Meseret Media


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


መሠረት ሚድያ በኢትዮጵያ ለበርካታ አመታት በጋዜጠኝነት ሙያ ላይ የሰሩ ባለሙያዎች ወቅታዊ መረጃዎችን ለህዝብ ለማድረስ በማለም ያቋቋሙት ዲጂታል ሚድያ ነው።

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በፀደቁ ሁለት አዳዲስ አዋጆች ዙርያ ቅሬታ ያቀረቡ ፖለቲከኛ ዛሬ ጠዋት ታሰሩ 

(መሠረት ሚድያ)- ከሰሞኑ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በነበረ የምክር ቤት ስብሰባ ላይ ቀርቦ የፀደቀውን የየእርከኑ የምክር ቤት ተወካዮች ብዛት ለመወሰን የወጣ አዋጅ እንዲሁም የክልሉ ህገ መንግስትን እንደገና ለማሻሻል የወጣውን አዋጅ ተቃውመው ቅሬታ ያስገቡት ፖለቲከኛ ዛሬ ጠዋት ለእስር ተዳርገዋል።

መሠረት ሚድያ እንዳረጋገጠው የቦሮ ዲሞክራያዊ ፓርቲ የፖለቲካ አደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ እና የክልሉ የምክር ቤት ተመራጭ የሆኑን አቶ ዮሐንስ ተሰማ በፀጥታ ሀይሎች ተወስደዋል።

የቦሮ ዲሞክራያዊ ፓርቲ በውሳኔዎቹ ላይ ቅሬታ የነበረው ሲሆን ሶስቱ የምክር ቤቱ አባላት በወቅቱ ተቃውሞ አቅርበው ውሳኔውንም 'የህገ መንግስት አተረጓጎም ላይ የቀረበ ቅሬታ' በሚል ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ከተጨማሪ ጥያቄዎች ጋር አቅርበው ነበር።

"በዚህ ሁኔታ ያቀረቡትን ጥያቄ የተለያዩ አንድምታ እየሰጡ ይባስ ብለው ዛሬ አቶ ዮሀንስን አስረውታል" ብለው የክልሉ የመረጃ ምንጫችን ለሚድያችን ተናግረዋል።

የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ከየካቲት 10 እስከ 11 2017 ዓ/ም በአሶሳ ከተማ ባካሄደው መደበኛ ጉባዔ በስራ ላይ የሚገኘውን የክልሉን የምክር ቤት የመቀመጫ ቁጥር ከ99 ወደ 165 አሻሽሏል፡፡

የቦሮ ዲሞክራያዊ ፓርቲ ግን የህዝብና ቤቶች ቆጠራ ሳይደረግ 165ቱ የመቀመጫ ብዛት አሁን በስራ ላይ ለሚገኙ የምርጫ ክልሎች የተከፋፈለበት መንገድ የህዝብ ብዛትን ያማከለ አለመሆኑን እና ነባር የምርጫ ክልሎች የፈረሱበትና አዳዲስ ምርጫ ክልሎች የተቋቋሙበት ሂደት ህገ መንግስቱን የጣሰ በመሆኑን እንዲሁም በቂ ውይይትና ክርክር ያልተደረገበት መሆኑን በመግለፅ ቅሬታውን ገልፆ ነበር።

ፓርቲው በመግለጫው የክልሉ መንግስት "በሰላማዊና ህጋዊ መንገድ ያቀረብነዉን ጥያቄና ቅሬታ በሃይል ለመደፍጠጥ በፓርቲያችንና ፓርቲያችንን ወክለዉ የክልል ምክር ቤት አባል በሆኑ አመራሮቻችን ላይ የጀመረው ዛቻ፣ ማስፈራሪያና ወከባ የተጀመረዉን የመደብለ ፓርቲ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ላይ አደጋ የሚጥል በመሆኑ ከድርጊቱ እንዲቆጠብ እናሳስባለን" በማለት የካቲት 28/ 2017 ዓ/ም አሳስበው ነበር።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia

21.9k 0 21 10 220



'GTNA' ለሚድያ መገንቢያ የተሰጠውን 5 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ በ1 ቢልዮን ብር ሊሸጥ እያስማማ መሆኑ ታወቀ

- ቦታው ለጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ማስፋፊያ ተብሎ የተያዘ ነበር

(መሠረት ሚድያ)- ግሎባል ቴሌቭዥን ኔትዎርክ ኦፍ አፍሪካ (GTNA) በሚል ስያሜ የተቋቋመው እና በአፍሪካ ግዙፉ የሚድያ ተቋም ይሆናል የተባለለት ድርጅት ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሊዝ የተረከበውን 5ሺ ካሬ ሜትር ቦታ በደላሎች አማካኝነት ሊሸጥ መሆኑ ታውቋል።

