NiSiR Int. Broadcasting Co. (Official Telegram Channel)


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


NISIR International Broadcasting Co. is an impartial and independent media agency operates as social media & multimedia production.
Voice of voices
ንሥር ኢንተርናሽናል ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የማያዳላ እና ገለልተኛ የመገናኛ ተቋም ነዉ። ማህበራዊ ሚዲያ እና መልታይሚዲያ እምራች ሁኖ ይሰራል።
አማራ ድምፅ!

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


“ፕሮፓጋንዳ የመውጫ መንገዴ ነው” አገዛዙ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ከ8 በላይ የሆኑ አመራርና አባላቱ የፋኖና የሸኔ ሀይሎችን የተቀላቀሉበት አገዛዝ በዛሬው ዕለት የመከላከያ  ስነልቦና ግንባታ ዋና ዳይሬክቶሬት የፕሮፓጋንዳ ወታደሮቹን አሰልጥኖ ማስመረቁን ገለፀ።

በብልፅግና ቅልብ ጄኔራሎች የጦርነት አመራር በወገን ላይ ዘምቶ ህዝብ እየጨፈጨፈ ከህዝብ ልብ ውስጥ የወጣው ሰራዊት የመሪዎችን ህልውና ለማስጠበቅና ስርዓቱን ለማስቀጠል የሚያከናውነው ተግባር በፕሮፖጋንዳ ለማስደገፍ የሚተጉ አፈቀላጤ አመራርና አባላት ናቸው በሚዲያ ሙያተኝነት ስም መሰልጠናቸውን ከኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ ለኢትዮ 251 ሚዲያ መረጃውን አድርሰውናል።
  
የሰራዊቱን ልፋትና ድካም ለራሳቸው ሀብት መሰብሰቢያ ያደረጉት የወቅቱ የብልፅግና ጄኔራሎች በተለይ በትግራይ ፣ በአማራ ፣ በኦሮሚያ  ፣ በአፋር ፣ በሶማሌ በደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እንዲሁም በሲዳማና በጋምቤላ ክልሎች ያሉ ነባራዊ የእርስ በርስ ግጭቶችን በሌላ መልኩ ቀመዘገብና በመደበቅ እየሰሩ የቀጠሉ ሲሆኑ ከመንግሥት ኮሙኒኬሽን ፅ/ቤት እና ከመከላከያ የክብር አባላት እንዲሁም ብዙ ተከታይ ካላቸው ተከፋይ ቲክቶከሮችና ዩቲዩበሮች ጋር ወቅታዊ አጀንዳ እየተሰጣቸው በመናበብ የሚሰሩ መሆናቸውም ለኢትዮ 251 ሚዲያ ተጠቁሟል።

የሠራዊታችንን ሰነ ልቦና በውጊያም ሆነ ከውጊያ በኃላ የሚገነቡ ወታደራዊ ጋዜጠኞችን አሰልጥኜ አስመረቅሁ የሚለው በመከላከያ ሚዲያ ከከፍተኛ መኮንን እስከ መሰረታዊ ወታደር ድረስ ባለው የማዕረግ እርከን በመከላከያ ቴሌቪዥን ፣ ሬዲዬ ፣ ጋዜጣና ኦንላይን ክፍሎች የነበሩ ከ8 በላይ የሚሆኑ ወታደር ጋዜጠኞች ክፍሉ ላይ ባለው ጫና ምክንያት የፋኖ እና የኦነግ ሸኔ ሀይሎችን በተቀላቀሉቀት ወቅት ነው።
 
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተቋሙ የሚታወቁ ጋዜጠኞች ሳይቀር ወደ ፋኖ እና ሸኔ ሀይሎች እንዲሁም ወደየክልላቸው እየኮበለሉ ያሉበት የመከላከያ ሰራዊት ስነልቦና ግንባታ ዋና ዳይሬክቶሬት ከክፍሉ መሪ  ከሜጀር ጄነራል እንዳልካቸው ወልደ ኪዳን ጀምሮ ያለው በቤተሰባዊ ትስስር ዝውውርና ምደባ እየተደረገ በመሆኑና የጥቅም ቁርኝት ያለበት መሆኑ በዋናነት እንደሚጠቀስ የመከላከያ የመረጃ ምንጮችን ጠቅሶ ኢትዮ 251 ዘግቧል።


ነበልባለቹ በጠላት ምሽግ ታሪክ ሰሩ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የአማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክ/ጦር የነበልባል ብርጌድ በሚንቀሳቀስባቸው ቀጠና
የአገዛዙ 84ኛ ክ/ጦር እስካሁን 726 የግልና የብዱን መሳርያ ያጣው በአዲስ የመጣው አመራር በአንድ ወር የሄዱትን መሳርያ አስመልሳለሁኝ በማለት የለሊት ኦፕሬሽን ከጀመረ ሰነባብቷል ።

ይህም ህልሙ አልሳካ ያለው የአገዛዙ ሰራዊት  ተጨማሪ 17 መሳርያዎች እስካሁን ወደ ፋኖ ገቢ ሆነውበታል። አገዛዙ  በርካታ ሙትና ቁስለኛ እየሸከፈ ወደ ከተማ መፈርጠጥ  የቀን ተቀን መደበኛ ስራው ሆኗል።


በአዲሱ ዘዴው የለሊት ኦፕሬሽን የሚያደርገው የአገዛዙ ሰራዊት ተከትሎ ተናዳፊዎቹ የነበልባል ብርጌድ አዲስ አካሄድ ጀምሯል።

እንሆ ዛሬ 01/08/2017 ዓ.ም የአገዛዙ ሰራዊት እንደተለመደው  ኬላ ወደሚዘረጋበት እና ቀን ደፈጣ ወደሚይዝበት የተለመደ ምሽጉ ከባልጪ ወደ በሳ መስመር ወርካ ከጠዋቱ 2:00 አካባቢ  ኬላ ለመዘርጋት እና በኬላ የተለመደ ዘረፋውን ለመፈፀም ሲንቀሳቀስ በ50 አለቃ ሰለሞን አድነው የሚመራው ሻለቃ 3 ሻንበል 3 ቀድመው የጠላትን ምሽግ ይዘው ሲጠባበቁ የቆዩት ተርቦቹ የሺ አለቃ ሶስት ፋኖች አንግጦ ወደ ምሽግ የሚመጣውን ልብልብ የአገዛዙን ሰራዊት በገዛ ምሽጉ የመሸጉት የነበልባል አናብስቶች 12 ሆኖ ኬላ ጥበቃ የመጣውን አራዊት ሰራዊት በከፈቱበት ቅፅፈታዊ ተኩስ ስድስቱን ግንባር ግንባራቸውን በቀይ ጥይት ነቅሰው እስከወዲያኛው ከምድር ቆይታቸው ያሠናበቷቸው ሲሆን ስድስቱ እግሬ አውጭኝ በማለት እየፈረጠጡ ባልጪ ከተማ ገብተዋል ።
ነበልባሎቹም በሚገባ ግዳጃቸውን ፈፅመው ወደ ነፃ ቀጠናቸው በሰላም ተመልሰዋል።

