4-3-3 World News


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


ይህ የእርሶ፣ የአንተ፣ የአንቺ፣ የእናንተ፣ የኛ የሁላችንም ድምጽ ነው! ለሃሳብ አስተያየት ለመስጠት @atsbaha12 ይጠቀሙ

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


በኢሎን መስክ ላይ እየደረሰ ያለው ተቃውሞ!

ትራምፕ ምርጫውን ማሸነፋቸውን ተከትሎ ሥልጣን ያገኙት ኢሎን መስክ ላይ አሜሪካውያኑ ተቃውሞ ማሰማታቸው የቀጠለ ሲሆን የአሜሪካ ዜጎች ሊይዙት የሚገባውን ሥልጣን እና ውሳኔ ኢሎን መስክ ላይ ወድቋል ሲሉ ተቃውሟቸውን ገልጸዋል።

የተቃውሞ ድምጾቹም የሚከተሉት ናቸው፡፡

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንዲመረጡ ኢሎን መስክ ከ250 ሚሊዮን ዶላር በላይ ድጋፍ አድርገዋል፡፡

ትራምፕም የአሜሪካን አስተዳደራዊ ቁልፍ ለኢሎን መስክ እና ለባዕለጸጋዎች አሳልፈው ሰጥተዋል ሲሉ ተቃዋሚዎቹ አንስተዋል፡፡

ዴሞክራሲ ምን ማለት እንደሆነ እኛ የአሜሪካ ዜጎች እናውቃለን ኢሎን መስክን ግን ማንም አልመረጣቸውም የሚሉ ወቀሳዎችም እየተሰነዘረባቸው ይገኛል፡፡

በአሜሪካ ታሪክ ተፈጽሞ የማያውቅ ነገር እየተከናወነ ነው ይህን ድርጊት እንቃወማለን ሲሉ በአደባባይ ተቃውሞአቸውን አሰምተዋል፡፡

በ-ፍቅረሚካኤል ዘየደ

@Ethionews433 @Ethionews433


በአዲስ አበባና አካባቢዋ ድሮን ያለ ፈቃድ ማብረር አይቻልም- አገልግሎቱ

በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ ማንኛውንም አይነት ድሮን ያለ ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ፈቃድ ማስነሳትም ሆነ ማብረር እንደማይቻል የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታውቋል፡፡

አገልግሎቱ በአዲስ አበባ እና በዙሪያዋ የሚደረግ የድሮን እና ሌሎች በራሪ አካላት አጠቃቀምን በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል።

አገልግሎቱ በመግለጫው÷ተቋሙ በአዋጅ ቁጥር 1276/2014 በተሰጠው ስልጣን መሠረት የመሪዎችን፣ የቁልፍ መሠረተ-ልማቶችን እና ብሔራዊ ኩነቶችን ደኅንነት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የማስጠበቅ ኃላፊነት አለበት ብሏል።

ተቋሙ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በስፋት ጥቅም ላይ እየዋሉ የመጡ ድሮኖች እና መሰል ቴክኖሎጂ ወለድ መሣሪያዎች የሚፈጥሯቸውን ስጋቶች ለመከላከል የሚያስችል በቂ የቴክኖሎጂ እና የሰው ኃይል ዝግጅት ማድረጉንም ጠቅሷል፡፡

ሥራው ውጤታማ እንዲሆንም ለኅብረተሰቡ ግንዛቤ መፍጠር እና ጠንካራ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት እንደሚፈልግ ነው ያመላከተው፡፡

በተለይ ከመጪው የአፍሪካ ሕብረት ስብሰባ ጋር ተያይዞ ቅንጅቱን ማጠናከር አስፈላጊ በመሆኑ በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ ማንኛውም አይነት ድሮን ያለ ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት መሥሪያ ቤት ፈቃድ ማስነሳትም ሆነ ማብረር እንደማይቻል አጽንኦት ሰጥቷል፡፡

በሥራ ምክንያት ድሮኖች መጠቀም አስፈላጊ ከሆነ ጠያቂው አካል የበረራውን ዓላማ፣ የሚበርበትን ቦታ፣ የድሮኑን አይነት እና የሞዴል ቁጥር በመጥቀስ አስቀድሞ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱን መጠየቅ እና ፈቃድ ማግኘት እንደሚገባ  አስታውቋል፡፡

ይህ ሳይሆን ቀርቶ በዘፈቀደ የሚኒሱ እና የሚበሩ ድሮኖች ካሉ ተቋሙ አዲስ አበባንና ዙሪያዋን በጸረ-ድሮን ቴክኖሎጂ ያጠረ መሆኑን አስታውቋል፡፡

በዚኅም ቴክኖሎጂዎች በመጠቀም በማንኛውም ጊዜ ድሮኖቹን ከአየር ላይ በመለየት፣ በመጥለፍ እና ወደ አስፈላጊው ቦታ በማሳረፍ እንዲሁም የድሮን አብራሪዎቹን በቁጥጥር ስር በማዋል ተጠያቂነት የሚያረጋግጥ መሆኑን ገልጿል፡፡

