Фильтр публикаций


መድኃኔዓለም አባታችን ሁላችንንም በያለንበት ይጠብቀን!
     
"ሃይሌን ጉልበቴን ታድሳለህ"
ሃይሌን ጉልበቴን ታድሳለህ
ቀና ቀና እንድል ታደርጋለህ
መድኃኔሃዓለም መድሃኒቴ
መሪው አንተ ነህ ለህይወቴ

አዝ = = = =
ክንድህ ይዘርጋ ከሞት ልዳን
ባንተ ልሻገር ክፉን ዘመን
ከሚያስጨንቁኝ አድነኝ
ካለ አንተ በቀር ማን አለኝ

አዝ = = = =
በሩ ይከፈት ያ የሰርጉ
ጌታ አስቀመጠኝ ከማዕረጉ
እድፌን ጣለው ከፊትህ
ከዚህ በላይ ነው ምህረትህ

አዝ = = = =
ላገለገልህ ፈቅጄ አለሁ
እጄን ከፊትህ አንስቼ አለሁ
አጥንቴም ይቁም ባንተ ጸንቶ
መንፈስህ ይቃኘኝ ከላይ መቶ

አዝ = =  = =
በጎና መልካም ካንተ ነው
ከአለም ይሔንን አላገኘው
ክብሬ ነህ አንተ መድኃኒቴ
በቃልህ ዳነች ሰውነቴ

አዝ = = = =
በሩ ይከፈት ያ የሰርጉ
ጌታ አስቀመጠኝ ከማዕረጉ
እድፌን ጣለው ከፊትህ
ከዚህ በላይ ነው ምህረትህ
    *በሊቀ ልሣናት ቸርነት ሰናይ*

ሊንኩን በመጫን መዝሙሩን ያድምጡ
       
https://youtu.be/rQMFrInH53E
https://youtu.be/rQMFrInH53E
https://youtu.be/rQMFrInH53E
Subscribe Our Channel and stay updated! 🔔
ቻናላችንን ሰብስክራይብ ላይክ ኮሜንት ሼር በማድረግ በየቀኑ አዳዲስ መንፈሳዊ ዝማሬዎችን ይከታተሉ!




በመላው ዓለም የምትገኙ ኦርቶዶክሳዊያ የተዋሕዶ ልጆች እንዲሁም ሐገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን ወዳጆቼ በዚህ በዐቢይ ፃም ቁርሳችንን ለመቄዶንያ በሚል እኔም የምሳተፍበት የገቢ ማሰባሰቢያ ላይ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ማክሰኞ 25/06/2017  ከምሽቱ 12  ጀምሮ ስልክ በመደወል በዕለቱ ያቅማችሁን እንድታግዙ በእግዚአብሔር ስም እጠይቃለሁ!


💥 ዛሬ የእመቤታችን የወላዲተ አምላክ ወርኃዊ በዓሏ ነውና የፍቅር ልጆቿ በረከቷን እንሳተፍ ዘንድ በምትወዱት የሊቃወንት የምስጋና ቃል ወይም መዝሙር በአስተያየት መስጫው ላይ በጽሑፍ ትውልድ ኹሉ ብጽዕት የሚላትን አወድሷት። በረከቷ አንዲበዛለኝ በመመኘት እኔ በሊቁ በፕሮክልዩስ ዘቁስጥንጥንያ ቃል አወደስኳት፦

❖ “ሰው ሆይ፥ ኹሉንም ፍጥረት በሐሳብኽ ቃኝና ከአምላክ እናት ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር የሚነጻጸር አልያም ከርሷ የሚልቅ ነገር ይኖር እንደኹ ተመልከት። ዓለምን ኹሉ ዙር፣ ውቅያኖሶችን ኹሉ አስስ፣ አየሩን ቃኝ፣ ሰማያቱን ጠይቅ፣ ኹሉንም የማይታዩ ኃይላት ዐስብ እናም በመላው ፍጥረት ውስጥ ማንኛውም ሌላ ተመሳሳይ ድንቅ ነገር ይኖር እንደኹ ተመልከት፡፡ ወደፊት የሚኾኑትን ኹሉ ዐስብና በድንግል ልዕልና ተደነቅ። ርሷ ብቻ፥ ከቃላት በላይ በኾነ መንገድ ኹሉም ፍጥረት በፍርሃትና በመራድ ከፊቱ የሚንበረከኩለትን የርሱ የመርዐዊ ሰማያዊ ማደሪያ በሚኾን ማሕፀኗ ይዛዋለች።” (Proclus of Constantinople, Homily 5, 2)
(መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ)

https://youtu.be/OtCUpVTF-4M?si=W7gSvvz3foiARSoe
ሼር..............


