Ethiopian Press Agency/አማርኛ /


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


#መረጃ

በአዲስ አበባ በሚከናወነው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤና ሌሎች ተያያዥ ስብሰባዎች ምክንያት ከነገ ረቡዕ የካቲት 5 ቀን 2017 ዓም ረፋዱ 4፡00 ጀምሮ እስከ መጪው ሰኞ የካቲት 10/2017 ዓም ድረስ፤

✍️ አረቄ ፋብሪካ አጠገብ የነበረው ተርሚናል ወደ ዲያፍሪክ ሆቴል አካባቢ፤

✍️ ዋቢ ሸበሌ ሆቴል አጠገብ የነበረው ተርሚናል ወደ ለገሐር ተርሚናል፤

✍️ በተለምዶ ጠማማ ፎቅ የሚባለው አካባቢ የነበረው ተርሚናል ወደ ሳር ቤት ድልድይ ስር ተዛውረዋል።

ስብሰባዎቹ እንደተጠናቀቁ ወደ ቀድሞ ቦታዎቻቸው እንደሚመለሱ ተገልጿል።

የከተማዋ ነዋሪዎች ተርሚናሎቹ ወደ ነበሩበት እስኪመለሱ ድረስ ለሚያደርጉት ትብብር ከተማ አሰተዳደሩ እናመሰግኗል።

የካቲት 4 ቀን 2017 ዓም


#የአፍሪካ_ህብረት_መዲና_አዲስ_አበባ

በ46ኛው የአፍሪካ ሕብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ‼️


👉 የኬንያ የውጭና የዳያስፖራ ጉዳዮች ሚኒስትር ሙሳሊያ ሙዳቫዲ(ዶ/ር)

👉 የማዳጋስካር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራሳታ ራፋራቫቫቪታፊካ

👉 የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፓብሊኪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሲልቪ ባኢፖ-ቴሞን

👉 የደቡብ ሱዳን የውጭ ጉዳይና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር ራምዳን ሞሀመድ አብዱላሂ

👉 የሲሼልስ የውጭ ጉዳይ እና ቱሪዝም ሚኒስትር ሲልቬስትሬ ራደጎንዴ

በ46ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል።

46ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈፃሚዎች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ከነገ ጀምሮ ለሁለት ቀናት ይካሄዳል።

#ኢትዮጵያ  #ምድረቀደምት  #AU_ #አፍሪካህብረት #ዲፕሎማሲ

በቃልኪዳን አሳዬ

የካቲት 4 ቀን 2017 ዓም


"እንግዶቻችን የሚኖራችሁ ቆይታ ፍጹም ስኬታማና አስደሳች እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ" - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ የ38ኛው የአፍሪካ ኅብረት ጉባኤ ተሳታፊዎችን ወደ ምድረ ቀደምት፣ የፓን አፍሪካኒዝም መነሻ እንዲሁም የጥቁር ህዝቦች ሁሉ የነጻነት ተምሳሌትና ኩራት ወደ ሆነችው ኢትዮጵያ እንኳን በደህና መጣችሁ ትላለች።

አዲስ አበባ እንደ ስሟ ዉብ እና አዲስ ሆና በድንቅ የእንግዳ ተቀባይነት ስሜት ልታስተናግዳችሁ ተዘጋጅታለች። ውድ የከተማችን ነዋሪዎችም በተለመደዉ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት እንግዶችን ተቀብላችሁ እንደምታስተናግዱ እምነቴ የፀና ነዉ።

የካቲት 4 ቀን 2017 ዓም


የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ተሳታፊዎች የመስህብ ስፍራዎችን እንዲጎበኙት በማድረግ ቆይታቸው ማረዘም ያሰፈልጋል
*******
(ኢ ፕ ድ)

የአፍሪካ ህብረት ጉባኤን ለመሳተፍ የሚመጡ እንግዶች የመስህብ ስፍራዎችን እንዲጎበኙት በማድረግ ቆይታቸውን ለማረዘም የተለያዩ ጥቅሎች መዘጋጀታቸውን የኢትዮጵያ ቱሪዝምና ሆቴል ማርኬት ማህበር አስታወቀ፡፡