ከሥራ ጋር በተያያዘ ድሮኖችን መጠቀም የሚፈልግ ማንኛውም አካል በ+251 983 00 02 98 እና +251 983 00 04 01 ስልክ ቁጥሮች በመደወል ተጨማሪ ማብራሪያ ማግኘት እንደሚችል በመግለጫው አሳስቧል።

@Ethionews433 @Ethionews433


የአሜሪካው የስለላ ድርጅት ሲአይኤ ሁሉንም ሰራተኞቹን ሊያሰናብት ነው

ተቋሙ የስራ መልቀቂያ ለሚያስገቡ ሰራተኞቹ የስምንት ወራት ደመወዝ እከፍላለሁ ብሏል

ሲአይኤ በአሜሪካ ህግን ተከትለው ከማይፈጸሙ ጥፋቶች ጀርባ እጁ አለበት የሚል ቅሬታ ቀርቦበታል

@Ethionews433 @Ethionews433


የዩክሬኑ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ ከፑቲን ጋር በቀጥታ ተገናኝተው መነጋገር እንደሚፈልጉ ገለጹ

የዲፕሎማሲ አማራጮችን ለመቃኘት ፈቃደኛ መሆናቸውን የገለጹት ዘለንስኪ ከዚህ ቀደም የሩስያ ጦር ሙሉ ለሙሉ ከዩክሬን ሳይወጣ ድርድር አይታሰብም የሚል አቋም ሲያንጸባርቁ ቆይተዋል፡፡(አል አይን)

@Ethionews433 @Ethionews433


ኔታንያሁ በነጩ ቤተ መንግስት

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ተገናኙ፡፡

ሁለቱ መሪዎች በነጩ ቤተ መንግስት ሲገናኙ ፍልስጤማውያን(የጋዛ ነዋሪዎች) ወደ ዮርዳኖስና ግብጽ መዛወር እንዳለባቸው ትራምፕ ደግመው ተናግረዋል፡፡

"እነሱ የሚሉት አንቀበልም ነው፥እኔምለው ግን ያረጉታል ነው "በሚል ልመና አይሉት ማስፈራሪያ ሀሳባቸውን አጽንዖት ሰተውበታል፡፡

ሌሎች አገራትም ይቀበሉታል የሚል እምነት አላቸው ትራምፕ፡፡

በፈራረሰው ጋዛ መኖር አይቻልም የሚሉት ትራምፕ ሀሳባቸው በበርካቶች ዘንድ ትችት እየተሰነዘረበት ነው፡፡

ወደ ሌላ ቦታ መወሰድ አለባቸው፡ በወደመው ህንጻ ምን ይሰራሉ ባይ ናቸው፡፡

ለበርካታ አስርት ዓመታት የሞት ምድር ከሆነው ጋእ ሰዎች ተዛውረው በደስታ ይኖራሉ ያሉ ሲሆን በሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ከፍተኛ ትችት እያስተናገዱም ነው፡፡

ኔታንያሁም በጋዛ ያስቀመጧቸውን ሶስት ግቦች አንድ በአንድ ማስፈጸማቸውን እንደሚቀጥሉ ለጋዜጠኞች መግለጻቸውም ስጋቱን የከፋ ያደርገዋል፡፡

ዘገባው የሲ ኤን ኤን እና አልጀዚራ ነው፡፡

@Ethionews433 @Ethionews433


ትራምፕ ዩክሬን ከአሜሪካ ያገኘችውን ድጋፍ በውድ ማዕድናት እንድትከፍል እንደሚፈልጉ ተናገሩ

ፕሬዝደንት ትራምፕ በኋይትሀውስ በሰጡት መግለጫ ዋሽንግተን በድጋፍ መልክ ካፈሰሰችው 300ቢሊየን ዶላር ጋር የሚስተካከል ክፍያ እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።

ትራምፕ በኋይትሀውስ በሰጡት መግለጫ ዋሽንግተን በድጋፍ መልክ ካፈሰሰችው 300ቢሊየን ዶላር ጋር የሚስተካከል ክፍያ እንደሚፈልጉና ለዚህም ዩክሬን ፈቃደኛ ነች ብለዋል።

