ተአምረ ማርያም ✤የእመቤታችን ተአምር የሚነገርበት✤ የቅዱሳን ህይወት የሚተረክበት


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


... መሠረቶችዋ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው፡፡›› (መዝ.86 ፥ 1) 
----------------✤✤✤---------------
"እነሆም፥ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት
ይሉኛል፤ "የሉቃስ ወንጌል ፩:፵፰
-----------------✤✤✤-------------
ስለእመቤታችን ተዓምሯን አማላጅነቷን እና በአምላክ ዘንድ መመረጧን የሚነገርበት
አስታየት መልዕክት ካለ ይላኩልን፡፡

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций






ኩኑ እንከ ንፁሐነ ከመ አበው ቀደምት ኄራን ወማእምራን ወለባውያን ።
ወአዕትቱ እምኔክሙ እኩየ ሥርዓተ።ወሕሱመ ልማደ፡ ዳእሙ ኅረዩ ለክሙ ፍኖተ ሕይወት ።

ደጋጎች አዋቆችና አስተዋዮች እንደሆኑት
እንደቀደሙት አባቶች ንጹሐን ሁኑ።
ከእናንተም ክፉ ሥርዓትንና ክፉ ልማድን አርቁ።ነገር ግን የሕይወት ጎዳናን ለእናንተ ምረጡ እንጂ።
        
            (ዲድስቅልያ.፲፥፩)

@Ewntegna
@Ewntegna
@Ewntegna




Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram


ምኲራብ

አቢይ ጾም ከገባ አሁን ሦስተኛው ሳምንት ላይ ደርሰናል። ይህ ሶስተኛው ሣምንት ደግሞ ስያሜው ምኲራብ ተብሎ ይጠራል ምኲራብ የተባለበትም ምክንያት ጌታችን ከምኩራብ ገብቶ ማስተማሩ ድውያንን መፈወሱ እና በምኲራብ የተለያዩ ተአምራቶችን ማድረጉ የሚነገርበት ሳምንት በመሆኑ ነው።
ምኲራብ
ምኲራብ የስሙ ትርጉም እንደ ኮረብታ እንደ ተራራ ያለ ታላቅ ህንፃ ቤት ማለት ነው።
መንፈሳዊ ትርጉሙም የጸሎት ቤት ማለት ነው ።
በዚህም አይሁዳውያን እየተሰባሰቡ 🙏ጸሎት ያደርሳሉ። ሕገ ኦሪቱን ይማራሉ ትንቢተ ነቢያትን ይሰማሉ። ምኲራብ ዋና አገልግሎቱም መንፈሳዊ ነገር ብቻ የሚከናወንበት እግዚአብሔር የሚመለክበት ነው። በዘመኑ የነበሩ የምኲራቡ ሹማምንት ግን ይህን መንፈሳዊ አገልግሎት ቸላ በማለት ለመንፈሳዊ ነገሮችም ግዴለሽ በመሆን። የጸሎት ቤት እና የአምልኮ ሥፍራ የሆነውን ይህን ምኲራብ የገቢያ ቦታ አደረጉት ።
እግዚአብሔርን ሣይሆን ገንዘብን ፈለጉበት።
ለእግዚአብሔር ትተው ለገንዘብ ተሯሯጡበት።

በዚህ የተነሣ ጌታ ወደምኲራብ በመግባት በምኲራብ የሚሸጡትን የሚለውጡትን በጅራፍ እየገረፈ ከምኩራብ አስወጣቸው። እንዲህም አላቸው “ርግብ ሻጪዎችንም፦ ይህን ከዚህ ውሰዱ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት አላቸው።”ዮሐንስ 2፥16
ምክንያቱም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእሱ የመጀመርያ የሆነውን ታላቁን የፋሲካን በዓል ለማክበር ወደኢየሩሳሌም ከወጣ በኋላ አገልጋዮቼ ካህናት እንዴት ናቸው? መስዋዕት እየሰው ነው ወይ፣ ጸሎትስ እያደረሱ ነውወይ፣ ሕዝቡንስ እየባረኩ እያስተማሩ ነው ወይ? በትንቢት የናፈቁኝ በሱባኤ የጠበቁኝ እኔ ሥጋ ለብሼ እነሱን ተዛምጄ ወደ እነርሱ ወደ ወገኖቼ መጥቻለሁና እስኪ ካህናቱን ልያቸው ብሎ ወደ ምኲራብ ገባ።