ኢትዮጵያ ከቱሪዝም ዘርፉ ማግኘት የሚገባትን ጠቀሜታ እንድታገኝ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል።

የማህበሩ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ሀስማ መፍቱ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ ለአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ተሳታፊዎች የታሪካዊ ቦታዎች ጉብኝትና የባህላዊ ጥቅሎች ተዘጋጅቷል፡፡

በሀገሪቱ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎችን እንዲጎበኙና በማድረግ ቆይታቸውን ለማረዘም እየተሰራ ነው ብለዋል።

የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ለእንግዶች ተገቢውን አገልግሎት መስጠት ግዴታቸው ነው ያሉትዳይሬክተራ ለ38ኛው የአፍሪካ ህብረት ተሳታፊዎች በቋንቋቸው ከማስተናገድ ጀምሮ ሌሎች የዝግጅት ሥራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል፡፡

የማሪዎት ሆቴል ረዳት የሽያጭ ማናጀር ተወዳጅ ሙሉጎጃም በበኩላቸው፤ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የጉባኤውን ተሳታፊዎች የኢትዮጵያን ባህል በሚገልጽ መልኩ ተቀብለን ለማስተናገድ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ስንሰራ ቆይተናል ብለዋል፡፡

38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ ሁለንተናዊ ዝግጅት መደረጉን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

በጉባዔው ከ15 ሺህ በላይ እንግዶች ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም አስታውቋል።

በማርቆስ በላይ እና በሄለን ወንድምነው

የካቲት 4 ቀን 2017 ዓም


ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ ለ20 ፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ ከሶስተ ቢሊዮን ዶላር በላይ አግኝታለች
*******
(ኢ ፕ ድ)

ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ ለ20 ፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ ከሶስተ ቢሊዮን ዶላር በላይ መውሰዷን የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ገለፁ።

23ኛው የአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ ጉባዔ የካቲት 11 በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገልጿል።

ሚኒሰትሩ የኢኒሼቲቩን የአምስት አመታት አፈፃፀምና የቀጣይ እቅድ አስመልክቶ በሰጡት ጋዜጠዊ መግለጫ፤ እስካሁን ከሃብት አሰባስቡ ጋር በተገኛኘ ለቀጣናው ሀገራት በኢኒሼቲቩ ለቀጣናው ሀገራት 15 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ኢንቨስትመንት በመነሻነት ለማሰባሰብ ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል።

ከዚህም ውስጥ ወደ 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላሩ ለፕሮጀክት ማስፈጸሚያ ውሏል። ኢትዮጵያም 20 ለሚሆኑ ፕሮጀክቶች ከሦስት ቢሊዮን ዶላር በላይ አግኝታለች ብለዋል።

ለአብነትም ባለፉት ዓመታት በነበረው የድርቅ አደጋ የድርቅ መረጃ ጠቋሚ መድህን መሰረት ያደረገ ሰፊ ሽፋን በቆላማ አካባቢዎች ተግባራዊ ተደርጓል ።በርካታ የውሃ መሰረተልማት ግንባታዎች በአርብቶ አደሩ አካባቢዎች ተገንብተዋል፡፡

ምርታማነትን ከማሳደግ በተጨማሪ 500 ሺህ ሔክታር መሬት ከአንበጣ ወረራ ለማዳን ተችሏል፡፡ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በተለያዩ ዘርፎች ያለንን ትብብር አሳድጓል ሲሉ አብራርተዋል፡፡

ኢኒሺዬቲቩ ከአምስት ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የመጣውን ሪፎርምና በቀጣናው ሀገራት የተጠናከረ ግኝኙነት ተከትሎ የተመሰረተ፤ ዓላማው በቀጠናው ያሉ ሀገራትን በኢኮኖሚ ትብብር የሚያስተሣሥሩ የልማት ፕሮጀክቶችን መተግበር ነው።

