Фильтр публикаций


የእግሊዝ የእግርኳስ ህግ አውጪዎች ማህበር አዲስ ህግ ማጽደቃቸዉ ተሰማ።

የሚባክኑ ደቂቃዎችን ለመቀነስ ሲባል አንድ ግብ ጠባቂ ለ 8 ሰከንድ ኳስ ይዞ የሚቆይ ከሆነ ለተጋጣሚው ቡድን የማእዘን ምት እንዲሰጥ የሚያደርግ ህግ ጸድቋል።

አዲሱ ህግ በአለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር ቦርድ (IFAB) ቅዳሜ በሰሜን አየርላንድ ባደረገው አመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ በሙሉ ድምፅ የጸደቀ ሲሆን በአሜሪካ ከጁን 15 እስከ ጁላይ 13 በሚካሄደው የፊፋ የአለም ክለቦች ዋንጫ ላይ ተግባራዊ እንደሚሆን ተነግራል።

ፕሪሚየር ሊግ 2ን ጨምሮ ከ400 በላይ ግጥሚያዎች ላይ የተሞከረው ህግ ተግባራዊ የተደረገው አሁን ያለው የስድስት ሰከንድ ህግ በአግባቡ ባለመተግበሩ ነው። አሁን ዳኞች ግብ ጠባቂዎችን ከመቅጣታቸው በፊት የአምስት ሰከንድ ቆጠራ ያስጠነቅቃሉ።

በተጨማሪም፣ IFAB በተጨማሪም አጥቂው አካል ከሁለተኛ እስከ የመጨረሻው ተከላካይ እኩል ከሆነ ከጨዋታ ውጪ የሚደረጉ ሙከራዎችን እንዲቀጥል ድምጽ ሰጥቷል።

via @mussesolomon


Репост из: Nexline Business Group
🚘 የሚፈልጉትን መኪና በባንክ 50/50 አማራጭ አቀረብንሎ👇

🆕 BYD Qin plus
🆕 BYD Yuan up
🆕 BYD Yuan plus
🆕 Toyota BZ3
🆕 Toyota BZ4X
🆕 Toyota Rav4
🆕 ID6 and ID4
🆕 BYD E2 እና ሌሎችም

💥አዲስ እና ፀዴ ፀዴ 😉 መኪናዎች፣ በተመጣጣኝ ዋጋ፣ በቀላል እና ፈጣን ሂደት፣ የሚፈልጉትን መኪና ከትንንሽ እስከ ቅምጡ መኪናዎች ሁሉንም ሞዴሎች አካትተን በባንክ አመቻችተን አቅርበንሎታል።

📞 ዛሬውኑን ያግኙን! +251911593030
+251911260700

👇ለበለጠ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ።👇

👉 https://t.me/NexlineBusinesGroup
👉 https://t.me/NexlineBusinesGroup


ዜጎቻቸው ዘግይተው ጋብቻ የሚመሰርቱባቸው ሀገራት

ጋብቻ የሰው ልጆች ህይወት ምርጫዎች መካከል አንዱ ሲሆን ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች ቀድመው አልይም ዘግይተው ጋብቻ ፈጽማሉ፡፡

በወጣው መረጃ መሰረት የምስራቅ አውሮፓ እና እስያ ሀገራት ዘግይተው ጋብቻ ይፈጽማሉ የተባለ ሲሆን አፍሪካዊቷ ሞዛምቢክ ደግሞ በወጣትነታቸው ጋብቻ የሚመሰረትባት ሀገር ተብላለች፡፡

በኢስቶኒያ በአማካኝ የሀገሪቱ ዜጎች በ36 ዓመታቸው ጋብቻ ይመሰርታሉ የተባለ ሲሆን በሞዛምቢክ ግን በ23 ዓመታቸው የሚያገቡ ሲሆን ጣልያን፣ ስሎቬንያ እና ናሚቢያ በአማካኝ ዘግይተው ጋብቻ ከሚፈጸምባቸው ሀገራት መካከል ዋነኞቹ ናቸው፡፡