GTNA መሬቱን ከተረከበ ሶስት አመት እንዳለፈው የጠቆሙት ምንጮቻችን አሁን ላይ ጋንዲ ሆስፒታል አካባቢ የሚገኘው ቦታው ታጥሮ ለመኪና ፓርኪንግ አገልግሎት ብቻ እየዋለ መሆኑን ከምስሎች እና ቪድዮዎች ጋር አያይዘው ለመሠረት ሚድያ ልከዋል።

"በመጀመርያ በደላሎች አማካኝነት ለሽያጭ የቀረበው በ1.4 ቢልዮን ብር ነበር፣ ገዢ ስላልተገኘ አሁን ላይ እስከ 1 ቢልዮን ብር እየተጠራበት ነው" የሚሉት ምንጮች አፍሪካን ማዕከል አድርጎ የአፍሪካን እውነት ለአለም ያሳውቃል የተባለለት ተቋም መሬቱን ለምን እንደሚሸጥ እንደማያውቁ ተናግረዋል።

አንድ የከተማ አስተዳደሩ ባልደረባ ግን መሬቱ ለሽያጭ መቅረቡን እንደሚያውቁ ለሚድያችን ገልፀው "በዲዛይኑ ላይ የተቀመጠውን ግዙፍ መንትያ ህንፃዎች ለመገንባት አበዳሪ ባንክ አልተገኘም፣ ምናልባት ሀብት ለማሰባሰብ ይሆናል" ብለዋል።

ግሩም ጫላ በተባለ ግለሰብ አማካኝነት በአፍሪካ ትልቅ ሚዲያ ሊገነባ እንደሆነ በርካታ ሚድያዎች ከሶስት አመት በፊት መዘገባቸው ይታወሳል። ለሚድያው ዋና መስሪያ ቤት የሚውለው ቁልፍ ቦታ ከጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ይዞታ ጭምር ተወስዶ እንደተሰጠ ምንጮቻችን ጠቁመዋል።

"መንግሥት ለጋንዲ መታሠቢያ ሆስፒታል የማስፋፊያ ህንፃዎች ግንባታ የሚሆን ሰፊ ቦታ አዘጋጅቶ ነበር፣ ይሁንና ከሆስፒታሉ ይዞታ ላይ 5,000 ካሬ ሜትር የሚሆን ቦታ በቂርቆስ ወረዳ 07 የግንባታ ፈቃድ ከሚሰጡ ሰዎች ጋር በተደረገ ውል በሆስፒታሉ ካርታ ላይ ሌላ አዲስ ካርታ ተሰርቷል" የሚሉት እኚህ የከተማ አስተዳደሩ ሰራተኛ በአንድ አጋጣሚ ለምን ብለው በጠየቁ የሆስፒታሉ ሰራተኞች ላይ ማስፈራራት ደርሶባቸው ነበርም ብለዋል።

ከጋንዲ ሆስፒታል ያገኘነው ተጨማሪ መረጃ እንደሚጠቁመው ሆስፒታሉ ለወላድ እናቶች አገልግሎት የሚውል የከርሰ ምድር ውሃ አስቆፍሮ የነበረ ሲሆን እሱም በGTNA ይዞታ ስር ሊሆን ይገባል የሚል አምባጓሮ ተነስቶ በመጨረሻም በ GTNA ይዞታ ስር እንደተጠቃለለ ታውቋል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia

29.7k 0 95 28 733



የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፍተኛ የስራ ሀላፊ የነበሩት ግለሰብ በኬንያ አየር መንገድ የካርጎ ማናጀር ሆነው ተቀጠሩ

- የኬንያ አየር መንገድ ልምድ ያላቸውን ኢትዮጵያውያን እያፈላለገ በከፍተኛ ደሞዝ እየቀጠረ ነው

(መሠረት ሚድያ)- የኬንያ አየር መንገድ (ኬንያ ኤርዌይስ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጭነት (ካርጎ) እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ማኔጂንግ ዳይሬክተር የነበሩትን አቶ ፍፁም አባዲን መቅጠሩ ተሰማ።

ኬንያ ኤርዌይስ አቶ ፍፁምን የካርጎ ክፍል ዳይሬክተር አድርጎ ከትናንት የካቲት 24/2017 ዓ/ም ጀምሮ በሃላፊነት እንደሾማቸው የመሠረት ሚድያ ምንጮች ጠቁመዋል።

አቶ ፍፁም በኢቪዬሽን ኢንደስትሪ ውስጥ ከ23 አመት በላይ የዘለቀ የስራ ልምድ ያላቸው ሲሆን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ በካርጎ አገልግሎት ዘርፍ በርካታ እውቀት እንዳላቸው ይነገርላቸዋል።

በተለይ በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ወቅት የአቪዬሽን ኢንዱስትሪው በከፍኛ ደረጃ በተጎዳበት ወቅት እና የኢትዮጵያ አየር መንገድም የመንገደኞች በረራ በተቀዛቀዘበት ወቅት ማኔጅመንቱ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የካርጎ ክፍሉ ከፍተኛ እንስቃሴ በማድረግ አየር መንገዱን ከኪሳራ መታደጉ ይታወሳል።

