ዲ/ን ዮናስ ዘ ሆለታ ደብረ ኤዶም


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


በዚህ ቻናሌ ላይ የኦርዶክስ ተዋህዶ መንፈሳዊ ትምህርቶች፣መዝሙሮች፣እንዲሁም የተለያዩ መረጃዎችን ያገኛሉ። ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉ

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций


❗እየተስፋፋ የመጣው የፌስቡክ እና የቴሌግራም❗
ዘረፋ የጥንቃቄ መልዕክት
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
🔴👉 ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ብዙ ሰዎች የፌስቡክ እና የቴሌግራም አካውንታቸው ባልታወቁ ሰዎች ተጠልፎ እየተወሰደባቸውና እና በነሱ አካውንት ደግሞ የጓደኞቻቸውን አካውንት እየወሰዱ ይገኛሉ !

🔵👉 ከስር ያስቀመጥኩላችሁ ፎቶዎች አካውንታቸው ተጠልፎ እነሱን የማይወክል የማጭበርበር ፅሑፍ የተለቀቀባቸው ናቸው። በፅሑፉ ላይ እንደምትመለከቱት እነሱ መጀመሪያ 35.000 ብር ገቢ እንዳደረጉ ከዛም 350.000 ብር እንደገባላቸውና ሌሎችም እንዲሳተፉ ሊንክ ተጫኑ ይላል።

🔷👉 እናንተም እውነት መስሏችሁ ሊንኩን ከተጫናችሁ አካውንታችሁ ይወስዱታል። ሊንክ መላክ ብቻም ሳይሆን ፎቶው ላይ እንደምትመለከቱት በውስጥ መስመርም ያወሯቿል። ስለዚህ በምታውቁት ሰውም ቢሆን ሊንኮች ሲላኩላችሁ ባለመጫን አካውንታችሁን ማትረፍ ትችላላችሁ። በተጨማሪም ለፌስቡካችሁ ውስብስብ የሆነ ፖስወርድ አድርጉ። ለምሳሌ ቁጥር , ፊደል , እና ሲምቦልን ያካተተ።

❗ወደ ቴሌግራም ስንመጣ ሰሞኑን❗

🔷👉 ቴሌግራም ፕሪሚየም በነፃ ተቀብለዋል!» የሚል የአማርኛ ጽሑፍ ከስሩ ሊንክ ያለው እየተሰራጨ ነው። ከስር በፎቶ አስቀምጬላቿለው። ልብ በሉ! ሊንኩን ከተጫናችሁት አካውንታችሁ 100% ተጠልፏል። በምታውቁት ሰው አካውንት ቢላክም፤ አውቆ ሳይሆን እርሱም ተጠልፎ ነው።
ሊንኩን በፍፁም እንዳትከፍቱ። ሊንክ ብቻም ሳይሆን በውስጥም በፅሑፍ ያወሯቿል። ይህንንም በፎቶ አስቀምጬላቿለው።

  ዲ/ን ዮናስ ዘ ሆለታ ደብረ ኤዶም
        መጋቢት 21 /2017 ዓ.ም
                 ሆለታ




🔴👉 ድንግል ሆይ ቅድስት ሆይ ❗
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
🔴👉 ክርስቶስን ያከበሩ፤ መንገዱን የተከተሉ ብዙ ሴቶች አሉ፤ እውነትን የመሰከሩ፤ ስለ ቃሉ የኖሩ ብዙ ሴቶች አሉ፤ መስዋዕትነትን የከፈሉ በሰማዕትነት ያለፉ ብዙ ሴቶች አሉ፤ ታላላቅ የምድር ነገስታትን፤ ታላላቅ ነቢያትን የወለዱ ብዙ ሴቶች አሉ፤ ከነዚህ ሁሉ ግን አንቺ ትበልጫለሽ፡፡

🔵👉 ቅድስት ድንግል ሆይ አንቺ እኮ፡- ሰማይ ዙፋኑ ምድር መረገጫው የሆነ፤ ድንቅ መካር ኃያል አምላክ የሰላም አለቃ፤ ሁሉ በእርሱ የሆነ ከሆነውም አንዳችም እንኳን ያለርሱ ያልሆነ፤ ዓለምን ሁሉ ከሞት ወደ ሕይወት የመለሰ፤ መንበሩን የሚሸከሙ ኪሩቤልና ሱራፌል የሚንቀጠቀጡለት፤ የሁሉ ፈጣሪ፤ የሁሉ አምላክ እናት ነሽ፡፡ በፊትም አሁንም ወደፊትም ካንቺ በቀር ፈጣሪዋን ልጄ ብላ የምትጠራ ሴት አልነበረችም፤ የለችም፤ አትኖርምም ክርስቶስም እናቴ ብሎ የሚጠራት ብቸኛዋ ሴት አንቺ ነሽ በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ፡፡

❗👉 እናት ስትሆኝ ድንግል፤ ድንግል ስትሆኝ እናት በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ፡፡ ትውልድ ሁሉ ብጽዕት ብሎ የሚጠራሽ ብቸኛዋ ሴት በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ፡፡ እግዚአብሔር መርጦና ጠብቆ ያስቀረሽ ዘር በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ፡፡ ለዓለም ሁሉ ድህነት ምልክት የሆንሽ በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ፡፡
.
❗እናቴ ሆይ እንግዲህ እኔ ምን ልናገር? ሺህ ቃላትን ብደረድር ያንቺን ክብር ልገልፀውስ እንደምን እችላለው? አዎ አሁንም እላለሁ “መልካም ያደረጉ ብዙ ሴቶች አሉ አንቺ ግን ከሁሉ ትበልጫለሽ፡፡”
ምሳ. 31፡29

❗ድንግል ሆይ❗ቅድስት ሆይ ❗
❗ጌታን የወለድሽ ንፅህት ሆይ❗

🔵👉 ወደ እኔ ትመጪ ዘንድ እንዴት ይሆናል እኔ ሀጥያተኛ አመፀኛ ነኝ ትእቢተኛ ተንኮለኛ ነኝ ሰማያዊን ህይወት ሳይሆን ለምድራዊ ህይወቴ የምሮጥ አለም ወዳድ ነኝ።

🔴👉 አንቺ ቅድስት ነሽ አንቺ ብሩክት ነሽ አንቺ ንግስት ነሽ ሰው ሆኖ እንዳንቺ የነፃ የለም ሰው ሆኖ እንዳንቺ የከበር ከፍከፍ ያለ ይለም አንቺ ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች ነሽ ከመላእክትም ወገን ቢሆን አንቺን የሚመስል የለም እናም እናቴ እመቤቴ ቅድስተ ቅዱሳን ንፅህተ ንፁሀን
ምእልተ ፀጋ, ፀጋን የሞላብሽ ድንግል ማርያም ሆይ በህይወት ዘመኔ ሁሉ እንዳመሰግንሽ እርጂ ምልጃሽ አይለየኝ ስምሽን ደጋግሜ ልጥራው ፈቃድሽ ይሁንልኝ የልጅሽ ቸርነት የአንቺ አማላጅነት ለአለም ህዝብ ሁሉ ይሁን።

🔴👉የቅድስት ድንግል ማርያም በረከቷ በሁላችን ላይ ይደር፤ ምልጃ ቃል ኪዳኗ ይጠብቀን፡፡

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
🙏⏩ሼር አድርጉ አይከፈልበትም

።።።።#ወስበሐት_ለእግዚአብሔር ።።።።
።።።።። #ወለወላዲቱ_ድንግል ።።።።።
።።።።። #ወለመስቀሉ_ክቡር ።።።።።

ዲ/ን ዮናስ ዘ ሆለታ ደብረ ኤዶም
መጋቢት 21 /2017 ዓ.ም
ሆለታ

ፔጁን #Like_Follow_Share በማድረግ ትክክለኛ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት እንዲሁም መረጃ ያግኙ

🔴👉 በቴሌግራም | Telegram
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/joinchat_yonas_holet_debreedom

