ስለ እውነት📢📢


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


ለአስታዬየት @zakiyo @silee_ewunet

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций


ሰዎች ያንተን ምንነትና ማንነት ሳይረዱ ህይወትን
በብዙ መንገድ ይተረጉሙታል ዝምታህን በፋራነት ቅንነትህን በሞኝነት ስለዚህ አንተ አንተ ብቻ ነህ ማንንም መሆንም መምሰልም አትችልም።

ንግግርህን ቆጥብ ብዙ ግን አዳምጥ
ወደድክ ጠላህም ተሳካልህም ወደክም ከሰዎች ትችት አታመልጥም አንተ ብቻ እግዚአብሔር ይቀበልህ ለሱ ንፁ ሁን እርሱ ለቅኖች ቅን ነው።

የሌሎች ስኬት ያንተ ህልም እንዳልሆነም እወቅ

አንተ ብቻ የምትፈልገውንን ለመሆን በቻልከው አቅም በደንብ ስራ ስራ ስራ እርሱ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው አትፍራ አትደንግጥ።

መፈለግህን ካላቆምክ መነካትህ የማይቀር ነው
የጊዜ ጉዳይ ነው።


@ewunetawu
@zakiyo




ተመስገን ነጋ 🌞🌞

ያለ ምክኒያት አይደለም አዲስ ቀን የተጨመረልን ዛሬን ሊያዩ የናፈቁ ግን ትላንት ላይ የቀሩ ብዙዎች ናቸው ታዲያ አንድ ቀን በእድሜያችን ሲጨመር ለክብሩ እንድንኖር በዞች ቀን እንድናመሰግነው አዲስ ቀን በተጨመረልን ቁጥር ተራ ህይወት ልንኖር አያስፈልገንም ለምን ነው ለኔ ዛሬ የተሰጠኝ ብለን ማሰብ አለብን እነዚህ ዛሬዎች ተደማምረው ነውና አመትን ዘመናትን የሚፈጥሩት ዛሬን ከተጠቀምንባት ነገአችን ያማረ ይሆናልና አሁናችንን ተራ ማሳለፍ የለብንም ክርስቲያን ለጨውነት እንጂ ለውሀነት አልተጠራምና የራሳችንን ህይወት ሳናጣፍጥ ወደ ሌሎች መጣፈጥ አንችልም ለዚህ ደግሞ እያንዳንዱ የተሰጡን ቀኖች ወሳኝ ናቸው እንጠቀምባቸው

Inbox @zakiyo
@ewunetawu


"ስጋ ደካማ ነው" ይሄ ለ ሀጢያታችን ማባበያ ሳይሆን ማስጠንቀቂያ ነው።🙂
@ewunetawu
@zakiyo


እምነታችን የሚወለደው የእግዚአብሔርን የፍቅር ልብና ለጋስ እጆች ከመመልከት ነው። እምነት ለራሳችን የምንሰጠው የተሳሳተ፣ ከፍ ያለ ግምት አይደለም። እንዲህ ዓይነቱ እብርይት የሚጋልበው ጸሎት፣ በእግዚአብሔር ዘንድ አፀያፊ ነው። የእግዚአብሔርን ቁጣ ከመቀስቀስ ውጪ፣ አንዳች ሰናይ ክትያ የለውም። የቅዱሳን እምነት የእግዚአብሔርን አባታዊ ፍቅር መሠረት ያደርጋል። ጸሎታችን እንዲህ ባለ እምነት ካልታጀበ አየር ላይ ይባክናል እንጂ ወደ ፈጣሪ ጆሮ አይገባም። እምነት የጎደለው ጸሎት ሰሚ በማጣት አየር ላይ ይንከራተታል። በጸሎት አንዳች ነገር ብንቀበል፣ ያንን ያስገኘልን እምነት ነው። ስለዚህ የሚለምን፣ “ሳይጠራጠር በእምነት ይለምን፤ ምክንያቱም የሚጠራጠር ሰው በነፋስ እንደሚገፋና እንደሚናወጥ የባሕር ማዕበል ነው። ያ ሰው፣ ከጌታ አንዳች ነገር አገኛለሁ ብሎ አያስብ።“ በእምነት የቀረበ ጸሎት ታላላቅ ነገሮችን ይከውናል። እግዚአብሔር እንዲህ ላለው ጸሎት፣ “በእኔ ተማምኖአልና አስጥለዋለሁ“ ሲል ይነሣል።
@ewunetawu
@ewunetawu
@zakiyo


Репост из: Aela Alessa
https://youtu.be/3cjmHxVsIws

ድንቅ የፋሲካ መዝሙር። ተመልከቱ፣ ሼር፣ ሰብስክራይብ አድርጉ። መልካም የፋሲካ/ትንሳኤ በአል! ተባረኩ!