በዚህ አስቸጋሪ ወቅት አቶ ፍፁም የስራ ባልደረቦቻቸውን በማስተባበር ቀን ከሌሊት በመስራት ብቃታቸውን እንዳስመሰከሩ ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።

አቶ ፍፁም በትምህርት ዝግጅታቸው ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቁ ሲሆን ከአሜሪካው ኒው ሃምፕሻየር ዩኒቨርስቲ እና ከእንግሊዙ ኦፕን ዩኒቨርስቲ ሁለት የማስተርስ ዲግሪ ወስደዋል።

አቶ ፍፁም የዛሬ ሁለት አመት ገደማ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ከለቀቁ በኋላ ኑሮዋቸውን ከቤተሰባቸው ጋር በአሜሪካ አድርገው የነበረ ሲሆን በቅርብ ቀን ግን ወደ ኬንያ፣ ናይሮቢ እንደሚያቀኑ ታውቋል።

ግለሰቡ በትግራይ ጦርነት ወቅት በአንዳንድ አክቲቪስቶች ከፍተኛ የስም ማጥፋት ዘመቻ ተከፍቶባቸው የነበረ ሲሆን ይህ ስም የማጠልሸት ዘመቻ በተመሳሳይ የደረሰባቸው የአየር መንገዱ የቀድሞ ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም እንዲሁ በተመሳሳይ ስራቸውን በመቀየር ለግዙፉ ደልታ አየር መንገድ በአማካሪነት መስራት መጀመራቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ተፎካካሪ የሆነው ኬንያ ኤርዌይስ ልምድ ያላቸውን ኢትዮጵያውያን እያፈላለገ በከፍተኛ ደሞዝ እየቀጠረ እንደሆነ ምንጮች ለመሠረት ሚዲያ ገልፀዋል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia

48.9k 0 99 34 574



የዲጂታል ካርታ ጥያቄ ያቀረቡ ተገልጋዮች ይዞታቸውን መነጠቃቸውን ተናገሩ

(መሠረት ሚድያ)- በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የዲጂታል ካርታ ጥያቄ ያቀረቡ ተገልጋዮች ይዞታቸው ለካራ ቆሬ አፓርታማ እንደተሰጠባቸው ተናገሩ።

ለመሠረት ሚዲያ አስተያየታቸውን የሰጡ ባለጉዳዮች እንዳሉት ለመኖሪያ ቤት የዲጂታል ካርታ ጥያቄ በኦላይን ካቀረቡና የአገልግሎት ክፍያ በቴሌ ብር በኩሉ እንዲከፍሉ ከተደረገ በኋላ የኦላይን አገልግሎቱ መቋረጡን እና ሰነዳችሁ አልተሟላም ተብለው በኦላይን መልስ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል። 

አገልግሎቱ ለምን እንደተቋረጠባቸው ለመጠየቅ ወደ ክፍለ ከተማው ባቀኑበት ጊዜ ደግሞ ይዞታቸው ለካራ ቆሬ አፓርታማ እንደተሰጠባቸው በመሃንዲሶች በኩል መገለጹን እንደሰሙ አስረድተዋል።

"መፍትሄ የሚሰጠን አካል የለም" የሚሉት የክፍለ ከተማው የዲጂታል ካርታ ተገልጋዮች "ለበርካታ አመታት ለፍተን የሰራነውን ቤትና ይዞታ በቀላሉ ለካራ ቆሬ አፓርታማ ተሰጥቷል መባሉን አንቀበልም" ብለዋል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia

41.9k 0 111 56 362

ገቢው ለመቄዶኒያ መርጃ የሚውል!

“ጀስቲሲያ” ፊልም በአሜሪካ፣ ሲልቨር ስፕሪንግ ከተማ፣ AFI ሲኒማ ቤት። ይሄን ምርጥ ስራ አጣጥማችሁ ለሜቄዶኒያም የበኩላችሁን ድጋፍ አድርጉ።

📍ቦታ፡ AFI Movie Theatre, 8633 Colesville Rd, Silver Spring, MD 20910
🎟 የመግብያ ዋጋ፡ $25
📞 ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ወይም ትኬት ለመቁረጥ በ 703-855-9422 ይደውሉልን

ሰው ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው።

44.2k 0 13 10 271

የማስታወቂያ እድል ከመሠረት ሚድያ ጋር!

