Peace tv amharic


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


ለሰው ልጆች ችግር ሁሉ መፍትሄ

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций


ፅንፈኛው የህንድ መንግስት ዶ/ር ዛኪርን ክስ መስርቶ ከሀገር አባረረው..! ታዲያ ዳዒ ምን ይገደዋል? ሌላ ቦታ ሒዶ ዳዕዋውን ይቀጥላል..! ይህ ከታች የምትመለከቱት ምስል በማሌዥያ ግዙፍ ስቴድየም ውስጥ የተደረገ የዳዕዋ ፕሮግራም ነው። ፕሮግራሙ ኢስላም ጠልነትን/Islamophobia/ በተመለከተ የቀረበ ሲሆን 100,000 የሚጠጋ ሰው እንደተከታተለው ተነግሯል። ሸይኸል ኢስላም ኢብን ተይሚያ رحمه الله በሚታወቁበት ወርቃማ ንግግራቸው እንዲህ ይላሉ፦ "ጠላቶቼ በኔ ላይ ምን ሊያደርጉ ይችላሉ? ቢገድሉኝ ሸሒድ (መስዋዕት) ነኝ ቢያስሩኝ አላህን ተገልየ አስታውሰበታለሁ፤ ከሀገር ቢያባርሩኝ በምሔድበት ዳዕዋ አደርጋለሁ"

እውነት ነው..! በአላህ ባሪያ ላይ ጠላቶች ምን ሊያደርጉ ይችላሉ?


የሰው ልጅ በህይወቱ ላይ የዝሙትን በር አንዴ ከከፈተ ወላሂ ለመውጣት እጅግ በጣም ይከብደዋል። ሱስ ይሆንበታል። ይጀምረዋል ማቆም ከባድ ይሆንበታል። ዝሙት አስፈሪ በሽታ ነው። ዝሙተኛ የነካው ነገር ሁሉ አላህ በረካውን ያነሳበታል። ገንዘብን ቢያገኝ እሳት ያቃጠለበት በሚመስል መልኩ በፍጥነት ያልቃል። ዝሙተኛ በዙሪያው ያሉ ጛደኞችን በረካ ጭምር ያነሳል። ዝሙት ውስጥ የገባ ህይወት ዝሙት ይገለዋል። ዝሙተኛ ሆኖ የሞተ ነፍስ ብርሃን ይናፍቀዋል፤ አላህ ያዘነለት በስተቀር።
ዝሙተኛ አግብቶም አርፎ አይቀመጥም። ሰዎች በጋብቻ ህይወታቸው ሲማግጡ የሚገኙት ለምን ይመስለናል? ከጋብቻ በፊት የተጀመረ በመሆኑ ነው።
አላሁ ሰላም!! አላህ ከዝሙት ይጠብቀን!!
https://t.me/peacetvamharic1


ብዙ ነገሮችን መመለስ ትችላለህ። ጊዜን መመለስ ግን አትችልም። ህይወትን መመለስ አትችልም። ጊዜ በገንዘብ አይተመንም። ስለዚህም አታባክነው። በልኩ ተጠቀምበት።


የዛሬ 16 አመት ሊጋቡ ወስነው ነበር እስራኤሎች እስር ቤት የከተቱት። 16 አመት እስር ቤት ቆይቶ ሲመለስ ፍፁም ያልጠበቀው ነገር ገጠመው። እስር ቤት ሲገባ የ17 አመት ልጅ የነበረችው እንስት ሌላ ወንድ ሳታይ ነበር በሰብር የጠበቀችው። ይህን ሁሉ አመት ጠንክራ በመስራት መሬት ገዝታ፣ ቤት ሰርታበት ከእስር ሲወጣ የሚጣድበትን ስራ አመቻችታ በእጇ በቂ ካሽ አዘጋጅታ ነበር። አላህ ትዳራቸውን ይባርክ🙏🙏


አንድ ትንሽዬ ልጅ በሁለት እጆቿ ሁለት አፕል(ፓም) ይዛለች። እናቷ መጣችና በፈገግታ በመታጀብ አንዱን አፕል እንድተሰጣት ጠየቀቻት። ትንሿ ልጅ እናቷን ቀና ብላ ለሰከንድ ተመለከተቻትና የያዘችውን ሁለቱንም ፓም በተራ ተራ ገመጠቻቸው። እናት በልጇ ድርጊት ደስተኛ ባትሆንም ፈገግታዋን ግን አልነፈገቻትም። ንዴቷንም በግልፅ ላለማሳየት ጥረት አደረገች። ልጅ ከገመጠችው አፕል አንዱን አንስታ "እማዬ ይሄ ያንቺ ነው፤ ከሁለቱ ይህኛው ይጣፍጣል" በማለት ጣፋጩን ለእናቷ አሳልፋ ሰጠች።

አንተ ማንም ሁን ማን፤ ምን ያህል አዋቂ ነኝ ብለህ ብታስብ፤ ለውሳኔ አትቸኩል ከዚህ ት/ት መልእክት አንዱ ነው።
https://www.facebook.com/peacetvamharic/


