⛪🌹#ወር በገባ በ30 መጥምቀ መለኮት ዮሐንስ🌹
📌☞ጸሎቱና በረከቱ ለዘአለዓለሙ ከኹላችን ህዝበ ክርስቲያኑ ይሁን፡ ነብይ ሐዋርያ ሰማዕት የሆነ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ያደረገው ተአምር ይኸ ነው፡።
🛐የመጥምቀ ቅድስ ዮሐንስ የበዓሉ መታሰቢያ በዕለተ እሁድ ውሎ በወርሀ ታህሳስ ኹለት ቀን በደብረ አንገች በተከበረ ጊዜ ከቅዳሴ በኃሏ የመጥመቀ መለኮት ዮሐንስ መጽሐፍ ገድልን በንዱ አረጋዊ መነኮሴ አንደበት ይሰሙ ዘንድ ካህናቱና ሕዝቡ ተሰበሰቡ፡፡
☞ያንጊዜም ወደዚህ ጉባኤ አንዲት ሴት ቀረበች፡፡ድምጿ አሰምታ እልል እያለች
ጮኽች፡፡ይህ የክርስቲያን ጉባኤ እስኪታወክ ሕዝብ ኹሉ እርስ በእርሳቸው ይቺ
ሴት ምንድናት ደስታዋ ምንድነው እስኪሉ ድረስ እልልታዋን አልተወችም፡፡ ያመነኩሴ ግን ልብ እንደተሳናት እንደሰከረችም ቁጠራት ዝም ትል ዘንድ ገሠፃት፡፡
☞ይኽች ሴት ግን አባቴ ካህኑ ሆይ እኔ ልቤ ያዘነበት ሴት ነበርሁ፡፡ዛሬ ግን ለምለም ፍሬ የሌላት ደረቅ ዛፍ በሚሉኝ ጎረቤቶቼ መሳቂያ ለጠላቶቼ መዘባበቻ የነበርኩ ማኀፀኔ የተዘጋ እኔ ባሪያውን በቸርነቱ በጎበኘኝ በወዳጄ በቅዱስ
ዮሐንስ አምላክ በእግዚአብሄር ልቤ ጸንቶል ከብዙ እድሜዬ በኃላ ልጅ ሰጥቶኛል እኔስ ዝም አልልም አለች፡፡
☞ያም መንፈሳዊ አባት መነኩሴ ወደሱ ትቀርብ ዘንድ የምትለውን ሕዝብ ይሰሙ ዘንድ ጠራት ይቺም ሴት ወደ ቤተክርስቲያኑ አደባባይ አደባባይ እልል እያለቾ ከወለደችው ልጇ ጋር ቀርባ አባቶቼ ና ወንድሞቼ እኅቶቼም ሆይ አንድ
ልጅ እንኳን በማጣት ብዙ ዘመን ሳዝን ስተክዝ ኖርሁ ዘመዶቼ ሳይቀሩ ጎረቤቶቼ ኹሉ የደረቀች ዛፍ ይሉኝ ነበር ፡፡
ስለዚህ አምና እንዳ ዛሬው ወደ ወዳጄ መጥምቁ
ቅዱስ ዮሐንስ መጥቼ ተሳልሁ ይኸንን መልኩ ያማረ ደምግባቱ የተወደደ ልጅ ሰጠኝ ድንቅ ተዐምር ለሚያደርግ ለመጥምቀ መለኮት ዮሐንስ እልል እላላሁ በመጥምቁ በቅዱስ ዮሐንስ አማልጅነት ይህን ልጅ ለሰጠኝ ለእግዚአብሔር እዘምራለሁ ስትል መሰከረች፡፡
☞ይህን የሰሙ ሕዝቡም ኹሉ አደነቁ በማግስቱ ያመነኩሴ ከካህናቲ ጋር ኾኖ ያን ሕፃን አጠመቀው፡፡እርሷም እልል እያለች እየዘመረች ወደ ቤቷ ተመለሰች፡፡ ☞የመጥምቀ መለኮት ቅድስ ዮሐንሰ ጸሎቱ በረከቱ በማላጅነቱ ለምታምኑ ሁሉ ከእናተ ጋር ይኹን፡፡
☞ገድለ ዮሐንስ መጥምቅ
☞ሲራክ ተክለጻዲቅ የተዋህዶ ልጅ
☞.
https://t.me/Orthodoxtewahdoc