መሠረት ሚድያ በሶሻል ሚድያ አካውንቶቹ ላይ ውስን የማስታወቂያ እድሎችን ይዞ ቀርቧል፣ በዚህም መሠረት ማስታወቂያ ማሰራት የምትፈልጉ እና ተገቢውን ምዝገባ ያደረጋችሁ ድርጅቶች ልታነጋግሩን ትችላላችሁ።

ኢሜይል: meseretmedia@dontsp.am

*የምዝገባ ፈቃዳቸውን እና አድራሻቸውን የሚያቀርቡ አስተዋዋቂዎችን ብቻ እንቀበላለን

*ለግዜው የሪል እስቴት ማስታወቂያዎችን አንቀበልም

መሠረት ሚድያ

@MeseretMedia

52.5k 0 17 15 261

በአዲስ አበባ ከተማ የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት በሽታ መከሰቱን የጤና ባለሙያዎች ጠቆሙ

(መሠረት ሚድያ)- በመዲናዋ ውስጥ የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት (አተት) በሽታ እንደተከሰተ የጤና ባለሙያዎች ለሚድያችን በሰጡት ቃል አሳወቁ።

የበሽታው መከሰትን ለመሠረት ሚድያ ያረጋገጡት እነዚህ በአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ስር ባሉ ጤና ጣቢያ የሚሰሩ የጤና ባለሙያዎች ስጋቱ ለህዝብ ይፋ ሆኖ የጥንቃቄ እርምጃዎችን በተመለከተ መልዕክት አለመተላለፉ የበለጠ ጉዳት እንዳያስከትል ስጋታቸውን ገልፀዋል።

"ሰሞኑ ከፍተኛ የአተት በሽታ ተከስቷል፣ ነገር ግን ምንም እየተባለ አይደለም። እኛም በየጤና ጣቢያ ሸራ ወጥራቹ ዝም ብላችሁ ስሩ እየተባልን ነው" ያለው አንድ የጤና ባለሙያ በአስደንጋጭ መልኩ 'vibrio cholerae' የተባለው የኮሌራ አምጪ ተህዋስም በምርመራ ወቅት በከተማው ውስጥ መገኘቱን ተናግሯል።

"እንደምናውቀው አተትም ሆነ ኮሌራ በጣም ተላላፊ ነው፣ ነገር ግን እየሆነ ያለው ነገር ፍፁም ተቃራኒ ነው" የሚሉት የጤና ባለሙያዎቹ ከ100 በላይ የበሽታው ተጠቂዎች አሁን ላይ ባሻ ወልዴ ተብሎ በሚጠራው የአራዳ ክፍለ ከተማ ጤና ማዕከል ገብተው እንደሚገኙ አረጋግጠዋል።

"አሁን በዚህ ሰአት በርካታ ታማሚዎችን ካለ በቂ መከላከያ እና መሸፈኛ እያከምን ነው፣ አስቸኳይ መፍትሄ እንሻለን" ያሉን ሌላኛው የጤና ባለሙያ ናቸው።

ከሰሞኑ በጋምቤላ ክልል ኑዌር ብሔረሰብ ዞን አራት ወረዳዎች የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት በሽታ ተከስቶ የዘጠኝ ሰዎችን ሕይወት መንጠቁ ታውቋል።

በዚህ ዙርያ ከጤና ሚኒስቴር ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት በመሞከር ማብራርያ እናቀርባለን።

ፎቶ: ፋይል

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia

49.5k 0 442 16 311

የግሪክ ኮሚኒቲ ትምህርት ቤት ቦታው ለኦሮሚያ ክልል ፕሬዝደንት ፅ/ቤት ማስፋፊያ ስለሚፈለግ እንዲነሳ ታዘዘ

(መሠረት ሚድያ)- እድሜ ጠገቡ የግሪክ ኮሚኒቲ ትምህርት ቤት እና የግሪክ ክበብ አሁን ላይ የሚገኙበት ቦታ ለኦሮሚያ ክልል ፕሬዝደንት ፅ/ቤት ማስፋፊያነት ስለሚፈለግ እንዲነሱ እንደተነገራቸው ማረጋገጥ ችለናል።

የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 የመሬት ልማት እና አስተዳደር ፅ/ቤት በቅርቡ ለትምህርት ቤቱ እና ክበቡ በፃፈው ደብዳቤ ይዞታው ከኦሮሚያ ክልል ፕሬዝደንት ፅ/ቤት ማስፋፊያነት እንደሚፈለግ ገልጿል።

ትምህርት ቤቱ ደብዳቤው እንደደረሰው ለቦርዱ እንዲሁም ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ለትምህርት ሚኒስቴር እና ሌሎች ለሚመለከታቸው አካላት ማሳወቁን እና መልካም ምላሽ እየጠበቀ መሆኑን መሠረት ሚድያ የደረሰው መረጃ ይጠቁማል።

ከአንድ አመት ተኩል በፊት የግሪክ ኮሚኒቲ ት/ቤት ከፍርድ ቤት የእግድ ትዕዛዝ ውጪ ግቢው በፖሊስ እንደተያዘበት ለህዝብ አሳውቆ ነበር። በወቅቱ ጉዳዩን ሰምተው ለማብረድ ወደ ስፍራው ያቀኑት በኢትዮጵያ የግሪክ አምባሳደር እንደተገፈተሩ እና ከግቢው ለቀው እንዲወጡ እንደተደረጉ ይታወሳል።

