ETHIO-MEREJA®


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


Addisababa, Ethiopia🇪🇹
News & Media Company®
.
USA : Washington
.
Buy ads: https://telega.io/c/ethio_mereja
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @ethio_merejabot

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


በወላይታ ዞን ሰርጉን አቋርጦ ቀዶ ህክምና የሰራው ሐኪም አድናቆት እየተቸረው ይገኛል

ዶ/ር ብሩክ ወይሻ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በወላይታ ዞን፣ በበሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የቀዶ ጥገና ስፔሻሊስት ነው።

ወጣቱ ሐኪም ታዲያ የራሱን የሰርግ ዝግጅት አቋርጦ ወጥቶ ታካሚን ቀዶ ጥገና በማድረግ ሕይወት የማዳኑ ጉዳይ የአካባቢው ነዋሪዎች መነጋገሪያ ሆኗል።

የሰርጉ ዝግጅት ከነበረበት ከ40 በላይ ኪሎ ሜትር በላይ ወደ ሆስፒታሉ ተጉዞ ቀዶ ጥገና በማድረግ የሰው ሕይወት ማዳን መቻሉን ዶ/ር ብሩክ ለኢቢሲ ተናግሯል።

ወጣቱ ሐኪም የተሟላ የቀዶ ጥገና ሕክምና ገና በቅርቡ በጀመረው ሆስፒታል የመጀመሪያው ስፔሻሊስት ቅጥር ሲሆን፤ በሆስፒታሉ ሥራ ከጀመረም ገና ሶስት ሳምንቱ ነው።

በቀዶ ጥገና የታከመው በሽታ ከጨጓራ ሕመም ጋር ተያይዞ የሚከሰትና ሕይወትን አደጋ ላይ የሚጥል ሲሆን፤ ታካሚው በሰዓቱ ሕክምና ባይደረግለት ኖሮ ሕይወቱ ሊያልፍ ይችል እንደነበርም ነው የተገለፀው።

ቀዶ ጥገና የሕክምና ባለሙያዎች የቡድን ሥራ ነው ያለው ዶ/ር ብሩክ፤ በአጠቃላይ በቀዶ ጥገናው ለተሳተፈው የሕክምና ቡድን ምስጋና አቅርቧል ።

የቀዶ ጥገና ሕክምናው የተደረገለት የ40 ዓመት ታካሚ በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ የገለፀው ዶ/ር ብሩክ፤ ከዚህ የሚበልጥ ደስታ የለም ብሏል።

በሙያዬ የፈፀምኩትን ቃለ-መሃላ እና የገባሁትን ቃል-ኪዳን መቼም ቢሆን አላጥፍም፤ ለሙያው የሚገባውን ክብር እሰጣለሁ ብሏል ወጣቱ ሐኪም ብሩክ ወይሻ።(Via ETV)

  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ

12.6k 0 11 18 312

ማንቼስተር ዩናይትድ 17ኛ ሽንፈቱን አስተናገደ

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ዩናይትድ በ2024/25 የውድድር ዘመን 17ኛ ሽንፈቱን አስተናግዷል፡፡

በኦልድትራፎርድ ዌስትሃም ዩናይትድን ያስተናገደው ዩናይትድ ጃሮድ ቦውን እና ቶማስ ሱቼክ ባስቆጠሯቸው ግቦች 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ተሸንፏል፡፡

በሌሎች የሊጉ 36ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ጨዋታዎች ክሪስታል ፓላስ ቶተንሃምን 2 ለ 0 ሲያሸነፍ ኖቲንግሃም ፎረስት ከሌስተር ሲቲ 2 አቻ ተለያተዋል፡፡

በሌሎች ጨዋታዎች ኒውካስትል ዩናይትድ ቼልሲን 2 ለ 0 ሲረታ፤ ቶተነሃም በሜዳው በክሪስታል ፓላስ 2 ለ 0 ተሸንፏል፡፡ ኖቲንግሃም ፎረስት እና ሌስተር ሲቲ ያደረጉት ጨዋታ 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።