"ዩክሬን ውድ ዋጋ ያላቸው ብርቅ የመሬት ማዕድን እንዳላት ነግረናታል" ብለዋል ትራምፕ። "ዩክሬን የሰጠናትን ድጋፍ በውድ ማዕድናት እንድትከፍለን እየተወያየን ነው።"
ትራምፕ ስለየትኞቹ ውድ ማዕድናት እያወሩ እንደሆነ ገልጽ አላደረጉም። ውደ ማዕድናት የሚባሉት ኃይልን ወደ እንቅስቃሴ በመቀየር ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች፣ ለሞባይ ስልክና ለሌሎች የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች የሚያገለግሉ 17 ማዕድናትን ያካተተ ቡድን ነው።
እስካሁን እነዚህን ብረቶች የሚተካ ማዕድን የለም።
እንደ አሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ መረጃ ከሆነ ኒኬልንና ሊቲየምን ጨምሮ 50 ማዕድናት ለአሜሪካ ኢኮኖሚና ብሔራዊ መከላከያ እጅግ ወሳኝ ተብለው ተለይተዋል።
ዩክሬን ከፍተኛ የዩራኒየም፣ ሊቲየምና የቲታኒየም ከፍተኛ ክምችት ያላት ቢሆንም በመጠን በአለም ቀዳሚ አምስት ውስጥ የለችበትም። አሜሪካ እነዚህን ጨምሮ ሌሎች ወሳኝ ማዕድናት ክምችት ያላት ሀገር ነች።
አሜሪካ በዝቅተኛ አቅም የሚንቀሳበስ አንድ የውድ ማዕድን ማውጫ ብቻ ያላት ሲሆን ቻይና በአንጻሩ ውድ ማዕድናትና ወሳኝ ማዕድናትን በምረት ከአለም ቀዳሚ ነች።

@Ethionews433 @Ethionews433


ትራምፕ ለደቡብ አፍሪካ የሚደርጉትን ድጋፍ እንደሚያቆሙ መዛታቸዉን ተከትሎ ከኤችአይቪ መከላከል የገንዘብ ድጋፍ በስተቀር ከዋሽንግተን የማገኘዉ ድጋፍ የለም ስትል ፕሪቶሪያ አጣጣለች

ደቡብ አፍሪካ ምንም አይነት መሬት "አልነጠቅችም" በማለት የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን የሰጡትን አስተያየት ሰኞ እለት ውድቅ አድርጋለች።የፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ፅህፈት ቤት ባወጣዉ መግለጫ "በቅርቡ የፀደቀው የንብረት መውረስ ህግ ለመዉረስ መሳሪያ ሳይሆን በህገ መንግስቱ የተደነገገ የህግ ሂደት የህዝብን መሬት በህገ መንግስቱ በሚመራ ፍትሃዊ መንገድ የሚያረጋግጥ ነው" ብሏል።

የደቡብ አፍሪካ መንግስት ምንም አይነት መሬት አልነጠቀም በማለት መግለጫዉ አክሏል፡፡ከፕሪቶሪያ ይህ መግለጫ ሊሰጥ የቻለዉ ትራምፕ እሁድ እለት በደቡብ አፍሪካ የሚደረጉትን የመሬት መንጠቅ እና “በተወሰኑ ሰዎች” ላይ የደረሰውን እንግልት በማንሳት ወደፊት ለደቡብ አፍሪካ የሚሰጠው የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያቋርጡ ከዛቱ በኋላ ነው።

“ደቡብ አፍሪካ መሬት እየነጠቀች ነው፣ የተወሰኑ ሰዎች ክፉኛ ተጎድተዋል። መገናኛ ብዙም መጥቀስ የማይፈልጉት መጥፎ ሁኔታ አለ። ትልቅ የሰብአዊ መብት ረገጣ ቢያንስ በሁሉም ላይ እየተፈጸመ ነው።” ሲሉ ትራምፕ የግል ንብረታቸዉ በሆነዉ ትሩዝ ማህበራዊ መድረክ ላይ ጽፈዋል፡፡የትራምፕ ንዴት የመጣው የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ባለፈው ወር የ1975ቱን ከዲሞክራሲ በፊት የነበረውን ህግ ከፈረሙ በኋላ ነው።አዲሱ ህግ የመንግስት አካላት ለህዝብ ጥቅም የሚውሉ ቦታዎችን ለተለያዩ ዓላማዎች የሚወስዱበትን ሂደት ያመቻቻል፡፡

ትራምፕ በጉዳዩ ላይ ጥልቅ ምርመራ እስካልተጠናቀቀ ድረስ ዩናይትድ ስቴትስ ለሀገሪቱ የምትሰጠውን ሁሉንም የገንዘብ ድጋፍ እንደምታቆም ተናግረዋል ።ሆኖም የራማፎሳ ጽህፈት ቤት ደቡብ አፍሪካ “በህግ፣ በፍትህ እና በእኩልነት ላይ የተመሰረተ ህገ-መንግስታዊ ዲሞክራሲያዊት ሀገር ነች” ብሏል።ደቡብ አፍሪካ የኤችአይቪ/ኤድስ መከላከል የገንዘብ ድጋፍ ብቻ ከአሜሪካ እየተቀበለች እንደሆነም አብራርቷል።"በደቡብ አፍሪካ ከዩናይትድ ስቴትስ የምትቀበለው ሌላ የገንዘብ ድጋፍ የለም" ሲል የፕሬዝዳንቱ ጽህፈት ቤት አክሏል፡፡