ወደ ምኲራቡ ገብቶ ያገኘው ግን ሊደረግ ቀርቶ ሊታሰብ እንኳ የማይገባውን ነውር ነበር።
ካህናቱ ሲያስተምሩ ሕዝቡም ቁጭ ብለው ሲማሩ፣
ኦሪቱ ሲነበብ ሕዝቡም ጸጥ ብለው ሲሰሙ፣
ካህናቱ ሲባርኩ ሕዝቡም ተባርኮ ጌታ ሆይ አንተ ታውቃለህ? እያሉ የውስጣቸውን ለአምላክ አደራ ሲሉ አይደለም። ይልቁንም አገልጋዮች ለዋጮች ሆነው፣ ተገልጋዮች አስለዋጮች ሆነው እና
መቅደሱም የገበያ ማእከል ሆኖ ነበር ያገኘው።
ጌታም የጸሎት ቤቱ የገብያ ማእከል ሲሆን አልታገሰም።
በመቅደስም በሬዎችንና በጎችን ርግቦችንም የሚሸጡትን ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው አገኘ፤
የገመድም ጅራፍ አበጅቶ ሁሉን በጎችንም በሬዎችንም ከመቅደስ አወጣቸው፥ የለዋጮችንም ገንዘብ አፈሰሰ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፥ርግብ ሻጪዎችንም፦ ይህን ከዚህ ውሰዱ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት አላቸው።ዮሐንስ.2፥14-16 ሁሉንም ግልብጥብጡን አወጣው ገለባበጠው።

አዎ ስለ መቅደሱ የሚጨነቅ የመቅደሱ ባለቤት ነው ስለልጅ የሚጨነቅ የወለደ ነው እንደሚባለው። የእግዚአብሔር መቅደስ የከብቶች ገብያ እና የለዋጫች መፈንጫ ከሆነ ሰነባብቷል። አማናዊ የእግዚአብሔር መቅደስ ሰውነታችን የእንስሳዊ ጠባይ ከተላበሰ ቆይቷል። እንደ እንስሳም ሆኖአል።እንስሳ ሲነዱት የት ልትወስዱኝ ነው ብሎ አይጠይቅም። ሰውም እንደ እንስሳ ሊታረድ ወደሞት እየሄደ የት ነው? ብሎ የማይጠይቅበት ዘመን ነው። ።እንስሳ የሚኖረው ለሥጋው ነው ።ሰውም የሚኖረው ለሥጋው ብቻ ሆኗል ። እንስሳ የዘወትር ሐሳቡ ሆዱ ነው ።ሰውም የነፍሱን ነገር ረስቶ ለሆዱ የሚተጋበት ዘመን ነው ።

እግዚአብሔር ዛሬም ቤቴ የጸሎት ቤት ነው ይላል ።
እናንተ ካህናት እየሰማችሁ ነው? ቤቴ የጸሎት ቤት ነው ። አትለዋወጡበት፣ አትጨቃጨቁበት፣ አትካሰሱበት፣ ጉቦ አትብሉበት፣ አትቀልዱበት የቅጥር መሥሪያ ቤት አታድርጉት። ተቀጣሪ አትሁኑ አገልጋዮች ሁኑበት እንስሳትን አስወጥታችሁ ጸሎት ሰአታት ኪዳን አድርሱበት። እግዚአብሔርን ፈልጉበት ገንዘብን አትፈልጉበት የእግዚአብሔር ቤት ባንክ ቤት አይደለምና። ቤቴ የጸሎት ቤት ነው።ዮሐንስ.2፤16