🔴👉 በዋትስአፕ | whatsapp
👇👇👇👇👇
https://whatsapp.com/channel/0029Va4Ter67T8bV5NlRGJ2w

🔴👉 1ኛ ዩትዩብ | 1st YouTube
👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@yonastube

🔴👉 2ኛ ዩትዩብ | 2nd YouTube
👇👇👇👇👇👇
https://youtube.com/@yonasmedia16




🔴👉 እኛም እግዚአብሔር ፈቅዶልን ከዚህ በፊት አንዲስ አመትን ምክንያት በማድረግ ከ700 በላይ የሚሆኑ የታሰሩ ወገኖቻችን ጠይቀናል በዓሉን አብረናቸው አክብረናል ! የልደት በዓልን ምክንያት በማድረግ ደግሞ የታመሙ ወገኖቻችንን ከእናንተ በተሰበሰበው ገንዘብ ለመድኃኒት መግዣ እንዲሆናቸው ሰጥተናል። ይህ የሆነው ደግሞ እናንተው አነሰ በዛ ሳትሉ ከ100 ብር ጀምሮ በሰጣችሁት ገንዘብ ነው ይህንንም በቪዲዮ ወደ እናንተ አድርሰናል።

🔷👉 በዚህም ለነብሳችን የሚበጃትን ስራ እንድሰራ የፈቀደልን አምላክ ስሙ ለዘላለም የተመሰገነ ይሁንልን ።

🔴👉 አሁንም የዛሬ ዓመት እንዳደረግነው እግዚአብሔር ቢፈቅድ ከፊታችን የሚመጣውን የጌታችንን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ ተርቤ አላበላችሁኝም ይላልና ቃሉ በዓሉን በየደብሩ ያሉ ነዳያንን አንድ ቦታ ሰብስበን በመመገብ እንዲሁም የሰው አይን ፈርተው በየቤታቸው ካሉ ከተቸገሩ እህት ወንድሞቻችን ጋር ለማሳለፍ ፕሮግራም ይዘናል !

🔵👉ስለዚህ እኛ በዓሉን በቤታችን ሁሉ ሞልቶልን ስናከብር ቃሉ እንደሚለው የተራቡ የተጠሙ የተቸገሩ ወንድም እህቶቻችንም ማሰብ ተገቢ ነውና ሁላችሁም አነሰ በዛ ሳትሉ እዚህ የበረከት ስራ ላይ ልትሳተፉ ያስፈልጋል !

🔴👉 ቢያንስ እዚህ መንፈሳዊ ቻናል ላይ ከ170 ሺ ሰው በላይ አለ ሁሉም መቶ መቶ ብር እንኳን ቢያዋጣ ትልቅ የበረከት ስራ መስራት ይቻላል እናንተ የምትሰጡት መቶ ብር ትልቅ ስራ መስራት ይችላል። ስለዚህ ይህንን ያነበባችሁ እዚህ የበረከት ስራ ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ በ 0902829657 በኢም, በዋትስአፕ , በቴሌግራም , አናግሩኝ ! ቃል መግባት የምትችሉም ቃል መግባት ይቻላል !

🔴👉 እንዲሁም ለዚሁ አላማ ተብሎ በሶስት ሰው ስም በተከፈተው ንግድ ባንክ አካውንትም ማስገባት ትችላላችሁ 👇👇

አካውንት ቁጥር :- 1000614809683
ስም :- ደሳለኝ እጅጉ & በረከት & ዋሲሁን

❗በሚጠፋው ገንዘባችን የማይጠፋውን ሰማያዊ ቤታችንን እንስራ❗

በዚህ ቻናላችን ላይ በአመት ሶስት ቋሚ የነብስ ስራዎችን አብረን እንሰራለን ።
👉 ለአዲስ ዓመት :- የታሰሩ መጠየቅ
👉 ለገና በዓል :- የታመሙ መጠየቅ
👉 ለፋሲካ በዓል :- የተራቡ ማብላት

❗ለሁሉም እንዲደርስ ላይክ ሼር አድርጉ❗

።።።።#ወስበሐት_ለእግዚአብሔር ።።።።
።።።።። #ወለወላዲቱ_ድንግል ።።።።።
።።።።። #ወለመስቀሉ_ክቡር ።።።።።

ዲ/ን ዮናስ ዘ ሆለታ ደብረ ኤዶም
መጋቢት 20 /2017 ዓ.ም
ሆለታ

ፔጁን #Like_Follow_Share በማድረግ ትክክለኛ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት እንዲሁም መረጃ ያግኙ

🔴👉 በቴሌግራም | Telegram
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/joinchat_yonas_holet_debreedom

🔴👉 በዩትዩብ | YouTube
👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@yonasmedia16


❗#ገብርሔር_የአብይ_ፆም ❗
🔴#ስድስተኛ ሳምንት
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
🔵👉 ገብርሔር ማለት ታማኝ አገልጋይ ማለት ነው። ገብርሄር የዓብይ ጾም ሥድስተኛ ሳምንት መጠሪያ ሲሆን ትርጉሙም ታማኝ አገለጋይ ማለት ነው።

🔴👉 በዚህ ሳምንት ሥለ ገብርሄር ( ታማኝ አገለጋይ)እና ገብርሃካይ (ክፉ አገለጋይ) መክሊት ማለትም ሥለ፦
~ባለ አምሥት መክሊት፤የተሰጠው
~ ባለ ሁለት መልክት፤ የተሰጠው እና
~ አንድ መክሊት፤ ሥለተሰጠው ባለ መክሊቶች ከነ ምስጢራቸው በሰፊው ይነገራል።

🔴 ማቴ፡፳፭፦
"ወደ ሌላ አገር የሚሄድ ሰው ባሮቹን ጠርቶ እንደሰጣቸው እንዲሁ ይሆናልና፤ ለእያንዳንዱ እንደ አቅሙ ለአንዱ አምሥት መክሊት፣ለአንዱም ሁለት ለአንዱም አንድ ሰጠና ወደ ሌላ አገር ወዲያው ኼደ።

🔵👉 አምሥት መክሊት የተቀበለው ሄዶ ነገደበት ሌላ አምሥት መክሊትም አተረፈ፣ እንዲሁ ሁለት የተቀበለውም ሌላ ሁለት አተረፈ፤ አንድ የተቀበለው ግን ሄዶ ምድርን ቆፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረው።

🔴👉 ከብዙ ዘመንም በሁዋላ የእነዚያ ባሪዎች ጌታ መጣና ተቆጣጠራቸው ፤ አምሥት መክሊት የተቀበለውም ቀረበና ሌላ አምሥት መክሊት አስረክቦ ጌታ ሆይ አምሥት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር እንሆ ሌላ አምሥት መክሊት አተረፍኹበት አለው።

🔵👉 ጌታውም መልካም አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ፡ በጥቂቱ ታምነኻልና በብዙ እሾምኻለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው። ሁለት መክሊት የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ ጌታ ሆይ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እንሆ ሌላ ሁለት መክሊት አተረፍኹበት አለው ። ጌታውም መልካም አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ፡ በጥቂቱ ታምነኻልና በብዙ እሾምኻለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው።

🔴👉 አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ ጌታ ሆይ: ካልዘራህባት የምታጭድ ካልበተንኽባትም የምትሰበስብ ክፋ ሰው መሆንህን አውቃለሁ። ፈራሁም ኼጀም መክሊትህን በምድር ላይ ቀበርኩት። እንሆ መክሊትህ አለህ አለው። ጌታውም መልሶ እንዲህ አለው :አንተ ክፋ እና ሀኬተኛ ባሪያ ካልዘራሁባት እንዳጭድ ካልበተንኹባትም እንድሰበስብ ታውቃልህን? ሥለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር።እኔም መጥቼ ያለ,ኝን ከትርፉ ጋር እወስድ ነበር። ሥለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት አሥር መክሊትም ላለው ስጡት።

🔵👉 ላለው ሁሉ ይ,ሰጠዋልና ይበዛለትማል ከሌለው ግን ያው ያለው እንኳን ይወሰድበታል። የማይጠቅመውንም ባሪያ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት በዚያ ልቅሶና ጥር,ስ ማፋጨት ይሆናል " ማቴ ፳፭፦፲፬-፴