  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ


በትግራይ ክልል እንዳትመሰክርብኝ በማለት የ14 ዓመት ታዳጊ በመድፈር በአሰቃቂ ሁኔታ የገደሉ ሁለት ግለሰቦች በእድሜ ልክ እስራት ተቀጡ

ያይንሸት ገብረዋህድ አመሃ የተባው ግለሰብ ነዋሪነቱ በፅምብላ ወረዳ ሲሆን መስከረም 25 ቀን 2016 ዓ/ም ከለሊቱ አምስት ሰዓት ላይ እንዳባጉና ከተማ ላይ ግሮሰሪ ከፍታ ራሷን የምታስተዳድርና የልጁ እናት የሆነቺውን ንግስቲ ገብረየውሃንስ የተባለች ሴት "አብረን እንደር ብየሽ እምቢ አልሺኝ" በሚል ቂም በመያዝና በቅናት በመነሳሳት ወደ መኖርያ ቤቷ በመግባት አልጋ ስር ተደብቆ በመቆየት የግል ተበዳይዋ በምትተኛበት ሰዓት ጭንቅላትዋ ላይ ሁለቴ በመምታት የግድያ ሙከራ መፈፀሙ የሰሜን ምእራብ ትግራይ ዞን አቃቢ ህግ አስታውቋል።

በዚህ ሳብያም ግለሰቡ በግድያ ሙከራ ወንጀል ተከሶ ጉዳዩ በፍርድ ሂደቴ ላይ ሳለ በዋስ እንዲወጣ ይፈቀድለታል። ይሄኔ ታድያ የግል ተበዳይ ልጅ የሆነችን የ14 ዓመት ታዳጊ ሄዋን ጎይትኦም በቀረበበት ክስ ላይ ምስክር ሆና መገለፆ በመገንዘብ እንዳትመሰክርብኝ በማለት በአሰቃቂ ሁኔታ ለመግደል አቅዶ ይንቀሳቀሳል።

በዚህም ታዳጊዋ አያቷ ጋር እንዳለች በማረጋገጥ ፈልጌሽ ነው ነይ በማለት ከአያቷ ቤት ይዟት በመውጣት ዓዲ ሰዱ እየተባለ ወደሚታወቅ ገደላማ ስፍራ ይዟት ይሄዳል። በመቀጠልም በአንገቷ በማነቅ መሬት ላይ የጣላት ሲሆን በሰአቱ አብሮት ከነበረ ተባባሪው መዓሾ ሰለሙን ደስታ የተባለ ግለሰብ ጋር በመሆን በታዳጊዋ ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመ ሲሆን የወንጀል ድርጊቱ ግን በዛ ያበቃ አልነበረም። የፈፀሙት ወንጀል እንዳይጋለጥ በሚል መረጃ ለማጥፋት በተደረገ ጥረት የታዳጊዋን ሁለት አይኖች በቢላ በማውጣት ተሸክመው ወደ ገደል በመወርወር ህይወቷ እንዲያልፍ አድርገዋል።

በዚህም መሰረት ቸዞኑ አቃቢ ህግ የፌ/ዲ/ሪ/ኢ የወንጀል ህግ አንቀፅ 539(1)(ሐ) በመጥቀስ በሁለቱም ግለሰቦች ላይ ግፍ የተሞላበት ወንጀል በመፈፀም ክስ የመሰረተ ሲሆን በዚህም መሰረት የቀረበለትን የክስ መዝገብ ሲመለከት የቆየው የዞኑ ፍርድ ቤት ሁለቱም ግለሰቦች በእድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ብይን መስጠቱን ብስራት ሬድዮ ከትግራይ ክልል ሰሜን ምእራብ ዞን አቃቢ ህግ ፅህፈት ቤት ያገኘው መረጃ ያሳያል።