https://youtu.be/3cjmHxVsIws


#ጉዞህን ቀጥል🚶‍♂️🚶‍♂️🏃‍♂️🏃‍♂️

የቢንቢ ልጅ የመጀመሪያ በረራዋን ስታደርግ ውላ ማታ ላይ ውሎዋን ስትናገር እማ ብታይ ሰዎች ሁሉ ሲያጨበጭቡልኝ፣ #ሲያጨበጭቡልኝ ዋሉ አለች። #ምስኪኗ ቢንቢ አላወቀች ሰዎች ሊያጨበጭቡላት ሳይሆን ሊገድሏት እየሞከሩ እንደሆነ።እንዲሁ አንዳንዴ በልባቸው ውድቀታችንን እየተመኙ ያጨበጨቡልን ሰዎች እያደነቁን መስሎን አሳባቸውን ልንስተው እንችላለን።ነገር ግን እውነታው ሌላ ነው። #አይደለንም እኛ እየሱስ ክርስቶስ እንኳን በዚች ምድር በነበረበት ሰዓት ያጋጠመው ነገር ነበር።"በጌታ ስም የሚመጣ ንጉሥ የተባረከ ነው፤ በሰማይ ሰላም በአርያም ክብር "እያሉ ጨርቃቸውን እያነጠፉለት በውርንጭላ ላይ አስቀምጠውት በክብር እና በሙገሳ ከተቀበሉት በኃላ መልሰው በዛ አፋቸው ይገደል፣ ይሰቀል እያሉ እየተጯጯሁ ወደ ጎልጎታ ተራራ ወስደውታል።
ነገር ግን እሱ ወደ እዚች ምድር የመጣበትን አላማ ጠንቅቆ ስለሚያውቅ የእነሱን ከበባና አጀብታ ከምንም አልቆጠረውም ነበር። #ምክንያቱም የመጣበት አላማ ግቡን መምታት ነበረበትና።ስለዚህም ከእየሱስ ሕይወት ብዙ መማር እንችላለን።
እናም አንባቢዬ ሆይ ለሕይወትህ እጅግ ጠቃሚ የሆነ ነገር ልነግርህ እፈልጋለው። #በዚች ምድር ላይ በምትመላለስበት ሰዓት ትኩረት ማድረግ የሚገባህ በተፈጠርክበት አላማ ላይ ነው እንጂ ሰዎች #በሚያዘንቡልህ ክብርና አድናቆት ላይ አይደለም።የሰዎች ድጋፍ እና ማበረታታት አያስፈልግም እያልኩህ አይደለም። #ነገር ግን የእነሱ ሙገሳ ከግብህ እንዳያስተጓጉልህ እና እንቅፋት ሊሆንብህ እንደማይገባ ላሳውቅህ እንጂ አንዲሁም የእነሱ ትችት፣ማንቋሸሽና ማጥላላት ፍፁም ከመንገድህ ሊያስቀርህ አይገባም። #እንዲያውም እልህና ወኔ በውስጥህ ሊጭርብህ ይገባል።
እነሱ የሚጠሉ እና የሚተቹ ወደው እንዳልሆነም ልትረዳ ይገባል አንተ #እነሱ መሆን የሚፈልጉትን ስለሆንክ እንጂ ጠላታቸው ሆነህ አይደለም ጠላታቸው አንተ ሳትሆን ራዕይህ ነው። #ቢሆንም ግን እመነኝ ማዕበሉ እና ወጀቡ እንዳለፈ ባህር ፀጥ ሲሉ ታያቸዋለ።
#አንድ መዘንጋት የሌለብህ ነገር ቢኖር ደግሞ አሸናፊዎች ትኩረታቸው ማሸነፍ ላይ ነው።ተሸናፊዎች ደግሞ ትኩረታቸው አሸናፊዎች ላይ ነው።ልዩነቱ እዚህ ጋር ነው።ስለዚህ ጉዞህን በፅናት ቀጥል!!!!




ከምታማኝ ቀርቤ ንገሬኝ
@zakiyo


#ይህንን_እናስብ!