❗👉 ውድ ክርስቲያኖች የጨዋይቱ የሳራ የቅድሥት ኦርቶዶክ,ስ ተዋህዶ ልጆች መክሊታችንን እንወቅ በተሰጠን ጸጋ ቤተክ/ን እናገልግል፤ ሁላችንም የየድርሻች እንወጣ መክሊቱን ቆፍሮ እንደቀበረው ክፍ አገልጋይ በውጭ እንዳንጣል እንትጋ። "እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ፥ በኀዘን ወይም በግድ አይደለም" ፪ኛቆሮ፱፦፯ "ክፉ ሰው በከንፈሩ ኃጢአት ይጠመዳል፤ ጻድቅ ግን
ከመከራ ያመልጣል።

🔴👉 የሰው ነፍስ ከአፉ ፍሬ መልካም ነገርን ትጠግባለች፥ ሰውም እንደ እጁ ሥራ ዋጋውን ይቀበላል። የሰነፍ መንገድ በዓይኑ የቀናች ናት፤ ጠቢብ ግን ምክርን ይሰማል ። የሰነፍ ቍጣ ቶሎ ይታወቃል፤ ብልህ ሰው ግን ነውርን ይሰውራል። እውነተኛን ነገር የሚናገር ቅን ነገርን ያወራል፤ የሐሰት ምስክር ግን ተንኰልን ያወራል።" ምሳ ፲፪፦፲፫

🔵👉 " ከሁሉ በሚያንስ የታመነ በብዙ ደግሞ የታመነ ነው፥ ከሁሉ በሚያንስም የሚያምፅ በብዙ ደግሞ ዓመፀኛ
ነው።"ሉቃ፲፮፦፲ " እንግዲያስ በዓመፃ ገንዘብ ካልታመናችሁ፥ እውነተኛውን ገንዘብ ማን አደራ ይሰጣችኋል?"
ሉቃ፲፮፦፲

🔴👉 ጌታችን ያዘዘንን ሁሉ እናድርግ ሰዎችን ሁሉ እንውደድ ከዘረኝነት አዙሪት እንውጣ ክርስትና ቃላት መደርደር ሳይሆን ተግባርና ስራ ነውእና። ልጄ ሆይ ኃይማኖትህ በስራህ ይገለጥ"እንዳለ ጠቢቡ። "በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ…ብዙዎች ናቸው፤ ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው።

🔵👉 ሥለ ኢትዮጵያ እንፀልይ፤ ሥለ ቤተክርስቲያንም እንፀልይ፤ ጾሙን ጾመን ፀልየን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም ያድርሰን ፤በመንፈስ ጀምረን በሥጋ
እንዳንጨርሰው የመድኃኒታችን ቸርነቱ አባትነቱ የድንግ እናትነትና ምላጃ ይርዳን አሜን ❗

የ100 ብር ቻሌንጃችን ተጀምሯል
ሁላችሁም ተሳተፉ
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
🔵👉 ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው እንዳለ። ሐዋ, 20፥35

🔴👉 ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች መፅሐፍ እንደሚለው ስንቶቻችን ከመቀበል ይልቅ ለመስጠት ዝግጁዎች ነን ? ስንቶቻችንስ በምፅዓት ቀን ለምንጠየቀው ጥያቄ መልስ ለመስጠት ሳይመሽብን ተዘጋጅተን ይሆን ?

🔵👉 በውኑ በምፅዓት ቀን ምንድን ነው የምንጠየው ትሉኝ ይሆናል እስቲ ከነ ፍርዱ መፅሐፍ የሚለውን እንመልከት 👇👇

🔴👉 ማቴዎስ 25
³⁴ ንጉሡም በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላቸዋል፦ እናንተ የአባቴ ቡሩካን፥ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ።
³⁵ ተርቤ አብልታችሁኛልና፥ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛልና፥ እንግዳ ሆኜ ተቀብላችሁኛልና፥ ታርዤ አልብሳችሁኛልና፥
³⁶ ታምሜ ጠይቃችሁኛልና፥ ታስሬ ወደ እኔ መጥታችኋልና።
³⁷ ጻድቃንም መልሰው ይሉታል፦ ጌታ ሆይ፥ ተርበህ አይተን መቼ አበላንህስ? ወይስ ተጠምተህ አይተን መቼ አጠጣንህ?
³⁸ እንግዳ ሆነህስ አይተን መቼ ተቀበልንህ? ወይስ ታርዘህ አይተን መቼ አለበስንህ?
³⁹ ወይስ ታመህ ወይስ ታስረህ አይተን መቼ ወደ አንተ መጣን?
⁴⁰ ንጉሡም መልሶ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ እንኳ ስላደረጋችሁት ለእኔ አደረጋችሁት ይላቸዋል።

🔴👉 ⁴¹ በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል፦ እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ።
⁴² ተርቤ አላበላችሁኝምና፥ ተጠምቼ አላጠጣችሁኝምና፥ እንግዳ ሆኜ አልተቀበላችሁኝምና፥
⁴³ ታርዤ አላለበሳችሁኝምና፥ ታምሜ ታስሬም አልጠየቃችሁኝምና።
⁴⁴ እነርሱ ደግሞ ይመልሱና፦ ጌታ ሆይ፥ ተርበህ ወይስ ተጠምተህ ወይስ እንግዳ ሆነህ ወይስ ታርዘህ ወይስ ታመህ ወይስ ታስረህ መቼ አይተን አላገለገልንህም? ይሉታል።
⁴⁵ ያን ጊዜ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ለአንዱ ስላላደረጋችሁት ለእኔ ደግሞ አላደረጋችሁትም ብሎ ይመልስላቸዋል።
⁴⁶ እነዚያም ወደ ዘላለም ቅጣት፥ ጻድቃን ግን ወደ ዘላለም ሕይወት ይሄዳሉ።

🔴👉 ወዳጆቼ እኛ የትኛውን ይሆን የምንፈልገው ? የአባቴ ብሩካን ኑ የሚለውን ነው ወይስ እናንተ ርጉማን ከኔ ሂዱ የሚለውን ነው ? እርግጠኛ ነኝ ሁላችንም የአባቴ ብሩካን ኑ መባልን መንግስቱን መውረስን ነው የምንፈልገው !

🔵👉 ታዲያ ይህንን እንድንባል የተራበ አብልተን ይሆን የተጠማ አጠጥተን ይሆን የታረዘ አልብሰን ይሆን የታሰረ ጠይቀን ይሆን ? የታመመ ጠይቀን ይሆን ? መቼስ ነው ይህንን የምናደርገው ? ወዳጆቼ መጠሪያችን አይታወቅምና ሳይመሽብን ለነብሳችን የሚበጃትን ስራ እንስራ !






❗ገናናው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ሆይ ❗
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
🔴👉 ቅዱስ ገብርኤል ሆይ እጅግ አጽናኝና አስደሳች የሆነውን ምሥጢረ ሥጋዌን ዜና ይዘህ ከሰማይ ወደ ምድር እንደወረድክ ድንግል ማርያም የአምላክ እናት ለመሆን ፈቃድዋ ሆኖ በተፈጸመ ጊዜ ደስ እንዳለህ እኛም እግዚአብሔርን በማክበርና ግዴታችንን በመፈጸም ደስ የምንልበትን ጸጋ አሰጠን።

🔵👉 ጠባቂያችን ቅዱስ ገብርኤል ሆይ ሦስቱን ወጣቶች ከሚያቃጥል እሳት እንዳዳንካቸው እኛንም በዚህ ዓለም ከሚወራው ከሚታየውና ከሚሰማው ክፉ ቀንና እለት ሁሉ አድነን እየነደደ የሚለበልበንን የኃጢያት እሳትም አጥፋልን፤ የኑሯችንን ቀጠሮ በክንፈ ረድኤትህ ከልለው ሰይጣን እንዳይሰለጥንብን፣ ክፉ አድራጊዎች፣ ሟርተኞች፣ ሰላቢዎች፣ ዘረኞችና ነፍሰ ገዳዮች እንዳያጠቁን ከልለን።

