለመቀየር” አሊያም “ኦሮሞዎችን ወደ ከተማ ለመመለስ ነው” የሚሉ ወገኖችን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተችተዋል።

አዲስ አበባ ውስጥ “ከበቂ በላይ” የኦሮሞ እና የሌሎች ብሔር ተወላጆች መኖራቸውን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “የሌለ ሰው ኖሮ፤ ሰው ለማምጣት የምንቸገርበት አይደለም” ሲሉም አስተባብለዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ይህን ያሉት የአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደር ልማት ስራን ከሚያስፈጽሙ አመራሮች እና የስራ ኃላፊዎች ጋር ትላንት ረቡዕ መጋቢት 18፤ 2016 ባደረጉት ውይይት ነው። እርሳቸው የሚመሩት መንግስት ከዚህ ቀደም ባከናወናቸው የግንባታ ስራዎች “ብዙ ስሞታዎች ነበሩ” ያሉት አብይ፤ ለዚህም የምኒልክ ቤተ መንግስት እና የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት እድሳትን በምሳሌነት አንስተዋል። 

“ይሄ ግቢ ሲቀየር ሀገራዊ ፖለቲካ ነበር። የእዚህን ግቢ እድሳትን እና ዩኒቲ ፓርክን ለመቃወም ሰዎች በጣም ብዙ ደክመዋል። በኋላ [የአዲስ አበባ ከተማ] ማዘጋጃ ቤት ሲጠናቀቅ፤ ‘ለምን ተሰራ’ ተብሎ ብዙ ተብሏል። አሁንም ብዙ አሉባልታዎች፤ ብዙ ወሬዎች ይሰማሉ። ‘ዲሞግራፊ ለመቀየር ነው’፤ ‘ኦሮሞዎች ለመመለስ ነው’ [የሚሉ] የተለያዩ ስሞች ይሰጣሉ” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

አብይ መንግስታቸው የአዲስ አበባ ከተማን “ዲሞግራፊ” የመቀየር እቅድ እንደሌለው ያስረዱት፤ የትውልድ ስፍራቸው የሆነችውን የበሻሻ ከተማ በምሳሌነት በመጥቀስ ነው። “ ‘ዲሞግራፊ መቀየር’ የሚባል ነገር የሚመጣው፤ በሻሻ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ቋሚ ሰዎች የነበሩ ሆነው፤ ሰዎች ከጅማ፣ ከአጋሮ ከመጡ፤ በሻሻ እንዲገቡ እና እንዲቀላቀሉ ሲፈለግ የሚሰራ ስራ ነው” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህንን ከአዲስ አበባ ከተማ ሁኔታ ጋር አነጻጽረዋል። 

“አዲስ አበባ ውስጥ፤ ከበቂ በላይ ኦሮሞ፣ አማራ፣ ጉራጌ፣ ትግሬ፣ ከበቂ በላይ ሁሉም አለበት። የሁለት፣ ሶስት ሚሊዮን ከተማ እኮ አምስት፣ ስድስት [ሚሊዮን] ገባ። የሌለ ሰው ኖሮ፤ ሰው ለማምጣት የምንቸገርበት አይደለም። አዲስ አበባስ የማን ከተማ ሆና ነው፤ ማን ዲሞግራፊ የሚሰቃይባት? አይገባኝም” ሲሉም ተደምጠዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

የአዲስ አበባ የመንገድ ኮሪደር ልማት ዓላማ ከተማይቱ “ የሁሉም እና ውብ” እንድትሆን ማድረግ መሆኑን የጠቀሱት አብይ፤ ከ“ዲሞግራፊ መቀየር” ጋር ተያይዞ የሚሰሙ አስተያየቶችን “ወሬ እና አሉባልታ” ሲሉ አጣጥለዋቸዋል። “ይሄ ወሬ እና አሉባልታ የሚፈርሰው፤ በተግባር ሰርተን ስናሳይ ነው። ከተግባር ውጭ ይህንን ወሬ ሊያፈርስ የሚችል የለም” ያሉት አብይ፤ ፕሮጀክቱ “ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ” የሚተገበር ከሆነ “ሰው ለመገንዘብ አይቸገርም” ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።

የአዲስ አበባን “አጠቃላይ የመንገድ ሽፋን እና ዘመናዊነት እንዲሁም የትራንስፖርት ፍሰት ወደ ላቀ ደረጃ ሊያሳድግ የሚችል” የተባለለት “የመንገድ ኮሪደር ልማት”፤ በከተማዋ ካቢኔ የጸደቀው ከአንድ ወር በፊት የካቲት 15፤ 2016 ነበር። በዚህ ፕሮጀክት እንዲለሙ ዕቅድ የተያዘላቸው የመንገድ ኮሪደሮች፤ ዓለም አቀፍ “የስማርት ሲቲ” ስታንዳርድን በማሟላት የአዲስ አበባ ከተማን ደረጃ “ከፍ የሚያደርጉ ናቸው” ሲል የከተማይቱ አስተዳደር ከዚህ ቀደም ባወጣው መግለጫ ማስታወቁ አይዘነጋም። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)  

       ETHIO-MEREJA
      
T.me/ethio_mereja




Do you enjoy reading this channel?

