Psychology (ሥነ-ልቦና) Zone 🧠


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Психология


Support channel for mental health awareness in Ethiopia. We post facts about psychology and psychological phenomenon.
''There is no health without Mental Health.''
Contact @FikrConsultSupportbot

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Психология
Статистика
Фильтр публикаций


እራስን ካለፉ መጥፎ ክስተቶች እስር ነፃ ማውጣት!

ህይወትህ ውስጥ በተፈጠረ አንድ አሉታዊ ክስተት ምክንያት፣ በአዕምሮህ አሁንም እየተመላለሰ የሚያስቸግርህ ሃሳብ አለ? ይህ ሃሳብ ስሜቱ ጠንካራ ከመሆኑ የተነሳ እንዴት አድርጌ ልርሳው ወይም ከትውስታዬ ልፋቀው ብለህ ታውቃለህ? 

አዕምሮህን እንደትልቅ ላይብረሪ ተረዳው። ከልጅነት እስከ እውቀት አንተ ጋር የተከናወኑ ነገሮች ሁሉ በትውስታ መልክ በውስጡ እንደመጽሃፍት ተሰድረውበት ይገኛሉ። ከእነዚህ ትውስታዎች አንዳንዶቹ  መልካም (አውንታዊ) ሲሆኑ ሌሎቹ ደግሞ መልካም ያልሆኑ (አሉታዊ) ሊሆኑ ይችላሉ። እነዚህ ትውስታዎች ቢያልፉም እንደተገነዘብናቸው መጠን ዛሬም ድረስ ውስጣችን አውንታዊ ወይም አሉታዊ  ስሜት ይፈጥራሉ።

በተለይ የአሉታዊ ክስተቶች ተፅዕኖ አሉታዊ ስሜት ውስጣችን በመፍጠር ብቻ የሚቆም አይደለም። ብዙ ግዜ በምንወስናቸው ውሳኔዎች ውስጥ ዛሬም ጣልቃ እየገቡ ትክክለኛ ውሳኔ እንዳንወስን ሊከለክሉንም ይችላሉ። ከዚያም ሲያልፍ ጉዳዩ በተፈጠረበት ወቅት ከደረስንባቸው መረዳቶችና ድምዳሜዎች የተነሳ፣ ወደፊት መፍጠር ከምንፈልገው ህይወት አንጻር የማይጠቅም እይታ (አመለካከት) እንድናዳብርም ያደርጋሉ።

የሚገርመው ብዙ ግዜ አሉታዊ ስሜት የሚፈጥሩትን ትውስታዎች በቀላሉ ማስታወስ፣ እንዲያውም እነዚህ ትውስታዎች ውስጥ ለረጅም ግዜ በመቆየት ራሳችንን ቶርቸር ማድረግ ለብዙዎቻችን ቀላል ነው። ምናልባት እነዚህ የምናስታውሳቸው ክስተቶች ያለፉና የማይደገሙ እንደሆኑ ብናውቅም አዕምሯችን ግን  ክስተቶቹ አሁን በዚህ ቅጽበት እየተከናወኑ ያሉ እስከሚመስል ድረስ በጠንካራ አሉታዊ ስሜት ውስጥ እንድንዘፈቅ ያደርገናል። ታዲያ እነዚህ ያለፉ፣ የማይደገሙ ክስተቶች አሁን እየፈጠሩብን ካለው አሉታዊ ስሜት፣ የውሳኔ ውስንነትና፣ ጎታች አመለካከት ተፅዕኖዎች ራሳችንን እንዴት ማላቀቅ እንችላለን?

ይህን ጥያቄ ስናነሳ ብዙዎች “እርሳው ባክህ”፣ ወይም “ለበጎ ነው” ወዘተ የሚል ምላሽ ይሰጡናል። ነገርግን “ያልተነካ ግልግል ያውቃል” ነውና እኛ ነገሩን ማስታወስ ፈልገን ሳይሆን አዕምሯችን ከኛ እውቅና ውጪ እያሳሰበን እንደሆነ ማን ይንገርልን?