🔴👉 ያንተን የእሳት አጥር ዘሎ ጠላት ያጠቃን ዘንድ ጠላት አይችልምና ጥበቃ ከእኛ ከባርያዎችህ አይለየን።

🔵👉 ቅዱስ ገብርኤል ሆይ ሕፃኑ ቂርቆስና እናቱ እየሉጣን በንፍር ውኃ ከመቀቀል እንዳዳንካቸው እኛ አገልጋዮችህም በማናውቀው ሁኔታ የተዘጋጀልንን የጥፋት ወጥመድ ሁሉ አስወግድልን በላያችን ላይም በክፉ ሰዎች ምክንያት የተነሳብንን እሳት አጥፋልን ለእውነተኛ ሃይማኖት የጨከንንና የቆረጥንም አድርገን።

🔴👉 የሰይጠንን ፈተና የምናልፍበት እውነተኛውን ጥበብ እንደ ነብዩ ዳንኤል አስተምረን።

🔵👉 ቅዱስ ገብርኤል ሆይ በደል በተገኘብኝ ቁጥር እያለቀስሁ እጠራሃለሁ፤ ጎስቋላ የምሆን በጥቃትና በሀዘን ውስጥ የምገኝ ልጅህ የአንተን ማፅናናትና ረዳትነት ያሻኛልና ፈጥነህ ናልኝ፡፡

🔴👉 ቅድስት ማርያምን ያበሰርክ ለዓለም ሁሉ የምታበር ገብርኤል ሆይ በሰራዊት አምላክ ይዤሃለሁ በዚህች ሰዓት ፀሎቴንና ልመናዬን ስማ፡፡

🔵👉 ቅዱስ ገብርኤል ሆይ ቀድመህ የደስታ የምሥራች ቃልህን ልታበስር ወደ ገሊላ እንደወረድህ ዛሬም ለአዘንን ለእኛ ከሠማይ ሠረገላ ናልን፡፡

🔴👉 የደስታንም ቃል አሰማን ቅድስት ድንግል ማርያምን ያበሰርክ ተወዳጁ ቅዱስ ገብርኤል ሆይ በምህረትና በይቅርታ ወደ እኛ ናልን ዓለም የጥፋት፣ የሞት፣ የክስረት፣ የውድመትና የተስፋ መቁረጥ ድምፅን ያሰማናልና አንተ ግን ጎስቁልናችንን የሚያነሳ ስብራታችንን የሚጠግን እንባችንን የሚያብስ የብስራት ድምፅህን አሰማን እንድንፅናናም አድርገን፡፡

🔵👉 እውነተኛ ጠባቂያችን ቅዱስ ገብርኤል ሆይ እኛን ለማዳን ሰው የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን፣ ማደሪያው የሆነችው ድንግል ማርያምን በጣም እንወዳታለን፤ በዚህ ዓለም የምሥጢረ ሥጋዌ ተካፋዮች በመሆናችን በመንግስተ ሰማያትም ተካፋዮች ለመሆን ሁላችንንም በምልጃህ አብቃን ለምንልን ለዘላለሙ

🔴👉ለአብ ምስጋና ይገባል፤ ለወልድ ዋህድ ኢየሱስ ክርስቶስ ምስጋና ይገባል፤ ለመንፈስ ቅዱስ ጰራቅሊጦስ ምስጋና ይገባል ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን

❗ለሁሉም እንዲደርስ ላይክ ሼር አድርጉ❗

።።።።#ወስበሐት_ለእግዚአብሔር ።።።።
።።።።። #ወለወላዲቱ_ድንግል ።።።።።
።።።።። #ወለመስቀሉ_ክቡር ።።።።።

ዲ/ን ዮናስ ዘ ሆለታ ደብረ ኤዶም
መጋቢት 19/2017 ዓ.ም
ሆለታ

ፔጁን #Like_Follow_Share በማድረግ ትክክለኛ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት እንዲሁም መረጃ ያግኙ

🔴👉 በቴሌግራም | Telegram
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/joinchat_yonas_holet_debreedom

🔴👉 በዋትስአፕ | whatsapp
👇👇👇👇👇
https://whatsapp.com/channel/0029Va4Ter67T8bV5NlRGJ2w

🔴👉 1ኛ ዩትዩብ | 1st YouTube
👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@yonastube

🔴👉 2ኛ ዩትዩብ | 2nd YouTube
👇👇👇👇👇👇
https://youtube.com/@yonasmedia16








❗ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ❗
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
🔴👉 ቅዱስ እስጢፋኖስ ቀዳሜ ሰማዕት፡- እስጢፋኖስ ማለት ‹‹መደብ›› ማለት ሲሆን በግሪክ ቋንቋ ‹‹አክሊል›› ማለት ነው፡፡

🔵👉 ትውልዱ ከነገደ ብንያም ሲሆን አባቱ ስምዖን እናቱ ሐና ይባላሉ፡፡ እነርሱም እግዚአብሔርን ከሚፈሩ ከነቢያትና ከጻድቃን ወገን ናቸው፡፡ ሁለት ወንድ ልጆችንም ወለዱ፡፡ አንዱ ይሁዳ ሲባል ሁለተኛውም ይህ ቅዱስ እስጢፋኖስ (አስተፓኖስ) ነው፡፡

🔴👉 እስጢፋኖስም ወደ ቅዱሳን ሐዋርያት በመሄድ ይላላካቸው ነበር፡፡ በኢየሩሳሌም ቤተ ክርስቲያን ከተሾሙት ከ7ቱ ዲያቆናት አንዱ ሲሆን የዲያቆናት አለቃ እርሱ ነው፡፡

🔵👉 ቅዱስ እስጢፋኖስ በመጀመሪያ ከታላቁ የኦሪት ምሑር የእነ ቅዱስ ጳውሎስ መምህር ከነበረው ከገማልያል የኦሪትን ሥርዓት ጠንቅቆ የተማረ ምሑረ ኦሪት ነው፡፡ ትንቢተ ነቢያትን ያውቅና የአዳኙን መሢሕ መምጣት በጸሎትና በተስፋ ሲጠባበቅ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የጌታችንን መንገድ ሲጠርግ ቢያገኘው ደቀ መዝሙር ሆነና በትጋት ሲያገለግለው ቆየ፡፡

🔴👉 ከ6 ወራት በኃላ ክብር ይግባውና ጌታችን በዮሐንስ እጅ ተጠመ፡፡ ከጌታችንም ጥምቀት በኃላ ቅዱስ እስጢፋኖስ ጌታችን ይመጣ ዘንድ ያለው መሢሕ እርሱ መሆኑን በአንክሮ ጠየቀው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስንም ቅዱስ እስጢፋኖስ ራሱን ጌታችንን አግኝቶት የአንደበቱን ቃል የእጁን ተአምራት አይቶ ይመን በማለት ወደ ጌታችን ዘንድ ላከው፡፡

🔵👉 ከዚህም በኃላ ቅዱስ እስጢፋኖስ የጌታችን ደቀ መዝሙር ሆነ፡፡ እርሱም አስቀድሞ ጌታችን ከዋለበት እየዋለ ካደረበት እያደረ ወንጌልን ተምሯልና ጌታችንም 72ቱን አርድእት ለስብከተ ወንጌል ሲያሰማራቸው ከእነርሱ ውስጥ አንዱ ቅዱስ እስጢፋኖስ ነበር፡፡ በበዓለ ሃምሳ መንፈስ ቅዱስን ከተቀበለ በኃላ ወንጌልን በአዋጅ ይሰብክ ጀመረ፡፡ ከዚህም በኃላ ቅዱስ እስጢፋኖስ ከጌታችን ዕርገት በሁኃላ ለአንድ ዓመት ያህል ስምንት ሺህ ማኅበርተኞቹን እየመራ ወንጌልን እየሰበከ ክርስትናን አስፋፋ፡፡

