Фильтр публикаций


እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከአሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ታሪካዊ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ አሜሪካን ሀገር ኬንታኪ ስቴት (Kentucky State) ከሚገኙ ሁለት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ዓለምአቀፋዊ ትስስር በመፍጠር የትምህርት እና የምርምር ጥራት ለማስጠበቅ፣ የመምህራን እና የተመራማሪዎችን አቅም ለማሳደግ እና ዓለምአቀፋዊ ገጽታዉን ለማሳደግ በያዘው እቅድ መሠረት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጋርዳቸው ወርቁ እና የአካዳሚክ ም/ፕሬዚዳንት ዶ/ር አእምሮ ታደሰ በአሜሪካን ሀገር ከሚገኙ ኬንታኪ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ( Kentucky State University) እና ከኬንታኪ ዩኒቨርሲቲ ( University of Kentucky) ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል።
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በአሜሪካ ከሚገኙ ዩኒቨርሲሰዎች ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሲፈራረም የመጀመሪያው ሲሆን ስምምነቱም ታሪካዊ ሊባል የሚያስችለው ነው።

ስምምነቱ በኬንታኪ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኮፊ አካክፓ፣ በኬንታኪ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ኮሌጅ ም/ዲን ፕ/ር ሱሬንድራናት ሱማን እና በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጋርዳቸው ወርቁ የተፈረመ ሲሆን የመግባቢያ ስምምነቱ በዩኒቨርሲቲዎች መካከል የመምህራን እና የተማሪዎች ልውውጥ( Faculty and students exchange)፣በጋራ ምርምር ማካሄድ እና የምርምር ፈንድ ማፈላለግ፣ ኮንፈረንስ እና ወርክሾፕ በጋራ ማከናወን እና የአጭር እና የረጅም ጊዜ ስልጠናዎችን የሚያካትት ነው።
https://www.facebook.com/share/r/19xG5tQo93/


የሀዘን መግለጫ

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ መጀመሪያ ዓመት የማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ የነበረው ተማሪ ሞላልኝ ልንገረው ባደረበት ህመም ምክንያት ወደቤተሰቦቹ ሄዶ በህክምና ሲረዳ የነበረ ቢሆንም የካቲት 10/2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በተማሪ ሞላልኝ ህልፈት ምክንያት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቹ እና ወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን ይመኛል!


"ስነ ምግባር፣ ሙስናና መከላከያ መንገዶቹ" በሚል ርዕስ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሠጠ፡፡
----
የካቲት 10/2017ዓ.ም፤እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የስነ ምግባር መከታተያ ስራ አስፈጻሚ ከዩኒቨርሲቲው ጠቅላላ አገልግሎት ስራ አስፈጻሚ ጋር በመተባበር ለግቢ ውበትና አትክልት ልማት ሰራተኞች በስነ ምግባር ግንባታ እና በሙስና መከላከል ስትራቴጂዎች ላይ ያተኮረ ስልጠና ሠጥቷል፡፡

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የስነ ምግባር መከታተያ ስራ አስፈጻሚ ደሳላው ጌታሁን ስልጠናው ስነ ምግባር፣ ሙስናና መከላከያ መንገዶቹ ላይ ያተኮረ መሆኑን ገልጸው የስነ ምግባር ችግር ለመልካም አስተዳደር እጦትና ለሙስና መንስኤ በመሆኑ እንደ ሀገር አሁን ላይ እየታዩ ላሉ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ከባቢያዊ ችግሮች ሁሉ ዋነኛ መንስኤያቸው የትውልድ የስነ ምግባር ጉደለት እንደሆነም ተናግረዋል፡፡ አቶ ደሳለው አክለውም ሰላምና መረጋጋት የሰፈነባት እና ለዜጎቿ ምቹ የሆነች ሀገር እንድትኖረን ከተፈለገ ሁሉም ዜጋ ለትውልድ ስነ ምግባር ግንባታ እና ለሙስና መከላከል ተግባራት ትኩረት መስጠት ይገባል ብለዋል፡፡

በስልጠናው የዩኒቨርሲቲው ግቢ ውበትና አትክልት ልማት ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡


“ብሄራዊ ጥቅሞቻችንና ቀጠናዊ ትስስር ለሚዛናዊ የሕዝቦች ተጠቃሚነት'' በሚል መሪ ቃል ውይይት ተካሄደ።

የካቲት 10/2017 ዓ.ም፤እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከሰላም ሚንስተር ጋር በመተባበር በሀገሪቱ ብሄራዊ ጥቅም እና የህዝቦች ተጠቃሚነት ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሂዷል፡፡

የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት እና የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ተወካይ ክንዴ ብርሃን(ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ከሰላም ሚንስተር ጋር በመተባበር “ብሄራዊ ጥቅሞቻችንና ቀጣናዊ ትስስር ለሚዛናዊ የሕዝቦች ተጠቃሚነት'' በሚል ርዕስ ያዘጋጀው ውይይት ዋና ዓላማ የውይይቱ ተሳታፊዎች በብሄራዊ ጥቅሞቻች እና በቀጠናዊ ትስስር ላይ ግንዛቤ ለመፍጠር መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ዶ/ር ክንዴ አያይዘውም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅምች በግዛት አንድነት መጠበቅ፣ ሰላምና ደህንነትን ማረጋገጥ፣ በተቋም ግንባታ፣ በህብረ ብሄራዊ አንድነት፣ በግብርና(በምግብ ራስን በመቻል)፣በአረንጓዴ አሻራ፣ በትምህርት ጥራት፣ በማህበራዊ ሀብቶች እና ቀጠናዊ ትስስር ላይ የተመሰረቱ መሆናቸውን ገልጸው ይህን ለማድረግ ሁላችንም ሀገራዊ ግዴታችን መወጣት አለብን ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ እንደ ሀገር የዜጎችን ጥቅም እንዲረጋገጥ ትስስር ለመፍጠር እና የሕዝቦች ተጠቃሚነትን ለማስፈን መሰል መድረኮችን በማዘጋጀት ምሁራን ጋር መወያየት እንደሚገባ ገልጸው የዩኒቨርሲቲው ምሁራንም የተለያዩ ጥናቶችን ማድረግ እንደሚጠበቅባቸውም ተናግረዋል፡፡
https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid02jkakBjYnNYZbzsNGHHLhK1eKt25dXWBYufJX1ZMTGe6Vq2N7auPUzjvNjJeQqKHAl/?app=fbl


ማስታወቂያ
----
ለሆቴል የሙያ ብቃት ምዘና ፈላጊዎች በሙሉ



Показано 6 последних публикаций.