የዓቢይ ጾም ሌላ ስያሜዎች

"እንኳን ለዓቢይ ጾም በሰላም አደረሳችሁ"

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ባሕልና ትውፊት እና ሥርዓት መሠረት የጾም ወራት ከሰባቱ አጽዋማት አንዱና ዋነኛው አብይ ጾም ጌታ ከተጠመቀ በኋላ የጾመው የአርባ ቀን ጾም ነው፡፡

ምእመናን ጌታቸው ያደረገውን ምሳሌ ተከትለው ይጾሙታል፡፡ ይህ ታላቅ የሆነው የጾማችን ወራት በተለያየ ስያሜ ይጠራል፡፡

1. ዐቢይ ጾም ይባላል፡፡

ሌሎች አጽዋማት ከቅዱሳን አበው የወረስናቸው የኑሮአቸው ፍሬዎች ዕብ.13:7 ሲሆኑ ይኼኛው ግን በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የተመሠረተ በመሆኑ ዐቢይ ታላቅ ይባላል፡፡ የጌታ ጾም ስለሆነ ታላላቅ የሰይጣን ፈተናዎች አርእስተ ኃጣውእ ድል የተነሡበት ድል የሚነሡበት ጾም ስለሆነም ዐቢይ ጾም ይባላል፡፡

2. ጾመ ሁዳዴ ይባላል፡፡

ሁዳድ ማለት የመንግሥት መሬት የመንግሥት ርስት ማለት ነው፡፡ የመንግሥት ሁዳድ በሚታረስበት ጊዜ አዝመራው በሚሰበሰብበት ጊዜ ልጅ ዐዋቂ ሳይባል የመንግሥቱ ዜጋ ሁሉ ለሥራ ታጥቆ እንደሚነሣ ይህንንም የጌታ ጾም የጌታ ወይም የጌታ ሁዳድ የክርስቶስ ዜጎች የሆኑ ምእመናን ሁሉ ይጾሙታልና ጾመ ሁዳዴ ይባላል፡፡

3. የካሣ ጾም ይባላል፡፡

አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን ከገነት የተባረሩት ለውርደት ሞት ለሲዖል ባርነት የበቁት በመብል ምክንያት ነበር፡፡ በሆዳምነቱ የወደቀውን የሰው ልጅ በፈቃዱ በጾመው ጾም ካሠው እንዲሁም አዳም ከገነት ሲባረር ረሃበ ጸጋ መንፈሳዊ ረሃብ ደርሶበት ነበርና ረሃቡን በረሃብ ካሠለት፡፡ የኛን ረሃብ እርሱ ተራበ፡፡

4. የድል ጾም ይባላል፡፡

ጌታችን ተጠምቆ ዕለቱን ወደ ገዳመ ቆሮንቶስ በመሔድ ከሰው ተለይቶ አርባ መዓልትና አርባ ሌሊት በመጾም አዳምና ሔዋንን በመብል የረታቸውን ዲያብሎስን እርሱ ድል አደረገላቸው፡፡ ዲያብሎስን ድል ያደርግ ዘንድ ከዚህ ዓለም ርቆ ወደ ገዳም መሄዱ አዳም ከዚህ ዓለም ርቃ በምትገኘው ገነት ድል ሆኖ ነበርና እርሱም ዲያቢሎስን በገዳም በዚህ ዓለም ርቆ ድል አደረገልን ለእኛም ፈቃደ ሥጋችንን የምናሸንፍበተ ኃይል ሰጠን፡፡ ይህ ጾም ጠላት ዲያቢሎስ የተሸፈነበት ነው፡፡

5. የመሸጋገሪያ ጾም ይባላል፡፡

ሊቀ ነቢያት ሙሴ ሕዝቡን ከሕገ ልቡና ወደ ሕገ ኣሪት ሲያሸጋግር አርባ መዓልትና ሌሊት በደብረ ሲና እንደ ጾመው ሁሉ ጌታችንም እኛን ከሕገ ኦሪት ወደ ሕገ ወንጌል ሲያሸጋግረን አርባ መዓልትና ሌሊት ጾመ፡፡ ስለዚህም የመሸጋገሪያ ጾም እንለዋለን፡፡

