Фильтр публикаций


  በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 343 መሠረት ውሳኔ ክርክሩ ሲመለስ በክርክሩ ጣልቃ መግባት  ይቻላል?

በመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ክርክር መኖሩን በሚገባ ያወቀ ወገን ጉዳዩ ወደ በላይ ፍርድ ቤት ደርሶ ክርክሩ በነጥብ በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 343 መሰረት ወደ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሲመለስ ጠብቆ የሚያቀርበው የጣልቃ ገብነት አቤቱታ ተቀባይነት የለውም።                                         
በክርክሩ ውስጥ ተካፋይ መሆን የሚገባው ወገን በፍብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 41 መሠረት ጣልቃ መግባት የሚችል መሆኑ የተመለከተ ቢሆንም የጣልቃ-ገብ ማመልከቻውን በየትኛው የክርክር ደረጃና እስከመቼ ጊዜ ድረስ ማቅረብ እንደሚችል በሕጉ በግልጽ የተመለከተ አይደለም፡፡ ሥነ-ሥርዓት ሕጉ መብቱ ሊነካ የሚችል ወገንን በክርክሩ የሚሳተፍበት ሥርዓት በመፍጠር መብትና ጥቅሙ የሚከበርበትን ዕድል የፈጠረ ሲሆን መብቱን ለማስከበር የሚፈልግ ወገንም መብቱን በምክንያታዊ ጊዜ እንዲያቀርብና አላስፈላጊ የክርክር አቀራረብ ሥርዓት እንዳይፈጥር ግዴታ የሚጥል መሆኑን ማየት ያስፈልጋል፡፡ ክርክሩ በይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ሆነ በሰበር ችሎት ደረጃ ታይተው ወደሥር ፍርድ ቤት እንደገና እንዲወሰኑ ከተመለሱ ክርክሩን መኖሩን ያወቀና በክርክሩ መሳተፉ ጥቅሙን ለማስጠበቅ አስፈላጊ መሆኑን ያሳየ ወገን በክርክሩ ጣልቃ እንዳይገባ ሕጉ የመከልከል ሀሳብ አለው ሊባል አይችልም፡፡ በክርክሩ እውነተኛ ጥቅሙ የተነካበት ወገን ክርክሩ መኖሩን ባወቀ በምክንያታዊ ጊዜ የጣልቃ-ገብ ማመልከቻውን ሊያቀርብ እንደሚችል ግምት መውሰድ ይቻላል፡፡ ከሥነ-ሥርዓት ሕጉ ክርክርን ውጤታማ፣ ወጭና ጊዜ ቆጣቢ በሆነ አግባብ የመምራት ዓላማዎች የምንገነዘበው በምክንያታዊ ጊዜ ውስጥ ያልቀረበና የዘገየ የክርክር አቀራረብ ተቀባይነት እንደሌለው ነው፡፡ 
በተያዘው ጉዳይ አመልካች የ2ኛ ተጠሪ ወኪል በመሆን ክርክሩ እስከ ሰበር ሰሚ ችሎት ደርሶ እስኪመለስ ድረስ ሲሳተፉ የነበረ መሆኑን የሥር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያረጋገጠው ፍሬ ነገር ነው፡፡ ክርክሩ እንደገና እንዲታይ ከተመለሠ በኋላ በ1ኛ ተጠሪ የቀረበው ክስ የተሻሻለ ወይም ጭብጡ የተለወጠ ባለመሆኑ ጉዳዩ ከተመለሠ በኋላ አመልካች መብታቸው የተነካ መሆኑን ክርክሩ አያሳይም፡፡ አመልካች የ2ኛ ተጠሪ ወኪል ሆነው ተከራክረው ክርክሩ ሰበር ሰሚ ችሎት ደርሶ ሲመለስ ክርክሩን መኖሩን ካወቁ በኋላ ዘግይተው በክርክሩ ጣልቃ ለመግባት ማመልከታቸው የክርክሩን አቅጣጫ በመመልከት ክርክርን እያረፉ ለማድረግና ወደኋላ ለመመለስ የተደረገ ነው ከሚባል በስተቀር እውነተኛ ጥቅማቸውን ለማስከበርና የሥነ-ሥርዓት ሕጉ ሦስተኛ ወገኖች በክርክሩ ጣልቃ እንዲገቡ የፈቀደበትን ዓላማ ጠብቆ የቀረበ ማመልከቻ ተደርጎ ሊቆጠር የሚችል ሆኖ አላገኘነውም፡፡ በመሆኑም አመልካች በመሬቱ ላይ ያለኝ መብትና ያቀረብኩት ማስረጃ አልተመረመረልኝም በማለት ያቀረቡትን የሠበር አቤቱታ አልተቀበልነውም፡፡  
Join👇👇
https://t.me/ethiolawtips

2k 0 66 4 10

ኑዛዜ ወደታች የሚቆጠሩ ተወላጆችን ከውርስ ይነቅላል የሚል ክርክር በተከራካሪ ወገኖች ካልተነሳ ፍርድ ቤቱ በራሱ ማንሳት የማይችል ስለመሆኑ የፌ/ጠ/ፍ/ሰ/ሰ/ችሎት በመ/ቁ 245258 መጋቢት 26 ቀን 2016 ዓ.ም በዋለው ችሎት አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡
https://t.me/ethiolawtips


