Ministry of Education Ethiopia


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Образование


This is Ministry of Education's Official Telegram Channel.
For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Образование
Статистика
Фильтр публикаций


43ኛው የኢትዮጵያ ተማሪዎች ህብረት መደበኛ ጉባኤ “ጠንካራ የተማሪዎች አደረጃጀት ለተሻለች ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ አስተናጋጅነት ተካሄደ፡፡
===========================
መጋቢት 16/2016 ዓ.ም (ትሚ) 43ኛው የኢትዮጵያ ተማሪዎች ህብረት መደበኛ ጉባኤ “ጠንካራ የተማሪዎች አደረጃጀት ለተሻለች ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ አስተናጋጅነት ተካሂዷል፡፡

ሙሉ ዜናው👇
https://www.facebook.com/share/p/4CyUSuffFwVaKnzr/?mibextid=Nif5oz


የከፍተኛ ትምህርት ፕሬዝዳንቶች ፎረም ተጠናቀቀ

............................................
መጋቢት 8/2016 ዓ.ም (ትሚ) መሪ ቃሉን “ከፍተኛ ትምህርት ከፍ ላለ ተጽዕኖ” (Higher Education for Higher Impacts) ያረገው የከፍተኛ ትምህርት ፕሬዝዳንቶች ፎረም ትናንት ተጠናቀቀ፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ በፎረሙ ማጠቃለያ ከፍተኛ ትምህርት ላይ እየተተገበሩ ያሉት ቁልፍ የለውጥ ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የዘርፉ ሃላፊዎች በትኩረት በመሰራት የድርሻቸውን መወጣት እንደሚገባቸውና የሁሉንም ባለድርሻዎች የላቀ ተሳትፎ እንደሚጠይቅ አሳስበዋል።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ጨምሮ ከመላው የሃገራችን ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዚደንቶችና ሌሎች የስራ ሃላፊዎች አንዲሁም ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት ፎረም በተጀመሩ የለውጥ መርሃ-ግብሮች አተገባበር፣የለውጥ ስኬቶችና ባጋጠሙ ተግዳሮቶች ዙሪያ ለተከታታይ ሁለት ቀናት ጥልቅ ውይይት ሲያደርግ የቆየ ሲሆን የቀጣይ ስራ አቅጣጫዎች ላይ በመምከር ተጠናቋል፡፡

በዕለቱ በጅማ ዩኒቨርስቲ (@ Jimma University ) የተዘጋጀ አውደርዕይ፣ የዲጂታል ትምህርት ስቱዲዮና Ict መረጃ ማዕከል እንዲሁም ሌሎች ካምፓሶች በፎረሙ ተሳታፊዎች ተኀብኝተዋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et ይከታተሉ!


የከፍተኛ ትምህርት ፕሬዝዳንቶች ፎረም እየተካሄደ ነው::
-------------------------//--------------

መጋቢት 7/2016 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት ፕሬዝዳንቶች ፎረም “ከፍተኛ ትምህርት ከፍ ላለ ተጽዕኖ/Higher Education for Higher Impacts” በሚል መሪ ቃል በጅማ ዩኒቨርሲቲ በዘርፉ የሚተገበሩ አዳዲስ ሪፎርሞች ላይ ትኩረት ያደረገ ውይይት በማካሄድ ላይ ነው::

በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሸኔ በውይይት መድረኩ ተገኝተው ካለፈው ተሞክሮ ስለተገኙ ቁም ነገሮችና ዘርፉ ያለበትን ቁመና አስመልክቶ ንግግር አድርገዋል::

ሚኒስትር ዴኤታው ባስተላለፉት መልዕክት የከፍተኛ ትምህርት ዘርፉ ለሃገር ከፍ ያለ አበርክቶ እንዳይኖረው አንቀው ከያዙት ማነቆዎች ሊላቀቅ እንደሚገባ ገልጸዋል።

ለፎረሙ ተሳታፊዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማቂ ነጻነት ፍኖተካርታ፣የዩኒቨርስቲ ትኩረት መስክና ተልዕኮ ልየታ፣ በከፍተኛ ትምህርት፣ ቴክኒክና ሙያ ሥልጠና፣ የምርምር
ተቋማት እና የኢንዱስትሪ ትስስር አዋጅ 1298/2015 ጨምሮ በከፍተኛ ትምህርት ዘርፉ ላይ የተከናወኑና በመከናወን ላይ ስላሉ አዳዲስ ትግበራዎችና የለውጥ አጀንዳዎች ዙሪያ የውይይት አጀንዳዎች ቀርበዋል::