በተያያዘ ዜና አገዛዙ አሁንም እዬፈራረሰ ሲገኝ ሶስት የአገዛዙ ሰራዊቶች አገዛዙን በመፀዬፍ የአማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክ/ጦር ነበልባል ብርጌድን ተቀላቅለዋል።

አዲስ ትውልድ
አዲስ ተስፋ።
ክብርና ሞገስ ለትግሉ ሰማእታት
  
ከአማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክ/ጦር ነበልባል ብርጌድ ሚድያ ክፍል።
          
       ሚያዚያ 1/8/2017ዓ.ም
              ነበልባሎቹ።
       
ድል ለአማራ ፋኖ
ድል ለአማራ ፋኖ

ንሥር ብሮድካስት መረጃ 
ረቡዕ ሚያዚያ  01 ቀን 2017 ዓ.ም
=====================
ቤተሰብ ይሁኑ! በጋራ ትግል፡ የጋራ ድል !
ዩቱብ: https://www.youtube.com/@nibcnews-Ethiopia
Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61574918731906
ትዊተር: x.com/nisirinternati1 
ቴሌግራም: https://t.me/nisirbroadcasting
ቲክታክ:- https://www.tiktok.com/@nisirbroadcast?
_t=ZP-8vDbj8Rmftu&_r=1
WhatsApp:  +1 (252) 574‑6084
Telegram:  +1 (252) 574‑6084pp




ዘመቻ አንድነት በጎጃም ግንባር!
           ፳፪|22ኛ ቀን
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ሀ. 10 የጠላት ሃይል ፋኖን ተቀላቀለ

1 ብሬንና 5 ክላሽ በመያዝ 6 አድማ ብተና አባላት/ ግልገል ፋኖዎች/ የደጀኑን ዛንብራ ብርጌድ ተቀላቅለዋል። በተመሳሳይ 4 መከላከያዎች ጃዊ መተከል መብረቁ ብርጌድ ተቀላቅለዋል።

በጥቅሉ ከ10 በላይ የጠላት ሃይል የአማራ ፋኖ በጎጃምን በዛሬው ቀን ብቻ ተቀላቅለዋል።

ለ. አውደ ውጊያ
 
1. ቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ ክፍለጦር በሁለት ግንባር ሲፋለም ውሏል።

በረኸኛው ጅበላ ሙተራ ብርጌድ የቦ ማርያም እና አርጀና  ላይ በደብረማርቆስ ማረማቤት አካባቢ ውጊያ ሲያደርግ አርፍዷል። በዚህ አውደውጊም ሁለት ቲዮታ ጠላት ሲደመሰስ አንድ ኦባማ ቁስለኛ ጭነው ወስደዋል።ሬሳቸውን  በየመንገዱ እያጠባጠቡ ቀብረዋል። ቀስተደማና ብርጌድም በተመሳሳይ በዛሬው እለት ጠላትን ሲረፈርፉት ውለዋል።

2. ጃዊ መተከል 4ኛ ክፍለጦር
መብረቁ ብርጌድ ቡኒጅራ የሚባል ቦታላይ አስደናቂ ኦፕሬሽን የተፈፀመዉ መብረቃዊ ጥቃት የሞቱት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ቁጥር ወደ 37 መድረሱን ማወቅ ተችሏል። እንዲሁም 4 የመከላከያ አባላት ከድተዉ ፋኖን ተቀላቅለዋል።በፋኖ ከባድ ምት የተበሳጨዉ የጠላት ሃይል ንፁሃን ማህበረሰብን በማሰቃየት በመዝረፍ የከዳ መከላከያ አለ አምጡት በማለት እየደበደባቸዉ ይገኛል። 2 በሬዎችን ዘርፎ በልቷል።

ዘመቻ አንድነት ይበጥላል።
አዲስ ትውልድ ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ!
[የአማራ ፋኖ በጎጃም ]
       
ድል ለአማራ ፋኖ
ድል ለአማራ ፋኖ

ንሥር ብሮድካስት መረጃ 
ረቡዕ ሚያዚያ  01 ቀን 2017 ዓ.ም
=====================
ቤተሰብ ይሁኑ! በጋራ ትግል፡ የጋራ ድል !
ዩቱብ: https://www.youtube.com/@nibcnews-Ethiopia
Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61574918731906
ትዊተር: x.com/nisirinternati1 
ቴሌግራም: https://t.me/nisirbroadcasting
ቲክታክ:- https://www.tiktok.com/@nisirbroadcast?
_t=ZP-8vDbj8Rmftu&_r=1
WhatsApp:  +1 (252) 574‑6084
Telegram:  +1 (252) 574‑6084pp


ሰበር ዜና!
፨፨፨፨፨፨

ከጅቡቲ ወታደራዊ መሳሪያ ጭኖ ወደ ሞጆ ሲጓዝ የነበረ ባቡር ተቃጠለ!