የኢኒሺዬቲቩን መመስረት ተከትሎ የልማት አጋሮች በቀጠናው ለሚከናወኑ ፕሮጀክቶች ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛሉ ያሉት ሚኒስትሩ ኢኒሼቲቩ ኢትዮጵያን፤ ጅቡቲን ኤርትራን፣ ኬንያን፣ ሶማሊያን፤ ሱዳንንና ደቡብ ሱዳንን ያቀፈ ነው።

በቀጠናው የመሠረተ ልማት ትስስር ማጎልበት፣ የንግድና ኢኮኖሚ ውህደትን ማጠናከር፣ የተፈጥሮና ሰው ስራሽ ችግሮችን የመቋቋም አቅምን መገንባት እና የሰው ሃይል ልማትን የሚያጠነክሩ ቀጠናዊ ፕሮጀክቶች ይደገፉባታል።

የአለም ባንክ፤ አውሮፓ ህብረትና የአፍሪካ ልማት ባንክ እንዲሁም በተባባሪነት የሙሰሩና የኢጋድ ሴክሬታሪያት ከጥንስሱ ጀመሮ ሲደግፉ የነበሩ ናቸው። ኢኒሺዬቲሹ የጀርመንና የእንግሊዝ መንግስትን ተጨማሪ አጋር ሀገራት በማድረግ ተቀበሏል።

የ23ኛው የፋይናንስ ሚኒስትሮች ስብሰባ የካቲት 11 ቀን 2017 ዓም በአዲስ አበባ ለማካሄድ ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸዋል። በጉባኤው የአለም ባንክ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ፣ የጀርመንና የእንግሊዝ መንግስት ተወካዮች፣ የአረብ ባንክ፣ የአሜሪካ እና የኔዘርላንድስ መንግስት ተወካዮች በታዛቢነት ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል።

በዳግማዊት አበበ

የካቲት 4 ቀን 2017 ዓም




አፍሪካውያን እህት ወንድሞቼ እንኳን ወደ ውቢቷ አዲስ አበባ በሰላም መጣችሁ"
- የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር)
***
(ኢ ፕ ድ)

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) በአፍሪካ ኅብርት ጉባኤ ለመታደም ለመጡ የተለያዩ የአፍረካ ሀገራት መሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመልዕክታቸው፤ ከመላው የአፍሪካ ሀገራት የመጣችሁ እህት ወንድሞቼ የአፍሪካ ዲፕሎማሲያዊ መዲና ወደ ሆነችው ደማቅና ውብ ከተማ አዲስ አበባ እንኳን ደህና መጣችሁ ብለዋል። በጉባኤው ስኬታማ ውይይት እንዲያደርጉ ተመኝተዋል።

የካቲት 4 ቀን 2017 ዓም


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
"እንኳን ወደ ቤታችሁ በሰላም መጣችሁ"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
*
(ኢ
ፕ ድ )

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ወደ ኢትዮጵያ ለመጡ እንግዶች እንኳን ወደ ቤታችሁ በሰላም መጣችሁ ሲሉ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡

በመልዕክታቸው ኢትዮጵያ ለ38ኛው የአፍሪካ ኅብረት ጉባኤ እንኳን በደህና መጣችሁ ብላ ስትቀበል ሁሉም ተሳታፊዎች ኢትዮጵያን በእውነትም ምድረ ቀደምት ያደረጓትን የታሪክ ሀብቷን፣ ብዝኃነት የሞላውን ባሕሏንና አስደማሚ መልክዓ ምድሯን ለመመልከት ቆይታቸውን እንዲያራዝሙ አበረታታለሁ ብለዋል።

ከጉባኤው ባሻገር ከጥንታዊ የቅርስ ስፍራዎች እስከ ደማቅ ባሕሎች፤ አቻ የለሽ የተፈጥሮ ውበቶችን ጨምሮ ልታውቋቸው የሚገቡ ብዙ መዳረሻዎች አሉ ሲሉም ገልጸዋል።

#ኢትዮጵያ #ምድረቀደምት #AU_ #አፍሪካህብረት #ዲፕሎማሲ

የካቲት 4 ቀን 2017 ዓም



Показано 9 последних публикаций.