  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ




የቡንደስሊጋው ሻምፒዮን ባየር ሙኒክ የሊጉን ዋንጫ በሜዳው አነሳ

ባየር ሙኒክ ከሞንች ግላድባህ ጋር በሜዳው ያደረገውን ጨዋታ 2ለ0 አሸንፏል።

ባየር ሙኒክ ተከታዩ ባየር ሊቨርኩሰን ከ ፍሬይ በርግ አቻ መለያየቱን ተከትሎ ለ34ኛ ጊዜ የጀርመን ሊግ ሻምፒዮን መሆኑን ማረጋገጡ ይታወሳል።

2 ጨዋታዎች እየቀሩት ሻምፒዮን መሆን የቻለው ባየር ሙኒክ በሜዳው አሊያንዝ አሬና የሊጉን ዋንጫ አንስቷል። ኢንግሊዛዊው የፊት መስመር ተጫዋች ሀሪ ኬንም የመጀመሪያ ዋንጫውን ከቡድን አባሎቹ እና ከደጋፊው ጋር አብሮ አጣጥሟል።

  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ


#ከቴምር ሪልስቴት
🎯🎯7ሳይቶችን ስርተን አስረክበናል አሁን ላይ ደግሞ መሀል ሣር ቤት አፓርትመንት እና ሱቅ ፒያሳ ለሽያጭ ያወጣነው 

👉2መኝታ 84ካሬ 5,392,800ብር ሙሉ ክፍያ
👉2መኝታ 94ካሬ 6,034,800ብር ሙሉ ክፍያ
👉3መኝታ 106ካሬ 6,869,400ብርሙሉክፍያ
👉3መኝታ 125ካሬ 8,025,000ብር ሙሉ ክፍያ

‼️ፒያሳ ሱቅ ሽያጭ 
👉3.9ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ900,000ብር 4ተኛ እና 5ተኛ
👉4.2ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.2ሚሊዮን 3ተኛ
👉4.8ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.5ሚሊዮን 2ተኛ
👉5.5ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2ሚሊዮን 1ኛ
👉 7ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2.8ሚሊዮን ግራውንድ በውስጥ በኩል
👉10ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 4ሚሊዮን ግራውንድ በውጪ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251939770177
     +251996856273
https://t.me/TemerRealEstateSalesConsultant
WhatsApp. https://wa.me/251939770177


5ኛ ዙር የ full stack development ስልጠና ምዝገባ በ ሃያሁለት ጀምረናል።

ከሚከተሉትን ያካትታል።
1. Python Programming Language
2. Front end Development (html,css, bootstrap and Javascript)
3. Backend development (PHP)
4. Database
5. Laravel Framework
6. Projects

በምዝገባ ላይ ነን :
☎️
0989747878
0799331774

በመራህያን የወደፊት ብሩህ ተስፋዎን የሚዘሩ ክህሎቶችን ይማሩ !!

አድራሻ፡ ሃያ ሁለት ፣ ከጐላጐል ወደ ቦሌ ሚወስደው ከ Hanan K Plaza አጠገብ ቢጫ ፎቅ ግራውንድ ፍሎር 10B

ለበለጠ መረጃ : @merahyan


የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና መቼ ይሰጣል?።

የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና መቼ ይሰጣል ?


👉በወረቀት ፈተናቸውን የሚወስዱ ተፈታኞች ፦ ሰኔ 23 ፣ ሰኔ 24 እና ሰኔ 25/2017 ዓ/ም

👉በበየነ መረብ (ኦንላይን) /ፈተናቸውን የሚወስዱ የ1ኛ ዙር ተፈታኞች ፦ ሰኔ 23 ፣ ሰኔ 24 እና ሰኔ 25/2017 ዓ/ም

👉በበየነ መረብ (ኦንላይን) /ፈተናቸውን የሚወስዱ የ2ኛ ዙር ተፈታኞች ፦ ሰኔ 26 ፣ ሰኔ 27 እና ሰኔ 30/2017 ዓ/ም

የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና መቼ ይሰጣል ?

