Фильтр публикаций


በፍ/ብ/ህግ ቁጥር 2472(1/2) ላይ እንደተደነገገዉ #ከብር 500 በላይ የሆነ የገንዘብ ብድር ዉል መኖሩን ማስረዳት የሚቻለዉ #በጽሁፍ ወይም #በፍርድ ቤት በተደረገ የእምነት ቃል ወይም #በመሃላ ካልሆነ በቀር በሌላ ማስረዳት አይቻልም፡፡
#የብድር ገንዘቡ ስለመከፈሉም ማስረዳት የሚቻለዉ በዚሁ አግባብ ብቻ ስለመሆኑ የዚሁ ድንጋጌ ንኡስ ቁጥር ሶስት ይዘት ያሳያል፡፡ሰበር መ/ቁ/205008 ሐምሌ 20 ቀን 2014 ዓ.ም👇
https://t.me/ethiolawtips


የማይንቀሳቀስ ንብረት ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ
በማቅረብ ብቻ የሚረጋገጥ አይደለም የሰ/መ/ቁ.
229608

በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ 33(2) መሰረት ከሳሽ ባቀረበው ክስ ላይ
መብትና ጥቅም የለውም ተብሎ የሚወሰነው ክስ ባቀረበበት
ጉዳይ ላይ መብት ያለው ስለመሆኑ ማስረጃ ሳያቀርብ ሲቀር ነው፡፡አመልካች በስር ፍ/ቤት ክስ ባቀረበበት ንብረት ላይ መብትና ጥቅም ያለው ስለመሆኑ የተለያዩማስረጃዎችን (በሰበር አቤቱታው ላይ የተዘረዘሩ) ከክሱ ጋር አያይዞ አቅርቦ ሳለ የስር ፍ/ቤቱ አመልካች ክሱን ለማቅረብ መብትና ጥቅም የለውም በማለት ክሱን ውድቅ በማድረግ የሰጠው ብይን እና ይግባኝ ሰሚው ፍ/ቤት የሰጠው ትእዛዝ መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ነው፡፡ የስር ፍ/ቤት መብትና ጥቅም የማይንቀሳቀስ ንብረት ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ በማቅረብ ብቻ እንደሚረጋገጥ አድርጎ ብይን የሰጠ ሲሆን ይህም የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ.መ.ቁ 36320(ቅጽ 9) በማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ ክስ ለማቅረብ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ማቅረብ ግዴታ አለመሆኑን እና ባለይዞታነት በሌላ መንገድ ሊረጋገጥ እንደሚችል ከሰጠው አስገዳጅ የህግ ትርጉም ውጪ በመሆኑ መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ነው።👇👇.
https://t.me/ethiolawtips


በጋብቻ ውስጥ የተፈራ ንብረት የክፍፍል ጥያቄ ጋብቻው ከፈረሰበት ቀን ጀምሮ በ10 ዓመት ውስጥ ካልቀረበ በይርጋ ይታገዳል የሚል ትርጉም መስጠት የተፋቾችን ሕገ መንግሥታዊ የንብረት መብት የሚጥስ ስለሆነ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 40(1፣ 7)፣ 50(5)፣ 55፣ 79(1)፣ እና 9(1) መሠረት ተፈጻሚነት የለውም::
ፌደሬሽን ም/ቤት መ/ቁ. 77/12 (ሰኔ 3/2012 ዓ.ም.)👇👇
https://t.me/ethiolawtips