መነሻውን ጅቡቲ መዳረሻውን ሞጆ አደርጎ ወታደራዊ መሳሪያዎቸን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ባቡር ሱማሌ ክልል ኤረር አካባቢ የተቃጠለ ሲሆን በዚህ ቃጠሎ ኮንታክት ዋየር፣ ሚሴንጀር ዋየር ሙሉ ለሙሉ ወድሟል፣ ፍርጎው ሙሉ ለሙሉ እየወደመ ሲሆን፣ ሀዲዱ በመቅለጥ ላይ ላይ እንዳለ ለኢትዮ 251 ሚዲያ የአይን እማኞች ገልጸዋል። ምንጮች አክለውም እሳቱን አሁን በከፍተና ሁኔታ እየነደደ እንደሆነ ገልጸው የሚፈነዳ ነገር ይሰማል ብለዋል፡፡

የተቃጠለው ኮንቲነር ከወታደራዊ መሳሪያዎች በተጨማሪ ምንነቱ ያልታወቀ ተቀጣጣይ ነገር ይዞ ሲጓዝ እንደነበር የወስጥ የመረጃ ምንጮች አክለው ገልጸዋል።




"ታጋይ ይሰዋል ትግል ይቀጥላል"
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ሚያዚያ 1 ቀን 2015 ዓ.ም አርበኛ ሻምበል ዳንኤል አለሙ ስለ አማራ ህዝብ ህልዉና መስዋዕትነትን የተቀበለበት ዕለት ነው።

አርበኛ ሻምበል ዳንኤል አለሙ የአማራን ህዝብ ሁለንተናዊ የህልዉና አደጋ ለመቀልበስና የአማራን ህዝብ እንደ ህዝብ "ሕልው" ለማድረግ ውድ ህይወቱን የሰዋበት ይህንን ቅዱስ የህልዉና ትግል "ሀ" ብሎ ያስጀመረበትና ችቦ የለኮሰበት ቀን ነው::

ገና በለጋ እድሜው የቀድሞዉን የሃገር መከላከያ ሰራዊት በመቀላቀል ትግል የጀመረው አርበኛ ሻምበል ዳንኤል አለሙ ከእግረኛ እስከ ሻምበልነት ማዕረግ ድረስ እንዲሁም የቀድሞው አግዓዚ ኮማንዶ አባል በመሆን ከሃገር ዉስጥ እስከ ዉጭ አገር ሰላም ማስከበር ተልዕኮ ድረስ ወጣትነቱን ለሃገሩ ገብሯል::

አርበኛ ሻምበል ዳንኤል አለሙ ከሃገር መከላከያ ሰራዊት ባጋጠመው ከባድ ቁስል ምክንያት በጡረታ ያገለለ ሲሆን ከ 2010 ዓ.ም ህዝባዊ እምቢተኝነት ቡሃላ ወጣቶችን በስፖርት በአካል ብቃትና በስነ ልቦና የማንቃት ስራ እየሰራ ቡሃላም ከነ ዋርካው ምሬ ወዳጆ ጋር የራያ ፋኖን በመመስረትና በመቀላቀል ፀረ ወያኔ ትግሉን ተቀላቅሎ ሁሉንም ተጋድሎዎች በመሪነትና በአሰልጣኝነት በድል ተወጥቷል:: የቀድሞው ምስራቅ አማራ ፋኖ ስልጠና መምሪያን እየመራ በመካነሰላም በደሴ በሃይቅ በወልድያ በቆቦና በራያ አላማጣ በርካታ ታጋዮችን ያሰለጠነና ያፈራ ሲሆን የአሁኑን የአማራ ህዝብ የህልዉና ትግል በሰራዊትና በመሪነት ላይ ያሉ በርካታ ጀግኖችን አፍርቷል:: በርካታ ጀግኖችን እያሰለጠነና እያስታጠቀ መሆኑን ያየው አገዛዙም በጥላቻ አይን ያየው ጀመረ:: 

ፀረ ወያኔ ትግሉን እነ አብይ አህመድና በድኑ ብአዴን በፕሪቶሪያው የድራማ ስምምነት ከቋጩት ቡሃላ የአማራ ፋኖን ህግ ማስከበር በሚል ሽፋን ትጥቅ ለማስፈታት በፌደራልና በክልል ደረጃ መከላከያ በማዝመት ዘመቻ በጀመሩበት ጊዜ ግጭቶች መጀመራቸው ይታወቃል:: በዚህም በተለያዩ ጊዜያት የምስራቅ አማራ ፋኖ ሰራዊትና አመራሮችን ቀዳሚ ኢላማ ያደረገ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ ቀጠለ::

አርበኛ ሻምበል ዳንኤል አለሙ ከዚህ የፖለቲካ ጥያቄ ካነገቡ ግጭቶች ጋር ተያይዞ የብርሃኑ ጁላ መከላከያ ሰራዊት ላይ ያይ በነበረው ፀረ ህዝብ ተግባርና ነዉር እጅግ ይበሳጭና ያዝን ስለነበር በአንድ ከአብይ አህመድ ጀኔራሎች ጋር ቆቦ ከተማ ሁለገብ አዳራሽ በተደረገ ስብሰባ የህዝብ ናችሁ ወይስ የብልፅግና? በሚል ይጠይቃቸዋል:: ያ ለራሱ ህዝብ ሳይሆን ሰላም ማስከበር ጎረቤት አገር ሄዶ ረሽኑን ለህዝብ ሰጥቶ ቅጠል በልቶ የሚያድር ሰራዊት የት ገባ? ሲል በመጠየቅ እስከ ሰላም ማስከበር በደረሰ ተልዕኮው የነበረዉን ህዝባዊነት በመጥቀስ ዙፋን ጠባቂ መሆናቸዉንና ነውራቸዉን ነገራቸው::

አይቀሬዉን ጦርነት የተገነዘቡትና የተረዱት የአማራ ህዝብ የቁርጥ ቀን ልጆች ከወሎ ምስራቅ አማራ ፋኖ ከሸዋ ከጎጃምና ከጎንደር ፋኖዎች ጋር በመሆን ጎንደር ሱዳን ጠረፍ የአማራ ፋኖ አንድነት ምክር ቤትን በመመስረት አርበኛ ሰፈር መለሰን ዋና አዛዥ እና ዋርካው ምሬ ወዳጆን ምክትል አዛዥ አድርጎ በመምረጥ እንቅስቃሴ ጀመረ:: ምስራቅ አማራ ፋኖ አጠቃላይ የትግል ጉዞዉን የሚዘክር ታላቅ የተሃድሶ ዝግጅት የምክር ቤቱ ዋና አዛዥ አርበኛ ሰፈር መለሰ እንዲሁም ከፍተኛ የመከላከያ ልዩ ሃይልና የብልፅግና አመራሮች የሃይማኖት አባቶችና የሃገር ሽማግሌዎች መላ ሰራዊቱና ህዝብ በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ አከበረ::