👉በወረቀት ፈተናቸውን የሚወስዱ ተፈታኞች ፦ ሐምሌ 1 ፣ ሐምሌ 2 እና ሐምሌ 3/2017 ዓ/ም

👉በበየነ መረብ (ኦንላይን) /ፈተናቸውን የሚወስዱ የ1ኛ ዙር ተፈታኞች ፦ ሐምሌ 1 ፣ ሐምሌ 2 እና ሐምሌ 3/2017 ዓ/ም

👉በበየነ መረብ (ኦንላይን) /ፈተናቸውን የሚወስዱ የ2ኛ ዙር ተፈታኞች ፦ ሐምሌ 4 ፣ ሐምሌ 7 እና ሐምሌ 8/2017 ዓ/ም


  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ


5days left❗️(በመላው ሀገሪቱ ስራ የማቆም አድማው 5ቀን ቀርቶታል)

በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የሕክምና ባለሞያዎች ሰልፍ እያደረጉ ነው!

የሕክምና ባለሞያዎች የደሞዝ ጭማሪ እና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች የሚጠይቁ ሰልፎችና የተለያዩ ትእይንቶች በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች እየተካሄዱ ይገኛሉ።

በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በደቡብ፣ በሲዳማ፣ በትግራይ እና በሌሎችም ክልሎች የደሞዝ ጭማሪ እና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች የሚጠይቁ ሰልፎች እየተደረጉ ይገኛሉ።

በትግራይ ክልል የተለያዩ ከተሞች የሚገኙ የሕክምና ባለሞያዎች፥ በጤና ተቋማት ውስጥ ሰልፍ ያካሄዱ ሲሆን የደሞዝ ጭማሪ እንደረግላቸው፣ የተለያዩ ጥቅማጥቅሞች እንዲረጋገጥላቸው እንዲሁም የሠሩበት የጦርነቱ ወቅት ያልተከፈለ የ17 ወራት ደሞዝ እንዲከፈላቸው ጥያቄ አቅርበዋል።

ይህ የኢትዮጵያውያን ህክምና ባለሙያወች ጥያቄ ነው?!

የአፍሪካ ዝቅተኛዋ ደሞዝ ከፋይ ሀገር

👉Specialist ሀኪም ወርሀዊ 120ዶላር
👉አጠቃላይ ሀኪም 84ዶላር
👉ነርስ 70ዶላር ወርሀዊ ክፍያ ምትከፍል ብቸኛ ሀገር ናት

ራሱን ለTB, Hepatitis, Virus, Hiv እና ሌሎች መሰል በሽታወች  አጋልጦ ሚሰራው ሀኪም የጤና insurance የለውም .... በትንሽ ክፍያ ሚሰራው የጤና ባለሙያ ለዚህ ሁሉ በሽታ ተጋልጦ እየሰራ  ያለ insurance እየሰራ የጤና መድህን እንኳን ተጠቃሚ እንዲሆን አይፈቀድለትም?

ህይወታችንን ሲያድኑ ኖረዋል አሁን ግን
ህይወታቸውን ልናድን ይገባል!!!

"የኢትዮጵያ መንግስት እና የጤና ሚኒስቴር ለህጋዊ ጥያቄዎቻችን እጅግ አስቸኳይ መፍትሄ ለመስጠት ሊሰሩ ይገባል " ብለዋል።


  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ

16.8k 0 18 32 245

ፒኤስጂ አርሰናልን አሸንፎ ለሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ ደረሰ
**

በአውሮፓ ሻምፒ
ዮንስ ሊግ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ፒኤስጂ አርሰናልን በድምር ውጤት 3 ለ 1 አሸንፎ ለፍፃሜው ደርሷል።

በመጀመሪያው ጨዋታ አርሰናልን በሜዳው 1 ለ 0 ያሸነፈው ፒኤስጂ ዛሬ ምሽት በሜዳው በተካሄደው ጨዋታም 2 ለ 1 አሸንፏል።

የዛሬውን የፒኤስጂ የማሸነፊያ ግቦች ፋቢያን ሩዪዝ ፔና በ27ኛው ዲቀቃ እና አሽራፍ ሐኪሚ በ72ኛው ደቃቂ ላይ አስቆጥረዋል።

አርሰናልን ከሽንፈት ያልታደገችውን ግብ ቡካዩ ሳካ በ76ኛው ደቂቃ አስቆጥሯል። ጨዋታውን በድምር ውጤት 3 ለ 1 ያሸነፈው ፒኤስጂ ትናንት ባርሴሎናን በማሸነፍ ለፍፃሜው ካለፈው ኢንተር ሚላን ጋር ለዋንጫ የሚጫወት ይሆናል።