Via @mussesolomon


ፖፕ ፍራንሲስ የመተንፈስ ችግር እንደገጠማቸው ቤተ ክርስቲያኗ አስታወቀች

ለሁለት ሳምንታት ያህል በሳንባ ምች ህመም ህክምና ላይ ያሉት የሮማ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ የመተንፈስ ችግር እንዳጋጠማቸው ቫቲካን አስታወቀች።

ያጋጠማቸው የመተንፈስ ችግር ከህመማቸው ጋር የማይያዝ እንደሆነም ቫቲካን ገልጻለች። አርብ ዕለት ሳል ካጋጠማቸው በኋላ ተከታታይ ማስታወክ እና ድንገተኛ የመተንፈስ ችግር እንደ ገጠማቸው ተናግረዉ ፤ ዶክተሮቻቸው በአሁኑ ወቅት ስለ ፖፑ ሁኔታ ከመናገር ተቆጥበዋል።

Via @mussesolomon


ቻይና የኤአይ(Ai) ባለሙያዎቿ ወደ አሜሪካ እንዳይጓዙ አገደች

የዓለም ቴክኖሎጂ የበላይ ለመሆን ብርቱ ፉክክር ላይ የሚገኙት አሜሪካ እና ቻይና አሁን ደግሞ ፉክክራቸው ወደ ኤአይ ዞሯል፡፡

እገዳው የተጣለው ምዕራባዊን ሀገራት የቻይና ባለሙያዎችን አስረው ሊደራደሩ ይችላሉ ተብሏል።

የዲፕሲክ ኤአይ ሞዴል መስራች በቅርቡ በፓሪስ በተካሄደው የኤአይ(Ai) ጉባኤ ላይ እንዲገኝ ቢጋበዝም በፍራቻ ምክንት ሳይገኝ ቀርቷል ተብሏል

Via @mussesolomon


ዜሌንስኪ በደጋሚ ወደ ዋይታ ሀውስ ለመመለስ ጥያቄ አቀረቡ

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮልድሚር ዜሌንስኪ በደጋሚ ወደ ዋይታ ሀውስ እንዲመለስ ጥያቄ አቅርቦ የነበረ ቢሆንም ትራምፕ ውድቅ አድርገነዋል ብለዋል። እሱ መዋጋት ነው የፈለገው እራሱ ይወጣው ብለዋል።

ፕሬዝዳንት ዜሌንስኪ ደግሞ "ትናንት ባደረከው ነገር ተፀፅተሃል ወይ ተብሎ ከFox news ለቀረበለት ጥያቄ "ጥሩ አልነበረም ብዬ አስባለሁ" ሲል ምላሽ ሰጥቷል አያይዘውም " እኔ እውነተኛ ሆኜ መኖር ብቻ እፈልጋለሁ፣ እንዲሁም አጋሮቻችን ሁኔታውን በትክክል እንዲገነዘቡ እፈልጋለሁ፣ እኔም ነገሩን በትክክል ለመረዳት እፈልጋለሁ። ይህ የወዳጅነታችንን እንዳንጣስ ስለሆነ ነው።" ብሎ ተናገረ።

Via @mussesolomon


ኢለን መስክ ለ14ኛ ጊዜ የልጅ አባት መሆኑ ተገለጸ

የዓለማችን ቁጥር አንድ ባለጸጋ የሆነው ኢለን መስክ ሰዎች ብዙ ልጆችን እንዲወልዱ በማበረታታት ይታወቃል እናም ለ14ኛ ጊዜ የልጅ አባት መሆኑ ተገለጸ፡፡

የ352 ቢሊዮን ዶላር የተጣራ ሀብት ባለቤት የሆነው ኢለን መስክ ቴስላ፣ X(Twitter)፣ ኒውራሊንክ ፣ ስፔስኤክስ እና ሌሎች በርካታ ኩባንያዎችን የመሰረተው እና ባለቤት የሆነው ኢለን መስክ በቅርቡ ወንድ ልጅ አባት መሆኑ ተገልጿል ።