እነዚህ በውስጣችን ተሰድረው ማለፋቸው ሳያንስ አሁንም ህይወታችንን ካመሰቃቀሉ ትውስታዎችን ለመፋታት የሚከተሉትን ማድረግ እንችላለን፦

1. እነዚህን ክስተቶች ከንደገና በማስታወስ ልንማርባቸው የምንችላቸው ነገሮች ካሉ ወረቀት ላይ በጽሁፍ ማስፈር።

2. እነዚህን ክስተቶች ከንደገና በማስታወስ ጉዳቱን የፈጠሩ ሰዎች ካሉ፣ በወቅቱ የነበረባቸውን የባህርይ፣ ስሜት እና የውሳኔ ውስንነት እንደገና አሁን ባለን መረዳት መመልከት። እነዚህ ውስንነቶች ባይኖሩባቸው ምን ሊያደርጉ ይችሉ እንደነበር ማሰብ፤ እነሱ የነበሩባቸውን ውስንነቶች እኛም ሳናውቅ እያንጸባረቅን እንዳልሆነ ማረጋገጥ።

3. የሚፈጥሩብን ስሜት ከባድ ከሆነና ከላይ ባደረግናቸው ልምምዶች ስሜቶቹንና ግንዛቤያችንን መለወጥ ካቃተን የባለሙያ ርዳታ እንፈልግ።

ዳንኤል አያሌው (Certified NLP Practitioner)

@melkam_enaseb


⬇️


ጤናማ ህይወትን መምራት እንዴት ይቻላል?

ጤናማ መሆን ማለት በአዕምሮ፣ በአካልና በስሜት ሙሉ ጤንነት ሲሰማን ማለት ነው፡፡

ጤናማ የአኗኗር ዘይቤን መከተል በበሽታ እንዳንጠቃ ከማገዙም በላይ ጤናችን ስንጠብቅ ለራሳችን ያለን ግምት መልካም እንደሚሆን የተለያዩ ጥናቶች ያስረዳሉ፡፡

ጤናማ የአኗኗር ዘይቤ ደስተኛ፣ የተረጋጋና ስኬታማ ህይወት እንድንኖር ይረዳናል፡፡

ምንም እንኳን የተለያዩ ውጫዊና ውስጣዊ ሁኔታዎች ጤናማ ህይወትን ለመምራት አሉታዊ ተጽዕኖ ቢፈጥሩም አኗኗራችንን እና ልማዶቻችንን በመቀየር ጤናማ ህይወት መኖር እንደሚቻል ነው ጥናቶች የሚያመላክቱት።

ጤናማ ህይወት ለመኖር የሰው ልጅ የተለያዩ የህይወት ዘይቤዎችን ይተገብራል፡፡ ከእነዚህም መካከል ዋና ዋናዎቹ፦

• የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ፣
• የተመጣጠነ ምግብ መመገብ
• ክብደትን መለካትና መቆጣጠር፣
• በቂ ውሃ መጠጣት፣
• ለረዥም ጊዜ ያለመቀመጥና ኮምፒውተርና ሌሎች ስክሪን ላይ የምናጠፋውን ጊዜ መቀነስ፣
• በቂ እንቅልፍ መተኛት፣
• ከመጠን ያለፈ አልኮል ያለመውሰድ፣
• ቁጣና መሰል ስሜቶችን መቆጣጠር፣
• ጭንቀትን ማስወገድ፣
•የጤና ክትትል ማድረግና መሰል የጤናማ አኗኗር ዘይቤዎች ይጠቀሳሉ፡፡

በተጨማሪም ከሰዎች ጋር ያለንን ማህበራዊ ግንኙነት በትኩረት መመልከት ያስፈልጋል። ከጓደኞች፣ ከቤተሰብና ጎረቤት እንዲሁም ሌሎች ሰዎች ጋር ያለንን የዕለት ተዕለት ግንኙነት ማሻሻልና መልካም ማድረግ ለጤናማ ህይወት አስፈላጊ እንደሆነ የሜዲሲን ኔት መረጃ ያመላክታል፡፡
 
@melkam_enaseb


ወርሃዊው የሜንታል ሄልዝ አዲስ መርሃ ግብር ቅዳሜ ጥር 25 ቀን 2016 ዓም አትላስ አካባቢ በሚገኘው በአዶር አዲስ ሆቴል ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ላይ ይደረጋል::

የዚህ ወር ርዕስም፡- “እንደ ህብረተሰብ የስነልቦና ቁስልን መገንዘብ” የሚል ሲሆን የዚህ ወር እንግዳችን የአሃ ሳይኮሎጂካል አገልግሎት መስራች እና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሞገስ ገ/ማሪያም ናቸው፡፡

ለመታደም ይህን መስፈንጠሪያ ይጫኑና ይመዝገቡ፡፡ ⬇️

https://forms.gle/Y8iPkGRELLR2cFW86

@melkam_enaseb


ታዳጊ ልጆች/ወጣቶች እና የአእምሮ ጤና፦

- የታዳጊ ልጆች እድሜ (ጉርምስና) ልዩና ወሳኝ ጊዜ ነው:: አካላዊ፣ ስነ-ልቦናዊና ማህበራዊ ለውጦቹም ከፍተኛ ናቸው።

- በዚህ ጊዜ ላይ ለድህነት፣ ለጥቃት (አካላዊም ፆታዊ) መጋለጥ እዚህ ዕድሜ ላይ ላሉ ልጆች ለአእምሮ ጤና መታወክ የበለጠ ተጋላጭ እንዲሆኑ ያደርጋል::