6. ጾመ አስተምህሮ ይባላል፡፡

ሁሉን ነገር በቅጽበትና ያለ ድካም ማድረግ የሚችለው አምላክ እኛን ልጆቹን ያስተምረን ዘንድ ራሱን ዝቅ አደረገ፡፡ መልካም መምህር ተማሪዎቹ ይገባቸው ዘንድ ዝቅ ብሎ በነርሱ ቋንቋ እየተናገረ በሚችሉት እየመሰለ እንዲያስረዳ ጌታችንም እኛን ወደርሱ ይወስድ ዘንድ አስቀድሞ እርሱ ወደ እኛ መጣ፡፡ ረሃባችንን ተራበ ድካማችንን ደከመ ፈተናችንን ተፈተነ ለእኛም አርአያ ሆኖ ትሕትናን ትዕግሥትንና ፈተናን በጾም ማሸነፍን አስተማረን፡፡

7. የቀድሶተ ገዳም ጾም ይባላል፡፡

እነ መጥምቁ ዮሐንስ እነ ነቢዩ ኤልያስ የኖሩትን የብሕትውና ኑሮ ጌታ ባርኮ ሰጠን፡፡ ከከተማ ወጥቶ ከሰው ርቆ በበረሃ ከአራዊት ጋር እየኖረ በዲያብሎስ ተፈትኖ ድል አደረገ፡፡ ዛሬም ልጆቹ በየገዳማቱ ድምፀ አራዊትን ግርማ ሌሊትን ተግሠው ዓለምን ንቀው ከሰው ርቀው በጾም በጸሎት ከአጋንንት ጋር ይታገላሉ ድልም ያደርጋሉ፡፡

8. የመዘጋጃ ጾም ይባላል፡፡

ለእሥራኤላውያን ስለ በዓለ ፋሲካ አከባበር ሲነገራቸው የፋሲካውን በግ ሥጋ ከመራራ ቅጠል ጋር እንዲበሉት ታዘው ነበር ዘጸ.12:18፡፡ ይኽም መራራ ቅጠል በግብፅ ይኖሩት የነበረውን የመከራ ኑሮ የሚያሳስባችውና ደግም ወደ ግብፅ ምድረ ፋይድ እንዳይመለሱ ከኃጢአተ ይርቁ ዘንድ የሚያስተምራቸው ነበር፡፡ የፋሲካው በግ ደግሞ እግዚአብሔር በፍቅሩ የሰጣቸውን ነፃነት ያሳስባቸዋል፡፡

ዛሬም በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከበዓለ ትንሣኤው በፊት የጾም ወራት ያስቀደምነው ለዚህ ነው፡፡ ከመብል ስንከለከል ለአዳምና ሔዋን የተሰጠውን ሕግ እናስባለን ረሃብ ሲሰማን በሰው ልጅ ላይ ደርሶ የነበረው የጸጋ ረሃብ የመንፈስ ረሃብ ይታወሰናል ስንደክም ስንጐሰቁል በአዳምና ሔዋን የደረሰው የመንፈስ ጉስቁልና የበደልን የዕዳ ቀንበር ተሸክመው የደረሰባቸው ድካም ይታሰበናል፡፡ እኛም በነርሱ የደረሰችው ሞት በእኛ እንዳትደርስ ዳግም ወደ ኃጢአት እንዳንመለስ ይመክረናል ያሳስበናል፡፡

በጾሙም መጨረሻ የሐዲስ ኪዳንን በግ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋና ደም እንቀበላለን፡፡ ያን ጊዜም ሞትን ካሸነፈው አምላክ ጋር አንድ እንሆናለን ዮሐ.6:55-58፡፡ ሞታችን በሞቱ እንዳለፈ እናስባለን 1ቆሮ.11፡26። በመሆኑም ይህ ወቅት በዓለ ትንሣኤ የሐዲስ ኪዳን ፋሲካን ለማክበር ሥጋ ወደሙን ለመቀበል ራሳችንን የምናዘጋጅበት የምንፈትንበት ነው 1ቆሮ.11፡27፡፡

9. የሥራ መጀመሪያ ጾም ነው፡፡

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማስተማር ሥራውን ከመጀመሩ የመንግሥተ ሰማያትን አንቀጽ ከማስተማሩ በፊት በገዳመ ቆሮንቶስ አርባ መዓልትና ሌሊት ጾመ፡፡ ይህም ለእኛ የማንኛውም ነገር መጀመሪያው ጾም መሆኑን ሲያሰተምረን ነው፡፡ ለዚህም ነው ሐዋርያት ጾምን የሥራቸው መጀመሪያ ያደረጉት፡፡