በዝግጅቱም ምስራቅ አማራ ፋኖ የአማራ ህዝብ በክልሉና በተለይ ከክልሉ ዉጭ እየደረሰበት ያለዉን ግፍና ጭፍጨፋ በማንሳትና በማስታወስ የአማራ ህዝብ የህልዉና አደጋ ተጋርጦበታል "ትግል ይቀጥላል" የሚል መልዕክት ለታዳሚው ለሰራዊቱና በዉስጥም በዉጭም ላለው መላው የአማራ ህዝብ በህዝብ ግንኙነቱ አርበኛ አበበ ፈንታው በኩል መልዕክት አስተላለፈ:: ይህንን ተከትሎም ከተሃድሶ ቡሃላ ትጥቅ ያስረክቡናል ይበተናሉ ስንል እንዴት ትግል ይቀጥላል ይላሉ በሚል የአገዛዙ ሹማምንት ከፍተኛ ንዴትና ድንጋጤ ዉስጥ ገቡ::

ይህንን ተከትሎም አገዛዙ የምስራቅ አማራ ፋኖ ቁስለኞችን ሳይቀር ሰራዊቱን ባገኘበት ምቹ አጋጣሚ ሁሉ መረሸን ጀመረ:: የለየለት ግጭትም ተጀመረ:: ጥቃት የማይወደው አርበኛ ሻምበል ዳንኤል አለሙም ሰራዊቱን በተጠንቀቅ እንዲቆምና ለሚመጣው ሁሉ ነገር ተመጣጣኝ አፀፋ እንዲሰጥ ድርጅቱና መሪው ዋርካው ምሬ ወዳጆ ያወረደዉን መመሪያ በመቀበል በአንድ ወቅት ምስራቅ አማራ ፋኖ ካምፕ ድረስ ከነ አጃቢዎቹ በፓትሮል የመጣን ኮሎኔል ከመኪናው ወርዶ እስኪፈረጥጥ ድረስ ቆፍጠን ያለ እርምጃዉን ጀመረ:: 

ምስራቅ አማራ ፋኖም ሰራዊቱን በምዕራብ በኩል ከራያ ቆቦ ጮቢ በር እስከ በላጎ እንዲሁም ወልድያ ዙሪያ ሳንቃና መቻሬ ድረስ ገዥ መሬቶች ላይ በማስፈር ለአይቀሬው ፍልሚያ ተዘጋጀ:: በበርካታ አካባቢዎች ከነበረው ግጭት ጋር ተያይዞ የነበረዉን ከፍተኛ ዉጥረትና የአማራ ልዩ ሃይል በበድኑ ብአዴን እና በነ አብይ አህመድ ሴራ መፍረሱን ተከትሎ ሚያዚያ 1/2015 አ.ም ረፋድ ላይ ቆቦ ከተማ በተጀመረ ከባድ ዉጊያ የአሁኑን የአማራ ህዝብ የህልዉና ትግል ጅማሮ ችቦ ለኩሶ አርበኛ ሻምበል ዳንኤል አለሙ መስዋዕትነት ተቀበለ:: የህልዉና ተጋድሎዉም ሸዋ በነበሩ የምስራቅ አማራ ፋኖ አሃዶችና የሸዋ ፋኖ አናብስቶች ተቀጣጥሎ ዛሬ በመላው አማራ የደረሰበት ደረጃ ደረሰ::

አርበኛ ሻምበል ዳንኤል አለሙ ስለ አማራ ህዝብ ህልዉና ቀይ መስመር ያለፈዉን በምድርም ይሁን በሰማይ ዘመኑ ያፈራዉን ጦር መሳሪያ እስከ አፍንጫው የታጠቀዉን ጨፍጫፊና ግፈኛ ፋሽስታዊ ስርዓት እስከ መጨረሻው ህቅታ ተናንቆ በጀግንነት ተሰዉቶ ችቦ ለኩሶ ይህንን የአማራ ህዝብ ቅዱስ የህልዉና ትግል ለዛሬ ካበቁ ጀግኖች መካከል ግንባር ቀደም ሆኖ አልፏል::

የተሰዋህለትን አላማ ከግብ እናደርሳለን!
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አማራ)
ሚያዚያ 1 ቀን 2017 ዓ.ም




የአማራ ፋኖ በጎጃም ጃዊ መተከል 4ኛ ክ/ጦር መብረቁ ብርጌድ በጠላት ላይ መብረቃዊ ጥቃት አደረሰ።

በቀን 30/07/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ወደ ቡኒጅራ ከተማ በመግባት ጥበብ በተሞላበት ወታደራዊ ቴክኒክ ከበባ በማድረግ 2 ከፍተኛ የመከላከያ አመራርን ጨምሮ 23 የሚደርሱ የጠላት አባላትን መደምሰስ ሲቻል፣ ቁጥራቸዉ ያልታወቁ በርካታ ቁስለኛዉን በመጫን ወደ ፓዊ ሆስፒታል እንደገቡ ማወቅ ተችሏል።

የወገን ጦር አደረጃጀቱን በማዘመን ዘመናዊ መሳሪያ በመታጠቅ በጠላት ላይ ኪሳራ እያደረሰ ይገኛል።በማለት የአማራ ፋኖ በጎጃም ጃዊ መተከል 4ኛ ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት ሃለፊ  ያዕቆብ ጌታሁን ገለጿል።
       
ድል ለአማራ ፋኖ
ድል ለአማራ ፋኖ

ንሥር ብሮድካስት መረጃ 
ረቡዕ ሚያዚያ  01 ቀን 2017 ዓ.ም
=====================
ቤተሰብ ይሁኑ! በጋራ ትግል፡ የጋራ ድል !
ዩቱብ: https://www.youtube.com/@nibcnews-Ethiopia
Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61574918731906
ትዊተር: x.com/nisirinternati1 
ቴሌግራም: https://t.me/nisirbroadcasting
ቲክታክ:- https://www.tiktok.com/@nisirbroadcast?
_t=ZP-8vDbj8Rmftu&_r=1
WhatsApp:  +1 (252) 574‑6084
Telegram:  +1 (252) 574‑6084pp


ምርኮ የለመደው ግዪን ብርጌድ ጀብድ መስራቱን ቀጥሏል።የ፫ኛ ጎጃም አገዉ ምድር ክ/ጦር፣ግዮን ብርጌድ የሞርተር 120 ኦፒን ጨምሮ መማረክ ችሏል

በአጭር ውጊያው የተገኙ ድሎች
፦4 ተደምስሷል
፦3 የቆሰለ
፦300 የክላሽ ተተኳሽ ተማርኳል።
አን የሞርተር 120 ኦፒ ተማርኳል።

በሌላ በኩል አንድ የአገዛዙ ኮማንዶ በስቦ ማስከዳት የግዮን ብርጌድ አባግስ ሻለቃን ተቀላቅሏል።ዘመቻ አንድነት በሁሉም ግንባር ተጠናክሮ ይቀጥላል!