እናንተም ምዕመናን እየሰማችሁ ነው ?
ቤቴ የጸሎት ቤት ነው ።
ዝሙት አትስሩበት፣ አትጋደሉበት፣ አትጣሉበት፣ ቂም አትያዙበት፣ በቀል አትቋጥሩበት፣ ቤቴን አታርክሱት፣
ዘር አትቁጠሩበት፣ ጭፈራ ቤት አታድርጉት ግሮሰሪ አታድርጉት ቤቴ የጸሎት ቤት ነው ። እናንተ የእግዚአብሔር መቅደስ ናችሁ። " ወይስ ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ።
(1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6:19-20)

ቤቴ የጸሎት ቤት ነው 🙏
መልካም የጾም ሳምንት

✍️Ermi

@Ewntegna
@Ewntegna
@Ewntegna


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram


ሰቆ ኤርምያስ.3፥40: ኖን።

መንገዳችንን እንመርምርና እንፈትን፥ ወደ እግዚአብሔርም እንመለስ።

41: ልባችንን ከእጃችን ጋር በሰማይ ወዳለው ወደ እግዚአብሔር እናንሣ።

@Ewntegna
@Ewntegna
@Ewntegna


ብዙ ወዳጆችን ቀየርን እግዚአብሔርን ግን የሚተካ አላገኘንም።
ብዙ ደጆች ደርሰን ስንመለስ ተዘጉ። እግዚአብሔር ግን በእኛ ላይ በሩን አልዘጋም። በወረቀት ፍቅሩን የሚገልጽልን ወዳጅ አጥተን ተቸግረናል።

በደም ነጠብጣብ እወዳችኋለሁ የሚለንን ውድ ጌታችንን ግን አጊንተናል ።
ቸሩ መድኃኔዓለም የወደደን ዋጋ ሊከፍሉት በማይቻል ውድ ዋጋ በደሙ ነው።

@Ewntegna
@Ewntegna
@Ewntegna


"አቤቱ አንተን ብቻ ያዩ ዘንድ ውሳጣዊ የዕውቀት ዐይኖችን ስጠን"

        (ቅዳሴ እግዚእ)

@Ewntegna
@Ewntegna
@Ewntegna


🎉የምስራች አሁን online ላላችሁ ብቻ ጥያቄ ና መልስ ልንጀምር ነው

1 ለወጣ 500 ብር ካርድ  💵
2 ለወጣ 250 ብር ካርድ 💵
3 ለወጣ 150 ብር ካርድ 💵

👉 ዝግጁ ከሆናችሁ 💸 START 💸 የሚለውን ይጫኑ 👇


ከ17 ደቂቃ ቦኃላ ይጠፋል


የ 200 ብር ካርድ የሚያስሸልም ጥያቄ!

በኢትዮጵያ በጣም አስቸጋሪ የነበረዉ  ረሀብ መች አመተምህረት ነበረ


❤️“ ንዑ ንትመሀር ልሳነ ግእዝ ”
🔅ኑ የግእዝ ቋንቋ እንማር🔅

📜 የሀገራችን የኢትዮጵያ ቀዳማዊና ጥንታዊ ስለሆነው የግእዝ ቋንቋ መሠረታዊ ትምህርት እንሰጣለን። እርስዎም አባቶቻችን ያቆዩልንን ቋንቋ በመማርና ለትውልድ በማስተላለፍ ኃላፊነትዎን ይወጡ!
📜


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም
የእመብዙኃን ቤዛዊት ዓለም ፍቅር
በሊቃውንት ዘንድ እንዲህ ነው 👇

👉ሊገለጽ የማይችል ረቂቅ ነው
    ከቃልም በላይ ነው ❤️

ልግለጸው እንኳን ቢባል ከፍቅር ጽናት የተነሣ ዕንባ ይቀድማል 😭 ።

ለዚህም ነው ሊቃውንት አባቶቻችን ስለእመቤታችን ሲጠየቁ ዕንባ 😭 የሚቀድማቸው። የእመቤታችንን ፍቅር በቃል ሳይሆን በእንባ የሚገልጹት።
ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬምም በማክሰኞው  ውዳሴ ማርያም 👇

የአብ ቃል እናቱ ንጽሕት ድንግል ሆይ
ስለአንቺ የሚነገረውን ነገር መናገር የሚቻለው ምን አንደበት ነው በማለት
የተናገረው ። ❤️❤️❤️❤️❤️