ማየት የማይችሉ ሰውዬ ከእግራቸው ጎን ጨርቅ አንጥፈው ይለምናሉ፡፡ ጨርቁ ላይ በብጣሽ ወረቀት “አይነ ስውር ነኝ እባካችሁ እርዱኝ” የሚል ፅሑፍ ተፅፏል፡፡የተወሰኑ ሰዎች የሰውዬውን ሁኔታና የተፃፈውን ወረቀት እያዩ ጨርቁ ላይ ሳንቲም እየጣሉ ይሄዳሉ፡፡ቢሆንም ግን ጨርቁ ላይ በጣም ትንሽ ሳንቲም ነው የሰበሰቡት፡፡

አንድ ልጅ በዛው መንገድ እያለፈ ነበር፤ ከኪሱ ሳንቲም አወጥቶ ጨርቁ ላይ ከጣለላቸው በሗላ የተፃፈውን ወረቀት አንስቶት በግልባጩ የተወሰኑ ቃላቶችን ፅፎበት ሄደ፡፡ የፃፈውን ሰዎች እንዲያዩት ወረቀቱን ገልብጦ አስቀምጦት ሄደ፡፡

በትንሽ ጊዜ ውስጥ ጨርቁ በሳንቲም ይሞላ ጀመር፡፡ ለአይነ ስውሩ ከቅድሙ ይልቅ ብዙ ሰዎች ሳንቲም ይሰጡት ጀመር፡፡ በዛው ቀን ከሰዐት ወረቀቱን የቀየረው ልጅ በመንገድ ሲያልፍ የሰውዬውን ሁኔታ ሊያይ ይቀርባቸዋል፡፡ አይነስውሩ የልጁን አረማመድ ስላወቁ “ልጄ ወረቀቱ ላይ የተፃፈውን የቀየርከው አንተ ነህ?” ብለው ጠየቁት፤ ልጁም “አዎ እኔ ነኝ” አላቸው፡፡
ሰውዬው ካመሰገኑት በሗላ “ምን ብለህ ፅፈህበት ነው?” አሉት
ልጁ “ እኔ የፃፍኩት እውነታውን ነው፤ በሌላ መልኩ ቢሆንም ያልኩት እርሶ ያሉትን ነው” አላቸው፡፡
ልጁ የፃፈው “ ዛሬ የሚያምር ቀን ነው፤ ነገር ግን ላየው አልቻልኩም” የሚል ነበር፡፡ ሱብሃነላህ!!

የመጀመሪያውና ልጁ የፃፈው አንድ አይነት ይመስላሉ አይደል? በርግጥ ሁለቱም ፅሑፎች የሰውዬውን አይነስውርነት ይናገራሉ፡፡ ነገር ግን የመጀመሪያው ፅሑፍ ሰውዬው እውር መሆኑን ብቻ ነው የሚናገረው፤ ሁለተኛው ፅሁፍ ሰዎች እንደ ሰውዬው አይነስውር ባለመሆናቸው እድለኛ መሆናቸውን የሚጠቁም ነው፡፡

“እርሱም ያ መስሚያዎችንና ማያዎችን ልቦችንም ለእናንተ የፈጠረላችሁ ነው፡፡ ጥቂትን እንጅ አታመሰግኑም፡፡” (ሱረቱል ሙዕሚኑን ምዕራፍ 23 አንቀፅ 78)
አልሃምዱሊላህ!!
https://www.facebook.com/peacetvamharic/


ኢማም አህመድ ልጅ እያሉ ነበር አባታቸው ያረፉት። ታዲያ ለዚህ ደረጃ ይበቁ ዘንድ እናታቸው ከፍተኛ ሚና አበርክተዋል። ኢማም አህመድ ለተማሪዎቻቸው የናታቸውን ጥረት ይነግሩ ነበር።

እናት በብርዳማዋ ባግዳድ ከተማ በለሊት አስቀድመው ተነስተው ልጃቸው አህመድ ሱብሂ ተነስቶ ይሰግድ ዘንድ ውሃ ያሞቁለት ነበር። ደርስ ላይ ከፊት እንዲቀመጥ በማሰብ ልብስ ደራርባ አልብሳቸው በድቅድቅ ጨለማ ከሱብሂ በፊት ዋናው መስጂድ ድረስ ታደርሰው ነበር። ተምሮ እስኪጨርስ ቁጭ ብላ በመጠበቅ ቤታቸው በሰላም ታደርስ ነበር።

ኢማም አህመድ 16 አመት ሲሞላቸው ያላትን ገንዘብ ሰብስባ "እውቀትን ፍለጋ ተጓዝ" ብላ ልካዋለች። በዚህ ሰበብ መካ መዲናን ጨምሮ የተለያዩ ከተማዎች በመጓዝ ታላላቅ አሊሞች ዘንድ ቀርቦ ለመማር ችሎዋል። ኢማም አህመድን በዚህ መልኩ በማሳደግ ከአራቱ ታላቅ ኢማሞች አንዱ ለመሆን ኢንዲበቃ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጋለች።
(አላህ ይዘንላቸው)