ትልቅ መሆንን ስንመኝ ከትንሽመጀመርን አንጥላ
ተራራ ላይ መውጣቱን ስንፈልግ የጉርጏዱን ዘመን አንናቅ
የከፍታን ዘመን ስናስብ የዝቅታውን ህመም አንጥላ
ተፅኖ ፈጣሪነትን ስናልም የመናቅን ወራት አንግፋው
ሁሉም ትልቅ ህይወት ትንሽነት ነበረበት
ሁሉም ሜዳሊያ እያንዳንዱ ዋንጫ አድካሚና እልህ አስጨራሽ ሌሊቶችና ልምምዶች ነበሩት
የንጉሱ ልጆች በአጋጣሚ የማራቶን ሪከርድ የሰበረ የለም::
ልንገራችሁ ህመሙ :ድካሙ :አድካሚውና ተስፋ አስቆራጩ መንገድ ውስጥ ነውና ሜዳልያው :ዋንጫው :ፉጨት:ጭብጭጨባው እና ተፈላጊነቱ ያሉት .......አሁን የምታልፉበትን መንገድ አክብሩት::

@ewunetawu 👈join
@ewunetawu


ካለፈው #ስህተትህ ተማር ፥ የሚበጅህን #መዝን ያልተመዘነ ህይወት ትርጉም የለውምና ፥ አረማመድህን #መትር እግሮችህ በደመነነፍስ አይርገጡ። በዚኛው በአዲሱ በተሰጠህ ዘመን እንደ #ተርታው ሰው አታስብ ፥ አመለካከትህ ሳይለወጥ ዘመኑ ቢለወጥ በጳጉሜ 5 እና በመስከረም 1 መሀል ምንም ልዩነት አይኖረውም ከግርግር ፣ ከፌሽታ ፣ ከኪሳራ ውጪ። ከማሰብ መብላት መጠጣትን የህይወት ትርጉም ጣሪያ አድርገህ አትመልከት ፥ ቀን ቀን ነው ባይሆን በቀኑ #ታሪክ መስራት ነው ሲወርድ ሲዋረድ የመጣን ነገር በግርድፉ ከመቀበል ይልቅ። ከስሜት #አዋጅ ተላቀህ #ደስታን #ከአንዲት ቀን #ማዕቀፍ ውስጥ #አውጥተህ ለቀሪ #ዘመንህ ደስታ #መሥራት ፣ የበዓላት #ባሪያ ሳትሆን የአውዳመቶች #ገዢ ሁን ፣ #ከጊዜው ይልቅ #ጊዜውን አንተ #ግዛው ፡፡ #የድል ዘመኔ ነው ፥ #የከፍታ ዘመኔ ነው ፥ #የመሻገር ዘመኔ ነው ፥ #የመጠርመስ ዘመኔ ነው ከሚል #የምኞት አለም ውጣ። ነገርኩህ #አስተሳሰብህ ሳይለወጥ ምንም #ብታውጅ ህይወትህ #አይለወጥም ፣ ትርፉ ዕድሜ #መቁጠርና ኦክስጅን #ማጣበብ ብቻ ነው።



━━━━━⊱✿⊰━━━━━
♻️ @ewunetawu ♻️
🔱 @ewunetawu 🔱


እንኳን አደረሰህ/ሽ
አዲሱ አመት🌻🌻
🏵️ያቆምከውን/ሽውን የምትቀጥልበት/ይበት
🌼የምትቀጣጠልበት/ይበት
🏵️የምትጨምርበት/ሪበት
🌼ክርስቶስን ይበልጥ የምታውቅበት/ቂበት
🏵️ከእርሱ ጋር ፍቅር በፍቅር ምትሆንበት/ኚበት
🌼ከጓደኛ በላይ የቅርብህ የምታደርግበት/ጊበት
🏵️ሰማይ ሰማይ ምትሸትበት/ቺበት
🌼በየስፍራው አምላክህን ምታስቀድምበት/ሚበት
🏵️ያሸነፈህን/ሽን ምታሸንፍበት/ፊበት
🌼አልጋፋ ያለህን/ሽን ምትገለብጥበት/ጪበት
🏵️ተስፋ ማትቆርጥበት/ጪበት
🌼ካሰብከው/ሽው በላይ ምትከናወንበት/ኚበት
🏵️እንደ አንበሳ ሞገሳም የምትሆንበት/ኚበት
🌼እንደ ንስር ከፍ የምትልበት/ይበት
🏵️አለምን የምታስደምምበት/ሚበት
🌼ራዕይህን ምታሳካበት/ኪበት
🏵️ፍጥረት አፉን ከፍቶ ሚሰማህበት/ሽበት
😍ይሁንልህ/ይሁንልሽ😍
❤️ውድድድድድድድ…… አደርግሃለው/ሻለው❤️

🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
ይሄን የእንኳን አደረስዎ መልዕክት ቢያንስ ለሚወዱት 15 ሰው በማድረስ መልካም ምኞትዎን ይግለፁ።