በፎረሙ ላይ ከተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ የዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንቶችና
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከፍተኛ ሃላፊዎች፣የትምህርት ሚኒስቴርና የጅማ ዩኒቨርስቲ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው።

ሙሉ ዜናው👇

https://www.facebook.com/share/p/9C4VF3Qk5MwsoM85/?mibextid=Nif5oz


በመውጫ ፈተና ኩረጃና ሌሎች የፈተና ስነምግባር ጥሰት የፈጸሙ 114 ተፈታኞች ውጤት ሙሉ በሙሉ ተሰረዘ
....................................................
መጋቢት 2/2016ዓ.ም (ትሚ) በመውጫ ፈተና ሞባይል ስልክ ይዞ መግባት፣ መኮረጅና የተለያዩ የፈተና ስነምግባር ጥሰት የፈጸሙ 114 ተፈታኞች ውጤት ሙሉ በሙሉ መሠረዙን የትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ መጋቢት 2/2016 ዓ.ም ለሁሉም የመንግስትና የግል ዩኒቨርሲቲዎች በጻፈው ደብዳቤ አሳውቋል።

የፈተና ስነምግባር ጥሰት የፈጸሙት 114 (አንድ መቶ አስራ አራት) ተፈታኞች ውጤታቸው ሙሉ በሙሉ መሠረዙንና የሚወሰዱ ተጨማሪ እርምጃዎች በቀጣይ የሚገለጽ መሆኑ በደብዳቤው ተመልክቷል ።

ከየካቲት 6-11/2016 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ የመንግስት ተቋማት በተሰጠው ሁለተኛ ዙር የመውጫ ፈተና 119, 145 ተፈታኞች ተፈትነዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ጥራትን ለማረጋገጥ ከጀመራቸው ሪፎርሞች አንዱ የሆነው መውጫ ፈተና ተመራቂዎች በዩኒቨርስቲ ቆይታቸው ተገቢውን እውቀትና ክህሎት መቅሰማቸውንና ብቁ መሆናቸውን ዒላማ ያደረገ በመሆኑ ፈተናው በጥብቅ ዲስፕሊን የሚመራ ነው።

የትምህርት ሚኒስቴርን መረጃዎች በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-

በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et ይከታተሉ


እንኳን ለ128ኛው የአድዋ ድል በዓል በሰላም አደረሰን!

የአድዋ ድል የጥቁር ሕዝብ ነጻነት የታወጀበት ኢትዮጵያውያን ቅኝ ሊገዛ የወረራቸውን የጣሊያን ጦር ድል አድርገው አዲስ የታሪክ ምዕራፍ የከፈቱበት ታሪካዊና የአሸናፊነት ተምሳሌት ነው።

ጀግኖች አባቶቻቸን በዘርና ቋንቋ ሳይከፋፈሉ በአንድነት ድልን ተቀዳጅተው የጥቁር ህዝቦች ኩራት የሆነውን የድል ታሪክ፣ በደማቅ ጽፈው አልፈዋል።

የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር!

የትምህርት ሚኒስቴርን መረጃዎች በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-

በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et ይከታተሉ


በአፍሪካ 9ኛው በኢትዮጰያ አምስተኛው የትምህርት ቤት ምገባ ቀን በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ተከበረ፡፡
=============================

የካቲት 22/2016ዓም (ትሚ) በአፍሪካ 9ኛው በኢትዮጰያ አምስተኛው የትምህርት ቤት ምገባ ቀን " ለሀገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባ መዋዕለ ንዋይን ማፍሰስ ለተሻለ ትውልድ ግንባታ!!" በሚል መሪ ቃል በሀገር ደረጃ በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ተከበረ፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበዓሉ ላይ ተገኝተው የትምህርት ቤት ምገባ ወጪ ሳይሆን በመጪው ሀገር ተረካቢ ትውልድ ላይ የሚደረግ አዋጭና ዘላቂ የሰብዓዊ ልማት ኢንቨስትመንት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

መርሃ-ግብሩ በአግባቡ ከተተገበረ የልጆችን አካላዊና አዕምሮኣዊ ዕድገት በማፋጠንና ጤንነታቸውን በመጠበቅ የተማሪዎችን የትምህርት ውጤታማነት እንዲሻሻል በማድረግ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለውም ጠቁመዋል፡፡

ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ የትምህርት ቤት ምገባ እንደሃገር በመንግሰት ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶት እየተተገበረ ያለና ከ6.2 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች ተጠቃሚ ያደረገ ፕሮግራም መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም የመንግስት አካላት፣የልማት አጋሮች፣ የግሉ ዘርፍ ባለሀብቶችና ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች የነገ ሀገር ተረካቢ የሆኑ ታዳጊዎችን ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ለመገንባት በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን ጥረት ለመደገፍ እያበረከቱ ላሉት አስተዋጽኦ አመስግነው በቀጣይም ድጋፋቸውን ይበልጥ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ሙሉ ዜናው👇

https://www.facebook.com/share/p/JX9bp4LQb6KfhXr7/?mibextid=Nif5oz


የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞችና አመራሮች 128ኛውን የአድዋ ድል በዓል በተለያዩ ሁነቶች አከበሩ፡፡

።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የካቲት 21/2016 ዓ.ም(ትሚ) «ዓድዋ የጥቁር ሕዝቦች ድል!»በሚል መሪ ቃል ዘንድሮ ለ128ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአድዋ ድል በዓል የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞችና አመራሮች ሰንደቅ አላማ በጋራ በመስቀልና ሊሎች መርሃግብሮች አክብረዋል፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ባስተላለፉት መልዕክት የአድዋ ድል የመላው ጥቁር ህዝቦች የነጻነት ችቦ እና አርማ በመሆኑ የድሉን እሴቶችና ቱሩፋቶች በሚገባ ጠብቆ ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

ሚኒስትር ዴኤታዋ አክለውም 128ኛው የዓድዋ ድል በዓል እንደሃገር የዓድዋ ድል መታሰቢያ የሆነው አድዋ ዜሮ ዜሮ ፕሮጀክት ተጠናቆ በተመረቀበት የሚከበር በመሆኑ ድሉን ድርብ ያደርገዋልም ብለዋል

ሰንደቅ ዓላማ በጋራ የመስቀል መርሃ ግብሩን ተከትሎ በማህበራዊ ሳይንስ ስርዓተ ትምህርት ሃላፊ አቶ ኡመር ኢማም የውይይት መነሻ ያቀረቡ ሲሆን የህዝቦች አብሮ የመኖርና የመልማት እንዲሁም የሀገርን ሉዓላዊነትን የማስከበር ጉዳዮች ላይ ይህ ትውልድ ከአባቶቹ ብዙ መማር እንደሚገባው አመላክተዋል፡፡

ሙሉ ዜናው👇

https://www.facebook.com/share/p/xzABkDHNRqFwizd4/?mibextid=oFDknk


የአፍሪካ የትምህርት ቤት ምገባ ቀን የካቲት 22/2016 ዓ.ም ይከበራል!
.........................................................................................................................................................
የካቲት 21/2016 ዓ.ም (ትሚ) የአፍሪካ የትምህርት ቤት ምገባ ቀን ነገ የካቲት 22/2016 ዓ.ም ይከበራል።

የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች እኤአ አቆጣጠር ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ እንዲከበር በወሰኑት መሠረት የአፍሪካ የትምህርት ቤት ምገባ ቀን በየአመቱ ማርች አንድ በህብረቱ አባል ሀገራት አስተናጋጅነት እየተከበረ የቆየ መሆኑ ይታወቃል፡፡

በዚህ አመትም 9ኛው የአፍሪካ ትምህርት ቤት ምገባ ቀን  "አካታችና የበለጸገች አፍሪካን እውን ለማድረግ ሀገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባ ላይ መዋዕለ ንዋይን በማፍሰስ በትምህርት ሥርዓቱ ላይ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ይገባል” በሚል መሪ ቃል ነገ በድሬደዋ ከተማ  ይከበራል፡፡

በኢትዮጵያ ከ6.2 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች የትምህርት ቤት ምገባ ተጠቃሚ ሲሆኑ የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራምን ማጠናከር መጠነ ማቋረጥን ለመቀነስና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ ትልቅ ድርሻ ያለው በመሆኑ የሁሉንም ዜጋ ትብብር ይሻል!

የትምህርት ሚኒስቴርን መረጃዎች በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-

በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et ይከታተሉ


#ማስታወቂያ

ለሁሉም የግልና የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሙሉ

የ2016 ዓ .ም አጋማሽ የመውጫ ፈተና ውጤት ከየካቲት 18/2016 ዓ ም ጀምሮ ስለተለቀቀ

https://result.ethernet.edu.et

ሊንክ ማየት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

ትምህርት ሚኒስቴር!