"አምና ትምህርት ቤቱ ላይ ያ ሁሉ ወከባ እና የስም ማጥፋት ሲደርስ ለምን እንደነበር የገባን አሁን ነው፣ መሬቱን ለመንጠቅ የተጠነሰሰ ሴራ ነበር" በማለት አስተያየታቸውን የሰጡ አንድ ጉዳዩን የሚከታተሉ የኮሚኒቲው አባል ደብዳቤው ለብዙዎች አስደንጋጭ እንደሆነ ጨምረው ተናግረዋል።

የግሪክ ኮሚኒቲ ትምህርት ቤት ለበርካታ አስርት አመታት ተማሪዎችን ተቀብሎ ሲያስተምር የቆየ ሲሆን የግሪክ ኮሚኒቲ በኢትዮጵያ ያለውን ከ200 አመት በላይ ታሪክ ይዞ የቆየ መሆኑ ይነገርለታል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia

44.8k 0 185 52 507

ዋልታ ከፋና ጋር ከተዋሀደ በኋላ በርካታ የስራ ቅጥሮች በትውውቅ እየተፈፀሙ እንደሚገኙ ሰራተኞች ተናገሩ

(መሠረት ሚድያ)- ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በቅርቡ ከዋልታ ሚድያ እና ኮሙኒኬሽን ማዕከል ጋር ውህደት መፈፀሙን ተከትሎ በርካታ ህገወጥ የሆኑ የትውውቅ የስራ ቅጥሮች እንደተፈፀሙ ሰራተኞች ተናግረዋል።

እነዚህ ሰራተኞች ለመሠረት ሚድያ በሰጡት ጥቆማ ፋና ውህደቱን ተከትሎ አብዛኛውን ነባር፣ ጠንካራ እና ታታሪ የሚባሉ ሰራተኞቹን ያገለለ የደረጃ ሹመት ሰጥቷል ብለዋል።

"በሹመቱ 95 ፐርሰንት የሚሆነውን ቦታ ያገኙት የቀድሞዋ የፋና ብሮድካስቲንግ ባልደረባ፣ የአሁኗ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ የቅርብ ወዳጆች ናቸው" የሚሉት ሰራተኞቹ ከዳይሬክተር እስከ ስራ አስፈጻሚነት ደረጃ እንዲሾሙ የተደረጉት በዚህ መልኩ መሆኑን አስረድተዋል።

ቀደም ሲል ለሀገርና ለተቋሙ በታታሪነት የሚሰሩ ሰዎች እንዲገፉ ምክንያት ሆኗል በተባለው አካሄድ ዙርያ አስተያየት የሰጡን አንድ የተቋሙ ሰራተኛ "እንደበቀል እንዳያድጉ እና እንዲገፉ የተደረጉ በርካቶች ናቸው" ብለዋል። በሌላ በኩል ካለምንም መስፈርት፣ ብቃትና ለዘርፉ ልምድ ሳይኖራቸው በስራ አስፈጻሚነት እና በዳይሬክተርነት እንዲሾሙ የተደረጉ በርካቶች እንዳሉ ከነማስረጃው ለሚድያችን ሰጥተዋል።

መሠረት ሚድያ የተመለከተው አንድ የተቋሙ የቅርብ የቅጥር አካሄድ ከዳይሬክተር በታች ያሉት ብቻ ለውድድር ክፍት ሆነው ሌላውን በሹመት መፈፀሙን ያመላክታሉ። በዋልታ ይሰሩ የነበሩ በርካታ አንጋፋ ባለሙያዎችም ከስራ እንደተገለሉ ወይም ዝቅ ብለው እንዲሰሩ እንደተደረጉ በተጨማሪ ታውቋል።

ሚድያውን በዚህ ዙርያ ለማነጋገር የሞከርን ቢሆንም ምላሽ አላገኘንም፣ ወደፊት ተጨማሪ ማብራርያ ካገኘን በዜናው ዙርያ እንመለስበታለን።

ከፋና በተጨማሪ በሌላኛው የመንግስት ሚድያ ኢቢሲ ውስጥ 400 ሰራተኞች በሀሰተኛ ወይም ፎርጅድ ዶክመንት ተቀጥረው መገኘታቸውን መሠረት ሚድያ በቅርቡ መዘገቡ ይታወሳል። ይህን የኢቢሲ ድርጊት ያጋለጠው የተቋሙ ሰራተኛ የሽብር ክስ ቀርቦበት ለእስር ተዳርጎ እንደነበር መረጃ አቅርበን ነበር።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia

37.5k 0 82 22 464



የዲጂታል ስክሪን ማስታወቂያ ባለቤቶች ከነገ ጀምሮ የብልፅግና ፓርቲ ማስታወቂያን በግዴታ እንዲያሳዩ ሊደረጉ መሆኑ ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የዲጂታል ስክሪን ማስታወቂያ ባለቤቶች እና ህንፃዎቻቸው ላይ የማስታወቂያ ስክሪን የገጠሙ ባለሀብቶች ከነገ ጀምሮ የብልጽግና ፓርቲ መልእክት የሆኑ ምስሎችን እና ጽሁፎችን በአስገዳጅነት እንዲያሰራጩ ጥብቅ ትዕዛዝ እንደተላለፈላቸው ታውቋል።

በራሳቸው ወጪ አውጥተው የሰሩትን የዲጂታል ስክሪን ለፖለቲካ ፓርቲ መልዕክት ማስተላለፊያ መደረጉ በህዝብ ዘንድ ለአንድ ወገን ያደሉ ወይም የፓርቲ አባል እንደሆኑ እንዳይወሰድባቸው የሰጉት ግለሰቦቹ አማራጭ እንዳጡ እና አጣብቂኝ ውስጥ እንደገቡ ተናግረዋል።

የብልጽግና ሹሞች ቁጣ በተቀላቀለበት መልዕክት በአስገዳጅነት ማስታወቂያውን ከነገ ጀምሮ ለማሰራጨት እንዳስገደዷቸው ጨምረው ተናግረዋል።

"ከሳምንት በፊት ለአፍሪካ ህብረት ስብሰባ መሪዎች ሲመጡ 'እንኳን ደህና መጣችሁ' የሚልና ስለ አፍሪካ ህብረት ስብሰባ ተመሳሳይ ትዕዛዝ ተላልፎ  ያስተላለፍነው የፖለቲካ ይዘት የሌለው በመሆኑ ነበር" የሚሉት የማስታወቂያ ድርጅቶቹ "አሁን የታዘዝነው የፖለቲካ ፓርቲ  መልእክት ገበያው በተዳከመበት መሀል ከህዝቡ ጋር እንዳያቃቅረን ስጋት አለን" ብለዋል።

በሌላ በኩል በአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ስብሰባ ወቅት በርካታ የመኪና ኪራይ ስራ ላይ የተሰማሩ ድርጅቶች ተሽከርካሪዎቻቸውን በነፃ ለስብሰባው አገልግሎት እንዲሰጡ ተገደው እንደነበር ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።

"ቢዝነስ በተዳከመበት በዚህ ወቅትም ይሁን ድሮ በአመት አንዴ ጥሩ ስራ የምንሰራው እንደ አፍሪካ ህብረት ያሉ ስብሰባዎች ሲመጡ ነበር" የሚሉት የመኪና አከራዮቹ አሁን ግን እሱንም በግዴታ እንደተነጠቁ እና መኪናዎቻቸው የተመለሱላቸው ስብሰባው ካለቀ በኋላ መሆኑን አስረድተዋል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia

70.3k 0 70 29 600



ኮምቦልቻ አቅራቢያ በእስር ላይ የነበሩ ከ890 በላይ እስረኞች በዛሬው እለት ተለቀቁ

(መሠረት ሚድያ)- በደቡብ ወሎ ኮምቦልቻ ከተማ አቅራቢያ 'ጮሬሳ' ተብሎ በሚጠራው ካምፕ ውስጥ ከ890 በላይ የፖለቲካ እስረኞች በምግብ እና በውሃ ብክለት ምክንያት ታመው እንደነበር መሠረት ሚድያ የዛሬ ሳምንት ቅዳሜ መዘገቡ ይታወሳል።

ሚድያችን ከእስረኞች ቤተሰቦች በወቅቱ የደረሰው መረጃ እንደሚጠቁመው ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ እስረኞች ህይወታቸው አልፏል።

አሁን በደረሰን መረጃ መሠረት በዚህ ካምፕ ውስጥ ታስረው የነበሩ ሁሉም እስረኞች በዛሬው እለት ተለቀዋል፣ የተለቀቁበት ምክንያትም ግን እንዳልተነገራቸው ታውቋል።

በሽታው በካምፑ ውስጥ የተቀሰቀሰው የካቲት 6/2017 ዓ/ም መሆኑን የተናገሩት የታሳሪ ቤተሰቦች ለእስረኞቹ የሚቀርበው ውሃ ከወንዝ እየተቀዳ በመሆኑ ለበሽታው ምክንያት ሳይሆን አይቀርም ብለው ነበር።

አሁን ነፃ የሆኑት ግለሰቦቹ በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሰውን የፋኖን ኃይል ትደግፋላችሁ በሚል ከመስከረም ወር ጀምሮ ከተለያዩ የአማራ ክልል ወረዳዎች በማሰባሰብ ከኮምቦልቻ ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኛው ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ ታስረው እንደነበር ቤተሰቦቻቸው ተናግረዋል።