ዳጉ ጆርናል

@Ethionews433 @Ethionews433


በፈረንሳይ አንስቴዥያ በመስጠት 299 ታካሚ ህፃናት ላይ ጾታዊ ጥቃት ያደረሰው የቀዶ ህክምና ሀኪም ክስ መታየት ሊጀምር ነው

በመቶዎች የሚቆጠሩ ወጣት ታካሚዎችን በማንገላታት የተከሰሰው የቀድሞ የቀዶ ህክምና ሀኪም፣ ብዙ ጊዜ በማደንዘዣ ስር እያሉ ህፃናት ላይ ጾታዊ ጥቃት ሲፈፅም ቆይታል።በዚህ ወር በፈረንሳይ ታሪክ ትልቁ የህፃናት ጥቃት ሙከራ ችሎት ሊቀርብ እንደሆነም ተገልጿል። እ.ኤ.አ. ከ1989 እስከ 2014 ዓመታ ባሉት ጊዜያት
የ73 ዓመቱ ጆኤል ለ ስኮዋርኔክ 299 ህጻናትን በማጥቃት ወይም በመድፈር ተከሷል ። አንዳንድ ክሶችን ቢያንም አብዛኛውን ግን ክዷል።

የገዛ ቤተሰቡ አባላት የሌስኮርኔክን በህፃናት ላይ የሚፈፀመ ጾታዊ ጥቃት ሱስ ወይም ፔዶፊሊያ እንዳለበት ቢያውቁም ነገርግን ማስቆም ተስኗቸዋል ተብሏል። በጉዳዩ ላይ የተሳተፈ አንድ ጠበቃ እንደተናገረው "የቤተሰቡ ዝምታ እና ምንም ማድረግ አለመቻል ይህ በደል ለአስርተ አመታት እንዲቀጥል ምክንያት ሆኗል ብለዋል። ሌስኮርኔክ በአንድ ወቅት የተከበረ የቀዶ ህክምና ሐኪም ነበር።

ከ2017 ጀምሮ በእስር ላይ ይገኛል። የእህቱን ልጅ አስገድዶ በመድፈር ተጠርጥሯል። ተጎጂዋ አሁን ላይ በ 30 ዎቹ የእድሜ ክልል ውስጥ ትገኛለች። እንዲሁም የስድስት አመት ሴት እና አንድ ወጣት ታካሚ ጨምሮ ቡጾታዊ ጥቃይ በ2020 የ15 አመት እስራት ተፈርዶበታል። ፖሊስ በቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ በቤቱ ላይ ባደረገው ፍተሻ ህጻናትን የሚያክሉ የወሲብ አሻንጉሊቶችን፣ ከ300,000 በላይ የህፃናት ጥቃት ምስሎችን እና በሺዎች የሚቆጠሩ በጥንቃቄ የተጠናቀሩ ማስታወሻ ተገኝቷል።ሌስኮርኔክ ከ25 ዓመት በላይ በሆናቸው ወጣት ታካሚዎቹ ላይ የፈፀመውን ጥቃት ፈፅሟል የሚል ክስ ተመስርቶበታል።

በስምኦን ደረጄ

@Ethionews433 @Ethionews433


በሌባ አይደፈርም የተባለው ቅንጡ መኪና ከተገዛ ከአንድ ቀን በኋላ ተሰረቀ....

ጆን የተባለው እንግሊዛዊ ከሰሞኑ ነበር ቅንጡ የተባለውን ሬንጅ ሮቨር መኪና በ227 ሺህ ዶላር የገዛው፡፡ ግለሰቡ ይህን መኪና ለመግዛት ያነሳሳው ድርጅቱ ባራጨው ማስታወቂያ ያለ ባለቤቱ ፈቃድ በፍጹን የማይንቀሳቀስ መኪና መስራቱን አስታውቋል፡፡

በሀገሪቱ በቅንጡ መኪኖች ላይ የሚፈጸም ስርቆት እየጨመረ መምጣቱ ያሳሰበው ይህ መኪና ገዢም ከስርቆት ነጻ የሆነ መኪና በገበያ ላይ ካለ ለምን አልገዛም በሚል ግዢውን እንደፈጸመ ተናግሯል፡፡

ልዩ የደህንነት ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ተሰርቷል የጠባለው ይህ ሬንጅ ሮቨር 2024 ኤስቪ ሞዴል 500 መኪኖችን ብቻ ለገበያ እንዳቀረበም ኩባንያው አስታውቋል ተብሏል፡፡

ይህ እንግሊዛዊውም ሊሰረቅ አይችልም የተባለውን መኪና ስሙ ካልተጠቀሰው ከዚህ ኩባንያ በገዛ በ60 ሰዓት ውስጥ በሌቦች እንደተሰረቀ ለሚዲያዎች ተናግሯል፡፡

መኪናዋ በቆመችበት ቦታ የተቀመጠው የደህንነት ካሜራ ቀርጾ ያስቀረው ምስል ሲታይ ሶስት ሌቦች በቀላሉ መኪናውን አስነስተው ሲሄዱ ያሳያል፡፡

መኪናውን የሰረቁ ሰዎች ቁልፉን ፍለጋ ካሁን አሁን ወደ መኖሪያ ቤቴ አካባቢ ሊመጡ ችላሉ ብዬ ብጠብቅም እስካሁን ይህ አልሀነም ሲል ለዴይሊ ሜይል ተናግሯል፡፡