እንዲሁም ይህ የጾም ወቅት የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡ ተኩላዎች እንድንጠነቀቅ ያስተምረናል፡፡ ጠላት ዳያብሎስ ጌታችንን ሲፈትን ከመጽሐፍ ቅዱሰ እየጠቀሰ ነበር መዝ 2ዐ:11፡፡ የእግዚአብሔርን ስም የጠራ ጥቅስ የጠቀሰ ሁሉ መንፈሳዊ ሰው እውነተኛ ክርስቲያን ሊባል አይችልም፡፡ መጥቀስማ ዲያብሎስም ይጠቅሳል ሕይወቱን አይኖረውም እንጂ፡፡

እንዲሁም በዚህ የጾም ሰሞን ጠላታችን ዲያብሎስ ያዘጋጀልንን ወጥመድ አስበን ለገድል የምንዘጋጅበትም ነው፡፡ ጌታን ወደ መቅደስ ጫፍ አውጥቶ ወደ ታች ተወርወር እንዳለው ሁሉ እኛንም በትዕቢትና በከንቱ ውዳሴ ወደ ላይ አውጥቶ በኃጢአትና በውርደት በኃፍረትና ከመንፈስ በማራቆት ሊወረውረን ይሻል፡፡

ስለዚህ ትሕትናን በምታለብስ ጾም ድል እንንሣው፡፡
እንግዲህ ዐቢይ ጾም ማለት፡-ጌታ ስለኛ ባየው መከራ የምናዝንበት በሰጠን ኃይል ከሰይጣንና ከፈቃደ ሥጋ የምንዋጋበት በበደልነው ተገብቶ የካሠልንን እያሰብን ዳግም ወደ ኃጢአት ላንመለስ ቃል የምንገባበት አርአያ ሆኖ ከሠራልን ሥርዓት፣ ከኖረልን ሕይወት የምንማርበት ራሳችንን ለፋሲካው በግ ለሥጋ ወደሙ የምናዘጋጅበት ሰሞን ነው፡፡

በመሆኑም በሰላም በፍቅር በትሕትና ጾመን ለበዓለ ትንሣኤው በሰላም እንድንደርስ ጾመን ለማበርከት እንዲያበቃን እግዚአብሔር በቸርነቱ ይጠብቀን አሜን፡፡
https://youtu.be/ci_FTLkihIc
ሰብስክራይብ,ሼር በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ






መቄዶንያን የመደገፍ፣ የመርዳት፣ የበረከት፣ የበጎነት፣ በአረጋውያን የመመረቅ ታላቅ እድል

የመቄዶኒያ ታላቅ የገቢ ማሰባሰቢያ ስርጭት
ከዛሬ የካቲት 1 ጀምሮ ሁላችንም እንሳተፍ
በ Seifu on EBS YouTube

ሰው ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው
ሼር.......


መድኃኔዓለም የልቦናችንን መሻት ይፈጽምልን።
     
"ሃይሌን ጉልበቴን ታድሳለህ"
ሃይሌን ጉልበቴን ታድሳለህ
ቀና ቀና እንድል ታደርጋለህ
መድኃኔሃዓለም መድሃኒቴ
መሪው አንተ ነህ ለህይወቴ

አዝ = = = =
ክንድህ ይዘርጋ ከሞት ልዳን
ባንተ ልሻገር ክፉን ዘመን
ከሚያስጨንቁኝ አድነኝ
ካለ አንተ በቀር ማን አለኝ

አዝ = = = =
በሩ ይከፈት ያ የሰርጉ
ጌታ አስቀመጠኝ ከማዕረጉ
እድፌን ጣለው ከፊትህ
ከዚህ በላይ ነው ምህረትህ

አዝ = = = =
ላገለገልህ ፈቅጄ አለሁ
እጄን ከፊትህ አንስቼ አለሁ
አጥንቴም ይቁም ባንተ ጸንቶ
መንፈስህ ይቃኘኝ ከላይ መቶ

አዝ = =  = =
በጎና መልካም ካንተ ነው
ከአለም ይሔንን አላገኘው
ክብሬ ነህ አንተ መድኃኒቴ
በቃልህ ዳነች ሰውነቴ

አዝ = = = =
በሩ ይከፈት ያ የሰርጉ
ጌታ አስቀመጠኝ ከማዕረጉ
እድፌን ጣለው ከፊትህ
ከዚህ በላይ ነው ምህረትህ
    *በሊቀ ልሣናት ቸርነት ሰናይ*