በአንድ አጋጣሚ ለዶር ዛኪር አንድ ተመልካች በጥያቄና መልስ ዝግጅት ላይ "ልጄን መልካምና ዲኑን የሚጠቅም አድርጌ ማሳደግ እፈልጋለሁ። ምን ትመክረኛለህ?" ብሎ ጠይቆት ነበር። ዶር ዛኪር ጠያቂው ባለትዳር መሆኑን ካረጋገጠ በሗላ "በርግጥ ዘግይተሃል። ስለ ልጅህ አስተዳደግ መጠየቅ የነበረብህ እናቱን ከመምረጥህ በፊት ነበር" ብሎ ምላሹን የጀመረለት። ሀቅ ነው ልጅን በመልካም ስብዕና አንፆ ለማሳደግ የእናት ድርሻ ትልቁን ቦታ ይይዛል። አለማችን ላይ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችን ብንመለከት ከጀርባቸው የእናት ልፋት ውጤት ሆኖ እናገኘዋለን።
https://www.facebook.com/peacetvamharic/


ሰሃብዩ "በ 3 ሁኔታ ላይ ሆኜ ብሞት ከአላህ ጀነትን እከጅላለሁ" አለ።

1ኛ ጀናዛ ሳስቀብር ልቤ የሚሰማው የአላህ ፍራቻን ሳስብ በዚህ አይነት ሁኔታ ብሞት ጀነትን ያለጥርጥር እከጅላሁ አለ። እኛ ዛሬ ጀናዛ እያስቀበርን እንስቃለን እናወራለን እንጫወታለን አላህ ይዘንልን። አብደላህ ኢብን መስዑድ አንዴ ሰው እያስቀበሩ አንድ ልጅ ሲስቅ አዩት። "አንተ ጀናዛ ፊት ቆመህ ትስቃለህ?? በአላህ ይሁንብኝ ከእንግዲህ አላወራህም" አሉት። ራሳችንን እንፈትሽ።

2ኛ ቁርዓን እያነበብኩ ብሞት ከአላህ ጀነትን እከጅላለሁ አለ። ቁርዓን ከቀራን ስንት ጊዜ ሆነን?? መቅራታችን በዝቶብን ካዳመጥን ስንት ጊዜ ሆነን?? ቤታችን ይቁጠረን።

3ተኛ የነብዩን ሃዲስ እየሰማሁ ብሞት ከአላህ ጀነትን እከጅላለሁ አለ። የነብዩ ንግግር ለሩህ ቀለብ ናት። ሀገር የሚጠፋው፣ ሰው እርስ በርስ የሚጣላው፣ ወንጀል የሚንሰራፋው ሰው ምግብ ተርቦ ሳይሆን ሩህ መልካም ንግግር በማጣቱ ነው።
https://www.facebook.com/peacetvamharic/


ሰዎች በድለውሀል? ረሱሉላህ ﷺ ተበድለዋል፤ ተሰደዋል ባልደረቦቻቸው ተርበው ለ3 አመት ቅጠል ሲበሉ ከርመዋል። ነገር ግን ለስቃይ የዳረጓቸውን በሙሉ ይቅርታ አድርገዋል።

ሰዎች ጎድተውሃል? ኡትባ የነብዩ ሙሀመድን ﷺ ልጅ ነበር ያገባው። ነብዩ ﷺ ስለ አምላክ አሃዳዊነት መስበክ ሲጀምሩ ኡትባ ነብዩን ﷺ ለመጉዳት አስቦ ልጃቸውን ፈቶዋል። ከአመታት በዃላ ሊሰልም መጣ። ይቅርታ አደረጉለት።

ብቸኛ ነህ? ረሱሉላህ ﷺ አባታቸውን እናታቸውን አያታቸውን ገና በ8 አመታቸው ነው ያጡት።

የምትበላው የለህም? ረሱሉላህ ﷺ ተርበዋል። ከመራባቸው ብዛት ሆዳቸው ላይ ድንጋይ ያስሩ ነበር።

የምትወደውን አጥተሃል? ረሱሉላህ ሁሉንም ወንድ ልጆቻቸው እና 3 ሴት ልጆችን በህይወት ሳሉ አጥተዋል።

ሰዎች ይስቁባቸዋል እርሳቸው ግን ለሰዎች ያለቅሱ ነበር። ሰዎች ይቀልዱባቸው ነበር እርሳቸው ዱዓ ያደርጉላቸዋል። ተሰብስበው ይዶልቱባቸዋል እርሳቸው ግን መልካምን ይመኙ ነበር።
ስትኖር እንደ ሀቢቢ ሙስጠፋ ﷺ ሆነህ ኑር።
ሰለዋቱላሂ ወሰላሙ አለይህ!!
https://www.facebook.com/peacetvamharic/


በጥያቄና መልስ ፕሮግራም አንድ እህታችን ለዶር ዛኪር ይህን ጥያቄ ጠይቃው ነበር።
"በዚህ ፕሮግራም መጠየቅ የምፈልገው ለእስልምና ያለኝ ክብር እንደተጠበቀ ሆኖ ጣዖት ማምለክና ከአላህ በስተቀር አምላክ አድርጎ መያዝ በእስልምና ከባድ ወንጀል እንደሆነና እነዚህን ሰዎች አላህ እንደማይምራቸው ነግረኸናል።

እንደዛ ከሆነ ከእስልምና ውጪ በሆነ ሀይማኖት ቤተሰብ የተወለዱ ልጆች ምን ሊሆኑ ነው?
ስለ እስልምና ምንም የማያውቅ ብዙ ሰው አለ። ያስተማራቸውም የለም። የነዚህ እጣ ፈንታ ምንድነው?