━━━━━━✦✗✦━━━━━━━━━
⇲⇲⇲⇲ሼር ያድርጉ!! ⇲⇲⇲
አዘጋጅ፦
@ewunetawu
@ewunetawu
@ewunetawu
─── ❖ ── ✦ ── ❖ ───


#ባለራዕይ

✔ባለራዕይ ሰው ራዕዩ ላይ ለመድረስ ባይችልም እንኳ አይጸጸትም። ባለራዕይ ሰው ሌሎች ራዕዩን እንዲያዩለት ይጓጓል።

✔ባለራዕይነት መነሻ ላይ ሆኖ መድረሻን መመልከት ነው። ባለራዕይነት ሰው ሆኖ የተፈጠሩበትን አላማ ማውቅና አላማውን ለመተግበር በጽናት የሚከፈል መስዋዕትነት ነው።

✔በሕይወቴ ሁለት ቀኖችን አከብራለሁ አንደኛው ወደ ጌታ የመጣሁበትን ቀን ስሆን ሁለተኛው ለምን እንደተወልድኩ እና በክርስቶስ ኢየሱስ እኔ ማን እንደሆንኩኝ ደግሞ በዘመኔ ምን ሰርቼ ማለፍ እንዳለብኝ ያወኩበትን ቀን ነው ሃሌሉያ ክብር ለመንፈስ ቅዱስ ይሁን።

🇪🇹🇪🇹 ሀገሬ ኢትዮጵያ ውስጥ አንድ የትውልድን አእምሮ የያዘ ከርስ አለ በኢየሱስ ስም የተሰበረ ይሁን አሜን በፍጹም በዘመኔ አይቀጥልም ይህም ''ለምን እንደተወለድን ምን ለመስራት እንደመጣን ሳይሆን የተወለድንበትን ቀን ብቻ በየአመቱ እንቆጥረዋለን ግን እድሜያችን ምንም ሳንሰራ እንደጉድ እየሮጠ መሆኑን ማሰብ ዘንግተናል በተለይ ክርስቲያኖች እኛ።

✔ባለራዕይ መሆን የዛሬን መድከም ሳይሆን የነገን ስኬት ለማየት ያግዛል።

✔ ባለራዕይነት ማለት መጪውን ትውልድ በማሰብ ለመጪው ትውልድ መጨነቅንና ለመጪው ትውልድ የሚሆንና የሚጠቅም ነገር ከእግዚአብሔር ለመቀበል መፀለይ እና መስራትን በዚህም መደሰትን ይጠቁማል። ራዕይ ውስጥ ለመግባት ወይም ራዕይ ለመጀመር በዙሪያችን ያለውን ነገር ማየት የለብንም በፍጹም። አሜሪካን ያሉ ዘመዶችን ዱባይ ያሉ አክስትና እህት ቤተሰብ ውስጥ ያሉ ባለሀብቶችን ማየት የለብንም እነኝህን አይተን ራዕይ ከጀመርን አደጋ አለ። ምንም ነገር በእጃችን ባይኖርም ማንም ከጎናችን ባይሆንም ምንም ችግር የለውም እንደውም በጣም አሪፍ ነው ምክንያቱም እመነታችን በእግዚአብሔር ላይ ብቻ ይሆናል ደግመው እምነታችን በእግዚአብሔር ላይ ብቻ ከሆነ ማንም ከራዕያችን ወደኋላ ልመልሰን አይችልም።
ይቀጥላል ......

ቻናሉን ይቀላቀሉ
🔥🔥 @ewunetawu 🔥🔥
🔥🔥 @ewunetawu 🔥🔥
🔥🔥 @ewunetawu🔥🔥


👉“በአለም ላይ ያለዉ ጨለማ ሁሉ የአንዲት ሻማን ብርሃን ሊያጠፋ አይችልም!”

⩩ለምን አልክ ባትሉኝም እንግዲህ ማንም ያለ ተስፋ አልተፈጠረም ብዬ አላስብም፤
- ማንም እኔ ያለ ተስፋ ነው የተፈጠርኩት ቢል የእውነቴን ነው የምችሁ እየዋሸ ነው፣ ገና ምንም ሳናውቅ የእናታችንን ጡት የምንጠባው ተስፋ ስላለን ነው፣ የምን ብትሉኝ :- ምግብ የመመገብ ተስፋ፣ የማደግ ተስፋ፣ እንዲሁም ሌሎችም ነገር ግን የሚገርመው ነገር እኛ ሁላችን ከልጅነታችን የተሰጠንን ነጻ የሆነውን ስጦታ ተስፋችንን በቀላሉ ለመተው እንፈልጋለን ብዬ ብናገር አላፍርም ምክንያቱም በህይወታችን ውስጥ ማደግ በፈለግን ቁጥር ሊያሳድገን በሚመጣው ፈተና ውስጥ በገዛ ፈቃዳችን ገብተን ተስፋ የምንቆርጠው ነገር እንዳለ እኔ ብቻ ሳልሆን ሁላችንም የምንመሰከረው እውነት ነው። #እንዲህ አይደለም! እኔ የራሴ የሆነ ምክንያት አለኝ ብትሉኝም፣ ምክንያታችሁ እኔ ካነሳሁት ምክንያት ሊለይ የሚችለው ብዬ የማስበው ፈተናው ሳልፈልገው መጥቶ እኔን ስላደከመኝ ልትችሉ ትችላላችሁ፣ እንዲሁም ሌሎች መኖር እንዲያስጠላችሁ የሚያደርጓቸችሁ የራሳችሁ ምክንያት ሊኖራችሁ ይችላል።