Via @mussesolomon


ቻይና በዓለማችን ውድ የሚባለውን አዲስ ማዕድን አገኘች፡፡

የዓለማችን ሁለተኛዋ ልዕለ ሀያል ሀገር የሆነችው ቻይና ቶሪየም የተሰኘውን ተፈላጊ ማዕድን ማግኘቷን አረጋግጣለች፡፡

አሁን ላይ የዓለም የሀይል ምንጭ ወደ ታዳሽ እና የከፋ የአካባቢ ብክለት የማያደርስ አማራጭ በመፈለግ ላይ ሲሆን የጸሀይ ሀይል፣ ከውሃ የሚመነጭ የሀይል አማራጭ እና የኑክሌር ሀይል ዋነኛ አማራጮች ናቸው፡፡

ዩራኒየም እና ቶሪየም ደግሞ ለኑክሌር ሀይል አማራጭ ዋነኛ ግብዓት ሲሆኑ ዩራኒየም ማዕድን እንደ ልብ አለመገኘት፣ ማዕድኑም በተወሰኑ የዓለማችን ሀገራት ብቻ መገኘቱ እጥረቱን ሲያባብሰው ቆይቷል።

ቻይና አገኘሁት ያለችው ቶሪየም ማዕድን አንድ ሚሊዮን ቶን መጠን አለው የተባለ ሲሆን፤ ሀገሪቱ የሀይል ፍላጎቷን ለ60 ሺህ ዓመታት እንድትሸፍን ይጠቅማታል ተብሏል፡፡ እንደ መንግስታዊው የሳውዝ ቻይና ፖስት ዘገባ ከሆነ ቶሪየም ማዕድኑ የተገኘው በደቡባዊ የሀገሪቱ አካባቢ ሞንጎሊያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው፡፡

ቶሪየም ማዕድን በተለይም የኑክሌር ሀይልን ለማመንጨት፣ ቴሌስኮፕ ሌንሶችን፣ ሴራሚክ፣ ካሜራዎችን እና ሌሎች ተፈላጊ የኤሌክትሮኒክስ ምርቶችን ለማምረት ይውላል ።

Via @mussesolomon


ጄዲ ቫንስ "አመስጋኝ አይደለህም ፤ያ ጥሩ ነገር አይደለም" ሲሉም ፕሬዝዳንት ዜሌንስኪ ተናግረዋል ።

ይህንን ተከትሎ ፕሬዝዳንት ቮልድሚር ዜሌንስኪ በX ገጹ ላይ "አሜሪካ አመሰግናለሁ፣ ስለ ድጋፍህ አመሰግናለሁ፣ ለዚህ ጉብኝት አመሰግናለሁ። @POTUS፣ ኮንግረስ እና የአሜሪካን ህዝብ እናመሰግናለን።

ዩክሬን ፍትሃዊ እና ዘላቂ ሰላም ያስፈልጋታል፣ እናም እኛ በትክክል እየሰራን ነው። ብለዉ አመስግነዋል ።

Via @mussesolomon


1446ኛው  የረመዳን ወር ነገ  ቅዳሜ የካቲት 22 ይጀመራል።

የካቲት 21/2017 በሳዑዲ አረቢያ መንግሥት የጨረቃ ክትትል ኮሚቴ የረመዳን ወር ጨረቃ ዛሬ መታየቷን አስታውቋል። በዚህም መሰረት ነገ ቅዳሜ የ1446ኛው የረመዳን ፆም የመጀመሪያው ቀን ይሆናል። ዛሬ የተራዊህ ሶላት የሚጀመር ሲሆን ነገ የረመዷን ጾም ይጀምራል።

Via @mussesolomon


የዓለማችን በጣም አማላይ የእግር ኳስ ተጫዋች

የቼልሲው ኮከብ ኮል ፓልመር በአድናቂዎች ዳሰሳ ላይ 'የእንግሊዝ አማላይ ተጫዋች' ተብሎ ተሰይሟል።

በዳሰሳ ጥናቱ ላይ 2,500 የብሪቲሽ ጎልማሶች የተጠየቁ ሲሆን የጥናቱ ውጤት እንደሚያሳየው የቼልሲ ኮከብ ኮል ፓልመር በ19 በመቶ ድምጽ አግኝቶ አንደኛ ወጥቷል በመቀጠልም የሪል ማድሪድ ኮከብ ቤሊንግሃም በ17 በመቶ ድምጽ ሁለተኛ ወጥቷል። ክርስቲያኖ ሮናልዶ በ6 በመቶ ድምጽ በማግኘት የስምንተኛ ደረጃን ይዟል።