አጋላጮች፦
▫️የአቻ ግፊት
▫️አካባቢያዊ ተጽዕኖዎች
▫️አካላዊ ወይም ጾታዊ ጥቃት
▫️የቤት ውስጥ ሰላም መጓደል
▫️የማንነት ጥያቄ
▫️የሚዲያ ተጽዕኖ
▫️ከፍላጎት ጋር ተያይዘው የሚመጡ ችግሮች የተወሰኑት ናቸው።

- በተለይም የአዕምሮ እድገት ውስንነት፣ የተለያዩ የነርቭ ችግሮች፣ የቅርብ ቤተሰብ ድጋፍ የሌላቸው ታዳጊ ልጆች/ወጣቶች ደግሞ የበለጠ ለአዕምሮ ጤና መታወክ የተጋለጡ ናቸው።

ከስሜት ጋር የተያያዙ ችግሮች፦
* ከልክ በላይ ጭንቀት
* የስሜት መዋዠቅ
* ድባቴ፣ ራስን ማግለል አልፎም *በህይወት መቆየት አለመፈልግ

የባህሪ ችግሮች፦
° ትኩረት ማጣት፣
° ለነገሮች መቸኮል፣
° የፀባይ ለውጥ መኖር

የአመጋገብ ችግር፦
➡ ውፍረት እንዳይመጣ ከሚል ከፍተኛ የሆነ የአመጋገብ ችግር ነው።

የስነ-ልቦና ቀውስ፦
• ትምህርታቸውን በአግባቡ እንዳይከታተሉ ያደርጋል።
• ራሳቸውን በተለያዩ ሱሶች ይጎዳሉ።
• ከማህበረሰብ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ከፍተኛ ተጽዕኖ ያሳድርበታል።

- ይህ እንዳይሆን ምን እናድርግ?
▪️ቤተሰብ ልጆቹ በሰውነታቸው ላይ ለውጥ እየተካሄደ እንደሆነ በመረዳት ለልጆቹ ከምን ጊዜውም በላይ ቅርብ መሆን አለበት።
▪️ራሳቸውን በተለያዩ ዓይነት ስራዎቸ(እንደ ስፖርት ያሉ ነገሮች ላይ እንዲሳተፉ ማድረግ)፣ የመፍትሄ ሰዎች እንዲሆኑ፣ በጤነኛ ቤት ውስጥ እንዲኖሩ  በማድረግ ሁሉም ሰው የድርሻውን ማድረግ አለበት።

#WHO #TikvahEthiopia

@melkam_enaseb


የውድድር ስነ-ልቦና!

የውድድር ስነ ልቦና እንደዘርፉ ባለሙያዎች ትንታኔ በርካታ ጠቀሜታዎች አሉት፡፡

ውድድር ሰዎች አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ለማነሳሳት እንደሚረዳና አውጥተውም እንዲያሳዩበት እድል የሚፈጥር መሆኑ ይነገራል፡፡

ሆኖም የውድድር መንፈስ እንደጥቅሙ ሁሉ በትክክል መያዝ ካልተቻለ ችግር ሊሆን ይችላል፡፡ ጤናማ ያልሆነ ውድድርም የተለያዩ የጤና እክሎችን እንደሚያስከትልም ነው የሚነገረው፡፡

የውድድር ስነ-ልቦና ሰዎች በህይወታቸው ያልተመለከቱትን አቅጣጫ የሚመለከቱበት ነው። በተጨማሪም በተለያዩ መንገዶች የተሻለ ለመሆን እገዛ የሚያደርግ ነው።

ውድድር አሸናፊና ተሸናፊዎች ያሉበትና ሽንፈትን ፈጽሞ አለመቀበል ራስን አላስፈላጊ ጭንቀት ውስጥ ሲከት ይታያል፡፡ ከቤተሰብ ወይም ከጓደኛ አልያም በስራ አካባቢ የበዛ የውድድር መንፈስ ሲታይ ተመልክተው ይሆናል፡፡

ይህ የውድድርና የአሸናፊነት ጥማት የሌሎችን ስኬት ዕውቅና ከመንፈግ ጀምሮ የራስን ማንነት አለመቀበል ሊያስከትል እንደሚችልም ይገለጻል፡፡