🔴👉 የሰማዕታት መጀመሪያ የሆነው ቅዱስ እስጢፋኖስ በትምህርቱና በተአምራቱ ብዙዎችን ወደቀናች ሃይማኖት ስለመለሰ ክፉዎች አይሁድ ቀኑበትና የሐሰት ምስክር አዘጋጁበት፡፡ ‹‹በእግዚአብሔርና በሙሴ ላይ የስድብን ቃል ሲናገር ሰምተነዋል›› ብለው በሐሰት ከሰሱትና በሸንጎአቸው አቆሙት፡፡ ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስም ከአብርሃም ጀምሮ እስከ ጌታችን ያለውን ሁሉንም እየጠቀሰ የሃይማኖትን ነገር አስተማራቸው፡፡ ነቢያትን ስለማሳደዳቸውና ስለመግደላቸው እየወቀሰ ሲናገራቸው በትምህርቱ ተናደው ጆሮአቸውን ይዘው በመጮህ በድንጋይ ወግረው ይገድሉት ዘንድ እየጎተቱ ከከተማው ውጭ አወጡት፡፡ በድንጋይ ወግረው ሲገድሉት ከጌታችን የተማረውን ‹‹አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይህን ኃጢአት አትቁጠርባቸው›› እያለ ስለገዳዮቹ ምሕረትን ይለምን ነበር፡፡ ሰማይም ተከፍቶ የእግዚአብሔርን ክብር ተመለከተ፡፡

🔵👉 ቅዱስ ጳውሎስ ይኸውም የቀድሞው ሳውል ቅዱስ እስጢፋኖስን በድንጋይ ሲወግሩት የገዳዮቹን ልብስ ይጠብቅና ድንጋይ ያቀብል ነበር፡፡ ‹‹የሰማዕትህንም የእስጢፋኖስን ደም ባፈሰሱ ጊዜ፥ ራሴ ደግሞ በአጠገባቸው ስቆም ተስማምቼ የገዳዮችን ልብስ እጠብቅ ነበር አልሁ›› ብሎ ራሱ ቅዱስ ጳውሎስ መስክሯል፡፡ ሐዋ 22፡20፡፡ የቅዱስ እስጢፋኖስ መምህር የነበረው ምሑረ ኦሪቱ ገማልያልና ልጁ አቢብ በእስጢፋኖስ ትምህርትና የሞቱ ሰዎች የሰጡትን ምስክርነት አይተው ከይሁዲነት ተመልሰው በክርስቶስ አምነው ተጠምቀዋል፡፡

🔴👉 ስለ ሰማዕቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንዲህ ተብሎ ነው የተጻፈው፡- ‹‹እስጢፋኖስም ጸጋንና ኃይልን ተሞልቶ በሕዝቡ መካከል ድንቅንና ታላቅ ምልክትን ያደርግ ነበር፡፡ የነፃ ወጪዎች ከተባለችው ምኵራብም ከቀሬናና ከእስክንድርያም ሰዎች ከኪልቅያና ከእስያም ከነበሩት አንዳንዶቹ ተነሥተው እስጢፋኖስን ይከራከሩት ነበር፤ ይናገርበት የነበረውንም ጥበብና መንፈስ ይቃወሙ ዘንድ አልቻሉም፡፡ በዚያን ጊዜ በሙሴ ላይ በእግዚአብሔርም ላይ የስድብን ነገር ሲናገር ሰምተነዋል የሚሉ ሰዎችን አስነሡ፡፡ ቀርበውም ያዙት ወደ ሸንጎም አመጡትና ‹ይህ ሰው በዚህ በተቀደሰው ስፍራ በሕግም ላይ የስድብን ነገር ለመናገር አይተውም፤ ይህ የናዝሬቱ ኢየሱስ ይህን ስፍራ ያፈርሰዋል ሙሴም ያስተላለፈልንን ሥርዓት ይለውጣል ሲል ሰምተነዋልና› የሚሉ የሐሰት ምስክሮችን አቆሙ፡፡ በሸንጎም የተቀመጡት ሁሉ ትኵር ብለው ሲመለከቱት እንደ መልአክ ፊት ሆኖ ፊቱን አዩት፡፡›› ሐዋ 6፡8-15፡፡

🔴👉 ቅዱስ እስጢፋኖስም እንዲህ አላቸው፡- ‹‹ከነቢያትስ አባቶቻችሁ ያላሳደዱት ማን ነው? የጻድቁንም መምጣት አስቀድሞ የተናገሩትን ገደሉአቸው፤ በመላእክት ሥርዓት ሕግን ተቀብላችሁ ያልጠበቃችሁት እናንተም አሁን እርሱን አሳልፋችሁ ሰጣችሁት ገደላችሁትም፡፡ ይህንም በሰሙ ጊዜ በልባቸው በጣም ተቈጡ ጥርሳቸውንም አፋጩበት፡፡

🔴👉 መንፈስ ቅዱስንም ተሞልቶ ወደ ሰማይ ትኵር ብሎ ሲመለከት የእግዚአብሔርን ክብር ኢየሱስንም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየና፡፡ እነሆ ሰማያት ተከፍተው የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አያለሁ አለ፡፡ በታላቅ ድምፅም እየጮኹ ጆሮአቸውን ደፈኑ፣ በአንድ ልብ ሆነውም ወደ እርሱ ሮጡ፤ ከከተማም ወደ ውጭ አውጥተው ወገሩት፡፡ ምስክሮችም ልብሳቸውን ሳውል በሚሉት በአንድ ጎበዝ እግር አጠገብ አኖሩ፡፡

🔵👉 እስጢፋኖስም ‹ጌታ ኢየሱስ ሆይ ነፍሴን ተቀበል› ብሎ ሲጠራ ይወግሩት ነበር፡፡ ተንበርክኮም ‹ጌታ ሆይ ይህን ኃጢአት አትቍጠርባቸው› ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ፡፡ ይህንም ብሎ አንቀላፋ፡፡ ሳውልም በእርሱ መገደል ተስማምቶ ነበር፡፡ የሐዋ 7:52-60፡፡

🔴👉 የቅዱስ እስጢፋኖስ ልደቱና ዕረፍቱ ጥር 1 ቀን ነው፡፡ መእመናንም ሥጋውን ወስደው በክብር ቀብረውታል፡፡ ጥቅምት 17 የተሾመበት በዓሉ ሲሆን መስከረም 15 ቀን ደግሞ ፍልሰተ ሥጋው ነው፡፡

(ምንጭ፡- የመስከረምና የጥቅምት ወር ስንክሳር)

❗የቀዳሜ ሰማዕት የቅዱስ እስጢፋኖስ ምልጃ ተራዳኢነቱ በረከቱ ሁሉ በሁላችን ላይ ይደርብን❗

🔷👉አንብበው ጨርሰዋል? እንግዲያውስ ጠቃሚ ነው ብለው ካሰቡ ሼር በማድረግ ወንጌን ያዳርሱ!!