እኔ ግን አንድ ነገር ልንገራችሁ ወርቅ ከእርሱ ጋር አብሮት ካለው አፈር ለመለየት ከፈለገ ግዴታ ወደ እሳት መግባት አለበት፤ ነገር ግን እሳቱ ያቃጥለኛል ብሎ አልነጠርም ቢል መፍቱ ነው ግን አብሮት ካለው አፈር ጋርም መኖር ግዴታው ነው።
ስለዚህ እኔም ለእናንተ ፈተና በዛብኝ፣ ተስፋም የለኝም ለምትሉ ሰይጣን ተስፋ ሳይኖረው ሰው ተስፋ ካስቆረጠ አኛ ተስፋ እያለን ለምን ተስፋ እንቆርጣለን።
የተስማማ ካለ እኔም አረጋግጥለታለው :- #“በአለም ላይ ያለዉ ጨለማ ሁሉ የአንዲት ሻማን ብርሃን ሊያጠፋ አይችልም!”
@silee_ewunet
@silee_ewunet
#ከወደዳችሁት ማንበብ አለበት ለምትሉት ስው ሁሉ SHARE ማድረሃችሁንም እንዳትረሱ

@ewunetawu
@ewunetawu


Anbibut




❗❗ onliy ለ ድላ ከተማ ለምገኙ ቅዱሳኖች ❗❗

ሰላም ለ እናንተ ይሁን የተወዴዳችው ውድ የ ስለ እውነት ግሩፕ አባላት እንድሁም በ ጌደኦ ዞን በ( ድላ ) ከተማ የምትገኙ የጌታ ብሩካኖች ሰላም ለ እናንተ ይብዛ ። 🙏🙏 በ መቀጠል በድላ ከተማ የምትገኙ ቅዱሳን ወጣቶች ተማርም ይሁን ሰራተኛ እንድሁም በየትኛውም እድሜ ክልል ውስጥ የምትገኙ ቅዱሳን በ ሆነ ሐሳብ ለመካፌል ወይም ለመወያዬት ስለምንፌልግ ቀጥሎ ባለው አድራሻ እንታናግሩን በ ጌታ ፍቃድ እንጠይቃለን 🙏🙏 ስልክ +25935163708 ወይም በ ቴለግራም ሊንክ @zakiyo አደራን የድላ ልጅ ከሆንክ/ሽ ኤሄን መልክት ብያስንስ ለ 10 ሰው ሼር አድርግ። ስላደሬጋችው የ ሰማይ አባታችን ይባርካችው።🙏🙏Ⓜ @silee_ewunet


​​የጣፈጠ ህይወትን ይፈልጋሉ?
❤❤❤❤❤❤❤❤❤
አንተ ልዩ ሆነህ የተፈጠርከው በፈጣሪ ፈቃድ ነውና ምንም ሳታማርር ህይወትህን ኑራት። ባለህ እየኮራህ ህይወትህን አጣፍጣት።
ሰዎችን ለመምሰልና የነሱ ግልባጭ ለመሆን አትጣር። የአንተ ንጹህና እጹብ ድንቅ ያልታየ ማንነት የሚወጣው በራስህ መተማመን፣መኩራትና እራስህን ማክበር ስትጀምር ነውና።

በዙሪያህ ምንም አይነት ዝነኞች ትልቅና ልዩ ሰዎች ቢኖሩም በአንተ ውስጥ ያለው ልዩ ስጦታ ግን ከሁሉም ይለያል!
ይልቃል! ይበልጣል!