ከእስረኞቹ ውስጥ 220ዎቹ ፍርድ ቤት ቀርበው ዋስትና የተፈቀደላቸው ቢሆንም ታሳሪዎቹን የተረከበው የፌደራል ፖሊስ እስረኞቹን መልቀቅ የሚችለው መከላከያ እንጂ ፍርድ ቤት አይደለም በሚል ሊለቃቸው ፍቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል እንደነበር ታውቋል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia


በምሥራቅ ጎጃም በድሮን ጥቃት ሕፃናትን ጨምሮ 16 ሰዎች መገደላቸውን የዓይን እማኞች እና ቤተሰቦች ተናገሩ

(መሠረት ሚድያ)- በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ሐሙስ የካቲት 13/2017 ዓ.ም. ተያይዘው በተሠሩ አራት ቤቶች ላይ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት 16 ሰዎች ሲገደሉ 10 ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን ቤተሰቦች እና የዓይን እማኞች ለቢቢሲ ተናገሩ።

ጥቃቱ በዞኑ ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ እነገሽ ቀበሌ (ሐሙስ ገበያ) በተባለች አነስተኛ የገጠር ከተማ ሐሙስ ረፋድ 5፡00 ሰዓት አካባቢ በሦስት ሱቆች እና ሻይ ቤት ላይ መድረሱን ቢቢሲ ያናገራቸው ነዋሪዎች ገልጸዋል።

"[ድሮን] ስትዞረን ነበር" ያሉ አንድ የዓይን እማኝ ጥቃቱ ከደረሰበት ስፍራ በግምት 100 ሜትር ርቀት ላይ እንደነበሩ ጠቅሰው፤ የጥቃቱ ሰለባዎች መንገድ ላይ ሲጫወቱ የነበሩ ህፃናት፣ ገበያተኞች እና ሻይ እየጠጡ የነበሩ ሰዎች ናቸው ብለዋል።

ከፍተኛ ፍንዳታ መፈጠሩን የሚናገሩት እማኙ፤ ወዲያው "አካባቢውን አቧራው፤ የቤቱ ፍርስራሽ በጭስ" እንዳፈነው እና ድንጋጤ እና ግርግር እንደተፈጠረ ገልፀዋል።
ሌላ የዓይን እማኝም በፍንዳታው አካባቢው በአቧራ ጭስ መሸፈኑን ጠቅሰው፤ በስፍራው ለመተያትም አስቸጋሪ እንደነበር ተናግረዋል።

በደቂቃዎች ውስጥ ጥቃቱ ወደ ተፈፀመባቸው ቤቶች ደርሰው የቆሰሉ ሰዎችን እንዳወጡ እና አስከሬን እንዳነሱ የተናገሩት ሌላ የዓይን እማኝ "የሚጫወቱ ህፃናት እና ቆርቆሮ ሊገዙ የመጡ ሰዎች ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል" ብለዋል።

Via BBC News Amharic

@MeseretMedia

45.1k 0 26 20 492

ኤርትራ በአዲስ አበባ ያለውን ኤምባሲዋን እየዘጋች መሆኑ ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- ካለፉት ሁለት አመታት ወዲህ ግንኙነታቸው እየሻከረ የመጣው የኢትዮጵያ እና ኤርትራ መንግስታት የቃላት ጦርነት መጀመራቸውን ተከትሎ ኤርትራ በአዲስ አበባ የሚገኘውን ኤምባሲዋን እየዘጋች መሆኑ ታውቋል።

የዛሬ ሰባት አመት ገደማ ግንኙነታቸውን ያደሱት ሁለቱ ሀገራት በትግራይ የተካሄደው ደም አፋሳሽ ጦርነት ላይ በጋራ ቆመው ቢዋጉም የፕሪቶሪያው ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ ግንኙነቱ መሻከር መጀመሩ ይታወሳል።

"ኤምባሲው ከዚህ በኋላ የአፍሪካ ህብረት ተወካዩን ይዞ ይቀጥላል፣ በኢትዮጵያ ያለውን የኤምባሲ ስታፍ ግን እያሰናበተ ነው" ያሉን አንድ የኤምባሲው ምንጫችን ሂደቱ በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

ከቀናት በፊት የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ የኤርትራ መንግስት የአፍሪካ ቀንድን የማተራመስ አላማ ይዞ እየተንቀሳቀሰ ነው፣ በአስቸኳይ እንዲቆም መደረግ አለበት በማለት አልጀዚራ ላይ በቀረበ ፅሁፋቸው አስነብበው ነበር።

የኤርትራው የኢንፎርሜሽን ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል ለዚህ ምላሽ የሰጡ ሲሆን የፕሬዝደንቱን አስተያየት አጣጥለው የኢትዮጵያን መንግስት የቀጠናውን ሀገራት በመተንኮስ ከሰዋል።