ድንግል ሆይ ፍቅርሽ በልባችን
ጥዑም ምስጋናሽ በአንደበታችን
ህያው ሆኖ ለዘለዓለም ይኖር ዘንድ
ሰዓሊ ለነ ቅድስት ❤️❤️❤️❤️
🙏🙏🙏🙏🙏❤️❤️❤️❤️
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
@Ewntegna
@Ewntegna
@Ewntegna


👉   ክብር

ክብር ላከበሩን እስካሁንም ላስከበሩን በደምና በአጥንት ለገነቡን ደማቸውን አፍሰው ላለመለሙን
ጀግኖች፣ አርበኞችና አይበገሬዎች አባቶቻችን ይሁን🙏


በዓለም ካሉት ሃይማኖቶች ሁሉ የምትገፋና መከራ የሚበዛባት ሃይማኖት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ናት። እንደዚሁም ሁሉ በዓለም ካሉት ሐገሮች ሁሉ በተለያዩ ሴራዎች የምትናጥ ሐገር ብትኖር ኢትዮጵያ ናት።

ዲያብሎስ አቅም ቢያገኝ ማጥፋት ሚፈልገው ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖትን ብቻ ነው። ሌላው ግን ስለተስማማው ጠፋ አልጠፋ ግዴታው አደለም።

ዓለምም ቢችል በአንድ ቀን ጸጥ ማድረግ የሚፈልጋት ሐገር አለች እስዋም የምስራቋ ኮከብ፣ የድንግል የአሥራት ሐገር፣ የሆነች የፈጣሪ ገጸ በረከት ኢትዮጵያ ናት ።

ለዛም ነው በእየ ጊዜው መንገድ እየቀያየሩ የተለያዩ ሴራዎችን በመጠንሰስ ሐገሪቷን እረፍት የነሷት።
እግዚአብሔር ግን በቸርነቱ እስካሁን ጠብቆ አኑሯታል ምንም የውስጥ ችግር ቢፈጠርም ለጠላት ግን አሳልፎ አልሰጣትም። ችግሩንም የኛ የአስተሳሰብ ድክመት፣ በደል ያመጣው እና የጠባብ ርዮት ያላቸው አዋቂነን ባዮች ያመጡት ነገር ነው እንጂ እግዚአብሔር ሕዝቡን ጠልቶት አይደለም ችግር የመጣው ። 

ይህስ ለምንድን ነው እንዲህ የሚያደርጉት ካልን በአድዋ የሽንፈትን ጽዋ ስለተጎነጩ  እና። የአሰቡት ቀርቶ ያላሰቡት ነገር ስለመጣባቸው ነው። ለዛም ነው ዳግም አርባ ዘመን ቆይተው የበለጠ ተጠናክረው የመጡት ባይሳካላቸውም። መቼም አይሳካላቸውም 💪 አድዋ
                         👉   ይህ አድዋ

ይህ አድዋ ለነጭ ሐሣር ለጥቁር ክብር ነው።በሰማይም በምድርም በተለያዩ ብረት ለበስ የጦር መሳሪያ ታጅቦ በእብሪት የመጣውን የእብሪተኛውን ጣሊያን ትዕቢት አስተንፍሰው ምንም ዘመናዊ የጦር መሣሪያ ሳይኖራቸው

በእግዚአብሔር ኃይል በድንግል አማላጅነት በቅዱስ ጊዮርጊስ ተራዳኢነት ታቦት ይዘው ዘምተው ጸሎት አድርገው ኪዳን አድርሰው
ኃይል የእግዚአብሔር ነው።
ማዳን የእግዚአብሔር አንመካም በጉልበታችን። እግዚአብሔር ነው የእኛ ኃይላችን። ብለው ዘምረው በጽናት ተዋግተው እኛ ልጆቻቸው ተሸማቀን በባርነት አንገት ደፍተን እንዳንኖር የደምና የአጥንት ዋጋ ከፍለው ለጥቁር ሁሉ የነጻነትን ፋና አባቶቻችን የአበሩበት ቀን ነው።
                    👉   አድዋ