ዋስትና ላይ የተሰጠ ትርጉም (1).pdf
615.1Кб
ሰ/መ/ቁ 233903 ጥቅም 08 ቀን 2015 ዓ.ም
በወንጀል ጉዳይ ተከሳሽ የመኖሪያ አድራሻው ሌላ ቦታ መሆኑ እንዲሁም የስራ ሁኔታው ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ የሚያንቀሳቅሰው መሆኑ በሚል የዋስትና መብቱ ሊያጣ አይገባም።
በመዝገቡ ላይ የችሎቱ ሐተታ እንደሚከተለው ይነበባል።
“በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገመንግስት አንቀጽ 32 ለማንኛውም ኢትዮጲያዊ ከተረጋገጠው የመዘዋወር መብት አኳያ አመልካቾች በሐገሪቱ አካባቢ የመዘዋወር እና የመኖሪያ ቦታ የመመስረት መብት አላቸው ፡፡ ስለሆነም አመልካቾች የሌላ ቦታ ነዋሪ መሆናቸው ብቻውን በሕገ መንግስቱ አንቀፅ 19 ንዑስ አንቀፅ 6 የተረጋገጠላቸው በዋስ የመልቀቅ መብት እንዲነፈግ የማድረግ እና በሕገ መንግስቱ አንቀፅ 25 የተደነገገውን በሕግ ፊት እኩል የመሆንና እኩል የሕግ ጥበቃ የማግኘት መብትን የሚጥስ በመሆኑ ተቀባይነት ያለው ምክንያት አይደለም፡፡”
Join👇
https://t.me/ethiolawtips




ክርክር ተደርጎ ዉሳኔ ከተሰጠ በኋላ በፍ/ብ/ስ/ስ ህግ ቁጥር #358 መሰረት ያቀረበችዉ መቃወሚያ #ክርክር መኖሩን #አታዉቅም ነበር ለማለት ጣልቃ ገብታ መከራከር ሲትችል ከቅን ልቦና ዉጪ ዉጤቱን ጠብቃ ያቀረበችዉ አቤቱታ ነዉ የሚለዉን ለመወሰን በእርግጥም የመቃወም አመልካች ቀደም ሲል ክርክር ሲደረግ የነበረ መሆኑን ክርክሩም የእሷን መብት የሚመለከት መሆኑን ታዉቅ እንደነበር መረጋገጥ ያለበት ፍሬነገር ጉዳይ ነዉ

#በክርክሩ ተካፋይ ያልሆነ ወገን ባልተሳተፈበት ክርክር ተድርጎ መብቱን የሚነካ ፍርድ መሰጠቱን ባወቀ ጊዜ ፍርዱን በመቃወም መብቱን ማስከበር እንደሚችል በፍ/ብ/ስ/ስ/ህግ 358 ላይ ተደንግጓል፡፡ይሁንና ይህንን መብት በመጠቀም ረገድ ክርክሩ መኖሩን እያወቀ በቸልተኝነቱ ወይም በእሱ ጉድለት የክርክሩ ተካፋይ ሳይሆን የቀረ ወገን ከቅን ልቦና ዉጪ ጉዳዩን ለማጓተት የሚያቀርበዉ መቃወሚያ ተቀባይነት ሊኖረዉ እንዳማይገባ ሰበር ችሎቱ ገዥ ዉሳኔ የሰጠበት መሆኑ ይታወቃል(ሰበር መ/ቁ/56795፣40229፣93987 እና ሌሎች መሰል መዝገቦችን ይመለከታል)፡፡
#ተከሳሽ ባልና ሚስት ሆነዉ አይነጋገሩም ወይም ክርክሩን አያዉቁም ተብሎ አይገመትም የሚል (መነሻ) ያለማስረጃ ሊገመት አይገባም።


#የመንደር ዉል ተብሎ በሚታወቀዉ በዉል አዋዋይ ፊት ባልተደረገ የስምምነት ሰነድ መሠረት የቤት ሽያጭ ዉል አለ ለማለት ተከሳሽ የሆነዉ የቤቱ ሻጭ #በግልጽ የሽያጭ ዉሉን ማድረጉን ማመን ይኖርበታል፡፡ ከዚህ ዉጪ #በመሸሽ ነዉ #የካደዉ ወይም በግልጽ #በማስረጃ አላስተባበለም በሚል ከፍ/ብ/ሕ/ቁ 1723 ዓላማ ዉጪ ያለን መስፈርት መጠቀሙ ተገቢ አይደለም፡፡የሰ/መ/ቁጥር---230810  ቀን- ጥቅምት 09 ቀን 2016 ዓ.ም👇👇👇
https://t.me/ethiolawtips


Репост из: Ethio corporate attorney
National Bank Of Ethiopia 1359_2025.pdf
45.3Мб
👇👇👇https://t.me/henoktayelawoffice
National Bank Of Ethiopia proclamation 1359_2025.pdf

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ አዋጅ ቁጥር 1359/2017



Показано 9 последних публикаций.