እነዚህ ልዩ ያልካቸው ሰዎች በአፈጣጠራቸው የተለዩ ሆነው ሳይሆን ይህንን ምስጢር ስላወቁትና ስለተገበሩት ብቻ ነው ከሌሎች ተለይተው አሁን ያሉበት የደረሱት።

አንተም እንደነሱ የደረሱበት እንደውም ከነሱበላይ መስጠት መስራትና ማበርከት ከፈለክ ወደ እኔ ጠጋ በልና ጆሮህን ስጠኝ እኔም ሚስጢሩን ሹክ ልበልህ። ተጠጋኸኝ ልጀምር? "እራስህን ሁን! እራስህን አክብር!

እራስህን ውደድ!" እራስህን እንደማትወደው እንደማታከብረውና እንደማትሆነው ስታስብ ከማይመረመረው ከፈጣሪ እውቀት ጋ እየተደራደርክ ነውና ሁለቴ አስብ።

ሰዎች ከሚሉህ በላይም ፈጣሪ ሲፈጥርህም ምክንያት አለውና የሌለህን ትተህ ያለህን ዋጋ ስጥ። በሌለህ ነገር ስለምታገኘው ሳይሆን ባለህ ነገር ስለምትለውጠው ተመራመር።

በሌለህና ባልተጨበጠው ነገር ትልቅ ነገር ለመስጠት ከማሰብ ይልቅ ባለህ ነገር ትንሽ ነገር ለመስጠት ሞክር። ያኔ አንተ ውስጥ የተደበቀው ከሌሎች የተለየው ድንቅ ፍልቃቂ ማበብ ይጀምራል።

ብርሀንህ በዓለም ሁሉ ይሰፋል። ስምህም በሰዎች ልብ ውስጥ ይነግሳል።

በምድር ላይ በኖርክበት ዘመን ሁሉ ዘመንህ የጣፈጠ ይሆንልሀል።
━━━━━━✦✗✦━━━━━━━
❤❤❤❤❤❤❤❤❤
☑️ @ewuneta
☑️ @ewuneta


ወጣትነት ፋሽን ተከታይ ዘናጭ ተሽቀርቃሪ መሆን ማለት አይደለም! ወጣትነት ራስን በሱሶች ማጠር ማለት አይደለም! ወጣትነት በምክንያታዊነት ሳይሆን በስሜታዊነት እየተነዱ ራስንና ሌላውን አደጋ ውስጥ መዝፈቅ ማለት አይደለም! ወጣትነት ብዙ ጃንቦ የጠጣ ጀግና ማን ነው መባባል ማለት አይደለም! ወጣትነት ብረት ገፍቶ ደረትን ማሳበጥ ማለት አይደለም! ወጣትነት ሺሻ ቤት ተቀምጦ ጭስ ማቡነን ማለት አይደለም!
.
.
ወጣትነት በወሲብ ሱስ ከዚህም ከዚያችም ጋር በዝሙት ተወጥሮ መልከስከስ ማለት አይደለም! ወጣትነት በጥላቻ እና በዘረኝነት ተሞልቶ መታወር፣ መደባደብ እና መነታረክ ማለት አይደለም! ወጣትነት ተመልሶ የማይመጣውን ተፈጥሮ የሰጠችንን ታላቅ ሃይል በማይረባው ነገር ጊዜን ማቃጠል ማለት አይደለም! ወጣትነት ግዜያዊ ስሜትን ብቻ እያዳመጡ እንደፈረስ ጋሪ መነዳት ብቻ አይደለም! ወጣትነት በሀሜት፣ በአሉባልታ፣ በወሬ ሱስ፣ በአቃቂር፣ በተንኳሽነት፣ በቧልት መሞላት ማለት አይደለም!
.
.
ወጣትነት ይሄንንም ያንንም ይቺንም ያቺንም መጀንጀን መጀናጀን ማጀናጀን ማለት አይደለም! ወጣትነት በባዶ ጭንቅላት ምርጥ አልባሳትን ለብሶ እየተጀነኑ በባዶ ኩራት ተወጥሮ መሬትን ለመርገጥ እየተጸየፉ መራመድ ማለት አይደለም! ወጣትነት በግዴለሽነት፣ በተስፋ መቁረጥ፣ ከነፈሰው ጋር መንፈስ ማለት አይደለም! ወጣትነት በራስ ወዳድነት መንፈስ መወጠር እና እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል ማለት አይደለም! ወጣትነት በማይረባው በቀበሌኛው አመለካከት መታጠር ማለት አይደለም! ወጣትነት ቁንጫ የምታክል እውቀት በመያዝ ይቺ እውቀት ብቻ ትበቃኛለች እያሉ አጉል መመጻደቅ ማለት አይደለም...
.
.
ወጣትነት ባህር ነው። ወጣትነት ውቂያኖስ ነው። ወጣትነት አድማሰ ሰፊነት ነው። ወጣትነት እውቀትን ለማስፋት የምንጋደልበት ሰአት ነው። ወጣትነት በማስተዋል ብርሃን መሞላት ነው። ወጣትነት ችግር ፈጣሪነት ሳይሆን ችግር ፈቺነት ነው። ወጣትነት በዘረኝነት ተሞልቶ አማራ፣ ትግሬ፣ ኦሮሞ፣ ወላይታ...ቅብርጥሶ እየተባባሉ ቡድን በመስራት ስለ ቀበሌኛ አስተሳሰብ መስበክ ሳይሆን ወጣትነት ስለ ኢትዮጵያዊነት ከተቻለም አለም አቀፋዊ እይታን ማስፋት ነው።
.
.
ወጣትነት ፍቅርን እና አንድነትን መስበክ ነው። ወጣትነት በዝሙት ባህር መንቦራጨቅ ሳይሆን ስሜትን የመግዛት ጥበብ ማዳበር መቻል ነው። ወጣትነት ብርሃን ነው። ወጣትነት ተስፋ አለመቁረጥ ነው። ወጣትነት በቀናነት መሞላት ነው! ወጣትነት እስከመጨረሻው ጠብታ ህልምን ለማሳካት መፍጨርጨር ነው። ወጣትነት ማንበብ ነው ። ወጣትነት መጠየቅ ነው ። ወጣትነት ስለዓለም፣ ስለ ህይወት፣ ስለ ጥበብ፣ ስለ እውቀት ብዙ ለማወቅ መጠማት ነው ። ወጣትነት ለሌሎች መኖር ነው። ወጣትነት ለአገሬ ምን ልስራላት ብሎ ራስን መጠየቅ ነው። ወጣትነት ስለነገ ትልቅ ህልም እና እቅድ መሰነቅ ነው። ወጣትነት እሳት ነው። ወጣትነት ቤንዚል ነው። ወጣትነት ቅጠል ነው። ወጣትነት ጤዛ ነው። ወጣትነት ታክሲ ነው። ወጣትነት ምርጫ ነው። ወጣትነት በባህር ላይ ያለች ጀልባ መሆን ነው። ወጣትነት የመቶ ሜትር ሩጫ ያህል ነው። ወጣትነት ውስጥን ፈተናን ለማለፍ ማጀገን ነው። ወጣትነት ከፍርሃት፣ አልችልም እና አይሳካልኝም የሚለውን እስር በጣጥሶ ማለፍ ነው። ወጣትነት ለአንዳች ስኬት በኩራት እና በሞራል መራመድ ነው ...።
.
ምንጭ "ኤጭ" በአዘርግ @ewunetawu @ewunetawu @ewunetawu