ይህም ሰዎችን መዋሸት፣ ጫናዎች፣ ጭንቀት፣ የበታችነት ስሜት መሰማትና በቂ ነገር የለኝም በማለት ያሉበትን ቦታ አለመውደድ እና የማንነት ቀውስ ውስጥ ያስገባል።

ያለአግባብ የውድድር መንፈስ በራስ መተማመን የሚያመጣው ስሜት ነው፥ የራሴ ነገር በቂ አይደለም በሚል ሃሳብ ሌሎችን ለመምሰል ይሞክራሉ፡፡ ይህ ስሜት እየቆየ ሲሄድም ቁጣ፣ ንዴት፣ ቅናት እና መሰል ስሜቶች መገለጥ ይጀምራሉ፡፡

ይህ ስሜት ከየት እንደመነጨ ማስተዋል፣ የሰዎችን ስኬት መቀበል፣ የውድድሩ ፍላጎት ራስን ከማሳደግ የመነጨ ነው ወይስ ሌላ ምክንያት አለው የሚለውን መለየት ችግሩን በወቅቱ ለመፍታት እንደሚያግዝም ይነገራል፡፡

ባርኮት ጌቱ (የስነ-ልቦና አማካሪ)

@melkam_enaseb


ወርሃዊው የሜንታል ሄልዝ አዲስ መርሃ ግብር ቅዳሜ ጥር 4 ቀን 2016 ዓም በብይነ መረብ ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ላይ ይደረጋል::

በዕለቱ በአእምሮ ጤና ዙሪያ የሚያጠነጥነው “የሁሉ” የልብወለድ መፅሃፍ ላይ ከዶ/ር አዜብ አሳምነው ከዶ/ር ዮናስ ላቀው እንዲሁም ከደራሲው ከዶ/ር ዳዊት አሰፋ ጋር የኦንላይን ውይይት ይደረጋል፡፡

በዕለቱ ለመታደም ይህን መስፈንጠሪያ ይጠቀሙ፡፡ ⬇️

https://meet.google.com/gsd-iztg-rop

@melkam_enaseb


ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሠላም አደረሳችሁ!

መልካም በዓል!

@melkam_enaseb


ራስን ማጥፋት (suicide)

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በውጭ ሀገር በስፋት የምንሰማው ራስን የማጥፋት (suicide) ተግባር በሀገራችን በተለይም አንዲት እንስት 'ብንሄድ ይሻላል' ብላ Facebook ከለጠፈች እና ራሷን ካጠፋች ብኋላ በሀገራችን በተለይም በወጣቱ ዘንድ እንደተስፋፋ ግልፅ ነው።

ከዚህ ቀደም በሚዲያ አንሰማው ይሆናል እንጂ ይህ ራስን የማጥፋት ድርጊት በዩኒቨርስቲዎች እና በተለያዩ የትምህርት እና ስራ ቦታዎች ላይ ሲከሰት ነበር።

ምናልባትም ይህንን በራሳችን ላይ ለመፈፀም የሚያስገድዱ ሁኔታዎች ውስጥ ያለፍን ልንኖር እንችላለን። ሰው ነፍሱን በራሱ ለማጥፋት ምክንያት የሚሆኑ በጥቂቱ ብንጠቅስ፦

ሕይወት ፊቷን ስታዞር እና ቀን ሲጨልምበት፣ በሚያመነው ሰው ሲከዳ እና ተስፋውን ሲያጣ፣ የኑሮ ፈተና ሲበዛ እና መውጫ መንገድ ሲጠፋበት፣ በሚያሰበው ልክ ነገሮች ሳይከናወኑለት ሲቀሩ፣ በሚያየው ሁሉ ነገን ኣሻግሮ ማየት ሲያቅተው፣ በቤቱ፣ በትዳሩ ክብርን እና ተቀባይነት ሲነፈግ ወ.ዘ.ተ ናቸው።

በርግጥ በግለሰቡ ሁኔታ እና ጫማ ውስጥ ሆነን ነገሩን መመልከት እስካልቻልን ድረስ ስለዚህ ሁኔታ በድፍረት መናገር አንችልም።

የራስን ማጥፋት ውሳኔ ቅፅበታዊ ነው። ጥቂት ሰከንዶች ሺህ ዘመን መስለው ይታያሉ። ስቃይ እና ፈተና ዘላለማዊ ይመስልና አዕምሯችን ለውሳኔ እንድንጣደፍ ሆርሞኖችን ይቀሰቅሳል። ከዚያ ነገሮች ያበቃሉ። ሰዎች የሰዎችን ሁኔታ አያዩም እንጂ በርካቶች ለተመሳሳይ ወጥመድ ተጋልጠው በተዓምር ይሁን በራሳቸው ብርታት አምልጠዋል። ለዚህ ምስክሮችን መጥራት አያስፈልግም።

በዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ ራሳችንን እንዳናገኝ እነዚህ ነገሮችን ብንተገብር መልካም ነው ብዬ አስባለው።

1. ከእምነት ተቋማት አለመራቅ። ሀይማኖታዊነትን መላበስ በራሱ የመንፈስ ጥንካሬ ይሰጣል ብዬ አምናለው።

2. Multi-Professional-Friends ሊኖሩን ይገባል። በአንድ ሙያ መስክ ብቻ የተሰማሩ ጓደኞች አይኑሯችሁ። ሕይወትን ከተለያዩ አቅጣጫዎች ሊያስመለክቱ የሚችሉ ወዳጆችን መፍጠር ያስፈልጋል።

3. በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ የምክር አገልግሎት የሚሰጡ - Counselling and Guidance Service ተቋማትን መጎብኘት ያስፈልጋል። በዩኒቨርስቲዎች ውስጥ የሚገኙ እነዚህ ተቋማት በመሰል ማህበራዊ አገልግሎት ሰጪ ቦታዎች በየከተማው ላይ መስፋፋት አለባቸው።

ራሳቸውን ላጠፉ ፈጣሪ እዝነቱን ያድርግላቸው!

Credit: Workineh Gebeyehu Gomera

#EliasMeseret

@melkam_enaseb




⬆️ የእነዚህ ሁለት ምስሎች ትርጉም ጥልቅ ነው።

ምስል 1

ውጫዊ ገጽታው በፈገግታ የታጀበ ቢመስልም ውስጡ ግን ጥልቅ ሃዘን አለ::

ለዚያም ነው የቅርብ ሰዎቻችንን በፈገግታቸው ለክተን ውስጣዊ ህመማቸውን ሳናይላቸው ራሳቸውን ለማጥፋት ሲሞክሩ/ሲያጠፋ 'እኮ እንዴት' ብለን ስንገረም የምንስተዋለው።

ምስል 2

ይህ የፊት ገጽታ ለረጅም ጊዜ በድባቴ ስሜት ውስጥ ያለፋ ሰዎች ላይ የሚታይ የፊት ገጽታ ነው።

- Veraguth's fold (የአይን ቆዳቸው ቅጭም ማለት)
- Omega sign (የግንባር ቆዳቸው ኦሜጋ የምትባለዋን ፊደል የመስራት ያህል መሸብሸብ) ያመላክታል።

እና ምን ለማለት ነው የሳቀ ሁሉ ደስተኛ አይደለም። የውስጥ ስሜት ሁሌም ፊት ላይ ላይነበብ ይችላልና!

የድብርት ህመም ውጤታማ የስነልቦና እና የመድሃኒት ህክምና አለው!

ዶ/ር እስጢፋኖስ እንዳላማው (የአዕምሮ ህክምና ሬዚደንት ሃኪም)

@melkam_enaseb


የጭንቀት መነሻዎችና መፍትሄዎች!

የዓለም ጤና ድርጅት በፈረንጆቹ 2019 ባደረገው ጥናት በዓለም ዙሪያ 301 ሚሊየን ሰዎች በጭንቀት ውስጥ እንደሚኖሩ ገልጿል፡፡

ከእነዚህ ውስጥ 58 ሚሊየን የሚሆኑት ደግሞ ህጻናት እና ወጣቶች መሆናቸውንም ነው የገለጸው።

የአዕምሮ በሽታ ተብለው ከሚጠቀሱና በማህበረሰቡ በስፋት ከሚስተዋሉት መካከል ጭንቀት አንዱ ሲሆን፥ ከራስ ጋር እና ከሌሎች ሰዎች ጋር የሚኖር ግንኙነት ላይ ከፍተኛ ጫናን ሊፈጥር ብሎም የስራ ምርታማነትን እና ወደ ስኬት የሚደረገው ጉዞ ላይ እክል ሊፈጥር ይችላል፡፡

ይህም የተወሰነ የእድሜ ክልልን ብቻ ሳይሆን ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍልን የሚያጠቃ ነው፡፡

ያለበቂ ምክንያት ወይም ሊያስጨንቅዎት የሚገባው ነገር ካለፈ በኋላ ስሜቱ ሲቀጥል ጭንቀት ይባላል።

በአሁኑ ወቅት መረጃ ከመጠን በላይ መገኘት፣ ያለአግባብ የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም፣ ራስን ከሌሎች ሰዎች ጋር ማወዳደር፣ ጤና፣ ገንዘብ፣ የቤተሰብ ሁኔታ፣ የልጅነት ገጠመኞች፣ ከባድ አጋጣሚዎች፣ ለነገሩ የሚሰጡት ክብደት መጨመሩ እና ሌሎች የጭንቀት መንስዔዎች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