ምንድነው ጥፋታቸው?
ፈፅሞ ገነት አይገቡም ማለት ነው?
አላህ አይምራቸውም ማለት ነው?
ተወልደው ያደጉበት ቤተሰብ ያስተላለፈላቸውን ሀይማኖት መከተላቸው ስህተት ነውን? አላህ አያዝንላቸውም?
አመሰግናለሁ!

ዶር ዛኪር ከመቀመጫው በመነሳት ለጥያቄዋ ማብራሪያ እንደሚከተለው ሰጧት
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

"እህታችን እጅግ በጣም ጥሩ ጥያቄ ነው የጠየቅሽው። ሙስሊም ካልሆነ ቤተሰብ የሚወለዱ ልጆች እጣፋንታቸው ምንድነው፣ ጣዖት የሚያመልኩና የመሳሰሉት አላህ ይቀጣቸዋልን? የሚል ጥሩ ጥያቄ ጠይቀሻል።

ለዛም ነው ተወዳጁ ነብያችን(አ ሰ ወ) "ሁሉም የአደም ልጅ ሲወለድ ተፈጥሯዊ በሆነ ሀይማኖት ነው" ያሉት። ሙስሊም ሆነን ነው የምንወለደው።
በአይሁድ ቤተሰብ ይወለድ በክርስቲያን፤
በሂንዱም ይሁን በሙስሊም ቤተሰብ፤
ማንም ሰው ሲወለድ ሙስሊም ሆኖ ነው የሚወለደው።

ሙስሊም ብሎ ማለት ራሱን ለፈጣሪ ትዕዛዝ ያስገዛ ማለት ነው።
ስለዚህም ማንም ሰው ሲወለድ ራሱን ለፈጣሪ ትዕዛዝ ያስገዛ ሆኖ ነው። ከጊዜ በዃላ ግን በቤተሰቦቹ፤ በታላቆቹ ወይም በአስተማሪዎቹ ምክንያት ሊሆን ይችላል ጣዖትን፣ እሳትን የመሳሰሉትን ማምለክ ይጀምራል። በተሳሳተ መንገድ ይሄዳል።

ለዛም ነው አንድ ሰው ሲሰልም ወደ እስልምና ተቀየረ ከሚለው ቃል ይልቅ ወደ እምነቱ ተመለሰ የምንለው።
ተቀየረ የሚለው ቃል አይገልፀውም።
ተቀየረ የሚለውን ቃል የምንጠቀመው ከአንድ እምነት ወደ ሌላ እምነት ሲሄድ ነው። ተመለሰ የምንለው ግን መጀመሪያ ወደነበረበት እምነት ሲመለስ ነው።
ስለዚህ ትክክለኛው ቃል ተመለሰ የሚለው ነው።

ወደ ጥያቄሽ ስመለስ፤ ከሌላ እምነት ተከታይ ቤተሰብ የተወለደን ሰው አላህ ለምን ይቀጣዋል ላልሺው።

አንድ ህፃን ለአቅመ አዳም ሳይደርስ ከሞተ በአላህ ፍቃድ ጀነት ይገባል። ምክንያቱም ማንኛውም ህፃን ሲወለድ ራሱን ለፈጣሪ ያስገዛ ስለሆነ። የሂንዱ ስም ይኑረው የክርስቲያን ስም ለውጥ አይፈጥርም።

ለአቅመ አዳም እስካልደረሰ ድረስ በህፃንነቱ ከሞተ ጀነት ይገባል። ከሙስሊም ቤተሰብ ይወለድ ሙስሊም ካልሆነም ቤተሰብ ጀነት ይገባል።
ከጊዜ በዃላ ህፃኑ አድጎ ለአቅመ አዳም ሲደርስ ግን ለሚሰራው ስራ ሁሉ ሀላፍትና የሚወስደው ራሱ ነው።

ለዛም ነው ህፃን ልጅ ጥፋት ሲያጠፋ ህግ የማይቀጣው። ለአቅመ አዳም ሲደርስ ግን "አባቴ ስረቅ ስላለኝ ነው የሰረቅኩት" ቢል ከህግ ቅጣት የማይድነው።

ልጅ ካደገ በዃላ 22 አመት ሞላው ብንል እና ሲሰርቅ ፓሊስ ቢይዘው "አባቴ ስረቅ ስላለኝ ነው የሰረቅኩት" ሊል አይችልም። ይህን ማለቱ ከቅጣት ያድነዋል?
ህፃን እያለ 5 አመቱ ላይ ይህን ቢል ችግር የለውም። ህፃን ስለሆነ ይባላል። ለአቅመ አዳም ከደረሰ በዃላ ግን "አባቴ ስረቅ ስላለኝ ነው የሰረቅኩት" ቢል ነፃ ሊወጣ አይችልም።