  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ


“40 በመቶ የሚሆነው የትግራይ ግዛት በወራሪዎች ስር ነው የሚገኘው፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ዋነኛ ተልዕኮ የክልሉን የግዛት ወሰን ማረጋገጥ ነው” - ፕሬዝዳንት ታደሰ

“የትግራይ ክልል 40 በመቶ የሚሆነው ግዛት በወራሪዎች ቁጥጥር ስር ነው የሚገኘው” ሲሉ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ ገለጹ፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ዋነኛ ተልዕኮ የክልሉን የግዛት ወሰን ማረጋገጥ እና የተፈናቀሉትን ወደ ቀያቸው መመለስ ነው” ብለዋል።

ፕሬዝዳንቱ ይህንን የገለጹት #በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር የሆኑትን ጄነስ ሃኒፈልድ ዛሬ ሚያዚያ 28 ቀን 2017 ዓ.ም በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት ነው።

ፕሬዝደንት ታደሰ “40 በመቶ የሚሆነው የትግራይ ክልል ግዛት በወራሪዎች ቁጥጥር ስር ነው የሚገኘው፣ ከሁሉም ነገር በፊት እና ከምንም ነገር በላይ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ተልዕኮ በህገመንግስቱ የተከለለውን የክልሉን የግዛት ወሰን ማረጋገጥ እና የተፈናቀሉትን ወደ ቀያቸው መመለስ ነው” ሲሉ ለአምባሳደሩ መናገራቸውን ከጽህፈት ቤታቸው ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

በተጨማሪም ፕሬዝዳንቱ ከአምባሳደሩ ጋር በነበራቸው ውይይት “የመጀመሪያው ዙር 75ሺ ታጣቂዎችን ወደ ማህበረሰቡ የመቀላቀል ተግባር እስከ መስከረም ይጠናቀቃል፣ ሁለተኛው ዙር ግን ከክልሉ ግዛት መከበር ጎን ለጎን የሚፈጸም ነው” ሲሉ  መናገራቸውን ጽህፈት ቤታቸው አስታውቋል።

  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ


#ከቴምር ሪልስቴት
🎯🎯7ሳይቶችን ስርተን አስረክበናል አሁን ላይ ደግሞ መሀል ሣር ቤት አፓርትመንት እና ሱቅ ፒያሳ ለሽያጭ ያወጣነው 

👉2መኝታ 84ካሬ 5,392,800ብር ሙሉ ክፍያ
👉2መኝታ 94ካሬ 6,034,800ብር ሙሉ ክፍያ
👉3መኝታ 106ካሬ 6,869,400ብርሙሉክፍያ
👉3መኝታ 125ካሬ 8,025,000ብር ሙሉ ክፍያ

‼️ፒያሳ ሱቅ ሽያጭ 
👉3.9ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ900,000ብር 4ተኛ እና 5ተኛ
👉4.2ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.2ሚሊዮን 3ተኛ
👉4.8ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.5ሚሊዮን 2ተኛ
👉5.5ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2ሚሊዮን 1ኛ
👉 7ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2.8ሚሊዮን ግራውንድ በውስጥ በኩል
👉10ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 4ሚሊዮን ግራውንድ በውጪ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251939770177
     +251996856273
https://t.me/TemerRealEstateSalesConsultant
WhatsApp. https://wa.me/251939770177


5ኛ ዙር የ full stack development ስልጠና ምዝገባ በ ሃያሁለት ጀምረናል።

ከሚከተሉትን ያካትታል።
1. Python Programming Language
2. Front end Development (html,css, bootstrap and Javascript)
3. Backend development (PHP)
4. Database
5. Laravel Framework
6. Projects

በምዝገባ ላይ ነን :
☎️
0989747878
0799331774

በመራህያን የወደፊት ብሩህ ተስፋዎን የሚዘሩ ክህሎቶችን ይማሩ !!