።።።።#ወስበሐት_ለእግዚአብሔር ።።።።
።።።።። #ወለወላዲቱ_ድንግል ።።።።።
።።።።። #ወለመስቀሉ_ክቡር ።።።።።

ዲ/ን ዮናስ ዘ ሆለታ ደብረ ኤዶም
መጋቢት 17/2017 ዓ.ም
ሆለታ

ፔጁን #Like_Follow_Share በማድረግ ትክክለኛ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት እንዲሁም መረጃ ያግኙ

🔴👉 በቴሌግራም | Telegram
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/joinchat_yonas_holet_debreedom

🔴👉 በዋትስአፕ | whatsapp
👇👇👇👇👇
https://whatsapp.com/channel/0029Va4Ter67T8bV5NlRGJ2w

🔴👉 1ኛ ዩትዩብ | 1st YouTube
👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@yonastube

🔴👉 2ኛ ዩትዩብ | 2nd YouTube
👇👇👇👇👇👇
https://youtube.com/@yonasmedia16




🔴👉 በዋትስአፕ | whatsapp
👇👇👇👇👇
https://whatsapp.com/channel/0029Va4Ter67T8bV5NlRGJ2w

🔴👉 1ኛ ዩትዩብ | 1st YouTube
👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@yonastube

🔴👉 2ኛ ዩትዩብ | 2nd YouTube
👇👇👇👇👇👇
https://youtube.com/@yonasmedia16


❗#ኪዳነ_ምህረት_ማለት❗
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
🔴👉 ኪዳነምህረት ስንል የምህረት ቃልኪዳን ማለት ነው፡፡ በዚህ ውስጥም ምህረት አድራጊው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ምህረት ተቀባይም መላው የአዳም ዘር ነው፡፡እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በምድራዊ ቆይታዋ ዘውትር ወደ ክርስቶስ መካነ መቃብር ጎለጎታ እየወረደች ትፀልይ ነበር፡፡

🔷👉 ልጇ እና ወዳጇ ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያደረገችውን ልመናና ፀሎት ተመልክቶና ሰምቶ የምህረት ቃል ኪዳን ገባለት ፡፡

🔵👉 እንኳን የእናቱን ፀሎት እና ልመና ቀርቶ ዘውትር በሀጥያት የምንዘፈቀውን እኛን ክፉዎቹን የሚሰማ አምላክ ስለ አንቺ ፣ ስለ እናቴ ክብርና ፀጋ ስል ይኸው ቃሌ ብሎ ቃልኪዳን አደረገ፡፡
« ከመረጥሁት ጋር ቃል ኪዳኔን አደረግሁ። … » መዝ, 89 : 3 እንዲል መፅሐፉ፡፡

🔴👉 ስሟን ለሚጠሩ፣በእርሷ አማላጅነት ለሚታመኑ በምድር በረከትን በሰማይ የዘለዓለም መንግስትን እንደሚወርሱ የምህረት እና የቸርነት ቃልኪዳን ሰጥቷታል ፡፡

❗ታላቁ መፅሐፍ እንዲህ ይላል❗፦
ቀስቲቱም በደመና ትሆናለች፤በእኔና በምድር ላይ በሚኖር ሥጋ ባለው በሕያው ነፍስ ሁሉ መካከል ያለውን የዘላለም ቃል ኪዳን ለማሰብ አያታለሁ።" ኦሪት ዘፍ. 9 : 16

🔴👉 በዚህም መሠረት ቃልኪዳኗን ምክንያት በማድረግ ኪዳነ-ምህረት እያልን እንጠራታለን።

❗ የእመቤታችን ምህረት እና ረድዔት ፤በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን!❗

❗ የ100 ብር ቻሌንጃችን ላይ ሁላችሁም ተሳተፉ❗
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
🔵👉 ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው እንዳለ። ሐዋ, 20፥35

🔴👉 ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች መፅሐፍ እንደሚለው ስንቶቻችን ከመቀበል ይልቅ ለመስጠት ዝግጁዎች ነን ? ስንቶቻችንስ በምፅዓት ቀን ለምንጠየቀው ጥያቄ መልስ ለመስጠት ሳይመሽብን ተዘጋጅተን ይሆን ?

🔵👉 በውኑ በምፅዓት ቀን ምንድን ነው የምንጠየው ትሉኝ ይሆናል እስቲ ከነ ፍርዱ መፅሐፍ የሚለውን እንመልከት 👇👇

🔴👉 ማቴዎስ 25
³⁴ ንጉሡም በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላቸዋል፦ እናንተ የአባቴ ቡሩካን፥ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ።
³⁵ ተርቤ አብልታችሁኛልና፥ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛልና፥ እንግዳ ሆኜ ተቀብላችሁኛልና፥ ታርዤ አልብሳችሁኛልና፥
³⁶ ታምሜ ጠይቃችሁኛልና፥ ታስሬ ወደ እኔ መጥታችኋልና።
³⁷ ጻድቃንም መልሰው ይሉታል፦ ጌታ ሆይ፥ ተርበህ አይተን መቼ አበላንህስ? ወይስ ተጠምተህ አይተን መቼ አጠጣንህ?
³⁸ እንግዳ ሆነህስ አይተን መቼ ተቀበልንህ? ወይስ ታርዘህ አይተን መቼ አለበስንህ?
³⁹ ወይስ ታመህ ወይስ ታስረህ አይተን መቼ ወደ አንተ መጣን?
⁴⁰ ንጉሡም መልሶ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ እንኳ ስላደረጋችሁት ለእኔ አደረጋችሁት ይላቸዋል።

🔴👉 ⁴¹ በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል፦ እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ።
⁴² ተርቤ አላበላችሁኝምና፥ ተጠምቼ አላጠጣችሁኝምና፥ እንግዳ ሆኜ አልተቀበላችሁኝምና፥
⁴³ ታርዤ አላለበሳችሁኝምና፥ ታምሜ ታስሬም አልጠየቃችሁኝምና።
⁴⁴ እነርሱ ደግሞ ይመልሱና፦ ጌታ ሆይ፥ ተርበህ ወይስ ተጠምተህ ወይስ እንግዳ ሆነህ ወይስ ታርዘህ ወይስ ታመህ ወይስ ታስረህ መቼ አይተን አላገለገልንህም? ይሉታል።
⁴⁵ ያን ጊዜ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ለአንዱ ስላላደረጋችሁት ለእኔ ደግሞ አላደረጋችሁትም ብሎ ይመልስላቸዋል።
⁴⁶ እነዚያም ወደ ዘላለም ቅጣት፥ ጻድቃን ግን ወደ ዘላለም ሕይወት ይሄዳሉ።

🔴👉 ወዳጆቼ እኛ የትኛውን ይሆን የምንፈልገው ? የአባቴ ብሩካን ኑ የሚለውን ነው ወይስ እናንተ ርጉማን ከኔ ሂዱ የሚለውን ነው ? እርግጠኛ ነኝ ሁላችንም የአባቴ ብሩካን ኑ መባልን መንግስቱን መውረስን ነው የምንፈልገው !

🔵👉 ታዲያ ይህንን እንድንባል የተራበ አብልተን ይሆን የተጠማ አጠጥተን ይሆን የታረዘ አልብሰን ይሆን የታሰረ ጠይቀን ይሆን ? የታመመ ጠይቀን ይሆን ? መቼስ ነው ይህንን የምናደርገው ? ወዳጆቼ መጠሪያችን አይታወቅምና ሳይመሽብን ለነብሳችን የሚበጃትን ስራ እንስራ !

🔴👉 እኛም እግዚአብሔር ፈቅዶልን ከዚህ በፊት አንዲስ አመትን ምክንያት በማድረግ ከ700 በላይ የሚሆኑ የታሰሩ ወገኖቻችን ጠይቀናል በዓሉን አብረናቸው አክብረናል ! የልደት በዓልን ምክንያት በማድረግ ደግሞ የታመሙ ወገኖቻችንን ከእናንተ በተሰበሰበው ገንዘብ ለመድኃኒት መግዣ እንዲሆናቸው ሰጥተናል። ይህ የሆነው ደግሞ እናንተው አነሰ በዛ ሳትሉ ከ100 ብር ጀምሮ በሰጣችሁት ገንዘብ ነው ይህንንም በቪዲዮ ወደ እናንተ አድርሰናል።

🔷👉 በዚህም ለነብሳችን የሚበጃትን ስራ እንድሰራ የፈቀደልን አምላክ ስሙ ለዘላለም የተመሰገነ ይሁንልን ።

🔴👉 አሁንም የዛሬ ዓመት እንዳደረግነው እግዚአብሔር ቢፈቅድ ከፊታችን የሚመጣውን የጌታችንን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ ተርቤ አላበላችሁኝም ይላልና ቃሉ በዓሉን በየደብሩ ያሉ ነዳያንን አንድ ቦታ ሰብስበን በመመገብ እንዲሁም የሰው አይን ፈርተው በየቤታቸው ካሉ ከተቸገሩ እህት ወንድሞቻችን ጋር ለማሳለፍ ፕሮግራም ይዘናል !