ማንም ሰው ለአቅመ አዳም ከደረሰ በዃላ ለውሳኔው ሃላፍትና ራሱ ነው የሚወስደው። አንድ ሰው ለአቅመ አዳም ከደረሰ በዃላ እውነትን መፈለግ የራሱ ወይም የራሷ ሃላፍትና ነው።

የእስልምናን መልዕክት ሙስሊም ላልሆኑት ማድረስ የኛ የሙስሊሞች ሃላፍትና ነው። ነገር ግን መልዕክቱ ደረሳቸውም አልደረሳቸውም የሰው ልጅ በነፃነት ከተተወ ለምሳሌ እስከ 1950 ከአለም ስልጣኔ ጋር ምንም ንክኪ ያልነበራቸው ሁለት ጎሳዎች ነበሩ። አንዱ ጎሳ ከፓውኩ ሲባል ሁለተኛው አስትሮይድ አቦ ሪጅን ይባላል። እነዚህ ሁለት ጎሳዎች እስከ 1950 ድረስ ዘመናዊ ስልጣኔ የሚባል ነገር አያውቁም። ተመራማሪዎች የኑሮ ሁኔታቸውን ለማጥናት ሲሞክሩ ሁለመናቸው ኢስላም ሆኖ ነበር ያገኙት። ራሳቸውን ግን ሙስሊም አይሉም ነበር።

በአንድ አምላክ ያምናሉ
ፈጣሪ አምሳል እንደሌለው ያምናሉ
ጣዖት እንደሌለው ያምናሉ
ፈጣሪን ሱጁድ በማድረግ ይገዛሉ
ከስም በስተቀር ነገረ ስራቸው እስልምና ይመስል ነበር።

ህፃን ልጅ ውጫዊ ተፅዕኖ ባይኖርበት ራሱን ለፈጣሪ ያስገዛ ሆኖ ያድግ ነበር። በዛም መንገድ ይፀና ነበር። ለአቅመ አዳም ሲደርስ የእስልምና ሀይማኖት መልዕክትን እኛ ሙስሊሞች የማድረስ ሃላፍትና አለብን። ካላደረስን አላህ ዘንድ ተጠያቂዎች ነን።

ነገር ግን መልዕክቱን የማድረስ ስራውን ሰራንም አልሰራንም ተጠያቂዎች ብንሆንም አላህ(ሱ ወ) በተከበረው ቁርዓን ሱረቱል ፉሲለት ምዕራፍ 41 አንቀፅ 53 ላይ "እውነት መሆኑ እስኪገለፅላቸው ድረስ በአፅናፎቹ ውስጥና በነፍሶቻቸውም ውስጥ ያሉትን ተዓምራቶቻችንን በርግጥ እናሳያቸዋለን" ይላል። አላህ(ሱ ወ) ያለማንም እገዛ ለእያንዳንዱ ሰው እውነታውን ሊያሳይ በራሱ ላይ ሀላፍትና ወስዶዋል።

እኛ መልዕክቱን አደረስንም አላደረስንም ጥሩ ምሳሌ ሆንም አልሆንም አላህ ራሱ በቀጥታ በእያንዳዱ የሰው ልጅ ልብ ላይ እውነታውን ያሳየናል።
ሙስሊም ብንሆንም ባንሆንም ስለ ፈጣሪ አንድ መሆን እውነታውን ያሳየናል።

እውነታው ከተገለፅን በዃላ መቀበል አለመቀበል የኛ ምርጫ ነው። አንዳንዱ እስልምናን ከተቀበልኩ መጠጥ ላቆም ነው፤ ከሴት ጋር ልቅ መሆን፤ መጨፈር የመሳሰሉ በሀይማኖቱ ክልክል የሆኑ ድርጊቶችን ላቆም ነው በሚል መሰል ምክንያቶች እውነትን ላይቀበል ይችላል። ምርጫው የራሱ ነው፤ ከዛ ግን ይጠየቅበታል።

በተመሳሳይ አባት ለልጁ ስህተትን ካስተማረው ለምሳሌ መስረቅን ቢያስተምረው መስረቅ ወንጀል መሆኑን መለየት የልጅ ሃላፍትና ነው። ልጅ ዳኛ ፊት ቆሞ "አባቴ ስረቅ ብሎ ስላስተማረኝ ነው የሰረቅኩት" ቢል ነፃ ሊወጣ አይችልም።

በተመሳሳይ አላህ(ሱ ወ) እውነታውን በእያንዳዳችን ልብ ይገልፅልናል። ስለ ሀቅ፣ ስለፈጣሪ አንድ መሆን፣ ጣዖት ማምለክ ወንጀል መሆኑን ይገልፅልናል። እውነቱ ከተገለፀለት በዃላ ተግባሩን የቀጠለ ሰው በድርጊቱ ተጠያቂ ይሆናል።

ለዛም ነው በምፅዓት ቀን በአላህ(ሱ ወ) ፍትሃዊነት ዙሪያ አንድም ሰው ቅሬታ የሚያቀርብ እንደማይኖር አላህ የነገረን። ምክንያቱም የሰውነታችን አካል በኛ ላይ ይመሰክራሉ፣ አይናችን፤ እጃችን እኛ ላይ ይመሰክሩብናል።