አድራሻ፡ ሃያ ሁለት ፣ ከጐላጐል ወደ ቦሌ ሚወስደው ከ Hanan K Plaza አጠገብ ቢጫ ፎቅ ግራውንድ ፍሎር 10B

ለበለጠ መረጃ : @merahyan


አ.አ ነገ ዝግ የሚደረጉ መንገዶች!!

116ኛውን የኢትዮጵያ ፖሊስ ምስረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።

በዚህም መሠረት፦

👉 ከ22 አደባባይ ወደ ወደ ቅዱስ ዑራኤል -መስቀል አደባባይ
👉 ከአትላስ መብራት ወደ ቅዱስ ዑራኤል አደባባይ
👉 ከቦሌ ወሎ ሠፈር መታጠፊያ ወደ ኦሎምፒያ አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ)
👉 ከወሎ ሠፈር ጀምሮ እስከ ጋዜቦ አደባባይ
👉 ከመስቀል ፍላዎር አደባባይ ወደ ጋዜቦ አደባባይ (መስቀል ፍላዎር አደባባይ ላይ )
👉 ከጋዜቦ አደባባይ ወደ ኤግዚብሽን ውስጥ ለውስጥ ወደ ፊላሚንጎ
👉 ከቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክርሰቲያን ወደ ለገሃር መብራት
👉 ከአጎና መስቀለኛ ወደ ጥላሁን አደባባይ
👉ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ ለገሀር መብራት
👉ከፓርላማ መብራት ወደ ውጭ ጉዳይ (ፓርላማ መብራት ላይ )
👉ከጥይት ቤት ወደ ቅዱስ ገብርኤል
ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ
👉ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ ቶታል (ሴቶች አደባባይ ላይ) ከንጋቱ 10:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ዝግ ይሆናሉ።
በተጨማሪም፦
👉 ከቅዱስ ዑራኤል ወደ መስቀል አደባባይ
👉 ከኦሎምፒያ ወደ መስቀል አደባባይ
👉 ከጥላሁን አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ
👉 ከለገሃር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ
👉 ከሀራምቤ መብራት ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም
👉 ከብሔራዊ ቤተጰመንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ ከዛሬ ማለትም ከ25/08/2017 ዓ/ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ጀምሮ ዝግ ሲሆን እንዲሁም ለዚሁ ፕሮግራም ሲባል ከቀኑ 10:00 ሰዓት ጀምሮ በመስመሮቹ ላይ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳስቧል።

  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ


DV 2026 ውጤት ይፋ ሆነ!

መልካም እድል ለውድ ኢትዮጵያውያን!

በፈረንጆቹ 2026 ወደ አሜሪካ ለመሄድ እድላቸውን ለመሞከር ባለፈው ዓመት (October 2 to November 7, 2024) ለDV ሎተሪ የተመዘገባችሁ ውድ ኢትዮጵያውያን በሙሉ፣ ዛሬ የአሜሪካ መንግስት በይፋ የDV 2026 እድለኞችን ዝርዝር ይፋ አድርጓል!

ውጤቱን ለመመልከት ምንም አይነት ክፍያ አይጠየቅም። የአሜሪካ መንግስት ይፋዊ ድረ-ገጽ ላይ በመግባት በቀጥታ ማረጋገጥ ትችላላችሁ።

ይህ ነው ይፋዊው ድረ ገጽ፡ https://dvprogram.state.gov/ESC/

ይህንን ሊንክ በመጠቀም እድላችሁን ገብታችሁ ተመልከቱ!

ውጤቱ የወጣላችሁ እድለኞች እስከሚቀጥለው ዓመት መስከረም ወር ድረስ አስፈላጊውን የኢሚግሬሽን ሂደቶች አጠናቃችሁ ወደ አሜሪካ መግባት ይኖርባችኋል። አለበለዚያ ያገኛችሁት እድል ይሰረዛል።

  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ

24.6k 0 255 37 145


Показано 16 последних публикаций.