የኢትዮጵያ የድል ገድል የአፍሪካ የነጻነት አክሊል ነው ።
ይህ አድዋ የኢትዮጵያ ኩራት የአፍሪካ ነጻነት ነው ።
ይህ አድዋ የነጭን ታሪክ ያጠቆረ
የጥቁርን ታሪክ በጉልህ አንጽቶ ያሳየ ነው ።
ይህ አድዋ ትቁሮችን ሲያነጻ ነጮችን ያጠቆረ የሽንፈት ጥላሸት የቀባ ግዙፍ ታሪክ ነው ።

ይህ አድዋ የዓለምን ፍልስፍና ውድቅ አደረገ።
ይህ አድዋ የዓለምን ፖለቲካ በደቂቃ ውስጥ ቀየረ።
ይህ አድዋ የዓለምን ፍልስፍና አልፈሰፈሰ።
ይህ አድዋ አፍሪካን ቀና አውሮፓን ዝቅ አደረገ።

                            👉በአድዋ

የባርነት ቀንበር ያጎበጠው ጀርባ ሁሉ ቀጥ አለ።
በጥቁርነቱ ተሸማቆ ባርያ ነኝ ሲል የነበረው ሁሉ እኔ ጥቁር ነኝ ግን ውብ ነኝ ማለት ጀመረ
የነጭ ሞተ ኩነኔ የተፈረደባቸው ሁሉ ነጻ ወጡ።

አፍሪካ ከአድዋ በፊት ለዜጎችዋ ባቢሎን ሆና የመከራ ምድር ነበረች ከአድዋ በኋላ አፍሪካ ከነዓን ሆናለች።

ክብር ወድቀው ላነሱን አባቶቻችን 💪
ክብር ሙተው ላኖሩን አርበኞቻችን💪
ክብር ኮርተው ላኮሩን ኩሩዎቻችን💪
ክብር ከብረው ላስከበሩን ጀግኖቻችን 💪
ክብር ድል አድርገው ድል አድራጊነትን ላወረሱን💪 የኢትዮጵያ ሐገራችን ባለውለታዎች ሁሉ ይህንልን።💪

ermi  ✍️ የካቲት.23/2017

@Ewntegna
@Ewntegna
@Edntegna


Репост из: ࿇EL҉O҉H҉E҈ P҉I҉C҉T҉U҉R҉E҈S҉࿇
✨ ELOHE PICTURE

እምኵሉ ዕለት ሰንበት አክበረ
ወእምኵሉን አንስት ማርያምሃ አፍቀረ


♡ ㅤ  ⎙ㅤ    ⌲        ✉️    Lᶦᵏᵉ   ˢᵃᵛᵉ    ˢʰᵃʳᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ
ቶሎ ቶሎ እንድንለቅ ሪያክሽን እንዳይረሳ ❤️
     ➪ ꌗꃅꍏꋪꍟ ꌩꂦꀎꋪ ꎇꋪꀤꍟꈤꀸ

🔻🔻ይቀላቀሉን 🔗🔗⏰
https://t.me/+Ci5F1FcleWtlZThk


Репост из: ࿇EL҉O҉H҉E҈ P҉I҉C҉T҉U҉R҉E҈S҉࿇
እንኳን ለኢትዮጵያ ጠባቂ ለአድዋው አርበኛ፣ ለፍጡነ ረድኤት፣ ለገባሬ ተአምር ሊቀ ሰማዕታት ለቅዱስ ጊዮርጊስ በ1888ዓ.ም በአድዋ ጦርነት ንጉሠ ነገሥትን ምኒልክና ሰራዊቱ ለረዳበት፤ ኢትዮጵያ በሮማውያንን (ጣልያንን) ድል ለተቀዳጀችበት ለ128 (ለአንድ መቶ ሃያ ስምንተኛው) ለአድዋ በዓል በሰላም አደረሰን።


