#ተሐድሶ (Reformation)
ተሐድሶ ግን ምንድን ነው?
ተሐድሶ ማለት ማደስ፣ መለወጥ፣ ማበረታታት፣ አዲስ ነገር ማውጣት፣ ... ማለት ነው። (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ገጽ .435)
ተሐድሶ ማለት ያረጀን፣ የተበላሸን፣ የቀድሞ ይዘቱን የለቀቀን ነገር ቀድሞ ወደነበረበት ይዘት መመለስ ወይም አዲስ ማድረግ ማለት ነው። (ጌታቸው ኃይሌ)
ተሐድሶ የሚለውን ቃል የሚተኩት የእንግሊዝኛ አቻዎቹ #Reformation, #Renewal & #Restoration ናቸው።
Reformation _ ማለት እንደገና መለወጥ፣ የተበላሸውን እና የተመሰቃቀለውን ቦታ ስርዓት አስይዞ ማስቀመጥ፣ ፈር የለቀቀውን አዲስ ሥርዓት ማስያዝ ማለት ነው።
Renewal _ ማደስ፣ የቀድሞ መልክና ውበትን መመለስ ማለት ነው።
Restoration _ ወደ ቀድሞ ስፍራው መመለስ ማለት ነው።
"ተሐድሶ ማለት የነገረ መለኮታዊ፣ የአስተሳሰብ፣ የድርጅታዊ እና የፕሮግራም አወቃቀሮችን ዳግም ማደስ ማለት ነው።" ቦቢ ግሊያም
(ተሐድሶ _ #በጸጋአብ #በቀለ)
ተሐድሶ የሃይማኖት ድርጅት ወይም ተቋም አይደለም!. ተሐድሶ ሰዋዊ አስተሳሰብ አይደለም!. ተሐድሶ የማይጨበጥ ሕልም አይደለም!. ተሐድሶ የግለሰብ መጠሪያ ስም አይደለም!. ተሐድሶ ወቅታዊ እንቅስቃሴ አይደለም!. ተሐድሶ በሰው የሚለኮስ ችቦ አይደለም!.
ተሐድሶ ንጹሕ የሆነው የእግዚአብሔር ቃል የሚያስነሳው አብዮት ነው!. ተሐድሶ ከራሱ ከእግዚአብሔር የሚነሳ አብርሆት ነው!. የተሐድሶ አቀጣጣይ ራሱ እግዚአብሔር ነው!. ተሐድሶ ወቅታዊ ሳይሆን ሂደታዊ ነው!. ተሐድሶ በአማኞች ኑሮ ቀጣይነት ያለው ለውጥ እንዲመጣ ያደርጋል!.
ተሐድሶ ... በእግዚአብሔር እውቀት ላይ የሚነሳሳን የሰው አሳብ ያመክናል!. ተሐድሶ ዘመን ያስቆጠሩ ቢሆኑ እንኳን እንደ ቃሉ ያልሆኑ ትምህርቶችን፣ ትንቢቶችን፣ ሥርዓቶችን፣ ልምዶችን፣ ልምምዶችን፣ አካሂያዶችን እና አደራረጎችን ይነቅላል።
The Way Reformation Ministry, Ethiopia.
ለሌሎች አካፍሉ፦
#Grace #Commission
https://t.me/inchrist_life