የማይሰረቅ መኪና ሰርቻለሁ በሚል ማስታወቂያ ያስነገረው ይህ ኩባንያም በደንበኛው ላይ የተከሰተው ነገር ሲነገረው የሰጠው ምላሽ ደግሞ ፈገግ ያሰኛል፡፡

ኩባንያው በዓለማችን ላይ የትኛውም መኪና ከስርቆት ሊጸዳ አይችልም ሲል ለደንበኛው ምላሽ መስጠቱ ተገልጿል፡፡

መኪናው ውድ ተብለው በገበያ ላይ እየተሸጡ ካሉ መኪኖች መካከል አንዱ ሲሆን ጎማው ብቻ ከ10 ሺህ ዶላር በላይ ወጪ ይጠይቃሉ ተብሏል፡፡[አል አይን]

@Ethionews433 @Ethionews433


ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚደንት ሆነው ተመረጡ‼️

የገዢው ብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) የፓርቲው ፕሬዜዳንት አድርጎ በከፍተኛ ድምጽ እንደመረጣቸው ፓርቲው አሳውቋል።

ተመራጩ የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት በጉባኤተኛው ፊት ቃለ መሀላ እንደፈጸሙ ተገልጿል።

በተያያዘ ዜና ጉባኤው አቶ ተመስገን ጥሩነህን እና አቶ አደም ፋራህን የፓርቲው ምክትል ፕሬዚደንቶች አድርጎ ከፍተኛ በሆነ ድምጽ መምረጡ ተነግሯል።

ሁለቱ ምክትል ፕሬዚደንቶች በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት በጉባኤተኛው ፊት ቃለ መሀላ ፈጽመዋል።

@Ethionews433
@Ethionews433


በቁጥጥር ስር የዋለው የካሊፎርኒያ ሰደድ እሳት

ለተከታታይ ሶስት ሳምንት በሰደድ እሳት ስትታመስ በከረመችው ካሊፎርንያ እጅግ አውዳሚ የነበሩት የኢተን እና የፓሊሳዴስ እሳቶች ሙሉ ለሙሉ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለጸ።

በደቡብ ካሊፎርኒያ የተነሱት እና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ቤት አልባ ያደረጉት ሁለቱ አውዳሚ የእሳት ቃጠሎዎች ከ24 ቀናት አድካሚ የማጥፋት ዘመቻ በኋላ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ነው የካሊፎርኒያ የደንና የእሳት አደጋ መከላከያ ዲፓርትመንት የተገለጸው ።

የ12 ሰዎች ህይወት የቀጠፈው የፓሊሳዴስ እሳት 23,448 ሄክታር ሲያቃጥል ከ6,800 በላይ ህንጻዎችንና ቤቶችን ወደ አመድነት ቀይሯል ።

በተመሳሳይ የኢተን እሳት በአልታዴና እና ፓሳዴና ውስጥ 14,021 ሄክታር መሬት አውድሞ የ17 ሰዎችን ህይወት ቀጥፏል።

በካሊፎርንያ እና በአከባቢው ከተቀሰቀሱ እሳቶች እጅግ አውዳሚ የተባሉት የኢተን እና የፓሊሳዴስ እሳቶች በአጠቃላይ ከ250 ቢሊዮን ዶላር በላይ ኪሳራን በኢኮኖሚ ላይ ማድረሳቸውም የወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

ዘገባው የኤን ቢ ሲ ኒውስ ነው

@Ethionews433 @Ethionews433


ሰመረ ባሪያው በቁጥጥር ስር ዋለ

በቴሌቪዥንና በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በሚያቀርባቸው ሂሶቹ የሚታወቀው የህግ ባለሙ ስውረ ካሳዬ (ሰመረ ባሪያው) አርብ እለት በፀጥታ ኃይሎች ተይዞ በቁጥጥር ስር እንደሚገኝ የቅርብ ቤተሰቦቹ ገልፀዋል።

ከእዚህ ቀደም በፋና ቲቪ በአሁኑ ወቅት ደግሞ በNBC Ethiopia ቴሌቪዥን እንዲሁም በቲክቶክ እና ዩቲዩብ አማራጮች በሚያቀርባቸው ማህራዊና  ፖለቲካዊ ጉዳዮች ዙሪያ በሚያጠነጥኑ ሂሶቹ የሚታወቀው ሰመረ ባሪያው በቁጥጥር ሥር የዋለበት ምክንያት ግልፅ አልተደረገም።

በአሁኑ ወቅትም በአዲስአበባ ፖሊስ ኮሚሽን በተለምዶ ማዕከላዊ በሚባለው እስር ቤት ታስሮ እንደሚገኝ የተገለፀ ሲሆን በቅርቡ ማህበራዊ ገፆች ላይ ያጋራቸው እና የመንግስት ኃላፊዎችን ተችቶባቸዋል የተባሉት ጉዳዮች የእስሩ ምክንያት ሊሆኑ እንደሚችሉ የሰመረ የቅርብ ሰዎች ገልፀዋል።