🔵👉ስለዚህ እኛ በዓሉን በቤታችን ሁሉ ሞልቶልን ስናከብር ቃሉ እንደሚለው የተራቡ የተጠሙ የተቸገሩ ወንድም እህቶቻችንም ማሰብ ተገቢ ነውና ሁላችሁም አነሰ በዛ ሳትሉ እዚህ የበረከት ስራ ላይ ልትሳተፉ ያስፈልጋል !

🔴👉 ቢያንስ እዚህ መንፈሳዊ ቻናል ላይ ከ170 ሺ ሰው በላይ አለ ሁሉም መቶ መቶ ብር እንኳን ቢያዋጣ ትልቅ የበረከት ስራ መስራት ይቻላል እናንተ የምትሰጡት መቶ ብር ትልቅ ስራ መስራት ይችላል። ስለዚህ ይህንን ያነበባችሁ እዚህ የበረከት ስራ ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ በ 0902829657 በኢም, በዋትስአፕ , በቴሌግራም , አናግሩኝ ! ቃል መግባት የምትችሉም ቃል መግባት ይቻላል !

🔴👉 እንዲሁም ለዚሁ አላማ ተብሎ በሶስት ሰው ስም በተከፈተው ንግድ ባንክ አካውንትም ማስገባት ትችላላችሁ 👇👇

አካውንት ቁጥር :- 1000614809683
ስም :- ደሳለኝ እጅጉ & በረከት & ዋሲሁን

❗በሚጠፋው ገንዘባችን የማይጠፋውን ሰማያዊ ቤታችንን እንስራ❗

በዚህ ቻናላችን ላይ በአመት ሶስት ቋሚ የነብስ ስራዎችን አብረን እንሰራለን ።
👉 ለአዲስ ዓመት :- የታሰሩ መጠየቅ
👉 ለገና በዓል :- የታመሙ መጠየቅ
👉 ለፋሲካ በዓል :- የተራቡ ማብላት

❗ለሁሉም እንዲደርስ ላይክ ሼር አድርጉ❗

።።።።#ወስበሐት_ለእግዚአብሔር ።።።።
።።።።። #ወለወላዲቱ_ድንግል ።።።።።
።።።።። #ወለመስቀሉ_ክቡር ።።።።።

ዲ/ን ዮናስ ዘ ሆለታ ደብረ ኤዶም
መጋቢት 17 /2017 ዓ.ም
ሆለታ

ፔጁን #Like_Follow_Share በማድረግ ትክክለኛ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት እንዲሁም መረጃ ያግኙ

🔴👉 በቴሌግራም | Telegram
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/joinchat_yonas_holet_debreedom




❗❗ #ሰማዕቱ_ቅዱስ_ቂርቆስ❗❗
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
🔴👉 ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ አባቱ ቆዝሚስ ፣ እናቱ ኢየሉጣ ይባላሉ። ሀገራቸውም ሮም ነበር። በዘመነ ሰማዕታት በጨካኙ እና በአረመኔው በዲዮቅልጥያኖስ ዘመነ መንግስት አዋጅ ታውጆ ነበር፡፡ይህም በ303 ዓ.ም ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ ብዙ ክርስትያኖች ተሰደዱ ፤ ቅድስት እየሉጣም የሦስት አመት ልጇን ይዛ ወደ ኢቆንዮን ሸሸች፡፡
.
🔷👉 ንጉሥ እለ እስክንድሮስ አስጠርቶ ክርስቶስን ካጅ ለጣዖት ስገጅ አላት። በእጅህ ሠርተህ ላቆምከው ምስል አልሰግድም አለች እምቢ ካልሽ በሰይፍ ትቀጫለሽ ብሎ አስፈራራት ፤ እርሷ ግን ምንም አልፈራችም - እምነታቸው ጠንካራ ነውና።
.
🔷👉 በብረት ጋን ውኃ አፍልታችሁ ከዚያ ውስጥ ጣሎአቸው ብሎ አዘዘ። የውኃው ፍላት እንደ ክረምት ነጎድጓድ ከ4 -15 ክንድ ያህል ይፈላ ነበር። በፈላው ውኃ ሊጨምሮቸው ሲወስዷቸው የኢየሉጣ ልብ በፍርሀት ታወከ በዚህ ግዜ በቅዱስ ቂርቆስ ላይ መንፈስ ቅዱስ አድሮ የእናቱን ፍርሀት አስወገደ፡፡እናቴ ሆይ በርች ፤ ጨክኝ ፤ አናንያን ፣ አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ ያድነን የለምን እያለ እናቱን እያደፋፈረ ከእሣቱ ቀረበ ፤ እርሷም ጨክና በፍጹም ልቧ ተያይዘው ከፈላው ውኃ ገብተዋል፡፡
.
🔴👉 ልዑል እግዚአብሔር መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ በበትረ መስቀሉ እሳቱን አጥፍቶ የፈላውን ውኃ አቀዝቅዞ አዳናቸው፡፡
.
🔷👉 ቅዱስ ገብርኤል ሆይ ሕፃኑን ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት እየሉጣን በንፍር ውኃ ከመቀቀል እንዳዳንካቸው እኛ አገልጋዮችህም በማናውቀው ሁኔታ የተዘጋጀልንን የጥፋት ወጥመድ ሁሉ አስወግድልን በላያችን ላይም በክፉ ሰዎች ምክንያት የተነሳብንን እሣት አጥፋልን ለእውነተኛ ሃይማኖት የጨከንንና የቆረጥንም አድርገን። የሰይጣንን ፈተና የምናልፍበት እውነተኛውን ጥበብ እንደ ነብዩ ዳንኤል አስተምረን።
.
🔴👉 ቅዱስ ቂርቆስና ቅድስት እየሉጣ ብዙ መከራ ከተቀበሉ በኋላ ጥር 15(፲፭) ቀን በሰይፍ ተመትተው ሰማዕትነትን ተቀብለዋል።

  ።።።።#ወስበሐት_ለእግዚአብሔር ።።።።
     ።።።።። #ወለወላዲቱ_ድንግል ።።።።።
     ።።።።። #ወለመስቀሉ_ክቡር ።።።።።

       ዲ/ን ዮናስ ዘ ሆለታ ደብረ ኤዶም
           መጋቢት 15/2017 ዓ.ም
                    ሆለታ

ፔጁን #Like_Follow_Share በማድረግ ትክክለኛ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት እንዲሁም መረጃ ያግኙ

🔴👉 በቴሌግራም | Telegram
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/joinchat_yonas_holet_debreedom

🔴👉 በዋትስአፕ | whatsapp
👇👇👇👇👇
https://whatsapp.com/channel/0029Va4Ter67T8bV5NlRGJ2w

🔴👉 1ኛ ዩትዩብ | 1st YouTube
👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@yonastube

🔴👉 2ኛ ዩትዩብ | 2nd YouTube
👇👇👇👇👇👇
https://youtube.com/@yonasmedia16




❗#ደብረ_ዘይት ❗
🔷የአብይ ፆም አምስተኛሳምንት
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
🔴👉 ደብረ ዘይት የዓብይ ፆም ፭ኛ ሳምንት ሲሆን ስለ ጌታችን እና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምፃት የዓለም ፍፃሜ የፍርድ ቀን በሰፊው
የሚነገርበት ሳምንት ነው። የማቴወስን ወንጌል ምዕ:፳፬/24ሙሉን ይመልከቱ።

🔵👉 ደብረ ዘይት ማለት የዘይት ተራራ ማለትም በወይራ ዛፍ የተሞላ በእሥራኤል ውስጥ የሚገኝ ተራራ ሲሆን ይኸውም ጌታችን እና አምላካችን መድኃኒታችን ፤ኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ቀን ሲያስተምር ውሎ የሚድርበት ተራራ ነው። ደብረ ዘይት ተራራ ጌታችን ለሐዋርያት ነገረ ምፅአቱን ያስተማረበት ታላቅ ቦታ ነው።

