የአእላፋት ዝማሬ | Melody of Myriads


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


እንዳልዘምር የሚከለክለኝ ምንድን ነው?

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций




ሳምንት 5 ደብረዘይት ቻሌንጅ

1) ራሳችንን ፈትሸን: ንስሐ ገብተን : ወደ ንስሐ አባቶቻችን ቀርበን የተናዘዝን : የተሰጠንን ቀኖና የጨረስን እና "እግዚአብሔር ይፍታ" ተብለን የተዘጋጀን ከንስሐ አባታችን ጋር በመማከር ከቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ መቀበል


2)ራሳችንን ፈትሸን ለኑዛዜ የተዘጋጀን ወደ ንስሐ አባቶቻችን በመቅረብ ኑዛዜ መፈጸም : ቀኖና መቀበል

3)ክርስቶስ ዳግም ሊፈርድ ሲመጣ የሚጠይቀንን 6ቱ ቃላተ ወንጌልን መፈጸም ለዚህም በግላችን ወይም ከ6ቱ ቃላተ ወንጌል ጉዞ መሳተፍ

4)የታሰሩ ሰዎችን መጠየቅ

5)በደብረዘይት ሰንበት በቅዳሴ የሚነበበውን ወንጌል
*ማቴ 24:1-36
የሚሰበከውን ምስባክ መዝ 45:2-3
እንዲሁም የሚነበቡትን መልእክታት
*1ኛ ተሰ 4:13-18
*2ኛ ጴጥ 3:7:15 ማስታወሻ በመያዝ ማጥናት

6)በሰው ከመፍረድ መቆጠብ

7)በዚህ ጾም ምን እንዳሻሻልን:ምን እንደተጠቀምን ራሳችንን መመዘን

ስለዚህ፥እናንተ ደግሞ ተዘጋጅታችኹ፡ኑሩ፥የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና" -ማቴ 24:44


ሳምንት 4 መጻጉዕ ቻሌንጅ

1.ለንስሐ መዘጋጀት(ከንስሐ አባታችን ጋር ለመገናኘት በቅድሚያ ከራሳችን ጋር በመሆን ለኑዛዜ መዘጋጀት)

2.በግል ወይም በቡድን በመሆን የታመሙትን: የሚረዳቸው ዘመድ የሌላቸውን ወገኖችን መጠየቅ

3)ቅርባችን በሚገኝ ጠበል ቦታ በመሔድ መጠመቅ/መጠጣት

4)በሐዘን/ጭንቀት ያሉትን በእግዚአብሔር ቃል ማጽናናት : ድካማቸውን ማገዝ

5)የበገና ዝማሬዎችን ማዳመጥ

6)ወንጌል ፡- ማር. 2 ፥ 1- 12
መልእክታት
ገላ. 6 ፥ 1– 9
ያዕ. 3 ፥ 14– 18

የሐዋ. 3 ፥ 12 - 16
መዝ. 40(41) ፥ 3 - 4


የቅድመ ጋብቻ ትምህርቱን ብቻ የምትፈልጉ በዚህ ሊንክ

https://forms.gle/3CdAefMd9SVsBvj68

የቅድመ ጋብቻ ትምህርቱንና የብዙኃን ጋብቻ ላይ መሳተፍ ለምትፈልጉ እጮኛሞች በዚህ ሊንክ

https://forms.gle/cFzxBNkYzro5cDNW7

ለበለጠ መረጃ
0922071777
+251111267883
ደውለው ይጠይቁ።
የትዳር ሕይወት ስንቅ እንዳልይዝ፤ ጋብቻዬንስ በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን እንዳላደርግ የሚከለክለኝ ምንድን ነው?




የሳምንት ሦስት ምኩራብ ቻሌንጅ ከዕለታዊ የመንፈሳዊ መግባራት መከታተያ ጋር

1)ብዙ ጊዜ የምናጠፋበት የእጅ ስልካችን ውስጥ ያሉ ወደ ክርስቶስ እንዳንቀርብ የሚያደርጉ አላስፈላጊ የሆኑ ገጾችን : ዘፈኖችን ሌሎችም የማይጠቅሙ ፋይሎች: መተግበሪያዎች ጠርጎ ማስወገድ

2) ለአእምሮአችን እረፍት በምናገኝባት ቅድስት ቤተክርስቲያን በመገኘት የጽሞና ጊዜ ማሳለፍ

3)በምኩራብ ሰንበት የሚነበበውን ወንጌል ዮሐ 2:12-ፍጻሜው
እንዲሁም መልእክታቱን ቆላ 2:16-ፍጻሜው
ያዕ 2:14-ፍጻሜው ማስታወሻ በመያዝ ማጥናት

4)በዚህ ሳምንት ውዳሴ ዘአምላክ የተባለውን የ7ቱ ቀናትን ውብ ጸሎት መጸለይ

5) ወንድምን ማማትን (ሀሜትን) ማስወገድ

ይህ ሳምንታዊ ቻሌንጅ እንዴት እየጠቀማችሁ እንደሆነ ያጋሩን::