የትምህርት ሚኒስቴርን መረጃዎች በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-

በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et ይከታተሉ


#ማስታወቂያ

የካቲት 15 ቀን 2016 ዓ.ም

ለምርምር ጆርናል ባለቤቶችና ለሀገር ውስጥ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፣ ለምርምር ተቋማት እና ሙያ ማህበራት

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር በሀገር ውስጥ የሚታተሙ የምርምር ጆርናሎች ጥራትና እይታን ለማሳደግ ሲባል የምዘናና እውቅና አሰራር ስርአት መዘርጋቱ ይታወቃል፡፡

ስለሆነም ከተመሰረተ 3 አመት የሞላቸው ጆርናሎችን የምታስተዳድሩና የእውቅና አሰጣጥ መመሪያ Amended Guideline for Evaluation of Journals Published in Ethiopia No.: Research 01/2019) መስፈርቶችን የምታሟሉ ተቋማት በጆርናሉ ዋና አርታኢ በኩል ይህ ደብዳቤ ከወጣበት ቀን አንስቶ በአስራ አምስት (15) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ

http://survey.ethernet.edu.et/index.php/888858?lang=en

የተቀመጠውን ቅጽ በመጠቀም እንድታመለክቱ ጥሪ እያደረግን ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ
ethiojournalaccreditation@ethernet.edu.et

በመላክ መረጃ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

ማሳሰቢያ
ይህ ማስታወቂያ በ2015 ዓ.ም አራተኛ ዙር ያመለከቱትንና ለዳግም እውቅና አመልክተው ፍተሻው በሂደት ላይ ያሉትን ጆርናሎች አይመለከትም፡። ይሁን እንጂ የግምገማ ውጤቱ እንደታወቀ መስፈርቱን ባለማሟላት እውቅና ለማያገኙ አመልካቾች ሚ/ር መስሪያ ቤቱ ወደፊት በልዩ ሁኔታ የሚያስተናግድ መሆኑን እንገልጻለን፤

ማንኛውም አመልካች የሀገር ውስጥ ጆርናሎች ፍተሻ እና እውቅና አሰጣጥ Amended Guideline for Evaluation of Journals Published in Ethiopia No.: Research 01/2019) መስፈርቶችን ማሟላት ይጠበቅበታል፤

ትምህርት ሚኒስቴር


የማላዊ ሳይንስ፣ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ዳይሬክትር ከትምህርት ሚኒስቴር የስራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አካሄዱ::
::::::::::::::::::::::::::::::::::::::: ::::::::::::::::::::::::::::::::::::::: :::::::::::::::::::::::::::::::::::::::
የካቲት 13/2016 ዓ.ም(ትሚ) በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሸኔ የማላዊ ትምህርት ሚኒስቴር ሳይንስ፣ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ዳይሬክትር የሆኑትን ፕ/ር ቻሞራ ሜኬካን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡

ሁለቱ ወገኖች በተለያዩ የትብብር መስኮች በተለይም በምርምር እና ቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲሁም በዩኒቨርሲቲዎች መካከል ትብብር ለመፍጠር በሚያስችል ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ውይይት አድርገዋል፡፡

በተያያዘም በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ በኩል በመከናወን ላይ ያሉ የሪፎረም ተግባራትን አስመልክቶ በክቡር ሚኒስትር ዴኤታው በኩል ገለጻ ተደርጓላቸዋል፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የምርምር እና ማህበረሰብ ጉድኝት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሰለሞን ቢኖር በበኩላቸው ጉብኝቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የትብብር ፍላጎት ለመለየት እና ወደፊት በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ለማስጀመር መልካም አጋጣሚ የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል፡፡


የፊንላንድ መንግስት በትምህርት ዘርፍ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለጸ፡፡
::::::::::::::::::::::::::::::::::
የካቲት 12/2016 ዓ.ም (ትሚ) የትምህርት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በኢትዮጵያ የፊንላንድ አምባሳደርን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
የሁለቱ ወገኖች ውይይት ያተኮረው በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የትኩረት መስኮች ላይ መሰረት ያደረገ ሲሆን በዋነኝነትም በአካቶ እና የልዩ ፍለጎት ትምህርት ላይ ያሉ ጉድለቶችን ለመሙላት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በውይይቱ ወቅት ባደረጉት ገለጻ ኢትዮጵያ የትምህርት ጥራትና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ በምታደርገው ጥረት ውስጥ የፊንላንድ መንግሰትና ህዝብ እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