በፍርዱ ቀን እሳት የገቡት ሰዎች ሳይቀሩ በአላህ ፍትሃዊነት ላይ ቅሬታ የሚያቀርብ አታገኙም። የሚሉት "ጌታችን ሆይ አንድ እድል ስጠን" ነው። አላህም "ዘግይታችዃል" ይላቸዋል። ምድር ላይ ስንኖር ብዙ እድሎች ተሰጥቶናል። ምድር ላይ የምንኖረውም አንድ ጊዜ ብቻ ነው።

ስለዚህም የፍርዱ ቀን አንድም ሰው ሙስሊም ያልሆነ ይሁን ገሀነም የገባው ሳይቀር በአላህ ፍርድ ላይ ቅሬታ የሚያቀርብ ሰው የለም። "ጌታችን ሆይ ማረን" ይላሉ "አርፍዳችኳል" ይባላሉ።
ያለንበት አለም አላህ (ሱ ወ) በቁርዓን በሱረቱል ሙልክ ምዕራፍ 67 አንቀፅ 2 ላይ ይህኛው አለም ለቀጣዩ አለም የምንፈተንበት መሆኑን ነግሮናልና ነው።

ጥያቄሽን እንደመለስኩልሽ ተስፋ አደርጋለሁ።"
https://www.facebook.com/peacetvamharic/


ሸቂቅ ኢብን ኢብራሂም አነድ ጊዜ እንዲህ ብለው ነበር “ሰዎች እነዚህን አራት ነገራቶች ሲናገሩ ትሰማለህ ነገር ግን ስራቸው ፈፅሞ ከንንግግራቸው ጋር ሲጋጭ ትመለከታለህ”

1.ሁሉም የፈጣሪ ባሪያ ነኝ ሲል ትሰማለህ ነገር ግን ስራቸው የማንም ባሪያ አይመስሉም፤ ጌታቸው “ማንም” ሆኖ ታገኘዋለህ።

2.ሰዎች አላህ ነው የሚረዝቀን ሲሉ ትሰማቸዋለህ ነገር ግን የዱንያ ሀብት ከሌላቸው ልባቸው እርጋታን አጥታ ትመለከታለህ።

3.ሰዎች ከዚህ ሀገር ዱንያ መጪው ሀገር አኼራ እንደሚሻል ሲናገሩ ትሰማለህ ነገር ግን ቀንም ማታም በሀላልም ይሁን በሀራም መንገድ ዱንያን ሲያከማቹ ትመለከታለህ።

4.ሞት እርግጥ ነው ሲሉ ትሰማቸዋለህ ነገር ግን ስራቸውን ስትመለከት ፈፅሞ ሞት ያለባቸው አይመስልም፡፡


አል-ቁርዐን
https://www.facebook.com/peacetvamharic/


የንግግራችን ውጤት

ስለ አንድ ስብስብ ጌታችን አላህ ሲነግረን "በተናገሩት ምክንያት ጀነትን ሸለምናቸው..." ይላል(ሱረቱል ማኢዳ 85)

ስለ ሌሎች ስብስብ አላህ ሲነግረን "በተናገሩት ምክንያት ረገምናቸው..." ይላል። (ሱረቱል ማኢዳ 64)

የአላህ መልዕክተኛ ﷺ "አንድ የአላህ ባሪያ ሳያስበው አንድን ነገር ይናገራል። በንግግሩ አላህ ይደሰትና ደረጃውን ከፍ ያደርግለታል። ሌላኛው የአላህ ባሪያ የንግግሩን ውጤት ሳያስብ ይናገርና አላህን ያስከፋል። በዚህም ምክንያት ጥልቅ እሳት ውስጥ ራሱን ይከታል" ብለው ተናግረዋል። (አል ቡኻሪ)

ንግግራችን የጀነትና የጀሀነም ልዩነት ይኖረዋል። ሽልማት ወይም ቅጣት ይሆናል። ስለዚህም ከማውራታችን በፊት እናስተውል።
https://www.facebook.com/peacetvamharic/


የነብዩ ሙሀመድ ﷺ ተወዳጅ ልጃቸው ሩቅያ(ረ ዐ) በረመዳን 17 ነበር ወደ አሄራ የሄደችው።

ከበድር ጦርነት በፊት ነበር የታመመችው። ነብዩ ሙሀመድﷺ ወደ በድር ጦርነት ሲሄዱ የሩቅያ ባለቤት ሰይድና ኡስማን ኢብን አፋንን(ረ ዐ) ከዘመቻው ቀርቶ እንዲንከባከባት አዘዙት። በዚህም ምክንያት ታላቁ ሰሃቢ በእስልምና ታሪክ ትልቅ ቦታ የሚሰጠውን የበድር ጦርነት ሳይሳተፉ ቀርተዋል። የሁለቱ ባለትዳሮች ጥምረት እጅግ በጣም ደስ የሚል ጥምረት ነበር። ይዋደዳሉ ይፋቀራሉ ይተዛዘናሉ። ረሱሉላህﷺ አንድ ጊዜ ለባልደረቦቻቸው ተገርመው "ከሁለቱ የተሻለ የሚያምር ጥምረት አይታችሁ ታውቃላችሁን" ብለው ነበር።

