❗#ኪዳነ_ምህረት_ማለት❗
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
🔴👉 ኪዳነምህረት ስንል የምህረት ቃልኪዳን ማለት ነው፡፡ በዚህ ውስጥም ምህረት አድራጊው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ምህረት ተቀባይም መላው የአዳም ዘር ነው፡፡እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በምድራዊ ቆይታዋ ዘውትር ወደ ክርስቶስ መካነ መቃብር ጎለጎታ እየወረደች ትፀልይ ነበር፡፡
🔷👉 ልጇ እና ወዳጇ ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያደረገችውን ልመናና ፀሎት ተመልክቶና ሰምቶ የምህረት ቃል ኪዳን ገባለት ፡፡
🔵👉 እንኳን የእናቱን ፀሎት እና ልመና ቀርቶ ዘውትር በሀጥያት የምንዘፈቀውን እኛን ክፉዎቹን የሚሰማ አምላክ ስለ አንቺ ፣ ስለ እናቴ ክብርና ፀጋ ስል ይኸው ቃሌ ብሎ ቃልኪዳን አደረገ፡፡
« ከመረጥሁት ጋር ቃል ኪዳኔን አደረግሁ። … » መዝ, 89 : 3 እንዲል መፅሐፉ፡፡
🔴👉 ስሟን ለሚጠሩ፣በእርሷ አማላጅነት ለሚታመኑ በምድር በረከትን በሰማይ የዘለዓለም መንግስትን እንደሚወርሱ የምህረት እና የቸርነት ቃልኪዳን ሰጥቷታል ፡፡
❗ታላቁ መፅሐፍ እንዲህ ይላል❗፦
ቀስቲቱም በደመና ትሆናለች፤በእኔና በምድር ላይ በሚኖር ሥጋ ባለው በሕያው ነፍስ ሁሉ መካከል ያለውን የዘላለም ቃል ኪዳን ለማሰብ አያታለሁ።" ኦሪት ዘፍ. 9 : 16
🔴👉 በዚህም መሠረት ቃልኪዳኗን ምክንያት በማድረግ ኪዳነ-ምህረት እያልን እንጠራታለን።
❗ የእመቤታችን ምህረት እና ረድዔት ፤በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን!❗
❗ የ100 ብር ቻሌንጃችን ላይ ሁላችሁም ተሳተፉ❗
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
🔵👉 ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው እንዳለ። ሐዋ, 20፥35
🔴👉 ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች መፅሐፍ እንደሚለው ስንቶቻችን ከመቀበል ይልቅ ለመስጠት ዝግጁዎች ነን ? ስንቶቻችንስ በምፅዓት ቀን ለምንጠየቀው ጥያቄ መልስ ለመስጠት ሳይመሽብን ተዘጋጅተን ይሆን ?
🔵👉 በውኑ በምፅዓት ቀን ምንድን ነው የምንጠየው ትሉኝ ይሆናል እስቲ ከነ ፍርዱ መፅሐፍ የሚለውን እንመልከት 👇👇
🔴👉 ማቴዎስ 25
³⁴ ንጉሡም በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላቸዋል፦ እናንተ የአባቴ ቡሩካን፥ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ።
³⁵ ተርቤ አብልታችሁኛልና፥ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛልና፥ እንግዳ ሆኜ ተቀብላችሁኛልና፥ ታርዤ አልብሳችሁኛልና፥
³⁶ ታምሜ ጠይቃችሁኛልና፥ ታስሬ ወደ እኔ መጥታችኋልና።
³⁷ ጻድቃንም መልሰው ይሉታል፦ ጌታ ሆይ፥ ተርበህ አይተን መቼ አበላንህስ? ወይስ ተጠምተህ አይተን መቼ አጠጣንህ?
³⁸ እንግዳ ሆነህስ አይተን መቼ ተቀበልንህ? ወይስ ታርዘህ አይተን መቼ አለበስንህ?
³⁹ ወይስ ታመህ ወይስ ታስረህ አይተን መቼ ወደ አንተ መጣን?
⁴⁰ ንጉሡም መልሶ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ እንኳ ስላደረጋችሁት ለእኔ አደረጋችሁት ይላቸዋል።
🔴👉 ⁴¹ በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል፦ እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ።
⁴² ተርቤ አላበላችሁኝምና፥ ተጠምቼ አላጠጣችሁኝምና፥ እንግዳ ሆኜ አልተቀበላችሁኝምና፥
⁴³ ታርዤ አላለበሳችሁኝምና፥ ታምሜ ታስሬም አልጠየቃችሁኝምና።
⁴⁴ እነርሱ ደግሞ ይመልሱና፦ ጌታ ሆይ፥ ተርበህ ወይስ ተጠምተህ ወይስ እንግዳ ሆነህ ወይስ ታርዘህ ወይስ ታመህ ወይስ ታስረህ መቼ አይተን አላገለገልንህም? ይሉታል።
⁴⁵ ያን ጊዜ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ለአንዱ ስላላደረጋችሁት ለእኔ ደግሞ አላደረጋችሁትም ብሎ ይመልስላቸዋል።
⁴⁶ እነዚያም ወደ ዘላለም ቅጣት፥ ጻድቃን ግን ወደ ዘላለም ሕይወት ይሄዳሉ።
🔴👉 ወዳጆቼ እኛ የትኛውን ይሆን የምንፈልገው ? የአባቴ ብሩካን ኑ የሚለውን ነው ወይስ እናንተ ርጉማን ከኔ ሂዱ የሚለውን ነው ? እርግጠኛ ነኝ ሁላችንም የአባቴ ብሩካን ኑ መባልን መንግስቱን መውረስን ነው የምንፈልገው !