       [አማራ ፋኖ በጎጃም]
 

ድል ለአማራ ፋኖ
ድል ለአማራ ፋኖ

ንሥር ብሮድካስት መረጃ 
ረቡዕ ሚያዚያ  01 ቀን 2017 ዓ.ም
=====================
ቤተሰብ ይሁኑ! በጋራ ትግል፡ የጋራ ድል !
ዩቱብ: https://www.youtube.com/@nibcnews-Ethiopia
Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61574918731906
ትዊተር: x.com/nisirinternati1 
ቴሌግራም: https://t.me/nisirbroadcasting
ቲክታክ:- https://www.tiktok.com/@nisirbroadcast?
_t=ZP-8vDbj8Rmftu&_r=1
WhatsApp:  +1 (252) 574‑6084
Telegram:  +1 (252) 574‑6084pp




ከአማራ ፋኖ በጎጃም ቀኝ ጌታ ዮፍሔ ንጉሴ  6ኛ ክፍለ ጦር  ንጉስ ተክለሃይማኖት ብርጌድ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ

የአማራ ፋኖ ከብልፅግና መራሹ ዘራፊና ገዳይ ወንበዴ ቡድን ጋር የህልውና ትግል ከጀመረ ሰንበትበት ማለቱ ይታወቃል። በሚያዳርገውም የህልውና ትግል በብልፅግና መራሹ መንግስት ላይ ከባድ የሆነ ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ኪሳራዎችን እያደረበት ይገኛል።

በመሆኑም የብልፅግና መንግስት እያደረሰበት ያለውን ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ኪሳራ መቆቋም ሲያቅተው የከተማ ቦታዎችን በሊዝ በመሸጥ እና ገንዘብ በማስባሰብ የሚፈፅመውን የአማራን ህዝብ የዘር ጭፍጨፋ አጠናክሮ ለማስቀጠል እየሰራ ይገኛል።

በመሆኑም በደ/ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ውስጥ ደ/ማርቆስ ከተማና መሠረተ ልማት መምረያ  የቦታ ሊዝ ጨረታ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም የአማራ ፋኖ የህልውና ትግል ከጀመረ ጊዜ አንስቶ በጫረታም ይሁን በማንኛውም መንገድ ከመንግስት ወደ ግለሠቦች የሚዛመሩ ቦታዎች ህጋዊ እንዳማይሆኑና መሬቱ ተወርሶ ለትግል አላማ እንደሚውል በተደጋጋሚ ሲገለፅ ቆይቷል፡፡

ስለሆነም ይህንን መመሪያ በማንአለብኝነት ችላ ብላችሁ በመጣስ ከመንግስት ላይ መሬት በመግዛት  ለመግስት የገቢ ምንጭ በመሆን እንዲሁም ይህንን የሊዝ ጨረታ ለማስፈፀም የምህንድስና ባለሙያ በመሆን የአማራን ህዝብ  ሞት እና እንግለት የምትደግፍ ግለሠቦች  ላይ የማያዳግም ርምጃ እየወስድን በጨረታም ይሁን በማንኛውም መንገጃ  ያገኛችሁትን ቦታ በመውረስ ለትግል አላማ የምናውለው መሆኑን እየገለፅን በሚደረሰባችሁ ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊም ሆነ  ማህበራዊ ኪሳራ የአማራ ፋኖ ተጠያቂ እንዳማይሆን እየገለፅን ከዚህ ድርጊት በመቆጠብ የአማራነት ግዴታችሁን እንድትወጡና የታሪክ ተወቃሽ ከመሆን እንድትድኑ የአማራ ፋኖ በጎጃም ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ 6ኛ ክፍለጦር ንጉስ ተክለሃይማኖት ብርጌድ  መልዕከቱን ያስተላልፍል።

አዲስ ትውልድ!
አዲስ አስተሳሰብ!
አዲስ ተስፋ!

ባዬ ሽፈራው (ቀኜ)የንጉስ ተክለሃይማኖት
ብርጌድ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ

ድል ለአማራ ፋኖ
ድል ለአማራ ፋኖ

ንሥር ብሮድካስት መረጃ 
ረቡዕ ሚያዚያ  01 ቀን 2017 ዓ.ም
=====================
ቤተሰብ ይሁኑ! በጋራ ትግል፡ የጋራ ድል !
ዩቱብ: https://www.youtube.com/@nibcnews-Ethiopia
Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61574918731906
ትዊተር: x.com/nisirinternati1 
ቴሌግራም: https://t.me/nisirbroadcasting
ቲክታክ:- https://www.tiktok.com/@nisirbroadcast?
_t=ZP-8vDbj8Rmftu&_r=1
WhatsApp:  +1 (252) 574‑6084
Telegram:  +1 (252) 574‑6084pp




ጎጃም አገዉ ምድር ክ/ጦር !
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

መወያየት፣መመካከር፣ማደራጀት ተጠናክሮ ቀጥሏል።ዉይይቶቻችን በማህበረሰቡ እና በአርበኞቻችን በእቅድና ፕሮግራሙ መሰረት እየተኬሄደ ይገኛል

የአፋጎ ጎጃም አገዉ ምድር ክ/ጦር በስሩ ባሉ 7 ብርጌዶች በትግሉ  ዙሪያ ከማህበረሰቡ ጋር ሰፋ ያለ ዉይይት ያደረገ ሲሆን ከትግሉ ጅማሮ እስካሁን ድረሰ ያሉ ጠንካራና መስተካከል ያለባቸዉን ጉዳዮች ከማህበረሰቡ ጋር በተደረገ ሰፋ ያለ ዉይይት ግብዓት በመዉሰድ ለቀጣይ የትግል ሂደት ከማህበረሰባችን የተነሱ ሃሳቦችን በመቀበል አጠቃላይ ህዝባችን ለትግሉ ያለዉን ወኔ፣ፍቅር አደራም ጭምር የተረዳንባቸዉን ዉይይቶች አድርገናል በዉይይቱ ሁለም የክ/ጦር አመራሮች በየብርጌዱ በመገኘት ዉይይቱን መርተዋል