🔴👉 ዳግመኛም መምጣቱ በዚሁ ተራራ እንደሆነ ይታመናል፡፡ ይህን ዓለምንም አሳልፎ ለመረጣቸውና ላከበራቸው ዘላለማዊ መንግሥትን ሊያወርሳቸው እንደሚመጣ ይነገርበታል። ይህ ቀንም እኩለ ፆም በመባል የሚታወቅ ሲሆን በዚህች በተለየች ቀንም ሁሉም እንደ የሥራው ፍርዱን ከአምላክ የሚቀበልበት መሆኑ፤ መልካም ላደረጉ መልካም እንደሚመለስላቸው ክፉም ላደረጉ የክፋታቸውን ዋጋ እንደሚያገኙ ይሰበካል።

❗👉"እንሆ በቶሎ እመጣለሁ ለእያንዳንዱ እንደሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋርአለ"ራዕ፳፪፥፲፪

❗ባለው መሠረት ይመጣልና ሁላችንም ተዘጋጅተን እንጠብቀው። ❗

🔴👉 ዳግመኛም ሦስት ጊዜ የመለከት መነፋት ይሆናል ብለሃልና ይኸውም ሙታንን የሚያነቃ ነው ።

🔴#በመጀመሪያው አዋጅ
.    በዓለም ዳርቻ ሁሉ የተበተነ የሥጋ ትቢያ ይሰበሰባል
.    በላይ  ያለውና በታች ያለው
.    በባሕር ያለውና በየብስ ያለው
.    በአራዊትም ሆድ ያለው
.     በልዩ  ልዩ ሞት
.     ፈጽሞ ያረጀና የጠፋ
.     በምድር ላይ የወደቀ የሥጋ ቅርፊትም ሁሉ
.       #ወደ_ቀደመ_መገናኛው_ይሰበሰባል።

🔵#በሁለተኛውም አዋጅ
.      አጥንቶች ከሥጋና ከደም ጋራ ይያያዛሉ
.      ያለ መንቀሳቀስ ያለመነዋወጥ
.      እስከ ጊዜው ድረስ
.      #ፍጹም_በድን_ይሆናል ።

🔴#በሦስተኛው አዋጅ
  +  ሙታን እንደ ዓይን ጥቅሻ ይነሣሉ ።
     
🔵👉 ጻድቃንና ኃጥአን ክፉም ቢሆን በጎም ቢሆን በሕይወታቸው ዘመን ሁሉ
የሠሩትን ከምድር የተከተላቸውን ሥራቸውን ተሸክመው ይነሣሉ ።
     🔴ጻድቃንን    ===  በቀኝ
     🔵ኃጥአንንም === በግራህ
               ታቆማለህ ❗

🔴👉 ለመረጥሃቸው እንዲህ ብለህ በምስጋና ቃል ትነግራቸዋለህ።

🔴👉 #እናንተ_የአባቴ ቡሩካን
ዓለም ሳይፈጠር የተዘጋጀላችሁን
መንግሥተ ሰማያትን ትውርሱ ዘንድ
ወደ እኔ ኑ ።

❗ብራብ አብልታችሁኛልና
❗ብጠማ አጠጥታችሁኛልና
❗ እንግዳ ብሆን አሳድራችሁኛልና
❗ብታረዝ አልብሳችሁኛልና
❗ብታመም ጎብኝታችሁኛልና
❗ ብታሠር ጠይቃችሁኛልና

🔵👉ከዚህም በኋላ ወደ ግራህ ተመልሰህ ኃጥአንን በወቀሳ ቃል እግንዲህ ብለህ ትቆጣቸዋለህ

🔵👉 #እናንተ ርጉማን ከእኔ ወግዱ
ለሠይጣንና ለሠራዊቱ ወደ ተዘጋጀ
ወደ ዘላለም እሳት ሂዱ ።

ብራብ አላበላችሁኝምና
ብጠማ አላጠጣችሁኝምና
እንግዳ ብሆን አላሳደራችሁኝምና
ብታረዝ  አላለበሳችሁኝምና
ብታመም አልጎበኛችሁኝምና
ብታሠር  አላስፈታችሁኝምና

🔵👉 ያንጊዜ አመጽንና ሽንገላን ይናገር የነበረ  አፍና አንደበት ሁሉ ይዘጋል ።

🔵👉 ያን ጊዜ ሐዘን ይደረጋል ፤ የማይጠቅም ሐዘን ነው ።

🔵👉 ያን ጊዜ ጩኸት ይሆናል ፤ የማይጠቅም ጩኸት ነው ።

🔵👉 ያን ጊዜ ፍጅት ይሆናል ፤ የማይጠቅም ፍጅት ነው።

🔵👉 ያን ጊዜ ለቅሶ ይሆናል ፤ የማይጠቅም ለቅሶ ነው።

🔵👉 ያን ጊዜ ፍጻሜ ማኅለቅት እንደሌለው
እንደ ክረምት ውሃ እንባ ይፈሳል።

🔵👉 ነጣቂ መብረቅ ፤
የሚያስደነግጥ የነጎድጓድ ቃል ፤ የሚቆርጥና የሚከፍል ፤ የሚለይ ብርቱ ብልጭልጭታም ፤ ወደ እነርሱም ይላካል ፤ ይኸውም የኃጥአን እድላቸው ነው።

🔵👉 ያን ጊዜ ምድር አደራዋን ትመልሳለች ፤  እናትም የሴቷ  ልጅዋን ጩኸት አትሰማም ፤

🔵👉 ያን ጊዜ በሕይወትዋ ዘመን የሠራችው ፤ የነፍስ ሥራዋ ይገለጻል ።

❗በዚያም ጊዜ ትምረን ይቅርም ትለን ዘንድ

❗በበላነው ሥጋህ  በጠጣነውም ደምህ ተማጽነናል

❗አንተ ሥጋዬን ለበላ ደሜንም ለጠጣ
የዘላለም ሕይወት አለው ብለሃልና ።

❗#ዳግመኛም_በእናትህ_በማርያም_ተማጽነናል

🔴👉 ይህችውም አንተን በመውለድ እመቤታችንና የባሕርያችን መመኪያ ናት
አንተ  መታሰቢያሽን ያደረገ ስምሽንም የጠራ  የዘላለም ድኅነትነ
ይድናል ብለሃታልና ❗

🔴👉 ዳግመኛም በመላእክት አለቆችና በነቢያት ስደት  በሐዋርያትም ስብከት እና በካህናት ሥልጣን  በሰማእታትም በደማቸው ።

🔴👉 በወራዙትና በደናግል በመነኮሳትም ትዕግስት በወንዶችም በሴቶችም ምዕመናን ዕመነት ተማጽነናል ❗

🙏ዛሬ የስሙ ቀዳሽ ነገ ደግሞ የመንግስቱ ወራሽ ያደርገን ዘንድ የእርሱ መልካምና በጎ ፍቃዱ ይሁንልን። ከሠንበት ረድኤት በረከት ያሳትፈን። አሜን❗

🔴👉በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡት ጥቅሶችም፦

፩ተሰ.፬፥፲፫-እስከ ፍጻሜ፤
፪ጴጥ.፫፥፯-፲፭፤
የሐዋ.ሥራ ፳፬፥፩-፳፪ ።

  ።።።።#ወስበሐት_ለእግዚአብሔር ።።።።
     ።።።።። #ወለወላዲቱ_ድንግል ።።።።።
     ።።።።። #ወለመስቀሉ_ክቡር ።።።።።

       ዲ/ን ዮናስ ዘ ሆለታ ደብረ ኤዶም
           መጋቢት 14/2017 ዓ.ም
                    ሆለታ

ፔጁን #Like_Follow_Share በማድረግ ትክክለኛ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት እንዲሁም መረጃ ያግኙ

🔴👉 በቴሌግራም | Telegram
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/joinchat_yonas_holet_debreedom

🔴👉 በዋትስአፕ | whatsapp
👇👇👇👇👇
https://whatsapp.com/channel/0029Va4Ter67T8bV5NlRGJ2w

🔴👉 1ኛ ዩትዩብ | 1st YouTube
👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@yonastube

🔴👉 2ኛ ዩትዩብ | 2nd YouTube
👇👇👇👇👇👇
https://youtube.com/@yonasmedia16

Показано 20 последних публикаций.