Фильтр публикаций


ሁለቱ ዲሲፕሊን የማጣት ችግሮች!

1.  አልፈልገውም እኮ! . . . ግን አደርገዋለሁ!

ብዙ ሰዎች ማድረግ የማይገባቸውን ነገር በሚገባ ያውቁታል፣ ያንንም ነገር ማድረግ አይፈልጉም፡፡ ሆኖም ያንንው ነገር ደጋግመው ሲያደርጉት ራሳቸውን ያገኙታል፡፡

ይህ ሁኔታ መነሻው ከተለያዩ ነገሮች ጋር የሚገናኝ ቢሆንም፣ መሰረታዊው ችግር ግን ዲሲፕሊን ካለማዳበር ጋር የተነካካ ነው፡፡

ይህ የዲሲፕሊን ዘርፍ፣ “ያለማድረግ ዲሲፕሊን” ይባላል፤ አንድን ማድረግ የማይገባንን ነገር ያለማድረግን ዲሲፕሊን ማዳበር ማለት ነው፡፡

ይህንን አይነቱን ዲሲፕሊን ማዳበር ካልተጠበቁ አጉል ውጤቶች (unintended consequences) ይጠብቀናል፡፡ 

የማትፈልጉትን ተገቢ ያልሆነ ነገር ለማቆም ከፈለጋችሁ፣ ከፍተኛ የሆነን ዲሲፕሊን ማዳበር አስፈላጊ ነው፡፡ ይህ ደግሞ በስሜት ብልህነት የመብሰል ዘርፍ ነው፡፡

2.  እፈልገዋለሁ እኮ! . . . ግን አላደርገውም!

ከላይ ከተጠቀሰው በተቃራኒ፣ ብዙ ሰዎች ማድረግ የሚገባቸውን ነገር በሚገባ ያውቁታል፣ ያንንም ነገር ማድረግ ይፈልጋሉ፣ ሆኖም አንዳንድ ጊዜ ጀመር ቢያደርጉትም መልሰው ሲተውት ራሳቸውን ያገኙታል፡፡

ይህም ቢሆን መነሻው ከተለያዩ ነገሮች ጋር የሚገናኝ ቢሆንም፣ መሰረታዊው ችግር ግን ዲሲፕሊን ካለማዳበር ጋር የተነካካ ነው፡፡

ይህ የዲሲፕሊን ዘርፍ፣ “የማድረግ ዲሲፕሊን” ይባላል፤ አንድን ማድረግ የሚገባንን ነገር ካለማቋረጥ የማድረግን ዲሲፕሊን ማዳበር ማለት ነው፡፡

ይህንን አይነቱን ዲሲፕሊን ማዳበር በሕይወታችን የምንጠብቃቸውን መልካም ውጤቶች ከማጣት  ይጠብቀናል፡፡ 

የምትፈልጉትን መልካም ነገር ለመጀመርና ካለማቋረጥ ለመቀጠል ከፈለጋችሁ፣ ከፍተኛ የሆነን ዲሲፕሊን ማዳበር አስፈላጊ ነው፡፡  ይህ ደግሞ በስሜት ብልህነት የመብሰል ዘርፍ ነው፡፡

በዚህ ርእስ ላይ በሚገባ ለመብሰልና ብዙዎች ያመጡት አይነት ለውጥ ለማምጣት ከፈለጋችሁ የተዘጋጀው ስልጠና አያምልጣችሁ፡፡

ለመረጃው ከዚህ ጽሑፍ ጋር የተለጠፈውን ፖስተር ይመልከቱ፡፡

ለተጨማሪ መረጃ ከዚህ በታች ባለው የ telegram link inbox በማድረግ ፍላጎቶትን ሲገልጹ መረጃው ይላክሎታል::

Dr Eyob mamo

@revealjesus


ሁለቱ ዲሲፕሊን የማጣት ችግሮች!




ትህትናን ሳይለቁ ምስጋናን የመቀበል ሰፊነት

“ሌላ ያመስግንህ እንጂ አፍህ አይደለም ባዕድ ሰው እንጂ ከንፈርህ አይደለም” (ምሳ. 27:2)፡፡

የሚጋፉንና የሚያንቋሽሹን ሰዎች የመኖራቸውን ያህል የሚያደንቁንና የሚያመሰግኑን ሰዎች አሉ፡፡ የማይሳካልንና የምንሰናከልበት ነገር የመኖሩን ያህል የሚሳካልንና ልቀን የምንገኝበት ነገር አለ፡፡ ስለዚህም፣ አልሳካ ሲለን መልካም ጎናችንን ተመልክቶ “ጎበዝ፣ በርታ” የሚለን፣ ሲሳካልን ደግሞ “እንኳን!” የሚለን ሰው አይጠፋም፡፡