በሌላ በኩል ከአርበኞቻችን ጋር አጠቃላይ ከትግሉ ጅማሬ እስከ አሁን ያሉ ሂደቶችን ሃሳብ በማንሸራሸር ተጠናክረዉ መቀጠል ያለባቸዉ ተጠናክረዉ እንዲቀጥሉ እና መሻሻል ያለባቸዉ ጉዳዮች እንዲሻሻሉ በፓለቲካና ወታደራዊ መኮነኖች ስልጠና ተሰጧል በበሳል ኸታደረዊ መኮነኖች ታክቲካዊ ስልጠናም ለአርበኞቻችን የተሰጠ ሲሆን ግዙፉ የጎጃም አገዉ ምድር ክ/ ጦር ንስሮች ለቀጣይ ድል ራሳቸዉን በማዘጋጀት እንደ ንስር ከፍ ብለዉ ይገኛሉ

ፋኖነት አሸናፊነት

ፋኖ ይበልጣል የዉነቱ ጀግናዉ (እሳቱ) የክ/ጦሩ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ

ድል ለአማራ ፋኖ
ድል ለአማራ ፋኖ

ንሥር ብሮድካስት መረጃ 
ረቡዕ ሚያዚያ  01 ቀን 2017 ዓ.ም
=====================
ቤተሰብ ይሁኑ! በጋራ ትግል፡ የጋራ ድል !
ዩቱብ: https://www.youtube.com/@nibcnews-Ethiopia
Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61574918731906
ትዊተር: x.com/nisirinternati1 
ቴሌግራም: https://t.me/nisirbroadcasting
ቲክታክ:- https://www.tiktok.com/@nisirbroadcast?
_t=ZP-8vDbj8Rmftu&_r=1
WhatsApp:  +1 (252) 574‑6084
Telegram:  +1 (252) 574‑6084pp




30/07/2017 ዓ.ም

ከአማራ ፋኖ በሸዋ የተሠጠ መግለጫ

የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት በደ/ወሎ ዳውንት ላይ ከብልፅግና ጋር ባደረጉት ድርድርና ስምምነት መሠረት የአማራ ፋኖ አደረጃጀትን በጋራ ለመዋጋት የተስማሙበትን አክብረዋል። ለህዝባችን የሚያሳዝን ቢሆንም ተገደን ድርጅታችንን እና ትግሉን መጠበቅ ስላለብን የአፋሕድ ገረድ ቅጠረኛ ከነሹም አብዴታ ጋር በመሆን ድርጅታችን ላይ ወረራ ፈፅሟል በዚህ ወረራ በርካታ ሀይል ሲደመሰስ በርካቶች እጅ ሰጥተዋል።

ለዚህ ድርጊታቸው እኛ ላይ ለፈፀሙት ሳይሆን ታጋዩ ላይ ለወሰድነው እርምጃ የአፋሕድ እና የአማራ ፋኖ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አመራሮችን ይቅር የማንላቸው መሆኑን እና የትግሉ ጠላፊዎች እነሱ መሆናቸው እንዲታወቅልን እንወዳለን። የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ እና የአገዛዙ ሃይል በጥምረት በአማራ ፋኖ በሸዋ ላይ እኩይ ድንገተኛ ጥቃት መሰንዘራቸውን እያሳወቅን።
በተደረገበት ድንገተኛ ጥቃት የአማራ ፋኖ በሸዋ በድል ለመወጣት ተችሏል።

እንደሚታወቀው የአማራ ፋኖ በሸዋ በታሕሳስ ወር በ2017 ዓ.ም ለአማራ ሕዝብ ይጠቅማል ይበጃል ያልንውን አማራጭ በሙሉ በስራ አስፈፃሚዎች የወሰነና የነበረን ልዩነት በውይይትና በንግግር ይፈታል ብሎ በማመን በጥር ወር ለ14 ቀን የአንድነት መርሃ-ግብር አዘጋጅተን መነጋገራችንን በውስጥም በውጭም ያላችሁ አካላት የትግሉ ደጋፊዎች ታውቃላችሁ። ሆኖም ግን ይህንን የሠላም አማራጮች በመግፋትና የአማራን ሕዝብ ሠላም እና የሕዝባችንን የትግል ግብ አሳልፎ ለጠላት በመስጠት በድጋሜ የሕዝባችንን ሰቆቃ ለማስረዘም በአማራ ፋኖ በሸዋ ላይ በሰኔ 23/2016 ዓ.ም እንዳደረጉት ወረራ ዘረፋ ዘለፋና ግድያ ድጋሜ በዛሬዋ ዕለት ማለትም 30/07/2017 ዓ.ም ከለሊቱ 10:00ሰዓት ጀምረው ከአገዛዙ ሃይል ጋር በጥምረት በአማራ ፋኖ በሸዋ ላይ ጥቃት ፈፅመዋል።
የአማራ ፋኖ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ መነሻውን ከሞጃናወደራ ወረዳ በአራዳ ጎጥ በኩል ወደ በዞ ቀበሌ; በአይዞሽ አሞራ ወደ ጊፍት ቀበሌ ወረራ ያረጉ ሲሆን :- ሌላኛው የአገዛዙ ሃይል ለጠቅላይ ግዛቱ በማገዝ ከደ/ብርሃን ወደ ዘንደጉር ውጊያ በማቅናት ጦርነት ከፍቷል።

ይህንን ጥቃት የአማራ ፋኖ በሸዋ እንደ አመጣጡ ያለምንም ኪሳራ በማጥቃት በመደምሰስ ና ግብዓት በማግኘት ግስጋሴውን ወደፊት አድርጓል። የጠቅላይ ግዛቱ ሴራ ይህ ብቻ አይደለም : ነፃ ያወጧቸውን ቀጠናዎች አገዛዙን ከመፋለም ወንድሙን ለመውጋት ጥሎ በመንቀሳቀስ ለአገዛዙ ሃይል ምቹ መደላድልን በመፍጠር ዓፄ-ይኩኑ አምላክ ክ/ጦር ና 7/70 ክ/ጦር ለማገዝ እንዳይቀሳቀሱ ከሰንበቴ ወደ አላላ ሃይል እንዲጨምርና የኤፍራታ ግድም ወረዳን አገዛዙ እንዲቆጣጠረው አድርገዋል። በተጨማሪ የከሠም ክ/ጦር ለእገዛ እንዳይቀሳቀሱና እንዳይተባበር ለማድረግ ደ/ብርሃን ያለውን የአገዛዙን ሃይል ጋብዘዋል። ይህ ማለት ሰሞኑን 'አቶ ሽመልስ አብዲሳ 'የኦሮሚያ ክልል ፕ/ት የተናገረውን እና ያዘጋጁትን የሴራ ፖለቲካ ከጠላት ጋር በመተባበር በግልፅ አሳይተዋል። የሽመልስ አብዲሳ ንግግር :- ፋኖን በመከላከያ ስለማናሸንፈው በራሱ ሃይል በገንዘብና በሴራ ነው ፋኖን የምናጠፋው ያለውን አክብረውለታል ለአማራም ከሃዲነታቸውን ከወዲሁ አሳይተዋል። ''የአማራ ትግል ይጠራል እንጅ አይደፈርስም'' የአማራ ሕዝብና የፋኖ ሠራዊቶች እዲረዱን የምንፈልገው ለሠላም እጃችንን ዘርግተን እያለ በሴራ ከዋናው የአማራ ሕዝብ ጠላት ጋር በመጣመር በጦርነትም ይሁን በፖለቲካ ለሚዘምትብን በሙሉ እጃችንን እና እግራችንን አጣጥፈን የማንቀመጥ መሆናችንን ለማሳወቅ እንወዳለን። በእዚህ አጋጣሚ በሴረኞችና በጥቅመኞች ተታላችሁም ይሁን ተገዳችሁ ወደ እርስበርስ ጦርነት የገባችሁ ወንድሞችና እህቶች በሙሉ በሰላም ወደ አማራ ፋኖ በሸዋ መቀላቀል ለምትፈልጉ ያለምንም ጦርነት መቀላቀል ትችላላችሁ።