ሰመረ ባሪያው በማህበራዊ ትስስር ገፆች እና በቴሌቪዥን መስኮት ከሚያጋራቸው ሂሶቹ በተጨማሪ በኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ላይ ተሰናድቶ በሚቀርበው ታዲያስ አዲስ የሬድዮ ፕሮግራም በተባባሪ አዘጋጅነት እንደሚሰራ ይታወቃል።

[Hagergna media]

@Ethionews433 @Ethionews433


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ስድስት ሰው የያዘ አወሮፕላን አምቡላንስ በአሜሪካ ፊላደልፊያ ተከሰከሰ

ትላንት አርብ ለሊት በተከሰከሰው ሌርጄት 55  አምቡላንስ የተረፈ ሰው እንደሌለ የአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን እየዘገቡ ነው።

ክስተቱን ያይ ያይ የነበረ አንድ መንገደኛ  "አላሁ አክበር!  አላሁ አክበር!  ምንድን ነው ነገሩ፧  ምንድን ነው ነገሩ የሚል ድምፅ በማህበራዊ ሚዲያ በተለቀቀው ድምፅ ላይ ይሰማል።

ከቀናት በፊት ስልሳ አራት ሰው የያዘ አውሮፕላን እዛው አሜሪካ ከኤሌኮፍተር ጋር ተጋጭቶ መከስከሱ ይታወሳል።

[Hagergnamedia]

@Ethionews433 @Ethionews433


በአፋር ክልል በተፈጸመ የድሮን ጥቃት ስምንት ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ

ከትናንት በስቲያ ሐሙስ ምሽት በአፋር ክልል ኤሊዳዓር ወረዳ ሲያሩ ቀበሌ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት ስምንት ሰዎች መሞታቸውንና በርካቶች ቆስለዉ ዱብቲ ሆስፒታል መግባታቸዉን የአካባቢዉ ነዋሪዎች ተናግረዋል። የአካባቢዉ የጎሳ አስተዳዳሪ ልጂ የሆነዉ ሀመዱ አሊ ጀዋር የመጀመሪያው የድሮች ጥቃት ረቡዕ ምሽት 12 ሰዓት መፈጸሙን ገልጿል።[DW]

@Ethionews433 @Ethionews433


አሜሪካ ከዋሽንግተኑ ግጭት በኋላ የሄሊኮፕተር በረራን ከለከለች

ባሳለፍነው ረቡዕ በሬገን ብሔራዊ ኤርፖርት አቅራቢያ አውሮፕላን እና ሄሊኮፕተር ተጋጭተው 67 ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል

አደጋውን ተከትሎ እስካሁን የ41 ሰዎች አስክሬን የተገኘ ሲሆን ቀሪ አስክሬኖች እየተፈለጉ ነው

@Ethionews433 @Ethionews433


አሜሪካ በአንድ ሳምንት ሦስተኛ የአውሮፕላን አደጋ አጋጠማት
******

እናት ልጇን አሳክማ ስትመለስ ከአራት የአውሮፕላን ሰራተኞች ጋር ነው በአሜሪካ ፊላደልፊያ አቅራቢያ አደጋው የተከሰተው።

በፊላደልፊያ ህክምና የተደረገላት ልጅ እና አስታማሚ እናቷ ወደ መኖሪያቸው ሜክሲኮ በመጓዝ ላይ እያሉ ነበር አርብ ምሽት የሚጓዙባት አውሮፕላን መከስከሷ የተሰማው።

ይህን አደጋ ተከትሎ ቤቶች እና ተሽከርካሪዎች በእሳት መያያዛቸውን የሚያመላክቱ ተንቀሳቃሽ ምስሎች እየወጡ ነው።

የፊላደልፊያ ፖሊስ አደጋው መድረሱን ለሲቢኤስ ኒውስ አረጋግጧል።

የፊዴራል አቪዬሺን አስተዳዳር (ኤፍ ኤ ኤ) ደግሞ በተከሰከሰው አውሮፕላን ውስጥ ስድስት ሰዎች እንደነበሩ ይፋ አድርጏል።

ከእነዚህም ውስጥ አራቱ የአውሮፕላኗ ሰራተኞች ሲሆኑ ቀሪዎቹ ታካሚ ህጻን እና አስታማሚ እናት መሆናቸው ነው የተገለፀው።

በአውሮፕላኗ ውስጥ ከእናት እና ልጅ ውጭ አብራሪ እና ረዳት አብራሪን ጨምሮ ሁለት የህክምና ባለሞያዎች ሁሉም ዜጎቿ መሆናቸውን የሜክሲኮ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል።

የተከሰከሰችው "ሊርጀት 55" የህክምና አውሮፕላን ወደ መዳረሻዋ ሜክሲኮ በምታደርገው በረራ ስፕሪንግፊልድ አየር ማረፊያ ነዳጅ ለመሙላት የማረፍ እቅድ እንደነበራት ተገልጿል።