Репост из: ࿇EL҉O҉H҉E҈ P҉I҉C҉T҉U҉R҉E҈S҉࿇
🌟 ELOHE PICTURE

ድል መንሳት በእግዚአብሔር ኃይል ነው

👍ㅤ  ➡️ㅤ          💬 Lᶦᵏᵉ   ˢᵃᵛᵉ      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ
ቶሎ ቶሎ እንድንለቅ ሪያክሽን እንዳይረሳ
   😍 ➪ ꌗꃅꍏꋪꍟ ꌩꂦꀎꋪ ꎇꋪꀤꍟꈤꀸ

🔻🔻ይቀላቀሉን 🔗🔗⏰
https://t.me/+Ci5F1FcleWtlZThk


Репост из: ࿇EL҉O҉H҉E҈ P҉I҉C҉T҉U҉R҉E҈S҉࿇
🌟 ELOHE PICTURE

አድዋ



👍ㅤ  ➡️ㅤ          💬 Lᶦᵏᵉ   ˢᵃᵛᵉ      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ
ቶሎ ቶሎ እንድንለቅ ሪያክሽን እንዳይረሳ
   😍 ➪ ꌗꃅꍏꋪꍟ ꌩꂦꀎꋪ ꎇꋪꀤꍟꈤꀸ

🔻🔻ይቀላቀሉን 🔗🔗⏰
https://t.me/+Ci5F1FcleWtlZThk


-|- ቅድስት -|-

ታላቁ ጾም ከገባ አሁን ሁለተኛ ሳምንታችንን ይዘናል።
ስለዚህ ይህ ሁለተኛው ሳምንት ደግሞ
እንደቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ቅድስት በመባል ይታወቃል። እንግዲህ ቅድስት ማለት የስሙ ትርጓሜ
የተለየች የከበረች የተቀደሰች ማለት ነው። ይህች ሳምንትም ቅድስት የተባለችበት ዋና ምክንያትም " ለእስራኤል ልጆች ማኅበር ሁሉ እንዲህ በላቸው። እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ቅዱስ ነኝና እናንተ ቅዱሳን ሁኑ።"(ኦሪት ዘሌዋውያን 19:2) በማለት የተናገረ ቅድስና የባህርይ ገንዘቡ የሆነ ጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ ከጠገለጠ በኋላ በሰላሣ ዘመኑ በእደ ዮሐንስ ተጠምቆ ሳይውል ሳያድር ገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ ከዘረጋ ሳያጥፍ ከቆመ ሳይቀመጥ ከአራዊትጋር እየተጋደለ። (ማር.1፥13) የጾማት ልዩ እና ክብርት ከሁሉም አጽዋማት በአጿጿምም በቁጥርም ላቅ ያለች ጾም ስለሆነች ቅድስት ተብላለች።

ስያሜውንም የሰጣት በዚህ በታላቁ ጾም ውስጥ ለሚገኙት ሰንበታት ስያሜ እየሰየመ እግዚአብሔርን በጥዑም ዜማ ሲያመሰግን የነበረው የቤተክርስቲያናችን ሊቅ የሆነ ቅዱስ ያሬድ ነው።
በዚች ልዩ ጾም ደግሞ የሰውንልጅ ለውድቀት የዳረጉ፣ የሰውልጅ የሕይወቱ መቀርሳ የሆኑ፣ ሰውን ከእግዚአብሔር የለዩ፣ የዲያብሎስ ተክሎች የሆኑ ሦስቱ የኀጢአት ሥሮች ከስር ተነቅለው ወድቀዋል።
እነዚህም ሦስቱ የኃጢአት ሥሮች የሚባሉትም
ስስት
ትዕቢት
ፍቅረንዋይ ናቸው
በእነዚህም ቀዳማይ አዳም ድል ስለተደረገባቸው ዳግማዊ አዳም የአዳምን አካሉን አካል አድርጎ ሰውሆኖ እንደሠው ምንም ኃጢአት ሳይኖርበት ገዳም ገብቶ በመጾም ፈታኝም ቀርቦ እስኪፈትነው ድረስ በመታገስ
ስስትን በትዕግስት
ትዕቢትን በትህትና
ፍቅረ ንዋይን በጸሊዓ ንዋይ ድል አድርጓቸዋል።