ነገር ግን የበድር ጦርነትን ድል አድርገው ሲመለሱ አሳዛኝ ዜና ነበር የሰሙት። የሚወዷት ልጃቸው ሩቅያ(ረ ዐ) በወጣትነቷ ህይወቷ አልፎ ነበር። በዚህ አስቸጋሪ ወቅት እንኳ የነብዩ ሙሀመድﷺ ትዕግስትና አመስጋኝነት እጅግ አስገራሚ ነበር።

አላህ የሩቅያን(ረ ዐ) ደረጃ ከፍ ያድርገው። እህቶቻችንን በጀነት ላይ የሩቅያ ጎረቤት ያድርግልን🙏🙏
ሰለዋቱ ላሂ ወሰላሙ አለይህ!!
https://www.facebook.com/peacetvamharic/


ነብዩ ሙሀመድ ﷺ አባታቸውን ከመወለዳቸው በፊት ነበር ያጡት። ውዱ ነብያችን ﷺ በበረሃ ሃገራቸው እናታቸውን ገና በ6 አመት ሳሉ ነበር ያጡት። እናታቸው በህመም ሳሉ በአይናቸው አይተዋል፤ በዛ ልጅነታቸው ይህን አለም ለቃ ስትሄድባቸው ከጎን ሆነው መስክረዋል። አያታቸው ያሳድጓቸው ጀመር። እስከሚችሉት ድረስ ፍቅርና እንክብካቤን አድርገውላቸዋል። ነገር ግን ብዙም ሳይቆይ በ8 አመት ሳሉ አያታቸውንም አጡ። ባለቤታቸው አለም ላይ ካሉ ሰዎች እርሳቸው ዘንድ ተወዳጅ ነበረች። ነገር ግን በከባድ የፈተና ወቅት እርሷንም አጥተዋል።

8አመት ከሞላቸው በዃላ በአጎታቸው ስር ሆኑ። መካ ላይ አጎታቸው ለነብዩ ﷺ ከለላቸው ነበሩ። ነገር ግን ከነብዩ በፊት አለፉ። እንደ አባት ሆነው ያሳደጓቸውን አጎታቸው አሰቃቂ ሞት በአይናቸው አይተዋል። ልባቸው በሀዘን ተሰብሯል። እንደ እናት ሆና ያሳደገቻቸው አክስታቸውን በእጃቸው አፈር አንስተው ቀብረዋል።

ልጆቻቸው ገና ልጅ እያሉ ነው የሞቱባቸው። 4 ወንድ ልጆቻቸውን በህይወት ሳሉ ቀብረዋል። የተባረከ አይናቸው ብዙ አንብቷል። የሚወዷቸው ባልደረቦችና አብሮ አደጎቻቸው ሲሰቃዩና ህይወታቸው ሲያልፍ በህይወት ሳሉ አይተዋል። በድር ዘመቻ ሄደው ሲመለሱ ሴት ልጃቸው ወደ አሄራ መሄዷን ነበር የተበሰሩት። ህይወት ትቀጥላለች። ሌላ ሁለት ሴት ልጆቻቸውን በተባረከ እጃቸው አፈር አልብሰዋል። ምን ያህል ከባድ ነው? ምን ያህል ጥንካሬ ነው?

ይህ ሁሉ ሆኖ ሳለ አንድ ሰሃብይ ስለርሳቸው ሲናገር "ነብዩ ሙሀመድን ﷺ ፈገግታ ተለይቷቸው አይቼ አላውቅም" ብሎ ነበር። ሰለዋቱ ላሂ ወሰላሙ አለይህ!! ምንኛ ያማረ መልካም ባህሪ ነው?
የርሳቸውን ፈለግ የተከተለ በሙሉ አላህ ባጣነው ይተካልን ሰብሩንም ይለግሰን እላለሁ🙏🙏
https://www.facebook.com/peacetvamharic/


መውላና ሩሚ አንድ ጊዜ እንዲህ ብለው ነበር "ዝናብ ከሰማይ ይወርዳል። ጠብታዎቹ በፀዳ እጅ ላይ ካረፈ ለመጠጣት ትችላለህ። አሸንዳ ላይ አርፎ ከወረደ ጥራቱ ቀንሶ እጅህን ላትታጠብበት ትችላለህ። ሞቃታማ ቦታ ላይ ካረፈ ይተናል። ቅጠል ላይ ካረፈ ሲያንፀባርቅ ታየዋለህ። የሚወርደው ጠብታ ተመሳሳይ ሆኖ ሳለ ባረፈበት ቦታ ምክንያት ውበቱም ሆነ ጥቅሙ ሲለያይ ታየዋለህ"
የሰው ልጅም እንደዛው ነው። የምታርፍበትን ቦታ አስተውል። ጓደኛ ምረጥ። ከመልካም ሰዎች ጋር ቅረብ መልካም ሰው ትሆናለህ።
አላህ ይወፍቀን🙏🙏
https://t.me/peacetvamharic1