Via @mussesolomon


የንግድ ባንክ አዲስ ህግ

ከየካቲት 17 ጀምሮ ከንግድ ባንክ ስራ አስኪያጅ በተላከው ደብዳቤ መሰረት የባንኩ ቴለሮች/ገንዘብ ከፋዮች/ የባንኩን ደንበኞች ተቀማጭ ቀሪ ገንዘብ መጠን ማየት እንደማይችሉ ገልጸዋል። የደንበኞችን ቀሪ ሂሳብ ማየት የሚችሉት ከፍተኛ ማኔጅሮች ብቻ ናቸው። ባንኩ ይህን እርምጃ የወሰደው እየተንሰራፋ የሄደውን የገንዘብ ማጭበርበር ለከት ለማስያዝ እንደሆነ ተጠቁሟል።

Via @mussesolomon


" ከየካቲት 24 በኋላ የፋይዳ መታወቂያ የሌለው ደንበኛ የኢትዮ ጅቡቲ የባቡር ትኬት መቁረጥ አይችልም " - የኢትዮ ጅቡቲ ባቡር አክስዮን ማህበር

የኢትዮ ጅቡቲ የባቡር መንገድ አክስዮን ማህበር ለመንገደኞች የጉዞ ትኬት የሚያገኙበትን መንገድ ከሰኞ የካቲት 17/2017 ዓ/ም ጀምሮ  ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ ማድረጉን እና ክፍያው የሚፈጸመው በቴሌብር መሆኑን ገልጸው አገልግሎቱን ለማግኘት ለሃገር ውስጥ ተጠቃሚዎች የፋይዳ የምዝገባ ቁጥራቸውን ኢትዮጵያዊ ላልሆኑ ተጠቃሚዎች ደግሞ ፓስፖርታቸውን በመጠቀም ትኬት ማግኘት እንደሚችሉ አሳውቀዋል። በትኬት ዋጋ ላይ ምንም አይነት ጭማሪ አለመኖሩን እና ነባሩን ዋጋ ዲጂታላይዝ ብቻ መደረጉን ገልጸዋል ።

Via @mussesolomon


ትራምፕ አሜሪካ 5 ሚሊዮን ዶላር 'የወርቅ ካርድ' ለሀብታም የውጭ ዜጎች ትሸጣለች ብለዋል።

ፕሬዚዳንት ትራምፕ ለሀብታም የውጭ ሀገር ዜጎች በ 5 ሚሊዮን ዶላር የ"ወርቃማ ካርድ" መሸጥ እንደሚጀምሩ አስታወቁ። ይህ ካርድ ለመኖርና ለመስራት መብት የሚሰጥ ይሆናል።

ትራምፕ ፕሮግራሙ በሁለት ሳምንት ውስጥ እንደሚጀምር በማመን ሚሊዮኖች የሚሆኑ ካርዶች ሊሸጡ እንደሚችሉ አስተያየት ሰጡ። ይህ አዲሱ ተቀዳጀ የኢንቨስትመንት ቪዛ (EB-5) ፕሮግራምን የሚተካ ይሆናል።


Via @mussesolomon


ኑሮ ርካሽ የሆነባቸው የዓለማችን 10 ከተሞች የትኞቹ ናቸው?

መገበያያ ገንዘብ የመግዛት አቅም፣ የነዋሪ ብዛት ፣የተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ፣ የቆዳ ስፋት እና የሸቀጦች አማካይ ዋጋን መሰረት በማድረግ ኑሮ ርካሽ የሆነባቸው የዓለማችን ከተሞች ዝርዝር ይፋ ተደርጓል።

የሶሪያዋ ደማስቆ በአንጻራዊነት ኑሮ ያልተወደደባት ከተማ ሆናለች። የኢራኗ ቴህራንም ሁለተኛዋ ከተማ ተብላለች።




Via @mussesolomon


የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ማክሰኞ የካቲት 18 ቀን 2017 እንደሚያካሂድ አሳውቋል።