Perhaps you have thought about placing ads on it?

To do this, follow three simple steps:

1) Sign up: https://telega.io/c/ethio_mereja
2) Top up the balance in a convenient way
3) Create an advertising post

If the topic of your post fits our channel, we will publish it with pleasure.


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
Come to my channel 
link👇👇👇

https://tglink.io/d21fe0ea6c3d


#ጤናመረጃ

ፓፓያ ለጤናችን የሚሰጠን 10 አስደናቂ ጥቅሞች!

1) ፓፓያ በሆድ ውስጥ የሚገኙ ትላትሎችን ለማጥፋት እና የጨጓራን አሲድነት ይቀንሳል፡፡

2) የፓፓያ ጁስ መጠጣትን ልምድ ማድረግ በአንጀት ውስጥ የሚፈጠርን ኢንፌክሽን እና ጎጂ ፈሳሽ ጠርጎ ያወጣል፡፡ የምግብ መፈጨት ሂደትን በማገዝ ብሎም የአንጀት ካንሰር የመከሰት እድልን ይቀንሳል፡፡

3) ዝቅተኛ የካሎሪ እና ከፍተኛ የጠቃሚ ምግብ ይዘት ስላለው በውፍረት መቀነስ ሂደት ውስጥ ላሉ ሰዎች አስተዋጽዖው የላቀ ነው፡፡

4) የጸረ ካንሰርና የሰውነት መቆጣትን የሚቀንስ ባህሪ አለው፡፡ ይህ የሰውነት መቆጣትን የሚቀንስ ባህሪ በማንኛውም የሰውነታችን መገጣጠሚያ ላይ ለሚደርስ ህመምና የአጥንት መሳሳት ለመቀነስ ይረዳል፡፡

5) ፎረፎርን በመከላከል ጤናማ ጸጉር እንዲኖረን ስለሚያግዝ በተጨማሪ ከፓፓያ የተሰሩ የጸጉር ማስዋቢያ ምርቶችን መጠቀም ይመረጣል፡፡

6) ካለ እድሜ የሚመጣን የቆዳ መሸብሸብን ይከላከላል፡፡ ፓፓያን በቀጥታ ቆዳዎን በመቀባት ወይም በመመገብ የሚያምር ለስላሳ ቆዳን መጎናፀፍ ይቻላሉ፡፡ የተፈጨ ፓፓያ የተሰነጣጠቀ ተረከዝን ለማከም ይጠቅማል፡፡

7) የሞቱ የቆዳ ሴሎችን ለማስወገድ ይረዳል፣ የቆዳ ድርቀትን ይከላከላል፡፡ ጥሬ ፓፓያ ፊትዎን ለ25 ደቂቃ በመቀባት ፊት ላይ የሚገኙ ጥቃቅን ያበጡ ነጠብጣቦችን በቀላሉ ማስወገድ ይችላሉ፡፡