ክብር ለተሰውት ድል
ክብር ለአማራ ህዝብ
ድላችን በክንዳችን
የአማራ ፋኖ በሸዋ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ክፍል


በዛሬው እለት ማለትም 30/07/2017 ዓ/ም የአማራ ፋኖ በጎጃም 5ተኛ ክፍለ ጦር የአረንዛው ዳሞት ብርጌድ የሆነችው የፍኖተ ሰላም 1ኛ ሻለቃ ፍኖተ ሰላም ሸንበቁማ ልዩ ስሙ ነብዩ መለቀሻ ዋርካ አካባቢ መሽጎ የነበረውን የጠላት ሀይል ቦታው ድረስ በመሄድና በመክበብ በጠላት ላይ 3 ሙት እና 5 ቁስለኛ ጉዳት አድርሰዋል


ፊት አውራሪው አርበኛ ፋኖ ማረጉ ተማረ 5ኛ አመት መታሰቢያ!!!
የእምቢተኝነት እና የአማራነት ምልክቱ አርበኛ ማረጉ ተማረ መጋቢት 30 ቀን 2012 ዓመተ ምህረት ነበር በጀግንነት ጠላትን ተፋልሞ ኢላማ ውስጥ የገቡትን በመደምሰስ ለአማራ ህዝብ ነጻነት የሚከፈለውን የመጨረሻውን ውድ የህይወት ዋጋ የከፈለው።

መልኩ ጠየም ያለ አለባበሱ ሀገርኛ ፀጉሩ የተከመከመ ጎፈሬ ፊቱ እንደ ሰደድ እሳት የሚጋረፍ እምቢተኛ ጀግና በላስታ ወረዳ ብልባላ ቀጠና ውስጥ ተወለደ:: የዚህ ጀግና ስም ማረጉ ይሁን ተባለ::

እምቢተኛው ጀግና የጄኔራል አሳምነው ጽጌ ስርዓተ ቀብር ከተፈፀመ በኋላ በእለቱ እለት ነበር ከሌሎች 6 ጓዶቹ ጋር ፋኖ ሆኖ ብቅ ያለው:: ብልባላ ቀበሌ ውስጥ በድምሩ 7 ሆነው እነ አርበኛ ማረጉ ተማረ የላስታ ፋኖን አደራጅተው የጄኔራል አሳምነው መንፈስ ወራሽነታቸውን በይፋ አውጀው ለወገን አለኝታ እና ኩራት መሆን ችለዋል::

በጊዜ ሂደት ከሀውጃኖ ምትክ ከራያው ቅምጥል ዋርካው ምሬ ወዳጆ ጋር ቁርኝት ፈጥረው በዚሁ በብልባላ ቀበሌ ገንጅ ዋርካ ስር ተሰባስበው የጄኔራል አሳምነውን የትግል አደራ ለመወጣት መክረዋል::

እንዲህ እንዲያ እያሉ ኃይላቸውን ማጠናከር ሲጀምሩ የፋሽስቱ አብይ አህመድ መንግስት እነዚህን የአሳምነው ቅሪቶች ማጥፋት አለብኝ ብሎ ዘመቻ በመክፈቱ የተነሳ ተደጋጋሚ ወረራ ተፈጽሞባቸው በስተመጨረሻ መጋቢት 30 ቀን 2012 አመተ ምህረት በብልባላ ግንባር በተደረገ እልህ አስጨራሽ ውጊያ ሞት አይፈሬው ጀግና አርበኛ ማረጉ ተማረ 3 ጠላት ደምስሶ ተሰዋ::

በወቅቱ ከአማራ ልዩ ኃይል መካከል ግማሾቹ የብልጽግና ቅጥረኞች ሆነው ሌሎች ደግሞ የጄኔራል አሳምነው ልጆች ተሽለው ልዩ ኃይሉ የተከፋፈለ ስለነበር የብልጽግና ቅጥረኞች የሆኑት ከወልድያ እና ሰቆጣ ተነስተው ወደ ብልባላ መጥተው ነው እነ አርበኛ ማረጉ ተማረ ላይ ተኩስ የከፈቱት::

ተኩስ ከፋቾቹ የአማራ ልዩ ኃይል መቅደላ ክፍለ ጦር አንድ ሻለቃ አባላት ነበሩ:: እነ አርበኛ ማረጉ ተማረ በጀግንነት በጀግንነት ተፋልመው የብልጽግናን ቅጥረኞች በመመከት ታሪክ ሰርተዋል:: ቀደም ብለን እንደገለፅነው አርበኛ ማረጉ ተማረም ሶስቱን ጠላት ደምስሶ ነው በጀግንነት የተሰዋው::

አርበኛ ማረጉ ተማረ የአንድ ወንድ ልጅ አባት ሲሆን በህይወት ዘመኑ በጀግንነቱ እና በእውነት ሰውነቱ የሚታወቅ እንድሁም ትንሽ ትልቁ የሚያከብረው ጀግና ነው::