ሚኒስትር ዴኤታዋ እያይዘው በኢትዮጵያና ፊንላንድ መንግሰት መካከል ያለው ዘላቂ የትምህርት ትብብር በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጠንካራ የሁለትዮሽ ትብብር ማሳያ በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል ፡፡

በኢትዮጵያ የፊንላንድ አምባሳደር ሲኒካ አንቲላ በበኩላቸው ሀገራቸው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በተለያዩ የትብብር መስኮች በጋራ እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

ክብርት አምባሳደሯ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ባደረጉት ገለጻ ሀገራቸው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር በትምህርቱ ዘርፍ በተለይም በአካቶና የልዩ ፍላጎት ትምህርት ዘርፍ ያሉ ክፍተቶችን ለመሙላት የሚያስችሉ አዳዲስ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ለማድረግ በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
ሙሉ ዜናው👇
https://www.facebook.com/share/XjVxHDGGUvC37nLJ/?mibextid=oFDknk


የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የተማሪዎች ምዝገባ ተጀመረ ።

...................................................
የካቲት 7/2016 ዓ.ም (ትሚ) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2016ዓ/ም የኢትዮጵያ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና (12ኛ ክፍል) የተፈታኞች ምዝገባን በሚመለከት ለሚዲያ አካላት ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡

የአገልግሎቱ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ተፈራ ፈይሳ የ2016ዓ/ም የኢትዮጵያ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ተፈታኞች የመመዝገቢያ መስፈርቱን በማሟላት በተቀመጠው የጊዜ ገድብ መመዝገብ እንዳለባዉ አብራርተዋል፡፡

ም/ዋና ዳይሬክተሩ ምዝገባዉ የሚከናወነዉ በበይነመርብ /Online Registration / ሲሆን ከየካቲት 3 -30/2016 ዓ.ም ይሆናል ብለዋል።

በየደርጃዉ የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ትኩርት ማድርግ ያለባቸውን ጉዳዮችም እንደሚከተለው አሳስበዋል።

1. በተቀመጠው የጊዜ ገደብ መምዘገብ እንዳለባቸው ከየካቲት 3 -30 /2016 ዓ.ም ብቻ

2. ምንም አይነት ስህትት ማለትም የፆታ ߹የስም ስህተት߹የፎቶ ߹የትምህርት መስክ እና የመሳስሉት ችግሮች እንዳይፈጠሩ በትኩርት መስራት መቻል

3. ከየካቲት 30 /2016 ዓ.ም በኃላ የሚመጣ ምዝገባ ተቀባይነት እንደሌለዉ ማወቅ መቻል

4. የመደበኛና የማታ ተማሪዎች ምዝገባ የሚከናወንው በተማሩበት ት/ቤት እንደሚሆን

5. የግል ߹ የርቀት /የበይነ መርብ /ተፈታኞ ምዝገባ በክፍለ ከተማ ߹በወረዳና ትምህርት ፅ/ቤቶች እንደሚከናወን የየትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መረጃ ያመለክታል።




ሁለተኛው ዙር የመውጫ ፈተና ዛሬ በጤና ትምህርት ፕሮግራሞች  መሰጠት ጀመረ

..............................................
የካቲት 6/2016ዓ.ም (ትሚ)ሁለተኛው ዙር የመውጫ ፈተና ከዛሬ ካቲት 6/2016 ዓ.ም ጀምሮ መሰጠት ጀምሯል።

በዛሬው እለት በጤና ፕሮግራሞች በተጀመረው ፈተና ጠዋት 15,440 ተማሪዎች በ23 የጤና ፕሮግራሞች የተፈተኑ ሲሆን ከሰዓት 14,807 ተማሪዎች በ13 ፕሮግራሞች ተፈትነዋል።

ፈተናው በሁሉም የፈተና ማዕከላት ከተማ እየተሰጠ ሲሆን የመውጫ ፈተና አሰጣጡ ፍትሃዊነትና ተአማኒነት ለማስጠበቅና አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ እንዲቻል የተመደቡ ታዛቢዎችም በየተመደቡበት ተቋማት በመገኘት ስራ ጀምረዋል።

የሁለተኛ ዙር ፈተናው በ47 የመንግስት ተቋማት በ84 የፈተና ማዕከላት የሚሰጥ ሲሆን በመንግስትና ግል ተቋማት ለመጀመሪያ ጊዜ የሚፈተኑትን ጨምሮ 149,145  ተፈታኞች  በ204 የፈተና ፕሮግራሞች የሚፈተኑ ሲሆን የካቲት 11/2016 ዓ.ም ይጠናቀቃል።

Показано 15 последних публикаций.