ይሁን እንጂ መነሻ አውሮፕላን ማረፊያውን ከለቀቀች ከ30 ሴኮንድ በኋላ መከስከሷ ነው የተነገረው።

አነስተኛ የህክምና አውሮፕላን መከስከሷን ተከትሎ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ወደ ሰሜን ምስራቅ ፊላደልፊያ በማቅናት የነፍስ አድን ስራ ላይ እየተረባረቡ ነው።

አሜሪካ ባለፈው አንድ ሳምንት ውስጥ ብቻ ሶስት የአውሮፕላን አደጋ አጋጥሟታል።

እስካሁን ስለተሳፋሪዎቹ በህይወት መኖርም ይሁን አለመኖር በግልጽ የተባለ ነገር የለም ሲል ሲኤንኤን ዘግቧል።

ሀብተሚካኤል ክፍሉ

@Ethionews433 @Ethionews433


ቻይና በግዳጅ ላይ እያለ እንቅልፍ ወስዶታል ያለችውን የጸረ ፈንጅ ውሻ ቀጣች

ውሻው ከዚህ በፊት ለየት ያሉ እና ያልተጠበቁ ስራዎችን ሰርቷል በሚል በርካታ ሽልማቶችን በማግኘት ዝናን ያተረፈ ነበር

ቻይና የጸረ ፈንጅ ውሻዋ በግዳጅ ላይ እያለ እንቅልፍ ወስዶታል በሚል ቅጣት አስተላለፈች።

የዓለማችን ቁጥር ሁለት ልዕለ ሀያል ሀገር የሆነችው ቻይና እንደ ፈንጅ፣ አደንዛዥ እጾች እና ሌሎች ረቀቅ ያሉ ወንጀሎችን ለመከላከል የሰለጠኑ ውሻዎችን ትጠቀማለች።

ልዩ ስልጠናዎችን ወስደው ቻይናዊያንን ከጥቃት እየጠበቁ ካሉ ውሾች መካከል "ፉ ዛይ" የሚል ስያሜ የተሰጠው ውሻ አንዱ ነው።

የ18 ወራት እድሜ ያለው ይህ ውሻ ከአራት ወሩ ጀምሮ የተለያዩ ረቂቅ የፖሊስ ስልጠናዎችን ወስዷል።

ኮኬይን የተሰኘውን አደገኛ እጽ አነፍንፎ በመለየት የሚታወቀው ይህ ውሻ "ኮኬይን ኦፊሰር" የሚል ስያሜንም አግኝቷል።

በተለይም ፉዛይ በተጠናቀቀው የፈረንጆቹ 2024 ዓመት ውስጥ በተመደበበት ዌፋንግ የህዝብ ፖሊስ ክፍል ስር ላሳየው የላቀ አገልግሎት በርካታ ስጦታዎችን አግኝቶ ነበር።

ይሁንና ይህ ውሻ ከሰሞኑ በግዳጅ ላይ እያለ እንቅልፍ ወስዶት ተገኝቷል። ከዚህ በተጨማሪም አልጋው ላይ ሽንቱን ሸንቷል ተብሏል።

የቻይና ፖሊስ ኮሚሽን እንደገለጸው ውሻው ሀላፊነቱን በመዘንጋት የዲስፒሊን ግድፈት ፈጽሟል በሚል ቅጣት ተላልፎበታል።

በፉ ዛይ ላይ ከተጣሉበት ቅጣቶች መካከልም ከዚህ በፊት የተሰጡት ስጦታዎች እና ሽልማትን መቀማት፣ ዓመታዊ ቦነሱን ማስቀረት ዋነኞቹ ናቸው።

በልዩው የቻይና ፖሊስ ላይ ቅጣት እንደተጣለበት ከተገለጸ በኋላ በርካቶች አስተያየታቸውን በመስጠት ላይ ናቸው።
ዓመቱን ሙሉ ስኬታማ ሆኖ ለቆየ ፖሊስ አንድ ቀን ስህተት ሰርቷል በሚል ቅጣት መጣል የለበትም የሚለው አስተያየት የብዙዎች ሆኗል።

የፉዛይን እያንዳንዱ እንቅስቃሴ በማሳየት የሚታወቀው የማህበራዊ ትስስር ገጽ በትንሽ ቀናት ውስጥ ከ340 ሺህ በላይ ተከታዮችን እንዳፈራም ተገልጿል።(አል አይን)