ሊንኩን በመጫን መዝሙሩን ያድምጡ
       
https://youtu.be/rQMFrInH53E
https://youtu.be/rQMFrInH53E
https://youtu.be/rQMFrInH53E
Subscribe Our Channel and stay updated! 🔔
ቻናላችንን ሰብስክራይብ ላይክ ኮሜንት ሼር በማድረግ በየቀኑ አዳዲስ


መድኃኔዓለም የልቦናችንን መሻት ይፈጽምልን።
     
"ሃይሌን ጉልበቴን ታድሳለህ"
ሃይሌን ጉልበቴን ታድሳለህ
ቀና ቀና እንድል ታደርጋለህ
መድኃኔሃዓለም መድሃኒቴ
መሪው አንተ ነህ ለህይወቴ

አዝ = = = =
ክንድህ ይዘርጋ ከሞት ልዳን
ባንተ ልሻገር ክፉን ዘመን
ከሚያስጨንቁኝ አድነኝ
ካለ አንተ በቀር ማን አለኝ

አዝ = = = =
በሩ ይከፈት ያ የሰርጉ
ጌታ አስቀመጠኝ ከማዕረጉ
እድፌን ጣለው ከፊትህ
ከዚህ በላይ ነው ምህረትህ

አዝ = = = =
ላገለገልህ ፈቅጄ አለሁ
እጄን ከፊትህ አንስቼ አለሁ
አጥንቴም ይቁም ባንተ ጸንቶ
መንፈስህ ይቃኘኝ ከላይ መቶ

አዝ = =  = =
በጎና መልካም ካንተ ነው
ከአለም ይሔንን አላገኘው
ክብሬ ነህ አንተ መድኃኒቴ
በቃልህ ዳነች ሰውነቴ

አዝ = = = =
በሩ ይከፈት ያ የሰርጉ
ጌታ አስቀመጠኝ ከማዕረጉ
እድፌን ጣለው ከፊትህ
ከዚህ በላይ ነው ምህረትህ
    *በሊቀ ልሣናት ቸርነት ሰናይ*

ሊንኩን በመጫን መዝሙሩን ያድምጡ
       
https://youtu.be/rQMFrInH53E
https://youtu.be/rQMFrInH53E
https://youtu.be/rQMFrInH53E
Subscribe Our Channel and stay updated! 🔔
ቻናላችንን ሰብስክራይብ ላይክ ኮሜንት ሼር በማድረግ በየቀኑ አዳዲስ




የሊቀ  ልሣናት  ቸርነት  ሠናይ  ቁጥር-፯  ተወዳጅ  የሆኑ  መዝሙራት  እነሆ  አድምጡት!    
፩-አለኝ ውዳሴ
፪-እስኪ ላመስግንህ ተንበርክኬ
፫-ሰባቱ የእሣት መጋረጃዎቹ
፬-ለብድራትህ
፭-በፈረሰው ቦታ
፮-ይጋር ሰሀዱታ
፯-ነይ ነይ ሱላማጢስ
፰-በታች በምድር በላይ በሰማይ
፱-ኢየሱስ
፲-ክብርት ነሽ
፲፩-የነፍሴ አርነት
፲፪-የንጉሡ ልጅ ነኝ
፲፫-አንተ ነህ ሐገሬ
፲፬-አለ የታያቸው
https://youtu.be/u1D-3HmJdEg
Subscribe Our Channel and stay updated! 🔔
ቻናላችንን ሰብስክራይብ በማድረግ በየቀኑ አዳዲስ መንፈሳዊ ዝማሬዎችን ይከታተሉ!!


ጥር ፯ (እንኳን አደረሳችሁ)
የሥላሴ ምሕረት ቸርነት ከሁላችን ጋር ይሁን።

#tewahedo #ተዋህዶ_ለዘላለም_ትኑር #orthodoxchristian #EOTC #tewahedoሐበሻ💚💛❤ #ሀበሻ #ethiopia #eotc #orthodoxchristian #tewahedo #blessed #singer #gospel #addisababa #lalibela #hager #dc #maryland #virginia #america #sebket #memher #ተዋህዶ_ለዘላለም_ትኑር #ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ_ለዘለዓለም_ፀንታ_ትኑር #eritrea #mezmur #addisababa #bless #Godisgood










ጥር ፬
"ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ"
==========================