አብዛኞቹ የአዕምሮ በሽታዎች ያሉበት ደረጃ ባሕርያትና ሁኔታ ከሰውሰው ይለያያሉ፥ አንዳንዶቹ ላይ ቀለል ያለ ሌሎች ላይ ደግሞ ከባድ ወይም ውስብስብ ምልክቶችን ያሳያሉ።

የባህሪ መቀያየር እስከ ማህበራዊ ህይወት መገለል ያሉ ምልክቶችም ይታያሉ።

በተጨማሪም የእጅ መንቀጥቀጥ፣ ላብ ላብ ማለት፣ የልብ ምት መጨመር፣ የድካም ስሜት፣ የራስ ምታት፣ የተወሰኑ ነገሮች ላይ ደጋግሞ ማሰብ፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ደስታ ወይም ፍላጎት ማጣት ምልክቶች ናቸው፡፡

በአብዛኛው የማህበረሰብ ክፍል ሰዎች የሥነ-አዕምሮ በሽታ ተጠቂዎች እንደሆኑ አምነው ወደ ህክምና ተቋም ሄዶ መታከም አልተለመደም፤ ይህንን ተከትሎም በሽታው ከነበረበት ወደ ከፍተኛ ደረጃ በመድረስ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል።

የአዕምሮ ጤና ጉዳይ ከጊዜ ወደ ጊዜ አሳሳቢ ወደሆነ ደረጃ ተሸጋግሯል ይላሉ በዘርፉ ጥናት ያደረጉ ምሁራን፡፡

በአካባቢና በህይወትዎ የሚፈጠሩ ክስተቶች በአግባቡ ካልተቆጣጠሩት እና ራስዎ ላይ ትኩረት አድርገው ካልሰሩ የአዕምሮ ቀውስ ውስጥ ሊከትል ይችላል፡፡

አልፎ አልፎ ጭንቀትን በተለመደው የህይወት እንቅስቃሴ ውስጥ ለጥቂት ጊዜ ሊያጋጥም ይችላል። ሆኖም በጭንቀት ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች በራሳቸው ጥረትና በህክምና ባለሙያዎች እገዛ ተደርጎላቸው መዳን ይችላሉ፡፡

በዚህም ለራስ ጊዜ በመስጠት (በጥሞና) ነገሮችን ማሰላሰል፣ ተረጋግቶ የራስን ህይወት በትኩረት ማየት፣ አስተሳሰብ ላይ ረዘም ያለ ጊዜ በመውሰድ ፍተሻ ማድረግ፣ ለነገሮች የሚሰጡትን አመክንዮ እና ራስ ላይ በማተኮር መፍትሄ መስጠት ይቻላል፡፡

ከዚህ ባስ ካለ ወይም የባለሙያ እገዛ ካስፈለግዎ ሃኪምን ማማከር ተገቢ ነው፡፡

ቴዎድሮስ ድልነሳው (የሥነ-ልቦና ባለሙያ)

@melkam_enaseb




ወርሃዊው የሜንታል ሄልዝ አዲስ መርሃ ግብር ቅዳሜ ህዳር 22 ቀን 2016 ዓም አትላስ አካባቢ በሚገኘው በአዶር አዲስ ሆቴል ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ላይ ይደረጋል::

የዚህ ወር ርዕስም፡- “ራስን የማጥፋት” ስሜትን መረዳት'' የሚል ሲሆን የዚህ ወር እንግዳችን የሆኑት ገጣሚ ዶ/ር ፌበን ፋንጮ (ሳይካትሪ ሬዚደንት) ናቸው፡፡

ለመታደም ይህን መስፈንጠሪያ ይጫኑና ይመዝገቡ፡፡ ⬇️

https://forms.gle/uSWkjQdTrLmgLXVn9

@melkam_enaseb


ፀፀትን እንዴት ከራስዎ ያርቃሉ?