የመጀመርያው ስስት ነው

ስስት የመጀመርያው ኃጢአት ነው ስስት ያልተሰጠውን መፈለግ ነው ስስት በቃኝ አለማለት ነው ስስት የራስን ትቶ የሰውን መመልከት ነው። ለአዳም አባታችን ያልተሰጠው ነገር የለም። ወይም ከተሰጠው ነገር ሁሉ ያነሰው ነገር ወይም የጎደለው ነገር የለም። ቢፈልግ ሚበላው ቢፈልግ ሚጠጣው ቢፈልግ ሚለብሰው ቢፈልግ ሚነዳው ቢፈልግ ሚገዛው በቃ ምን ልበል ይህ ነው ተብሎ ተዘርዝሮ የማያልቅ ጸጋ ነው የተሰጠው። አዳም ግን በተሰጠው መኖር ትቶ የጎደለው ነገር ያለ ይመስል ሳሳ ስስት አደረበት። የአባቱን የእግዚአብሔርን ቃል ትቶ የጠላቱን ቃል መስማት ጀመረ ሰምቶም አልቀረ አደረገው።

በዚህም የነበረውን ሁሉ አጣ። የቆጡን አወርድ ብላ የብብቷን ጣለች እንደሚባለው የባህርይ አምላክነትን ሲመኝ የጸጋውን አጣ። ባዶውን ሆነ ባዶውን ቀረ ያኔ ያሳሳተው ሰይጣን እንኳ ለማጽናናት አጠገቡ አልተገኘም። ምን አገኘህ ብሎም አላዘነለትም። ሲያለቅስም ሶፍት አላቀበለውም። ስራውን ሰርቶ እቅዱን አሳክቶ ተሰውሯል እንጂ የለም። አዳምን ስስት ባዶውን አስቀረው ስስት ከጌታው ለየው ስስት አምላክነትን አስመኘው ይህን ስስት ሊሽረው አልቻለም በዚህ ምክንያት ጌታው መጥቶ ስስትን በትእግስት ድል አደረገው። መብላትን ባለመብላት መፈለግን በአለመፈለግ ሻረው። ሰው የሚኖረው በእንቸራ ብቻ አደለም በእግዚአብሔር ቃል ነው በማለት ድል አድርጎ (ማቴ .4፥4) እኛም ልጆቹ ድል የምናደርግበትን ጾም ሰጠን " ይህ ዓይነት ግን ከጸሎትና ከጾም በቀር አይወጣም አላቸው።"
(የማቴዎስ ወንጌል 17:21)

ሁለተኛው ትዕቢት ነው

ይህስ እንደምነው ካልን አዳም አባታችን አትብላ የተባለውን ዕጸበለስ በማን አለብኝነት ተነሣሥቶ በመብላ አምላክነትን ተመኘ። የሌለውን አምላክነት ወይም ሊገባው የማይቻለውን አምላክነት መመኘት አምላክ ነኝ ማለት በራሱ ኃጢአት ነውና ። ይህም ትዕቢት ነው። አምላክ ባይሆኑም እኔ አምላክ ነኝ ከሁሉ በላይ ነኝ በማለት የወደቁ ብዙ ናቸው።
መጽሐፍ እንዲህ ይላል " የሰው ልጅ ሆይ፥ የጢሮስን ገዥ እንዲህ በለው። ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ልብህ ኰርቶአል አንተም። እኔ አምላክ ነኝ፥ በእግዚአብሔር ወንበር በባሕር መካከል ተቀምጫለሁ ብለሃል፤ ነገር ግን ልብህን እንደ እግዚአብሔር ልብ ብታደርግም አንተ ሰው ነህ እንጂ አምላክ አይደለህም። "
(ትንቢተ ሕዝቅኤል 28:2) እንዲሁም "ልቡ ግን በታበየ በኵራትም ያደርግ ዘንድ መንፈሱ በጠነከረ ጊዜ፥ ከመንግሥቱ ዙፋን ተዋረደ፥ ክብሩም ተለየው። "
(ትንቢተ ዳንኤል 5:20)

