Фильтр публикаций


ማስታወቂያ

ጉዳዩ፡- የብሄራዊ ድህረ-ምረቃ (NGAT) መግቢያ ፈተና ቀንን
ስለማሳወቅ
በ2017 ዓ.ም የሶስተኛ ዙር የNGAT አመልካቾች ምዘገባ ተጠናቅቋል፡፡ በዚሁ መሰረት ለመፈተን ያመለከታችሁ አመልካቾች ፈተናው የሚሰጠው ዓርብ መጋቢት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት በምትመደቡበት የፈተና ማዕከላት እንድትገኙ እናሳውቃለን፡፡

ማሳሰቢያ፡-
1. ተፈታኞች ወደ ፈተና ማዕከል በምትሄዱበት ወቅት ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡
2. ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከመጀመሩ 3 ደቂቃ በፊት በፈተና ማዕከል መገኘት ይጠበቅበታል፡፡
3. የሞባይል ስልክ ይዞ በፈተና ማዕከል መገኘት ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡
4. የፈተና ማዕከላት ምደባ በምዝገባ ፕላትፎርም የሚገለጽ ይሆናል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር


የአጠቃላይ ዩኒቨርስቲዎች ማህበር ምሥረታ የመክፈቻ ጉባዔ በዛሬው እለት በመደወላቡ ዩኒቨርሲቲ ተጀመረ።
-------
የማህበሩ መክፈቻ ስነስርዓት ለሁለት ቀናት የሚካሄድ ሲሆን የአጠቃላይ ዘርፍ ዩኒቨርሲቲዎች እየተሳተፉበት ይገኛሉ።

በኢትዮጵያ ያሉ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ባላቸው የትኩረት መስክ ልየታ (differentiation ) መሠረት በአራት ምድብ የተመደቡ ሲሆን ከምድቦች አንዱ የአጠቃላይ ዩኒቨርስቲዎች (comprhensi ve) ነው።

በዚህ ምድብ 21 ዩኒቨርስቲዎች የታቀፉ ሲሆን እንጅባራ ዩኒቨርሲቲም ከአጠቃላይ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል አንዱ ሲሆን ዩኒቨርስቲዎች ከተሰጣቸው ተልዕኮ አንፃር በየጊዜው እየተገናኙ በጋራ ጉዳዮች ላይ ለመምከር እና ሀሳብ ለመለዋወጥ በዛሬው ዕለት በመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ማህበሩን በይፋ መስርተዋል።

በዚህ ምስረታ እንጅባራ፣ መደወላቡ፣ መቱ፣ ጋምቤላ፣ ራያ፣ ደብረ ታቦር ፣ ቦረና ፣ ዋቻሞ ፣ ሚዛን ቴፒ ፣ ቡሌ ሆራ፣ ጅንካ፣ ሰላሌ፣ ወራቤ፣ ደምቢ ዶሎ ፣ ደባርቅ ፣ ቦንጋ ፣ አዲግራት ፣ መቅደላ አምባ ፣ ወልድያ የማህበሩ አባል ዩኒቨርሲቲዎች መሆናቸው ተገልጿል።
ለሁለት ቀናት በሚካሄደው የአጠቃላይ ዩኒቨርሲቲዎች ማህበር ምስረታ የአስተዳደርና ልማት ም/ ፕሬዚዳንት የሆኑት ወሀቤ ብርሃን ( ዶ/ር ) እንጅባራ ዩኒቨርሲቲን በመወከል እየተሳተፉ ይገኛሉ።

መጋቢት 1/2017 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ


ለትራፊክ ፖሊሶች፣ለመንገድ ደህንነት ባለሙያዎች፣ለሹፈሮች እና ለመንጃ ፈቃድ ትምህርት ቤት ማሰልጠኛ ተቋማት ባለቤቶች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና መስጠት ተጀመረ፡፡

የካቲት 1/2017 ዓ.ም፤እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ከእንጅባራ ከተማ ለተውጣጡ
ለትራፊክ ፖሊሶች፣ለተማሪዎች፣ለመንገድ ደህንነት ባለሙያዎች፣ለሹፈሮች እና ለመንጃ ፈቃድ ትምህርት ቤት ማሰልጠኛ ተቋማት ባለቤቶች ‘‘የመንገድ ትራፊክ አደጋ በማህበረሰቡ ላይ የሚያደርሰውን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ስነ-ልቦናዊ እና ሰብዓዊ ቀውስ መቀነስ” በሚል ርዕስ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና መስጠት ተጀምሯል፡፡

ስልጠናውን ያስጀመሩት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስ እና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ዲን የሽዋስ ፈንታሁን እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በመማር ማስተማር፣ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ሰፊ ስራ እየሰራ እንዲሚገኝ አውስተው ይህ ስልጠና በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት አማካኝነት መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡ አክለውም የመንገድ ትራፊክ አደጋ በሀገራችን በርካታ ማህበራዊ ቀውሶችን እያደረሰ በመሆኑ ይህን ለመከላከል ሁሉም አካላት የድርሻቸውን አንዲወጡ ለማስቻል የሚያግዝ ስልጠና መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ስልጠናውን የሚሠጡት ከዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ትምህርት ክፍሎች የተውጣጡ መ/ር ወበቴ ልመንህ፣ መ/ር እንደገና አማረ፣ መ/ር ዳዊት ጥላሁን፣ መ/ር አበባው የኔነህ እና መ/ር አበራ የኔው ሲሆኑ ስልጠናው ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ አምስት ቀናት የሚሰጥ ይሆናል።


Electronic learning Management system (e-LMS) ዙሪያ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ፡፡
----
መጋቢት 1/2017ዓ.ም፤እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ኢ-ለርኒንግ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ከአይ.ሲ.ቲ ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር የ Electronic learning Management System (e-LMS) ለዩኒቨርሲቲው መምህራን ስልጠና መስጠት ጀምሯል፡፡

ስልጠናውን ያስጀመሩት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ኢ-ለርኒንግ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ይርጋ ያየህ(ዶ/ር) እንደገለጹት ስልጠናው በዋናነት የዩኒቨርሲቲው መምህራን በዲጅታል ትምህርት ዘርፍ የተሻለ ዕውቀት እንዲይዙ ለማደረግ በ3ዙር የሚሰጥ ስልጠና መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ዳይሬክተሩ አያይዘውም በመጀመሪያው ዙር the Nature of Online Learning, introducing Injibara University’s e-LMS, Introduction about e-learning program/courses, creating Learning Contents and design activities በሚሉ ርዕሶች ዙሪያ የጽንሰ ሀሳብ እና የተግባር ስልጠናዎች እንደሚሰጡም ተናግረዋል፡፡

ስልጠናውን የሚሠጡት መምህር ይርጋ ያየህ(ዶ/ር)፣ መምህር ባንታለም ደርሰህ(ዶ/ር)፣ መምህር ዘለቀ ወርቅነህ(ረ/ፕሮፌሰር) እና አዱኛ አለበል ሲሆኑ ከሁሉም ኮሌጆች ለተውጣጡ መምህራን ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ 5 ቀናት ይሰጣል፡፡



Показано 5 последних публикаций.