ለጨረታ የሚቀርበው የውጭ ምንዛሪ መጠን 60 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ሲሆን፣ ጨረታው ለሁሉም ባንኮች ክፍት እነደሚሆን ገልጿል።



Via @mussesolomon


በ አዋሽ_ፈንታሌ የወጣው የ ሚቴን ጋዝ መጠን እየጨመረ መሆኑን ተከትሎ እሳተ ገሞራ ሊያስከትል እንደሚችል ተገለ

በአዋሽ ፈንታሌ ከጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የወጣው የሚቴን ጋዝ መጠን እየጨመረ መሆኑን ተከትሎ እሳተ ገሞራ ሊያስከትል እንደሚችል በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የስነምድር መምህር  ጤናዓለም አየነው (ፕ/ር) ገለጹ።

የመሬት መንቀጥቀጥ እና የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ የተያያዙ ናቸው ያሉት ፕሮፌሰር ጤናዓለም፤ በኢትዮጵያ አዋሽ ፈንታሌ አካባቢ እስካሁን ባለው መረጃ መሰረት ፍንዳታ ከመከሰቱ በፊት የሚፈጠሩ ሁኔታዎች  እየተከሰቱ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ ካላት የኢነርጂ ሀብት አንዱ ከመሬት ውስጥ የሚወጣ የሙቀት ሀይል ቢሆንም የሚቴን ጋዝ መውጣት ጥሩ አጋጣሚ አለመሆኑን ተናግረዋል።

ሚቴን ጋዙ የአየርን የሙቀት መጠን የሚጨምር በመሆኑ በኢትዮጵያ የተከሰተው መጠኑ ከፍ እያለ ከሄደ በአካባቢ፣ በእጽዋትና እንስሳት ላይ ጉዳት ያስከትላል ሲሉ ተናግረዋል።

የአፋር ክልል ሰመራ ዩኒቨርስቲ ወደ ስፍራው ተመራማሪዎችን ልኳል።


Via @mussesolomon


ለሊት ከ8:46-8:48 ባለው ጊዜ ከወትሮ የተለየ በርካታ ሰዎችን ከተኙበት ጥንልቅ እንቅልፍ ሁሉ ሳይቀር የቀሰቀሰ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል።

እስካሁን ባለው መጠኑን  የዓለም አቀፍ ተቋማት ከ5.0 - 5.3 በሬክተር ስኬል መዝግበውታል።

የጀርመን ጂኦ ሳይንስ ጥናትና ምርምር ማዕከል መንቀጥቀጡ ከጭሮ ሰሜን ምዕራብ 60 ኪሎሜትር ላይ የተከሰተ ነው ብሏል።

የአሜሪካው ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ደግሞ ቦታውን በተመሳሳይ ገልጾ መጠኑ በሬክተር ስኬል 5.3 ነው ሲል አመልክቷል።



Via @mussesolomon


የጾመ ኢየሱስ ሱባዔ (ዐቢይ ጾም)ን አስመልክቶ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት መልዕክት አስተላልፈዋል።

መግለጫው ከላይ ተያይዟል።



Via @mussesolomon


አሜሪካ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ልትወጣ መሆኑ ተሰምቷል

የሪፐብሊካን ህግ አውጪዎች አሜሪካን ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለማስወጣት እንቅስቃሴ ጀመሩ።

ህግ አውጪዎቹ ዓለም አቀፉ ድርጅት የአሜሪካን ጥቅም ማስቀደም አልቻለም፤ ከፕሬዝዳንት  ትራምፕ “አሜሪካ ትቅደም” ፖሊሲ ጋር አይጣጣምም ብለዋል።

ድርጅቱ አምባገነኖች አሜሪካን እና አጋሮቿን የሚያጠቁበት መድረክ ሆኗል ሲሉ በመውቀስም ለዚህ ተቋም የሚከፈል ገንዘብ እንዲቆም ጠይቀዋል።

አሜሪካ ከየትኛውም ሀገር በበለጠ ለተመድ ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ የምታደርግ ሲሆን፥ በፈረንጆቹ 2022 ብቻ 18 ቢሊየን ዶላር ገንዘብ መስጠቷ መገለፁን አልዓይን ዘግቧል።


Via @mussesolomon

Показано 20 последних публикаций.