ሁሌ ጠዋት ጠዋት አረጋውያን መጦሪያ እየሄደ ይመግባታል። በአልዛይመር ምክንያት ባለቤቷን ሳይቀር ማስታወስ አትችልም። ሲመላለስ የሚያውቁት ሰራተኞች ለሰውዬው አዝነው "ከረሳችህ 5 አመት ሆኖታል። በየቀኑ ለምን ትመጣለህ?" ብለው ጠየቁት። ሰውዬው ፈገግ ብሎ "እኔ ማን እንደሆንኩ ባታውቅም፤ እርሷ ግን ማን እንደሆነች አውቃለሁ" ብሎ መለሰላቸው።
ይህ ነው ፍቅር❤️
https://www.facebook.com/peacetvamharic/




ከታች የምታዩት ፎቶ አል አብዋ የሚገኘው የነብዩ ሙሀመድﷺ እናት ሰይድና አሚና የተቀበሩበት ስፍራ ነው። በዚህ ስፍራ ረሱሉላህ ﷺ እናታቸውን የቀበሩት በ6 አመት ሳሉ ነበር። ከ50 አመት በዃላ በሺ ከሚቆጠሩ ባልደረባዎቻቸው ጋር እዚህ ስፍራ ላይ ብቅ ብለው ነበር። ለመጀመሪያ ጊዜ ነበርና የተመለሱት በጣም አለቀሱ ረዘም ላለ ሰዓታትም ቆዩ። የሳቸውን ማልቀስ ተያይዞ በቦታው የነበሩ ሰሃቦች ባጠቃላይ ፂማቸው እስኪረጥብ አልቅሰው ነበር። ረሱሉላህ ﷺ የፍጥረታቶች መሪና የአደም ልጆች አለቃ ቢሆኑም ልክ የሌለው እዝነታቸውና ለእናታቸው የነበራቸው ክብርና ፍቅር ወደር የለውም ነበር።

በቢሊየን የሚቆጠሩ ሴቶች ተፈጥረዋል ነገር ግን እሜቴ አሚና የረሱሉላህን ﷺ ብርሃን ትሸከም ዘንድ ተመርጣለች። ውብ መልካቸውን ለማየት፣ ለመሳም፣ ለማቀፍ የታደለችው የመጀመሪያዋ ሴት ናት። በርሳቸው ውልደት ምክንያት መካ ከማንፀባረቋ አስከትሎ እሜቴ አሚና ከነበሩበት መካ ሆነው የሻምን ቤተ መንግስቶች ለማየት ችለዋል። እሜቴ አሚና ባለቤቷን ገና ከማግባቷ ብዙም ሳይቆይ ማጣቷ እጅግ በጣም አሳማሚ የነበረ ቢሆንም ነብዩ ሙሀመድን ﷺ ካየች ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ ልቧ ሰላምን አግኝቷል።

ረሱሉላህ ﷺ ከልጅነታቸው አንስቶ ከባድ ፈተናዎችን አሳልፈዋል። ነገር ግን አላህ በሰጣቸው ፀጋ ላይ ትኩረት አድርገው አመስጋኝ ከመሆን ውጪ አማረው አያውቁም። አስቸጋሪ ጊዜያቶችን ሲጋፈጡ ቢከርሙም ለሰው ልጆች ሁሉ ያላቸው እዝነትና ርህራሄ ለሰከንድም ተለይቷቸው አያውቅም ነበር።
ሰላዋቱላሂ ወሰላሙ አለይህ!!

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=2981537458728672&id=1651332508415847


ሰይድና አኢሻ(ረ ዐ) ለነብዩﷺ እንዲህ ብላቸው ነበር "ፍቃዱ የግሌ ቢሆን ኖሮ አንቱን ከኔ ውጪ ከማንም ጋር እንዲሆኑ አልፈቅድም ነበር" ሰይድና ኡመር(ረ ዐ) ሲናገሩ "እርሶ ሰው ባይሆኑ ኖሮ ሙሉ ጨረቃ በሆኑ ነበር" ﷺ

ሰይድና አቡ ሁረይራ(ረ ዐ) ሲናገሩ "እንደ ነብያችንﷺ የሚያምር ነገር እዚህ ዱንያ ላይ አይቼ አላውቅም"

ሰይድና አሊ(ረ ዐ) "ከርሳቸው በፊትም ሆነ ከርሳቸው በዃላ እርሳቸውን የሚመስል አይቼ አላውቅም" ﷺ

ነብዩ ሙሀመድﷺ ወደ አሄራ ሲሄዱ አብደላህ ኢብን ዘይድ(ረ ዐ) "ከርሳቸው በዃላ ምንም ነገር ማየት አልፈልግም፤ አይኔን እውር ያድርገው" ብለው አላህን ተማፅነው አላህ(ሱ ወ) የፍላጎታቸውን ሞላላቸው። ሀጅ ለማድረግ ነብዩንﷺ ለመጀመሪያ ጊዜ ለማየት የታደሉ ሰዎች "ይህ የተቀደሰ ፊት ነው" ይሉ ነበር። አምር ኢብን አል አስ(ረ ዐ) ሲናገር "እስልምናን ከተቀበልኩ ጀምሮ ለነብዩﷺ ካለኝ ክብርና ውዴታ ቀና ብዬ ተመልክቻቸው አላውቅም"

እርሳቸውን ለመዘየር አላህ ያብቃን🙏
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=2981537458728672&id=1651332508415847



Показано 20 последних публикаций.

1 605

подписчиков
Статистика канала