📚ለኢየሱስ እና ለጸጋው እሺ በል

📖1 ቆሮንቶስ 1 (1 Corinthians)
30-31፤ ነገር ግን፡— የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ ተብሎ እንደ ተጻፈው ይሆን ዘንድ፥ ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥበብና ጽድቅ ቅድስናም ቤዛነትም በተደረገልን በክርስቶስ ኢየሱስ የሆናችሁ ከእርሱ ነው።

♦️ኢየሱስ ራሱ➡️ ጥበብህ ➡️ ጽድቅህ እንዲሁም➡️ ቅድስናህ ነው!
..✍እዚህ ጋ "ቅድስና" የተፈለጸው የግሪክ ቃል "ሀጊያስሞስ" የሚል ሲሆን መቀደስ ፥በረከት ለሚለው የተጠቀመው አንድ አይነት የግሪክ ቃል ነው።
👉ያ ማለት ቅድስናችን ወይም በረከታችን የተገኘው በኢየሱስ ነው። ስለዚህ ሃጥያትን እንድታደርግ የሚገፋፋህ ፥ የሚፈትንህ ንጹህ ያልሆኑ ሃሳቦች ሲኖሩህ ቆም በልና ወደኢየሱስ ወደ መስቀሉ ተመልከት።
☑እርሱ ለእርሷ ያለውን ፍቅሩን፥ምህረቱንና ጸጋውን ስተመለከት ፥ እርሱ በእያንዳንዱ ፈተና ፥ ሱስና እስራት ላይ ያንተ ድል መሆኑን ትገነዘባለህ!

