YABERUS WOLKITE SCHOOL


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Образование


Educational chanal
NANO የኤሌክትሮኒክሰ ማሰልጠኛ ማዕከል
%1 የሞባይል ሀርድዌር እና ሶፍትዌር ጥገና ስልጠና በተግባር
%2 የኮምፒውተር ሃርድዌር እና የሶፍትዌር ጥገና ስልጠና
%3የኦዲዮ (tv,tep,jipas dicoder......)
ለበለጠ መረጃ 0922730604,0913504243

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Образование
Статистика
Фильтр публикаций




Репост из: Неизвестно
Biology unit one for grade 12.pdf
483.4Кб












FIRST SEMISTER Civics Grade 9F&G.pdf
715.8Кб
From Grade 9F&G Civics Teachers






#ማስታወቂያ

በ 2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ)  ለመማር ያለፋችሁ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን በትምህርት ድህረገጽ እስከ ጥቅምት 14/2016 ዓ.ም ድረስ ማስተካከል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ማሳሰቢያ፡

 በልዩ ሁኔታ በአዳማ እና በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዪኒቨርሲቲዎች መማር የምትፈልጉ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና የማይሰጥ መሆኑን አውቃችሁ ምርጫችሁ ውስጥ በማካተት መመደብ የምትችሉ መሆኑ እናሳውቃለን።

የትምህርት ሚኒስቴር






For only yaberus


ማ ስታወቂያ

ውድ የ2015 ትምህርት ዘመን ተፈታኞች በሙሉ:

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ነገ በ29/01/2016 ዓ.ም ከጥዋቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ ተፈታኞች የሚከተሉትን ሶስት አማራጭ አድራሻዎችን ብቻ በመጠቀም ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ፡፡
• በዌብ ሳይት፡- eaes.et
• በአጭር የጽሁፍ መልዕክት፡- 6284
• ቴሌግራም አድራሻ፡- @eaesbot

ጥብቅ ማሳሰቢያ፡-

ከላይ ከተገለጹት የውጤት መግለጫ አማራጮች ውጪ ሌላ የውጤት መግለጫ መንገዶች የሌሉ መሆኑን እያሳወቅን በማመሳሰል ውጤት እንገልጻለን ከሚሉ ከማንኛውም አጭበርባሪዎች እራስዎን ይጠብቁ። በተጨማሪም ተቋሙ ውጤት ለማሳየት ክፍያ የማይጠይቅ መሆኑን ይወቁ።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

አጠቃቀም
በዌብ ሳይት ለማየት

1. eaes.et ብለው ብሮውዘር ላይ ይጻፉ
2. በመቀጠልም በሚመጣው ገጽ ላይ የአድሚሽን ቁጥር (ሬጅስትሬሽን ቁጥር) እና የመጀመሪያ ስም ይጻፉ
3. Check Result የሚለውን በመጫን ውጤትዎን ማግኘት ይችላሉ
በአጭር የጽሁፍ መልዕክት
6284 የአድሚሽን ቁጥር (ሬጅስትሬሽን ቁጥር ) ብቻ ጽፎ አንዴ ብቻ በማላክ መልስ እስኪያገኙ ይጠብቁ
በቴሌግራም ቦት
1. @eaesbot ይፈልጉ
2. የሚመጡ አማራጮችን በመከተል የአድሚሽን ቁጥር (ሬጅስትሬሽን ቁጥር) ያስገቡ በመቀጠልም መልስ እስኪያገኙ ይጠብቁ።




የ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይሆናል

ወላይታ ሶዶ፣ መስከረም 27፣ 2016 የ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ እንደሚሆን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ሚኒስቴሩ ተማሪዎች ትክክለኛውን መረጃ ከትምህርት ሚኒስቴር ገጽ ላይ እንዲከታተሉም አሳውቋል፡፡

በዚህም ዙሪያ ትምህርት ሚኒስቴር ነገ መስከረም 28 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ ስድስት ሰዓት ላይ መግለጫ እንደሚሰጥ ገልጿል፡፡

ምንጭ፦(ኤፍ ቢ ሲ)


በቅድሚያ የያበሩስ ወልቂጤ አጠ/2ኛ/ደ/ት/ቤት በ2016 ዓ-ም የሙሉ ቀን ት/ት
ትግበራ የጀመርን መሆኑን በታላቅ ደስታ
እየገለፅን ፡
የሠዓት የክፍለ ጊዜ ሠሌድ የሚከተለው
መሆኑን እናሳውቃለን ፡
*እስከ 2፡00 ሠዓት ተማሪዎች በቅጥር
  ግቢው መገኘት ይኖርባቸዋል
*ከ2፡00 - 2፡10 የሠንደቃላማ ስነ-ስርዓት
  ይከበርና ወደ ክፍል ይገባል
*ከ2፡10 -2፡30 የተማሪዎች ስም ጥር
  ይከናወናል
*በመቀጠል  ከ2፡30 - 8፡40 የመማር
ማስተማሩ ተግባር የሚከወን ሲሆን ፡
1ኛ ክ/ጊዜ=ከ2፡30 - 3፡15
2ኛ ክ/ጊዜ=ከ3፡15 - 4፡00
3ኛ ክ/ጊዜ=ከ4፡00 - 4፡45
       1ኛ ዕረፍት ከ 4፡45 - 5፡00
4ኛ ክ/ጊዜ=ከ5፡00 - 5፡45
5ኛ ክ/ጊዜ=ከ5፡45 -  6፡30
         2ኛ ዕረፍት ከ 6፡30 - 7፡00
ሲሆን የ2ኛ ዙር ስም ጥር ፡
       ከ7፡00 - 7፡10 ተከናውኖ
6ኛ ክ/ጊዜ=ከ7፡10 - 7፡55
7ኛ ክ/ጊዜ=ከ7፡55 - 8፡40 መሆኑን
ት/ቤት ያሳውቃል።

6.7k 0 0 78 300




Показано 20 последних публикаций.

4 915

подписчиков
Статистика канала