አርበኛ ማረጉ ተማረ ፋኖነትን ከጠነሰሱ እና አሳምነውነትን በልባቸው አትመው የድል ሰንደቅ ካደረጉ ወጣት አርበኞች መካከል አንዱ ሲሆን በአማራ ሕዝብ ላይ የተደቀነውን የሕልውና ስጋት በአግባቡ ተረድቶ ቀድሞ በመንቃት አብሪ ጥይት ተኩሶ ለእልፍ አዕላፍ ጀግኖች አርአያ ሆኖ አልፏል::

ጀግና ይሞታል ስም ግን አይሞትምና እነሆ አሁን ላይ በእሱ ስም ክፍለ ጦር ሰይመው የላስታ ወጣቶች የተቋም ሀውልት አቁመውለት በስሙ ታሪክ እየሰሩ ነው::

ማረጉ ተማረ ክፍለ ጦር ላስታ ውስጥ ካሉት የአማራ ፋኖ በወሎ ቤተ አማራ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ኮር ቅርንጫፍ ክፍለ ጦሮች መካከል አንዱ ሲሆን በከተማ ውጊያ አቻ የሌላቸው ጀግኖች የተሰባሰቡበት ክፍለ ጢር ነው::

አማራነት ወንጀል ተደርጎ ህይወትን የሚያሳጣ፣ በነፃነት
ተንቀሳቅሶ ሰርቶ መኖርን ህልም የሚያደርግ፣ ሃብትና ንብረትን የሚያስነጥቅ፣ ከመኖሪያ አካባቢ
የሚያፈናቅልና በጅምላ የሚያሰገድል ማንነት ተደርጎ በፋሽስትይ መንግስት ህዝባችን ሲጨፈጨፍ እና ሲሳደድ አርበኛ ማረጉ ተማረ ይህን እያየሁ አልቀመጥም ብሎ ዘረኛውን ስርዓት ታግሎ ታሪክ ሰርቶ አንድያ ህይወቱን ለአማራ ህዝብ አሳልፎ ሰጠ::

በወቅቱ አርበኛውን የገደሉት የልዩ ኃይል አባላትም እንደ ጥሬ ጨው ተበትነው ቀሩ:: እነሱ ዛሬ ላይ ተረስተዋል: ጀግናው ግን ከህዝብ ሲል ስለተሰዋ ዛሬም ስሙ ከመቃብር በላይ ሆኖ ማታገያ ስም ሆኗል::

በላስታ ግንባር በአጥንትና ደማቸው የህዝባቸውን ህልዉና ለማረጋገጥ ከፍተኛ መስዋእትነት እየከፈሉ ያሉ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች የአርበኛ ማረጉ ተማረ ቅምጥሎች ናቸው::

ሞት አይፈሬው ጀግና አርበኛ ማረጉ ተማረ ከራስ በላይ ህዝብን፣ ከከርስ በላይ ህሊናን በማስቀደም እንደ ሻማ ቀልጦ አልፏል:: የእሱን የትግል አደራ ሊወጡ የሚችሉ እና የጄኔራል አሳምነውን ራዕይ የሚያሳኩ ጀግኖችንም ፈጥሮ ነው ያለፈው::

የላስቴይቱ ልጅ ያ እንደ ነብር ቁጡው አርበኛ ማረጉ ተማረ በከፈለው መስዋዕትነት አሳምነውነት ሳይደበዝዝ ዛሬ ደርሷል:: የጄኔራል አሳምነው አስከሬን ጭምር ታግቶ በስንት ጣጣ ወደ ላስታ ከተላከ በኋላ በዚያው በቀብሩ ላይ በልባቸው ፋኖነትን ጠንስሰው የጄኔራሉን ራዕይ እና የእንደራጅ እንታጠቅ ፕሮጀክት አስቀጥለው ለመጪው ጊዜ መዘጋጀት የመሩት ልባሞች ፊታውራሪ ነው::

ይህ ጀግና ምንም እንኳን በአካለ ስጋ አሁን ባይኖርም ስሙ እና መንፈሱ ከታጋዮች የራቀ አይደለም::

ጀግና ይሰዋል ትግል ይቀጥላል!


ዘመቻ አንድነት ወሎ ቤተ-አማራ ግንባር
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ተጠናክሮ በቀጠለው ዘመቻ አንድነት ጥራሪ ክፍለ ጦር በጠላት ጦር ላይ የበላይነትን ተቀዳጀች።

የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) ላስታ አሳምነው ኮር ስር የምትገኘው በአርበኛ ኮማንዶ ብርሃን አሰፋ (ዘንዶው) የምትመራው ጥራሪ ክፍለ ጦር ተመስገን ሻለቃ የአገዛዙን ዙፋን ጠባቂ መከላከያ ሚሊሻና አድማ ብተና ከድልብ ከሳንቃና ከደቦት ከተሞች ተሰባስቦ የመጣውን 3ሻለቃ ሠራዊት በቅሎ ማነቂያ ከተማን ለማስለቀቅ ቢሞክርም ወደመጣበት አሳፍራ መልሳዋለች።

መጋቢት 30/ 2017 ዓ.ም ከጧቱ 1:30 ሰዓት አስከ 4:00 ሰዓት ለ2:30 ሰዓት በፈጀ አውደ ውጊያ የጥራሪ ክፍለ ጦር ተመስገን ሻለቃ ተወርዋሪ ፋኖዎች ወደ በቅሎ ማነቂያ ከተማ ተሰባስቦ የመጣውን 3ሻለቃ የጠላት ሃይል ከዛሬ 3ቀን በፊት ሞክሮት አሳፍረው እንደላኩት ዛሬም ሙትና ቁስለኛውን ይዞ ወደነበረበት አስፈርጥጠው መልሰውታል።

በዚህ አውደ ውጊያ አንድ ሻለቃ ፋኖዎች 3ሻለቃ መከላከያን እንዴት ሊያሸንፉን ይችላሉ በሚል ንዴትና ብስጭት ውስጥ የገባው የብልፅግና ሰራዊት ወደ ንፁሃን ዜጎች ከባድ መሳሪያ በመተኮስ የሞርታር ጥይት ንፁሃን ላይ በማረፉ አንድ የ12 ዓመት ህፃንና አንድ የ64 ዓመት አዛውንትን ገድሏል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ ተጋድሎ በዘመቻ አንድነት ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) ላስታ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ፋኖ ቢሆነኝ ቢያበይን ገልጿል።

ዘመቻ አንድነት!
ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን
የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ)
መጋቢት 30/2017 ዓ.ም

Показано 19 последних публикаций.