EthioTube


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Видео и фильмы


ኢትዪትዩብ፦ ኢትዮጵያዊ። ነፃ። ገለልተኛ።
Follow us on other our social media networks:
Facebook.com/EthioTube
Twitter.com/EthioTube
Youtube.com/EthioTube
Instagram.com/EthioTube

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Видео и фильмы
Статистика
Фильтр публикаций




በዛሬው ቻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታ ማንችስተር ሲቲ ሪያል ማድሪድን 1ለ0 ሲመራ ቢቆይም በሜዳው 3ለ2 በሆነ ውጤት ለሽንፈት ተዳርጓል።

የዘንድሮውን የቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ማን ያነሳዋል? 🤔

#ChampionsLeague #RealMadrid #ManchesterCity


ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው ከዩናይትድ ስቴትስ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይመለሱ የኢትዮያ አየር መንገድ የጉዞ ክልከላ አደረገብኝ አሉ። ፖለቲከኛው ዛሬ ባሰራጩት በፎቶ ግራፍ የተደገፈ የፅሁፍ መልዕክት ዛሬ የካቲት 3 ቀን 2017 ወደ ሀገር ቤት ለመመለስ አትላንታ አዉሮፕላን ማረፊያ ተገኝተው እንደነበር ገልጸዋል። ነገር ግን «የአገልግሎት ጊዜው ያላለፈ የኢትዮጵያ ፓስፖርት እና የተረጋገጠ የጉዞ ቲኬት ይዤ የተገኘሁ ቢሆንም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግን በአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲን አነጋግሬ የተለየ ፈቃድ ካልተሰጠኝ በስተቀር ወደ ኢትዮጵያ መጓዝ እንደማልችል በአትላንታ የኢትዮዽያ አየር መንገድ ሀላፊ በሆኑት በአቶ ተሾመ ገ/ስላሴ ተነግሮኝ ተመልሻለሁ።» ብለዋል።
ፖለቲከኛው አክለው « በአሸባሪነት ወንጀል ሊከሰኝ እንደሚፈልግና በቁጥጥር ስር እንድውል ከኢንተር-ፖል ጋር ጭምር እየተነጋገረ እንደሆነ ሲገልፅ የነበረው የኢትዮዽያ መንግስት ዛሬ በራሴ ፈቃድ ወደ አገሬ ለመመለስ ስሞክር በእኔ ላይ ህገ-ወጥ ክልከላ ማድረጉ አስገርሞኛል።» ብለዋል። «መንግስት እኔን በወንጀለኛነት ከጠረጠረኝ ሊከሰኝና ሊያስረኝ ይችላል እንጅ ወደ አገሬ እንዳልገባ ሊከለክለኝ አይችልም።» ያሉት ልደቱ «የሀገሩን የጉዞ ሰነድ የያዘ ዜጋን ወደ ሀገሩ እንዳይገባ ለመከልከል የህግ ማዕቀፍ የለም» ብለዋል።
ክልከላውን ተከትሎ በሌላ አየር መንገድ ተጓጉዘው ወደ ሀገር ቤት እንደሚመለሱም አቶ ልደቱ አረጋግጠዋል።
አቶ ልደቱ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ጉዞ ስለመከልከላቸው አየር መንገዱ ለጊዜው ያለው ነገር የለም ።

#LidetuAyalew #EthiopianAirlines


''ቀረፃው ከእኔ እውቅና ውጪ ነው'' የኢትዮጵያ አየርመንገድ

የግለሰቧ የአየር መንገድ ግቢ ውስጥ የልደት ምስል ቀረጻ ከተቋሙ እውቅና ውጭ የተደረገ ነው - አየር መንገዱ

ከሰሞኑ በማህበራዊ ትስስር ገጾች ሲዘዋወር የነበረው የአንዲት ግለሰብ የአየር መንገድ ግቢ ውስጥ የልደት ምስል ቀረጻ ከተቋሙ እውቅና ውጭ የተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታወቀ፡፡

አየር መንገዱ ባወጣው መግለጫ አንዲት ግለሰብ በአውሮፕላኑ መወጣጫ ደረጃ ላይ የተለያዩ ዲኮሮችን በማድረግ የተነሳችው ፎቶ ሲዘዋወር መታየቱን ገልጿል፡፡

ግለሰቧ የተነሳችው ለጥገና በቆመ አውሮፕላን ላይ መሆኑን የጠቆመው አየር መንገዱ÷ድርጊቱ ከተቋሙ እውቅና ውጭ የተደረገ መሆኑን አስታውቋል፡፡

አየር መንገዱ የሙያ አገልግሎት ሥነ-ምግባርን በመጠበቅ ደረጃውን የሚመጥን አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ አጽንኦት ሰጥቷል፡፡

ይሁን እንጂ ከጉዳዩ ጋር ተያይዞ ተቋሙ ከሙያዊ ሥነ ምግባር ውጪ ገንዘብ በመቀበል ለግለሰቧ ፈቃድ እንደሰጠ በማስመሰል በተሰራጨው መረጃ ማዘኑን አንስቷል፡፡

ጉዳዩን በተመለከተ ምርመራ እያደረገ መሆኑን የገለጸው አየር መንገዱ÷ ድርጊቱን በፈፀሙ አካላት ላይ አስተዳደራዊ ርምጃ እንደሚወስድ አረጋግጧል፡፡

#EthiopianAirlines #Ethiopia

በዚህ ጉዳይ ላይ አስተያየታችሁ ምንድነው? 🤔


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው በአፍሪካ አህጉር ሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና ላይ አተኩሮ በጋና አክራ በተካሄደው አመታዊው የ “2025 የአፍሪካ ፕሮስፔሪቲ ዲያሎግ” ላይ አፍሪካን በአየር ትራንስፖርት በማገናኘት ረገድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እየተጫወተ ላለው ሚና ላሳዩት የላቀ የአመራርነት ሚና የ “Leadership in Connecting Africa through Transport Award” ተሸላሚ ሆነዋል።
ይህ ሽልማት አፍሪካን እርስ በርስ በማገናኘት ቁርጠኛ የአመራርነት አስተዋፅዖ ላበረከቱ ግለሰቦች ዕውቅና የሚሰጥበት ሲሆን የዘንድሮው የ “2025 የአፍሪካ ፕሮስፔሪቲ ዲያሎግ” የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች፣ የታላላቅ አህጉር ዓቀፍ የንግድ ተቋማት መሪዎች እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች በተገኙበት በጋና አክራ ተካሂዷል።

ለተጨማሪ ንባብ ሊንኩን ይጫኑ:
https://corporate.ethiopianairlines.com/Press-release-open-page/ethiopian-airlines-group-ceo-honored-with-prestigious-leadership-in-connecting-africa-through-transport-award?fbclid=IwY2xjawIT04hleHRuA2FlbQIxMAABHVCok0vNq89NsFuUO9Ta4Vq_pp8oCZYCexS4Wwdhd55Ki_GLNqLPxJTZtw_aem_zG3snWW8DerWNkjQ0F7XRA

#የኢትዮጵያአየርመንገድ



Показано 6 последних публикаций.