ኢጃት ለሕፃናት ድጋፍ ለማድረግ ተጨማሪ የመግባቢያ ስምምነቶች ተፈራረመ።

| ጃንደረባው ሚዲያ | የካቲት 2017 ዓ.ም|

አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በጠቅላይ ቤተ ክህነት የማኅበራት ማደራጃ መምሪያ የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ከመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ፣ መንበረ ፓትርያርክ ቅ/ቅ ማርያም ገዳም እና ደብረ ገሊላ አማኑኤል ሰንበት ትምህርት ቤቶች ጋራ ለጋራ ሥራ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ::

በኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ስር ካሉት 23 ፕሮጀክቶች አንዱ የሆነው ጃን ቂርቆስ ከሰኔ 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ከመንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ እና ከገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ አጥቢያ ቤተክርስቲያናት ሰንበት ትምህርት ቤቶች ጋር በመተባበር ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው 100 ሕፃናት የገንዘብ፣ የአልባሳት፣ የህክምና፣ የስልጠና እና የመሳሰሉ ድጋፎችን ሲያደርግ ቆይቷል። የፕሮጀክቱ ዋና ዓላማም የሕፃናቱ አካላዊ እድገት፣ ጤና፣ የአዕምሮ መጎልበት፣ መንፈሳዊ እድገት አንዲሁም ማኅበራዊ ግንኙነት መዳበር ነው፡፡

በእነዚህ ሁለት አጥቢያ ቤተክርስቲያናት ላይ ፕሮጀክቱ የሕፃናቱን ሁለንተዊ እድገትን ከማስጠበቅ አኳያ አበረታች ውጤት ስለተገኘበት በያዝነው 2017 ዓ.ም. ደግሞ ተደራሽነቱን በማስፋት ከመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ፣ መንበረ ፓትርያርክ ቅ/ቅ ማርያም ገዳም እና ደብረ ገሊላ አማኑኤል ሰንበት ትምህርት ቤቶች ጋር በመተባበር ለ 230 ሕፃናት ለሶስት አመት የሚቆይ ድጋፍ ለማድረግ በኢትዮጵያዊው ጃንደረባው ትውልድ ማህበር እና በሰንበት ትምህርት ቤቶቹ መሀከል የመግባቢያ ስምምነት ተፈርሟል።


📥የሳምንት 2 ቅድስት ቻሌንጅ

ዳሩ ግን፦እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ኹኑ ተብሎ ስለ፡ ተጻፈ የጠራችኹ ቅዱስ እንደ ኾነ፡ እናንተ ደግሞ በኑሯችኹ ዅሉ ቅዱሳን ኹኑ፡፡ -1ኛ ጴጥ 1:15-16

👩‍🎤 Author: @janyared_2


ይህንን checklist ይጠቀሙ።


የሳምንት 2 ቅድስት ቻሌንጅ

ዳሩ ግን፦እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ኹኑ ተብሎ ስለ፡ ተጻፈ የጠራችኹ ቅዱስ እንደ ኾነ፡ እናንተ ደግሞ በኑሯችኹ ዅሉ ቅዱሳን ኹኑ።
-1ኛ ጴጥ 1:15-16


አንተ ሰይፍና ጦር ጭሬም ይዘህ ትመጣብኛለህ እኔ ግን ዛሬ በተገዳደርኸው አምላክ ስም በሰራዊት ጌታ በእግዚአብሔር ስም እመጣብሃለሁ።
1ኛ ሳሙ 17፡45

ዐድዋ - ቅዱስ ጊዮርጊስ ገበዘ ኢትዮጵያ


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
የሳምንት ፩ ዘወረደ ቻሌንጅ




የሳምንት 1 ዘወረደ ቻሌንጅ ከዕለታዊ መንፈሳዊ ምግባራት መከታተያ ጋር

1)በዚህ ጾም ከጌታ ዘንድ ምን መቀበል እንደምንፈልግ እናስቀምጥ
2)ማስወገድ የምንፈልጋቸውን ልማዶች/ኃጢአቶችን ለይቶ በማውጣት እግዚአብሔር ድል መንሳትን እንዲሰጠን መለመን

3)በ7ቱ የጸሎት ሰዓታት መጸለይ

4)ይህንን ወቅት በጽሞና እንዳናሳልፍ ከሚያደርጉን የሚያዘናጉ ነገሮች ታቅበን በአንጻሩ የሚያግዙ መጻሕፍትን ማንበብ: መዝሙራትን ማዳመጥ የመሳሰሉትን ማድረግ
41,64 በአቅማችን መስገድ

5)በቤተክርስቲያን በመገኘት የዕለቱን ወንጌል መማር

6)የማቴዎስ ወንጌል 4:1-11 ማስታወሻ በመያዝ ማጥናት
*እነዚን ሁሉ ከምጽዋት ጋር
*ዕለታዊ የመንፈሳዊ ምግባር መከታተያውን ከታች ያገኙታል::


ጾም የሥጋ ምኞትን የምታጠፋ የነፍስን ቁስል የምታደርቅ ለጎልማሶችም ጸጥታንና እርጋታን የምታስተምር ደገኛ ሥርዓት ነች፡፡

እያንዳንዱን ዕለት ከክርስቶስ ጋር ሆኖ ለማሳለፍ ዝግጁ ናችሁ? አብረን እንጓዝ።

ፍሬ የምናፈራበት ጾም ያደርግልን።

14k 0 102 366

Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
የሰርጉ ካርድ ላይ ምን ይላል?


ጾመ ነነዌ ሰኞ የካቲት ፫ ይገባል።

Показано 17 последних публикаций.