@Ethionews433 @Ethionews433


የጀርመን ምክር ቤት የስደተኞች ጉዳይ ረቂቅ ደንብን ዉድቅ አደረገ

የጀርመን ምክር ቤት በሐገሪቱ የሚኖሩና ወደ ሐገሪቱ የሚገቡ ስደተኞችን ለመገደብ የተረቀቀዉን አዲስ ደንብ ዛሬ ዉድቅ አደረገዉ።ተቃዋሚዎቹ ወግ አጥባቂ እትማማች ፓርቲዎች የክርስቲያን ዴሞክራቲክ ሕብረት (CDU)ና የክርስቲያን ሶሻል ሕብረት (CSU) ያረቀቁት ደንብ የሐገሪቱን ፖለቲከኞች ሲያሟግት ነበር።ረቂቁ፣ ጀርመን የሚኖሩ ስደተኞች በየትዉልድ ሐገራቸዉ ያሉ የቅርብ ቤተ-ሰቦቻቸዉን አባላት እንዳያስመጡ የሚያግድ፣ ሕገ-ወጥ የሚባሉ ስደተኞችን ወደየመጡበት ለመመለስ ፖሊስ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲያደርግ፣ ወደየመጡበትን በቀላሉ የመመለስ መብት እንዲሰጠዉ የሚጠይቅ ነበር።የዋናዉ ተቃዋሚ ፓርቲ የCDU መሪ ፍሬድሪሽ ሜርስ ረቂቁን በቀኝ ፅንፈኛዉ AFD ፓርቲ ድጋፍ ሕግ ለማድረግ መጣራቸዉ ከሕዝብም፣ ከግራ፣ ከመሐልና ለዘብተኛ ፖለቲከኞችም ከፍተኛ ቁጣና ተቃዉሞ ቀስቅሶ ነበር።የሐገሪቱ ሕግ መምሪያ ምክር ቤት (ቡንደስ ታግ) ዛሬ ባደረገዉ ስብሰባ ረቂቁን በ338 የድጋፍና በ350 የተቃዉሞ ድምፅ ዉድቅ አድርጎታል።(DW)

@Ethionews433 @Ethionews433


ዋሽግተን-ትራምፕ በBRICS አባል ሐገራት ሸቀጦች ላይ 100% የግብር ጭማሪ ለማድረግ ዛቱ

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ የBRICS አባል ሐገራት የአሜሪካዉን ዶላር ትተዉ በሌላ ገንዘብ ለመገበያየት ከወሰኑ ለዩናይትድ ስቴትስ ገበያ በሚያቀርቡት ሸቀጦቻቸዉ ላይ የ100% የቀረጥ ጭማሪ ለማድረግ ዛቱ።ትራምፕ Truth Social በተባለዉ የማሕበራዊ መገናኛ ዘዴያቸዉ ባሠራጩት ማስጠንቀቂያ እንዳሉት የBRICS አባል ሐገራት ከዶላር ለማፈንገጥ ማሰባቸዉ «ማብቃት አለበት።» ትራምፕ የBRICS አባል መንግሥታትን ለዩናይትድ ስቴትስ «የጠላትነት አዝማሚያ» የሚታይባቸዉ በማለት ወርፈዋቸዋልም።እነዚሕ ሐገራት፣ ትራምፕ «ግዙፍ» ያሉትን የአሜሪካን ዶላር ለመተካት አዲስ ገዘብ ካሳተሙ ወይም በሌላ ገንዘብ ለመጠቀም ከወሰኑ ከአሜሪካ ገበያ መሰናበት አለባቸዉ።ትራምፕ እንደሚሉት መስተዳድራቸዉ ወደ አሜሪካ በሚገቡ የየሐገራቱ ሸቀጦች ላይ የ100% የቀረጥ ጭማሪ ያደርጋል።ቡድኑን በመሠረቱት አምስት ሐገራት ስም የመጀመሪያ ፊደላት ተገጣጥሞ BRICS ተብሎ የሚጠራዉ ቡድን ባሁኑ ወቅት 10 አባል መንግስታትን ያስተናብራል። BRICS በኢንዲስትሪ የበለፀጉትን 6 ምዕራባዉያን ሐገራትና ጃፓንን የሚያስተናብረዉ ቡድን 7 የሚያደርሰዉን ተፅዕኖ ለመቋቋም ያለመ ነዉ። ሩሲያና ቻይናን የመሳሰሉ የBRICS ጠንካራ አባላትና መሥራቾች የአሜሪካ ዶላር በዓለም ገበያ ላይ የሚያደርሰዉን ጫና አጥብቀዉ ይተቻሉ።ማሕበራቸዉ አማራጭ መገበያያ እንደሚያስፈልገዉም ያሳስባሉ።የአሜሪካዉ ፕሬዝደንት ግን ዶላርን መተካት «አስደናቂ» ከሚሉት ከአሜሪካ ምጣኔ ሐብት መሰናበት ነዉ።[DW]

@Ethionews433 @Ethionews433


ሰሞኑን በሩዋንዳ ሚታገዘው የኤም 23 ታጣቂ ቡድን በማዕድን ብልፅግፅግ ያለችውን የኮንጎዋን ምስራቃዊ ከተማ ጎማን ይዟል። እነዚ ምታያቸው ታድያ በፊልክስ ፂሽኬዴ የኮንጎ ሰራዊት ወግነው ሲዋጉ በታጣቂ ቡድኑ የተማረኩ የኣውሮፓ ሀጋራት ፓስፖርት የያዙ ወታደሮች ናቸው። ቡድኑ ወደሩዋንዳ ልኳቸዋል ።ወደየሀገሮቻቸው ዲፖርት ይደረጋሉ ተብሏል።[ኤርምያስ በላይነህ]

@Ethionews433 @Ethionews433

Показано 20 последних публикаций.