🔵👉 ታዲያ ይህንን እንድንባል የተራበ አብልተን ይሆን የተጠማ አጠጥተን ይሆን የታረዘ አልብሰን ይሆን የታሰረ ጠይቀን ይሆን ? የታመመ ጠይቀን ይሆን ? መቼስ ነው ይህንን የምናደርገው ? ወዳጆቼ መጠሪያችን አይታወቅምና ሳይመሽብን ለነብሳችን የሚበጃትን ስራ እንስራ !
🔴👉 እኛም እግዚአብሔር ፈቅዶልን ከዚህ በፊት አንዲስ አመትን ምክንያት በማድረግ ከ700 በላይ የሚሆኑ የታሰሩ ወገኖቻችን ጠይቀናል በዓሉን አብረናቸው አክብረናል ! የልደት በዓልን ምክንያት በማድረግ ደግሞ የታመሙ ወገኖቻችንን ከእናንተ በተሰበሰበው ገንዘብ ለመድኃኒት መግዣ እንዲሆናቸው ሰጥተናል። ይህ የሆነው ደግሞ እናንተው አነሰ በዛ ሳትሉ ከ100 ብር ጀምሮ በሰጣችሁት ገንዘብ ነው ይህንንም በቪዲዮ ወደ እናንተ አድርሰናል።
🔷👉 በዚህም ለነብሳችን የሚበጃትን ስራ እንድሰራ የፈቀደልን አምላክ ስሙ ለዘላለም የተመሰገነ ይሁንልን ።
🔴👉 አሁንም የዛሬ ዓመት እንዳደረግነው እግዚአብሔር ቢፈቅድ ከፊታችን የሚመጣውን የጌታችንን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ ተርቤ አላበላችሁኝም ይላልና ቃሉ በዓሉን በየደብሩ ያሉ ነዳያንን አንድ ቦታ ሰብስበን በመመገብ እንዲሁም የሰው አይን ፈርተው በየቤታቸው ካሉ ከተቸገሩ እህት ወንድሞቻችን ጋር ለማሳለፍ ፕሮግራም ይዘናል !
🔵👉ስለዚህ እኛ በዓሉን በቤታችን ሁሉ ሞልቶልን ስናከብር ቃሉ እንደሚለው የተራቡ የተጠሙ የተቸገሩ ወንድም እህቶቻችንም ማሰብ ተገቢ ነውና ሁላችሁም አነሰ በዛ ሳትሉ እዚህ የበረከት ስራ ላይ ልትሳተፉ ያስፈልጋል !
🔴👉 ቢያንስ እዚህ መንፈሳዊ ቻናል ላይ ከ170 ሺ ሰው በላይ አለ ሁሉም መቶ መቶ ብር እንኳን ቢያዋጣ ትልቅ የበረከት ስራ መስራት ይቻላል እናንተ የምትሰጡት መቶ ብር ትልቅ ስራ መስራት ይችላል። ስለዚህ ይህንን ያነበባችሁ እዚህ የበረከት ስራ ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ በ 0902829657 በኢም, በዋትስአፕ , በቴሌግራም , አናግሩኝ ! ቃል መግባት የምትችሉም ቃል መግባት ይቻላል !
🔴👉 እንዲሁም ለዚሁ አላማ ተብሎ በሶስት ሰው ስም በተከፈተው ንግድ ባንክ አካውንትም ማስገባት ትችላላችሁ 👇👇
አካውንት ቁጥር :- 1000614809683
ስም :- ደሳለኝ እጅጉ & በረከት & ዋሲሁን
❗በሚጠፋው ገንዘባችን የማይጠፋውን ሰማያዊ ቤታችንን እንስራ❗
በዚህ ቻናላችን ላይ በአመት ሶስት ቋሚ የነብስ ስራዎችን አብረን እንሰራለን ።
👉 ለአዲስ ዓመት :- የታሰሩ መጠየቅ
👉 ለገና በዓል :- የታመሙ መጠየቅ
👉 ለፋሲካ በዓል :- የተራቡ ማብላት
❗ለሁሉም እንዲደርስ ላይክ ሼር አድርጉ❗
።።።።#ወስበሐት_ለእግዚአብሔር ።።።።
።።።።። #ወለወላዲቱ_ድንግል ።።።።።
።።።።። #ወለመስቀሉ_ክቡር ።።።።።
ዲ/ን ዮናስ ዘ ሆለታ ደብረ ኤዶም
መጋቢት 17 /2017 ዓ.ም
ሆለታ
ፔጁን #Like_Follow_Share በማድረግ ትክክለኛ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት እንዲሁም መረጃ ያግኙ
🔴👉 በቴሌግራም | Telegram
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/joinchat_yonas_holet_debreedom