ቅዱስ ዮሐንስ ከአስራ ሁለቱ ሐዋርያት መካልከ አንዱ ነው በመጀመሪያ ለደቀ መዝሙርነት የተመረጠው ከቅዱስ ጴጥሮስና ከቅዱስ እንድርያስ ጋር ሲሆን ቅዱስ ዮሐንስ ብዙ ስሞች አሉት ፦

ጌታ ይወደው የነበረ ሐዋርያ ( ፍቁረ እግዚእ )
ወልደ ዘብዴዎስ
ወልደ ነጎድጓድ
ነባቤ መለኮት ( ታኦሎጎስ )
አቡቀለምሲስ
ቁጹረ ገጽ እየተባለ ይጠራል ።

ቅዱስ ዮሐንስ ጌታን በመከራው ሰዓት ሳይሸሽ እስከ እግረ መስቀሉ ድረስ የተከተለ ፣ እኛን ወክሎ የእመቤታችንን እናትነት አደራ የተቀበለ ፣ የዕለተ ዓርቡን የጌታን መከራ እያሰበ ቀሪ ዘመኑን በዕንባ የኖረ ሐዋርያ ነው ።

ቅዱስ ዮሐንስ እመቤታችንን እየጠበቀ ለ16 ዓመታት ተቀምጧል ከኢየሩሳሌም ርቆ ያልሄደው እርሷን የመጠበቅ አደራ ስለነበረበት ነው ፤ በ49 ዓ.ም እመቤታችን አርፉ እንደ ልጇ በሦስተኛው ቀን ተነስታ ካረገች በኃላ ወደ ኤፌሶን ከተማ ገብቶ አስተምሯል በዚያም በአርጤምስ ቤተ መቅደስ የሚካሄደውን አምልኮ ጣኦት በመቃወሙ በጭካኔው በሚታወቀው በንጉሥ ድምጥያኖስ ዘመን ( ከ81 - 96 ዓ.ም ) በጣኦት አምላኪዎች ተከሶ ለፍርድ በድምጥያኖስ ፊት ቀረበ እርሱም በፈላ ውኃ በተሞላ በርሜል ውስጥ ካሰቃየው በኃላ ወደ ፍጥሞ ደሴት አጋዘው።

ቅዱስ ዮሐንስም በጠባብ ዋሻ ውስጥ ለሰባት ዓመታት ( ከ88 - 96 ዓ.ም ) ያህል በግዞት ተቀምጦ ሳለ ነው ራእዩን ያየውና የጻፈው።

በ96 ዓ.ም ድምጥያኖስ ሲገደል ቅዱስ ዮሐንስ ከግዞት ተመልሶ ነው ሦስቱን መልእክታቱንና ወንጌሉን የጻፈው።

ከሐዋርያት ሁሉ ቀድሞ ሰማዕት የሆነው ታላቅ ወንድሙ ቅዱስ ያዕቆብ ሲሆን ከሐዋርያት ሁሉ ረዥም እድሜ ( 99 ዓመት ) በምድር ላይ የቆየው ሐዋርያ ደግሞ ቅዱስ ዮሐንስ ነው።

በመጨረሻም ጌታ በገባለት ቃልኪዳን መሠረት ዮሐ 21 : 22 እንደ ሄኖክና ኤልያስ ሞትን ሳያይ ተሰውሮ ወደ ብሔረ ሕያዋን ተወስዷል።
https://youtu.be/ORm4pdwoxZw?si=32B79QH_ywcTQORB
https://youtu.be/ORm4pdwoxZw?si=32B79QH_ywcTQORB
ጸሎትና በረከቱ በሁላችን ላይ ይደርብን።




፩ ልደታ ለማርያም
   ከፀሐይ ሰባት እጅ የምታበራ፥የመልኳ ደም ግባት ከማርና ከስኳር  ይልቅ ደስ የሚያሰኝ፥የመዓዛዋ ሽታ ከሽቶዎች ሁሉ የሚበልጥ፥የእግዚአብሔር ስጦታ የሆነች የቅድስት ድንግል ማርያም ወርሐዊ  የልደቷ መታሰቢያ ነው። እንኳን አደረሳችሁ
💌💌💌💌💌💌💌
https://youtu.be/OtCUpVTF-4M?si=LsEINYL72Ih09OTX
https://youtu.be/OtCUpVTF-4M?si=LsEINYL72Ih09OTX
ቻናሉን Subscribe አድርጉልን፣
ለተዋህዶ ወንድምና እህቶቻችሁም Share አድርጉላቸው!

Показано 20 последних публикаций.