ኢትዮጵያ ከፍተኛ የተባለ የኮሌራ ወረርሽኝ እያስተናገደች መሆኗን የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ‼️
ኢትዮጵያ በታሪኳ ከፍተኛ የተባለ የኮሌራ ወረርሽኝ እያስተናገደች እንደምትገኝ የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ።
የዓለም ጤና ድርጅት በኢትዮጵያ ለሚያካሂደው ሥራ አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያስፈልገውም ገልጿል።
የድርጅቱ ዳይሬክተር ቴድሮስ አድሐኖም ድጋፉ የማይገኝ ከሆነ ድርጅታቸው በሀገሪቷ የሚያከናውነውን ከጤና ጋር የተገናኝ ሥራ ለመቀጠል እንደሚቸገር ተናግረዋል።
ዶክተር ቴድሮስ የተስፋፋ ድርቅና በሽታ በሚሊየን የሚቆጠሩ አትዮጵያውያንን ሕይወት አደጋ ላይ መጣሉንም አስረድተዋል።
በተለይም በትግራይ፣ አማራ፣ ኦሮሚያና ሌሎች አካባቢዎች የተፈጠረው ግጭት እና ጦርነት የከፋ ጉዳት አድርሷል ነው ያሉት።
በርካታ የጤና ተቋማት እና መሰረተ ልማቶች ላይ ውድመት መከሰቱን አስታውሰው የተለያዩ ወረርሽኞች መከሰታቸውንም ጠቅሰዋል።
የዓለም ጤና ድርጅት በኢትዮጵያ በሥምንት ክልሎች 41 ሺህ ሰዎች በኮሌራ በሽታ መያዛቸውንም ገልጿል።
በሽታው በዚህ ልክ በኢትዮጵያ ሲከሰት በታሪኳ ከፍተኛው እንደሆነም ነው ድርጅቱ የገለጸው።
ወባና ኩፍኝም ሌሎቹ ወረርሽኞች መሆናቸውን የጠቀሰው ድርጅቱ፥ በኢትዮጵያ ለሚያከናውነው የበሽታ መከላከልና ጤና አጠባበቅ ሥራ አፋጣኝ የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግለት ጥሪ አቅርቧል።
አስተያየት መረጃ ካሎት
@FANA_TV_BOT 👈ያድርሱን
🇪🇹🇪🇹🇪🇹ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@fana_televisions@fana_televisions