✔ፈተና ሲገጥምህ ማድረግ ያለብህ ፈተናውን በቃ ማለት ነው ብለው የሚያምኑ ሰዎች አሉ።ነገር ግን ይህን ለማድረግ የፈቃድ ሃይልህ ከሀጥያት ጋር ስለማይመጣጠን በራስህ ጥረት እምቢ ለማለት ስትሞክር የባሰ ይሆናል። ይህ አይነት ችግር የገጠመው ሐዋርያው ጳውሎስ ራሱ ትግሉን 📖" ሮሜ 7፥19" ገልጾታል።

✍ስለዚህ የሚፈታተንህን እምቢ ለማለት መደገፍ ያለብህ በራስህ የፈቃድ ሃይል ላይ ሳይሆን በእግዚአብሔር ጸጋ ላይ ነው። ስለዚህ በትግልህና በፈተናህ መካከል ለኢየሱስ እሺ በል።

🗣 "ጌታ ኢየሱስ፣ ጽድቄ፣ ቅድስናዬና ቤዛዬ ስለሆንክ አመሰግንሃለሁ " በል። እያንዳንዱ ፈተና ጳውሎስ እንዳደረገው ኢየሱስን ለመመልከትና ለማክበር አድርገህ ለውጠው!

📖በሮሜ 7 (Romans)
24፤ እኔ ምንኛ ጎስቋላ ሰው ነኝ! ለዚህ ሞት ከተሰጠ ሰውነት ማን ያድነኛል?
25፤ በኢየሱስ ክርስቶስ በጌታችን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን። እንግዲያስ እኔ በአእምሮዬ ለእግዚአብሔር ሕግ፥ በሥጋዬ ግን ለኃጢአት ሕግ እገዛለሁ።

👉በሃጥያት ላይ ድል ስለማግኘት የጳውሎስ ጥያቄ "ማን ያድነኛል?" እንጂ "የትኛው ህግ ያድነኛል" አልነበረም።

☑የሃጥያት ነጻነት የሚገኘው በኢየሱስ ነው።እርሱ ጽድቅህ እና ቅድስናህ ነው።
🗣እሺ በለው!ድክመት እንዳለብህ በሚሰማህ ቦታዎች ላይ እንደሚገባ ፍቀድለትና የእርሱ ጸጋ ከውስጥ ወደውጭ ይለውጥህ።
==========================


@Ewunetawu
@ewunetawu


ነብይ T.B. Joshua እ.ኤ.አ June 12, 1963 እስከ June 5, 2021 ዓ.ም.

“በእውነት ጌታ እግዚአብሔር ምስጢሩን ለአገልጋዮቹ ለነቢያት ሳይገልጥ፣ ምንም ነገር አያደርግም።”
— አሞጽ 3፥7

እ.ኤ.አ. June 5 ,2021 (እ.ኤ.አ.) Emmanuel Tv እንደዘገበው ነቢዩ T.B. Joshua “ለሁሉም ጊዜ አለው እዚህ ለፀሎት ለመምጣትና ከአገልግሎት በኋላ ወደ ቤት ለመመለስ ጊዜ አለው”ብሎ ተናገረ ፡፡

እግዚአብሔር ባሪያውን ነቢይ T.B. Joshua ወደ ቤቱ ወስዶታል - እንደ መለኮታዊ ፈቃድ መሆን አለበት ፡፡ በምድር ላይ ያሳለፋቸው የመጨረሻ ጊዜያት እግዚአብሔርን በማገልገል ላይ ውለዋል። የተወለደው ፣ የኖረውና የሞተለት ይህ ነው ፡፡ነብይ T.B. Joshua “ሕይወትን ለመጠቀም ትልቁ መንገድ በሕይወት ከሚኖሩት ነገሮች ጋር ማሳለፍ ነው” ይላል ፡፡

የነብይ T.B. Joshua የመጨረሻ ቃላት እነሆ-“ነቅተህ ጸልይ”
ለክርስቶስ አንድ ሕይወት ያለን ሁሉ ነው።አንድ ሕይወት ለክርስቶስ በጣም የተወደደ ነው ፡፡

በአለም ዙሪያ ላሉ ክርስቲያኖች በሙሉ መፅናናት ይሁን😥🙏


ሰበር ዜና !

ናይጄሪያዊ አገልጋይ ቲቢ ጆሽዋ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

ናይጄሪያዊው ፓስተር ቲቢ ጆሽዋ በትላንትናው እለት በ57 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፤ በርካቶች በአገልጋዩ ህልፈት ድንጋጤውስ መግባታቸው ተሰምቷል።

በናይጄሪያ ከፍተኛ ተቀባይነት ያለው አገልጋይ ሲሆን ከመንፈሳዊ ስራዎች በተጨማሪ ለበርካቶች የረድኤት ድጋፍ በማድረግ ይታወቃል፤ ይህው አገልጋይ ዓመት በፊት ኮሮና ይጠፋል ሲል መናገሩ አይዘነጋም።

Показано 20 последних публикаций.

196

подписчиков
Статистика канала