መስቀለኛ ይግባኝ/ ተከሳሽ ከሳሽነት ክስ
🛑🛑🛑♨️👇

• በይግባኝ ክርክር መልስ ሰጪ የሆነው ወገን በቀጥታ ይግባኝ ሳያቀርብ ተገቢውን ዳኝነት ከፍሎ ይግባኝ ባዩ ባቀረበው የይግባኝ ክርክር በመልስ ሰጪነት ከሚያቀርበው ክርክር ጋር በፍርዱ ቅር በመሰኘት የሚያቀርበው ይግባኝ

መስቀለኛ ይግባኝ ስለሚስተናገድበት ስርዓት በሕጉ በተለየ ሁኔታ በግልጽ የተመለከተ ነገር እስከሌለ ድረስ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 337 እና 338 ድንጋጌዎች የተመለከተው የክርክር አመራር ስርዓት ለመስቀለኛ ይግባኝም በተመሳሳይ ሁኔታ ተፈጻሚነት የሚኖረው በመሆኑ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 340(2) በተመለከተው መሰረት መልስ ሰጪው ወገን የሚያቀርበው የይግባኝ ማመልከቻ ግልባጭ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ.ቁ. 338 መሰረት ለይግባኝ ባዩ እንዲደርስ ሊደረግ የሚችለው ይግባኙ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/.ቁ. 337 መሰረት ያልተሰረዘ በሆነ ጊዜ ብቻ ነው፡፡ በመሆኑም መልስ ሰጪው ወገን ያቀረበው የይግባኝ አቤቱታ ከተሰማ በኋላ የሌላኛውን ወገን ክርክር መስማት ሳያስፈልግ ይግባኙ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 337 መሰረት እንዲሰረዝ የሚሰጥ ትዕዛዝ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 340(2) የተመለከተውን የክርክር አመራር ስርዓት የሚቃረን ነው ለማለት አይቻልም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 92043 ቅጽ 16፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 337፣ 338፣ 340/2
https://t.me/ethiolawtips


በአዋጅ ቁጥር 1249/13 ድንጋጌዎች አግባብ ለፌደራል ጠበቆችና የህግ አማካሪዎች ፈቃድ ለማሳደስ ሲመጡ የሚያስፈልጉ ዝርዝር መስፈርቶች






የሰ/መ/ቁ. 220119
ጥቅምት 1 ቀን 2015 ዓ.ም
የቅን ልቦና ገዥ
🔀🔀🔀
ወራሽነቱን በፍርድ ቤት አሳውጆ የቤት ስመ ንብረት ካዞረ ሰው ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት ቀርቦ የሽያጭ ውል በመፈፀም ቤት የገዛ ግለሰብ የቅን ልቦና ገዥ በመሆኑ በሌሎች ወራሾች ውሉ እንዲፈርስ የሚጠየቅበት አግባብ የለም።


#የውርስ_ንብረት በሆነ ጊዜ ክርክር መኖሩን ቢያውቁም በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ቁ አንቀጽ #358 መሰረት የማቅረብ መብት ያላቸው ስለመሆኑ የተሰጠ የሕግ ትርጉም
https://t.me/ethiolawtips


#አዲስ_የሰበር_ውሳኔ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤትነትን በሰው ምስክር ለማስረዳት የሚችሉበት የህግ መሠረት ባለመኖሩ ገዥ ቤቱን ገዝቼዋለሁ በማለት የሚያቀርቡት መከራከሪያ በሻጭ ሚስት ላይ ህጋዊ ውጤትን የሚያስከትል አይሆንም ሰ/መ/ቁ 224476 በቀን 05/02/2017ዓም የተወሰነ
==========================
የማይንቀሳቀስ ንብረት ካለዉ ልዩ ባህርይ አንፃር ንብረቱን ከአንድ ወደ ሌላ ሰዉ በሽያጭ ለማስተላለፍ የሚደረግ ዉል በሦስተኛ ወገን ላይ ህጋዊ ዉጤት ያስከትል ዘንድ ዉሉ በህግ አግባብ በሚመለከተዉ አካል ዘንድ ካልተመዘገበ ውሉ ፈራሽ እንደሚሆንና የፍ/ሕ/ቁ አንቀጽ 2878 ን ዋቢ በማድረግ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁ. 153664 ላይ አስገዳጅ የህግ ትርጉም የሰጠበት ሲሆን በተያዘው ጉዳይም ተጠሪው ይህ አከራካሪ ቤት ከአመልካችዋ ባለቤት ላይ በግዢ ያገኙት መሆናቸውን ከመግለጽ በቀር፤ ቤቱን በግዢ ስለማግኘታቸውና በህግ አግባብ ባለው አካል ዘንድ የግዢና የሽያጭ ውሉ የተመዘገበበት የሰነድ ማስረጃ ተጠሪው በሥር ፍርድ ቤት ያላቀረቡ በመሆኑና የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤትነትን በሰው ምስክር ለማስረዳት የሚችሉበት የህግ መሠረት ባለመኖሩ አመልካቹ ቤቱን ገዝቼዋለሁ በማለት የሚያቀርቡት መከራከሪያ በአመልካችዋ ላይ ህጋዊ ውጤትን የሚያስከትል አይሆንም
https://t.me/ethiolawtips

5k 0 122 3 19


Показано 10 последних публикаций.