ምክንያቱም ትዕቢት መጥፎ ነው ። ትእቢት የሰውን ልጅ ከነበረበት ክብር አውርዳ በውርደት ትፈጠፍጠዋለች ትዕቢት ሰውን አውሬ ታደርገዋለች ። ትዕቢት አምላክ እሆናለሁ ማለት ነው ።ትዕቢት አምላክነትንም መፈታተን ነውና። ስለዚህ ጌታችን ትዕቢትን በትህትና ድል አድርጓል። ኢየሱስም፦ ጌታን አምላክህን አትፈታተነው፡ ተብሎ ደግሞ ተጽፎአል፡ አለው። (ማቴዎስ.4፥7)
አዳምም አምላክነቱን በመፈታተኑ ወደቀ ጌታም ይህን አዳም ሊፈጽመው ያልቻለውን ትህትና የአዳምን ሥጋ በመልበስ ትዕቢትን በትህትና ድል አደረገ። " እንግዲህ ትህትናን፥ የዋህነትን፥ ትዕግሥትን ልበሱ።"
(ወደ ቆላስይስ ሰዎች 3:12)


ሦስተኛው ፍቅረንዋይ ነው

ፍቅረንዋይ ገንዘብን መውደድ ነው
ፍቅረንዋይ ይህን አለም መውደድ ነው። ፍቅረንዋይ ሥልጣን መውደድ ነው። ፍቅረንዋይ ለዓመፅ መገዛት ነው። ፍቅረንዋይ ከንቱ ነገርን መከተል ነው ፍቅረንዋይ ከጌታ ትዕዛዝ መሹለክ ነው። ፍቅረንዋይ እርም የሆነውን ነገር መውሰድ ነው። ፍቅረንዋይ ሰማያዊውን አለም በምድራዊው ዓለም መተካት ነው። ፍቅረንዋይ ጌታን መሸጥ ነው። ፍቅረንዋይ እንደ ዴማስ ሆዴ ይሙላ ደረቴ ይቅላ ብሎ ወደኋላ መመለስ ነው ። ፍቅረንዋይ ለሁለት ጌቶች መገዛት ነው (ማቴ.6፥24) ስለዚህ ከፍቅረ ንዋይ ተአቀቡ። " አካሄዳችሁ ገንዘብን ያለ መውደድ ይሁን፥ ያላችሁም ይብቃችሁ፤
(ወደ ዕብራውያን 13:5)

የአዳም ፍቅረንዋይ የሰማዩንም የምድሩንም ሐብት ገንዘብ ማድረግ ነበር አልተሳካም እንጂ። እንኳን ሊሳካ የነበረውንም አላገኘውም በዚህ በፍቅረንዋይ ድል ለተነሣው አዳም ክርስቶስ በጸሊዓንዋይ ገንዘብን በመጥላት ድል አድርጓል። አሁን በስስት በትዕቢት በፍቅረንዋይ ድል የምንነሣው (ጠበቅ) እኛ ወደን ፈቅደን እንጂ እኛ እጅ ካልሰጠን በነዚህ በሦስቱ አርዕስተ ኀጣውዕ ድል የምንነሣበት ምክንያት የለም። ሦስቱንም ከሦስቱ አካላት አንዱ ወልድ በሥጋ ተገልጦ አርባ መዓልት አርባ ሌሊት በመጾም እስከ ሚፈታተነን ድረስ። ሂድ አንተ ሰይጣን (ማቴ.4፥10 )በማለት ድል አድርጎልናል።

ክብር ለአከበረን እና ድል አድርጎ ድል የምናደርግበትን ሥልጣን ለሰጠን ጌታ ።እኛም ከሱ አብነት ነሥተን በመጾም በዘመናችን የአስቸገሩንን የለያዩንን ሦስቱን አርስተ ኃጣውዕ የሆኑብንን ከሕይወትም ከፈጣሪም ያራቁንን ያጣሉንን ዘረኝነትን ጥላቻን ጦርነትን ድል አድርገን ለሰላም እና ለነፃነት ትንሣኤ እንድንበቃ በነገር ሁሉ እግዚአብሔር ይርዳን። 🙏❤️🙏❤️🙏

መልካም ጾም ለሐገር ሰላም

@Ewntenga
@Ewntenga
@Ewntenga

Показано 20 последних публикаций.