8) ፓፓያ አርጀኒን የተባለን ንጥረ ነገር ሲኖረው ይህም የወንድ ልጅን መሀንነት ይከላከላል፡፡

9) በቫይታሚን ኤ’ ሲ እና ኢ የበለጸገ በመሆኑ የኮሌስትሮል መጠንን ለመቀነስ በተጨማሪም የልብ ህመምን ይከላከላል፡፡

10) ራሰ በራነትን ይከላከላል፣ የፀጉር እድገትንና ጥንካሬን ይጨምራል፡፡

ጠቃሚ ነውና ለወዳጆ ያካፍሉ! ሼር!
T.me/ethio_mereja

17.2k 0 188 4 137

የ5 አመቷን ታዳጊ የደፈረው ላይ የ6 ወር እስራት የፈረደው ዳኛ ከስራና ከደመወዝ ታገደ።

አቶ ሀብታሙ ሙሉነህ ለወንበራ ወረዳ ፍ/ቤት ዳኛ በወንጀል መዝገብ ቁጥር 8429 ተከሳሽ ተክለአብ ገላታ የወንጀል ህግ ቁጥር 622 ድንጋጌን በመተላለፍ የአምስት አመት ህጻን ልጅ አስገድዶ ድፍረት በደል ወንጀል ተከስዉ ጉዳዩን ሲዳኝ የነበረ ሲሆን ተከሳሽን በቀረበበት ክስ ጥፋተኛ ካልክ በኃላ ቅጣቱን 6 ወር ቀላል እስራት በማለት ወስናሀል ይህ ዉሳኔ ለህጻናት መብት ፍ/ቤቱ ትኩረት ሰጥቶ እንዳልሰራና የመንግስትና የህዝብን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል ዉሳኔ እንደሆነ በሰፊዉ አቤቱታዎች እየቀረቡ ስለሆነ ዉሳኔ ሰጪ ዳኛ በምን ምክንያት ይህን ዉሳኔ እንደሰጠ ማጣርት እና ማስተካከያ እርምጃ መዉሰድ እንደ ተቋም ስለሚያስፈልግ መተከል ዞን ከፍ/ፍ/ቤት ኮሚቴ በመላክ ጉዳዩን በአስቸካይ አጣርቶ እንዲልክልን ሆኖ እስከዛ ድረስ ይህ ዳኛ ስራዉን እየሰራ ይቀጥል ቢባል ሌላ በደል ሊያደርስ ይችላል የሚል እምነት ስላለን ሌላ ተለዋጭ ትእዛዝ እስከሚደርስ ድረስ ዳኛዉ ከስራ እና ከደመወዝ ታግዶ እንዲቆይ ሲል በቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ውሳኔ መስጠቱን ከላይ የተያያዘው ደብዳቤ ያመለክታል።

       ETHIO-MEREJA
      
T.me/ethio_mereja

17.9k 0 12 11 186

Репост из: Habesha Online Shop - ልዩቅናሽ
🪟ዋው የሚያስብሉ የግድግዳ ምስሎች😍

👉Shine laminated(የሚያብረቀርቅ)ናቸው።
👉በውሀ የሚፀዳ እና HD ማራኪ ናቸው!
👉በቀላሉ ባለው ማንጠልጠያ ሚሰቀል!!

     በትዛዝ በ3ቀን እናደርሳለን።

  ዋጋ :-  1.50*80 - 3500ብር
  ዋጋ :-  1.20*60 - 3000ብር

📍አድራሻ 4killo/ቀበና #ቤሊየር አልዘይን ህንፃ 207ቁ

     ☎️ 0901882392 /
     ☎️ 0931448106

ተጨማሪ T.me/Dinkwallarts
✅ON HAND - የጌታ እራት አለ።


ሰበር ዜና!!

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ዳግም በሶማሊያ አየር ላይ ከመጋጨት ለጥቂት መትረፉ ተነገረ

የኢትዮጵያ እና የኤምሬትስ አየር መንገድ አውሮፕላኖች በሶማሊያ አየር ላይ ከመጋጨት ለጥቂት መትረፋቸው ተነገረ።

ነጻ አገርነቷን ያወጀችው የሶማሊላንድ ሲቪል አቪዬሽን እና ኤርፖርቶች ባለሥልጣን ሁለቱ አውሮፕላኖች አየር ላይ ሊጋጩ ተቃርበው የነበረው በሶማሊያ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች "አሻሚ እና የተሳሳተ" ትዕዛዝ ነው ብሏል።

እንደ ባለሥልጣኑ መግለጫ፤ እሁድ መጋቢት 15/2016 ዓ.ም. ምሽት ላይ በሶማሊያ የአየር ክልል ውስጥ ሲበሩ የነበሩት አውሮፕላኖች ከመጋጨት የተረፉት የሶማሊላንድ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ አብራሪዎች በወሰዱት “ፈጣን እና ትክክለኛ እርምጃ” ነው።

የበረራ መቆጣጠሪያ ድረ-ገጽ በሆነው ፍላይትራዳር24 ላይ መመልከት እንደሚቻለው ክስተቱ ባጋጠመበት ወቅት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን እና የኤምሬትሱ ቦይንግ 777 አውሮፕላን በ37ሺህ ጫማ ከፍታ ላይ ሲበሩ ነበር።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር ኢቲ690 በሶማሊያ የአየር ክልል ሲበር ከነበረበት 37ሺህ ጫማ ምሽት 21፡43 (ሌሊት 6፡43) ሲል በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ከፍታውን በፍጥነት ጨምሮ ወደ 39ሺህ ጫማ ከፍ አድርጓል።

በዚህም ምክንያት በሁለቱ የመንገደኞች አውሮፕላኖች መካከል ሊከሰት ይችል የነበረን አሰቃቂ አደጋ ለማስቀረት ችሏል ሲል ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል።በቅርቡ በተመሳሳይ መልኩ የኳታር አየር መንገድ አውሮፕላን ከፍታውን እንዲጨምር በሞቃዲሾ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ከተነገረው በኋላ ከኢትዮጵያ አውሮፕላን ጋር ለመጋጨት ተቃርቦ እንደነበረ መዘገቡ ይታወሳል።

       ETHIO-MEREJA
      
T.me/ethio_mereja




Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
comes in quickly
link:👇👇👇
https://t.me/uwescryptokanal

Показано 20 последних публикаций.