የኤርትራ ኤምባሲ መዘጋት መጀመርን ተከትሎ በአስመራ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እጣ ፈንታ እስካሁን አልታወቀም። ላለፉት ጥቂት አመታት ኤምባሲው ክፍት ቢሆንም አምባሳደር ሳይመደብበት መቆየቱም ይታወሳል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia

54.7k 1 84 40 386

በአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ወቅት በጅምላ የታሰሩ ወጣቶች እስከ 20 ሺህ ብር ከፍለው እየተለቀቁ መሆኑ ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- እሁድ እለት የተጠናቀቀው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ስብሰባ ከመጀመሩ በፊት ባሉት ቀናት አዲስ አበባ ውስጥ የታሰሩ ወጣቶች ገንዘብ ከፍለው እየተለቀቁ መሆኑ ታውቋል።

እነዚህ ልደታ አካባቢ በአፈሳ መልክ የታሰሩ ወጣቶች ጦር ሀይሎች አካባቢ ታስረው የቆዩ ሲሆን አሁን ላይ እስከ 20 ሺህ ብር እየከፈሉ፣ ሌሎቹ ደግሞ ለህዳሴ ግድብ የ2 ሺህ ብር ቦንድ እንዲገዙ እየተደረጉ መለቀቃቸውን መሠረት ሚድያ ከታሳሪዎቹ እና ቤተሰቦቻቸው ሰምቷል።

"በስብሰባው ምክንያት ተሰብስባቹ ተቀመጣችሁ ተብለው ቁጭ ብለው ከሚበሉበት በረንዳ የታፈሱት ባለፈው እሮብ ነበር" የሚለው አንድ የመረጃ ምንጫችን ከትናንት ጀምሮ የተወሰኑት እየተፈቱ መሆኑን ተናግሯል።

"ቦንድ ያልገዙት ተቀምጠው እኛ ወጣን" ያለን ደግሞ ለቦንድ 2 ሺህ ከፍሎ ነፃ የወጣ ግለሰብ ነው።

ከሰሞኑ እንደ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ያሉ ተቋማት ከእስር ተፈቺዎችን እና ተገልጋዮችን ለማገልገል ወይም ከእስር ለመልቀቅ የ 500 ብር የህዳሴ ግድብ ቦንድ በግዴታ እያስገዙ እንደሆነም ለማወቅ ችለናል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia

55.5k 0 58 31 502

ባሳለፍነው ሳምንት ሸራተን ሆቴል አቅራቢያ ከፍተኛ የፍንዳታ አቅም ያለው ፈንጂ ተገኝቶ እንደነበር ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- ባሳለፍነው ሳምንት በአዲስ አበባ ከተማ ሸራተን ሆቴል አቅራቢያ ከፍተኛ የፍንዳታ አቅም ያለው ፈንጂ በአሰሳ ወቅት ተገኝቶ እንደነበር ታውቋል።

እሮብ እለት፣ ማለትም የካቲት 6/2017 ዓ/ም ምሽት አምስት ሰአት ላይ ከቤተመንግስት አቅጣጫ ወደ ሸራተን መውረጃ ጠመዝማዛው መንገድ አቅራቢያ TNT የተባለ ፈንጂ መገኘቱን የፀጥታ ምንጮች ለመሠረት ሚድያ አረጋግጠዋል።

የፈንጂው መገኘት አሁን ላይ ከተጠናቀቀው የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ጋር የተገናኘ ይሁን አይሁን እስካሁን ይፋ አልተደረገም።

ሚድያችን በዚህ ዙርያ ተጨማሪ መረጃ ከፌደራል ፖሊስ እና ከአዲስ አበባ ፖሊስ የጠየቀ ቢሆንም "መረጃው የለንም" የሚል ምላሽ አግኝቷል።

ይሁንና የፌደራል ፖሊስ ባሳለፍነው ሀሙስ፣ ወይም ፈንጂው ከተገኘበት ከአንድ ቀን በኋላ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ ችሎት ባቀረበው ክስ 13 ሰዎችን የአፍሪካ ህብረት የሚታደሙ ሰዎችን ለማጥቃት በማሴር ክስ መስርቷል።

ክሱ በግልፅ ድርጊቱ ይህ ሸራተን አካባቢ ጋር ከተገኘው ፈንጂ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ባይጠቅስም "የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ አባል ሀገራት እና ከተለያዩ የአለማችን ክፍሎች ስብሰባው ላይ ለመታደም በሚመጡ አመራሮች እና ጋዜጠኞች ላይ የሽብር ጥቃት እንዲፈፅሙ" ሲንቀሳቀሱ መያዛቸውን ይገልፃል።

በዚህ ዙርያ የመንግስት አካላት መግለጫ ሊሰጡ እየተዘጋጁ እንደሆኑ የደረሰን ተጨማሪ መረጃ ይጠቁማል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia

65.6k 0 67 20 343
Показано 20 последних публикаций.