ሰዎች የሚሰማቸው የሃዘን፣ የቁጭት እና የመረበሽ ስሜት ድምር ፀፀት ይባላል፡፡

ፀፀት የተሻለ ስራን ለመስራት ወኔ ቢፈጥርም ከልክ ካለፈ ግን ቀላል የማይባል ተጽዕኖን ይፈጥራል፡፡

ለፀፀት የሚዳርጉ ምክንያቶች፦

- ሥህተት መስራት እና
- እንከን የለሽ ሆኖ ማደግ፦ በልጅነት ጊዜያቸው ፍጹም በመሆን ተጽዕኖ ውስጥ ያለፉ መሆን

ፀፀት በርካታ ጉዳቶች አሉት፡፡ ከእነዚህም ውስጥ፦

– የመስራት አቅምን ይነጥቃል
– የበታችነት ስሜት ይፈጥራል
– ተስፋ መቁረጥ
– ኢኮኖሚ ችግር እና
– ማህበራዊ ችግር

ፀፀት የከፍተኛ ጭንቀትና ድባቴ ውስጥ ከሚከቱ የስሜት መዘበራረቆች መካከል አንዱ ሲሆን፥ ይህ ከተባባሰ የአካልና የአዕምሮ እክልን ያስከትላል ይላሉ ባለሙያው፡፡

ፀፀት ውስጥ እንዳይገቡ መፍትሄው ምንድን ነው?

– ስህተትን አምኖ መቀበል
– የሚታረም ከሆነ በቻሉት አቅም ለማረም ጥረት ማድረግ
– አካባቢን መቀየር
– ሥር የሰደደ እና ድጋፍ የሚያስፈልግዎ ከሆነ የህክምና ባለሙያዎችን ድጋፍ ማግኘትና የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ፡፡
 
ሔኖክ ሃ/ማርያም (የሥነ-ልቦና ባለሙያ)

@melkam_enaseb


በልጅነት የእድሜ ክልል ውስጥ ያለፉ የህይወት መጥፎ አጋጣሚዎች በሰዎች የወደፊት ህይወት ላይ ጣልቃ በመግባት ይረብሻሉ። 

ወላጆችን በተለያዩ ምክንያት ማጣት፣  ጾታዊ ጥቃት እና ሌሎች መሠል ችግሮች ሲያጋጥሙ ሰዎች ለሱሰኝነት፣ ለድብርት እና ተስፋ የመቁረጥ ስሜት ይዳረጋሉ ይህም ደግሞ ለጸጸት እንደሚዳርጋቸውም ይገለጻል፡፡

የምንተገብራቸው ጉዳዮችን ጥቅም እና ጉዳት ላይ ጊዜ ወስዶ አገናዝቦ አለመወሰን፣ ምክንያታዊ ሆኖ አለመወሰን፣ በሰዎች ላይ ጸጸትን ሊያስከትሉ ይችላሉ፡፡

የደስታ፣ የብስጭት እንዲሁም የሀዘን ስሜት በሰዎች ላይ የሚስተዋል ቢሆንም፦

- ስሜታዊ ሆኖ ማሰብ፣
- የጓደኛ/ አቻ ግፊት 
- አልኮል መጠጣት
- የአደንዛዥ እጽ መጠቀም ለጸጸት እንደ መነሻ ምክንያት ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡

ለምን አደረኩ ብሎ እራስን መውቀስ ጠቃሚ ቢሆንም ትናንት ላይ ከመኖር ይልቅ ስለ ነገ መልካም ነገሮች ማሰብ ይጠቅማል። ለዚህም ከትናንት መጥፎ  የህይወት ገጠመኞች ትምህርትን በመውሰድ ለነገ አዲስ ህይወት መዘጋጀት በሰዎች ዘንድ ሊለመድ ይገባል።

አንዳንዶች ትናንት በገጠማቸው የህይወት መጥፎም ሆነ ጥሩ  ገጠመኞች ተምረው ያልፋሉ። ነገር ግን አሁንም ድረስ ባለፈ የህይወት ታሪካቸው ተሸፍነው የሚኖሩም አሉ።

የሚጸጸቱ ሰዎች ላይ፦

- የመበሳጨት፣
- ያለመረጋጋት
- የመጨነቅ ምልክቶች ይስተዋላሉ።

ከሚጸጽታቸው ጉዳይ ወይም በተደጋጋሚ አእምሯቸው ላይ እየተመላለሰ የሚረብሻቸውን ጉዳይ ጊዜ በመውሰድ ሊረዱት አልያም በጉዳዩ ላይ የባለሞያን ምክር ማግኘት አለባቸው።

ከመጥፎ ስሜቶች ለመውጣት እንደየሰው ጥንካሬ ጊዜ የሚፈልግ በመሆኑ በቅድሚያ ግን እራስን ከመውቀስ ይልቅ ለእራስ ይቅርታ ማድረግ ተገቢ ነው፡፡

ብሩክ ዩሃንስ (የስነ ልቦና ባለሙያ)

@melkam_enaseb


ለራስ ማድረግ መቻል!

ለቤተሰብ፣ ለጓደኛ፣ ለሌሎች ሰዎች ብዙ የምናደርጋቸው ነገሮች አሉ። ለምሳሌ ያህል እናስብላቸዋለን፣ እንጋብዛቸዋለን፣ እናዳምጣቸዋለን፣ ደስተኛ እንዲሆኑ የቻልነውን እንሞክራለን።

ለኛ ለራሳችንስ ምን አድርገን እናውቃለን?

ራሴን መቼ ነው የጋበዝኩት?
ራሴን መቼ ነው ያዳመጥኩት?
ራሴን መቼ ነው ያሰብኩለት?
ራሴን መቼ ነው የተንከባከብኩት? ወዘተ

በሌሎች ሰዎች ዘንድ ተቀባይነት ለማግኘት የሚያስችሉንን ነገሮች ሁሉ እናደርጋለን። ነገር ግን መቅደም ያለበት እራሳችንን መቀበል ነው ወይንስ በሌሎች ዘንድ ተቀባይነት ማግኘት ነው?

ከእኔ ውጪ ላሉ ነገሮች ሁሉ መትረፍ የምችለው እኔ በጥሩ ሁኔታ መኖር ከቻልኩ ብቻ ነው። ይህ እንዲሆን ደግሞ ለራሴ ብለን የምናደርጋቸው ነገሮች ሊኖሩን ይገባል።

ይህ ራስ ወዳድ መሆን አይደለም። እኔነቴን መንከባከብ፣ ማፍቀርና ፍሬያማ ማድረግ እንጂ።

ተመስገን አብይ (የስነ-ልቦና ባለሙያ)

@melkam_enaseb


Yetena Weg Clubhouse Discussion!

ከዶ/ር አስናቀ ልመነህ ጋር "የአዕምሮ ጤና ሰብአዊ መብት ነው" በሚለው የዓለም የአዕምሮ ጤና ቀን መሪ ቃል ላይ የምናደርገውን ውይይት ይቀላቀሉ።

🗓ጥቅምት 18 (እሁድ)
⏰ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት (በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር)

ውይይቱን ለመቀላቀል እዚህ ይጫኑ! ⬇️

https://www.clubhouse.com/invite/tA8LVpvi

@melkam_enaseb


ትኩረት መነፈግና ተጽዕኖው!

የሰዎችን ትኩረት ማጣት ጭንቀትና ከፍተኛ የሆነ ድባቴ እንዲሁም ከፍተኛ የጤና ቀውስ ሊያስከትል ይችላል፡፡

ሰዎች በተለይም ህጻናት ከሚገባው በታች ትኩረት ሲያገኙ የወደፊት ህይዎታቸው ላይ ተጽእኖ ሊያደርስ ይችላል፡፡

አንድ ሰው የሚገባውን ያህል ትኩረት ካላገኘ ምንም ያሕል አቅም ቢኖረውም እንኳን አቅሙን አውጥቶ ሊጠቀምበት የሚችልበት ዕድል አናሳ ነው፡፡

ግለሰቡ ‘’ሰው አይቀበለኝም፤ ልክ ላልሆን እችላለሁ’’ ብሎ ስለሚያስብ ያለውን አቅም ለሕብረተሰቡ ሳያንጸበርቅ ሊቀር ይችላል፡፡

ከሰው መሸሽ፣ ለራስ ዝቅተኛ የሆነ ስሜት መኖር፣ ከፍተኛ የሆነ የእንቅልፍ ማብዛት፣ የምግብ ፍላጎት ማጣትና ሌሎች ተያያዥ ችግሮች ሊመጡ ይችላሉ፡፡

ይህን ተከትሎም ሕመሙ ሲባባስ ሕክምና ሊያስፈልገው እንደሚችል መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡

ይህ ጉዳይ አብዛኛውን ጊዜ ችላ ይባላል። ‘’አመሏ/ሉ ነው፤ ብቻው/ዋን መሆን ትወዳለች/ይወዳል’’ በማለት የተለያዩ ስሞች ይሰጣሉ።

ይህም ሣይታወቅ ከፍተኛ የሆነ የአዕምሮ ችግር ውስጥ ሊያስገባ እንደሚችል ማወቅ ይገባል፡፡

መፍትሄው ምንድነው?

- ከቤተሰብ ጋር ማውራትና ችግሮችን መፍታት፣
- ከተለያዩ ሰዎች ጋር ሃሳብ መለዋወጥ ካለባቸው ድባቴ ወይንም ጥሩ ያልሆነ ስሜት እንዲወጡ ያግዛል፡፡

አበበ አምባው (የተቀናጀ የአዕምሮ ጤና ስፔሻሊስት)

@melkam_enaseb


⬇️

Показано 20 последних публикаций.