እንደ እውነቱ ከሆነ ያለማሳካትን “ውርደት” መሸከም ካልቻልን፣ ያመሳካትን “ክብር” መሸከም አንችልም፡፡ ሁለቱም ቢሆኑ ሰፊነትን የሚጠይቁና የማይቀሩ የሕይወት ክስተቶች ናቸው፡፡

ያም ሆነ ይህ በሚሳካልን ጊዜና ራሳችንን ተራራ ላይ በምናገኘው ጊዜ ከሚመጣልን ምስጋናና ውዳሴ አልፈን በዓላማችን ላይ የምናተኩር “ቀለል” ያልን ሰዎች ለመሆን ልንከተላቸው የሚገባን አስፈላጊና መሰረታዊ መርሆች ሊኖሩን ይገባል፡፡

1. ግዴታን ማወቅ

“ስለዚህ እናንተም የታዘዛችሁትን ሁሉ ባደረጋችሁ ጊዜ፣ ‘ከቊጥር የማንገባ አገልጋዮች ነን፤ ልናደርገው የሚገባንን ተግባር ፈጽመናል በሉ”(ሉቃ. 17:10)፡፡

ማንኛውም በሕይታችን የምንተገብራቸው መልካም ነገሮች ከጌታ የተሰጠን አደራና ትእዛዝ መሆኑን ማስታወስ አስፈላጊ ነው፡፡ አለዚያ አንድን ነገር ባከናወንንና በተሳካልን ቁጥር የተለየን ሰዎች እንደሆንን ወደማሰብና በልባችን ወደመታበይ እናዘነብላለን፡፡ ስልዚህም፣ ምንም ነገር ካደረግን በኋላ “ልናደርገው የሚገባንን ተግባር ፈጽመናል” በማለት ዋናው ነገር ላይ የማተኮርን ሰፊነት ይዞ መቆየት የብሱልነታችን ምልክት ነው፡፡

2. በጸጋው መደገፍ

“ኃይልን በሚሰጠኝ በእርሱ ሁሉን ማድረግ እችላለሁ” (ፊል. 4፡13)፡፡

መስራት፣ መልፋት፣ መትጋት፣ ስኬትን ማስመዝገብ … መልካም ነው፡፡ የተፈጠርነውም ለዚሁ ነው፡፡ ሆኖም የዚህ ሁሉ ምንጩ የጌታ ጸጋ መሆኑን በማስታወስ ቀስ በቀስ ከጸጋው እንዳንወድቅ ማስተዋልም አስፈላጊ ነው፡፡ ጳወሎስ ይህንን ሁኔታ ሲያጠቃልለው፣ “ከሁሉም በላይ በትጋት ሠርቻለሁ፤ ዳሩ ግን እኔ ሳልሆን ከእኔ ጋር ያለው የእግዚአብሔር ጸጋ ነው” (1ቆሮ. 15፡10) ይለዋል፡፡ በጸጋው እንደገፍ፡፡

3. በጌታ መመካት

“ነገር ግን፣ የሚመካ በጌታ ይመካ፤ ምክንያቱም ጌታ ራሱ የሚያመሰግነው እንጂ፣ ራሱን በራሱ የሚያመሰግን ተቀባይነት አይኖረውም” (2ቆሮ. 10:17-18)፡፡

ይህ ክፍል ምንም ማብራሪያ እስከማያስፈልገው ድረስ ግልጽ ነው፡፡ በምናስመዘግባቸው ስኬቶች ምክንያት ወደ እኛ የሚመጣውን ምስጋና በቅጡ ለመያዝ፣ መመኪያችንን በጌታ ላይ ማድረግ አስፈላጊ ነው፡፡ ይህንን በጌታ የመመካት መርህ አለመከተል ቀስ በቀስ ራስን በራስ ወደማመስገንና በራስ ኃይል ወደመመካት እንድናዘቅጥ ያደርገና፡፡ የዚህን ሁኔታ ውጤት ደግሞ በግልጽ አስቀምጦልናል፡፡ ራስን በራስ ማመስገንና የጌታን መከታነት መዘንጋት ቀስ በቀስ ተቀባይነታችንን እየሸረሸረው ይሄዳል፡፡

ይህ ክፍል ተጠናቀቀ! በክፍል ሶስት እስከማገኛችሁ ጌታ ኢየሱስ ይባርካችሁ!

@revealjesus


ትህትናን ሳይለቁ ምስጋናን የመቀበል ሰፊነት


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram


DON’T_WASTE_YOUR_LIFE_John_Piper.pdf
2.1Мб
🎁reveal jesus spiritual book gifts 🎁

🎁መንፈሳዊ መጽሐፍትን ለናንተ

     share it to your friends    

@revealjesus


መርህን ሳይለቁ በዓለም የመሰማራት ሰፊነት

“ከክፉ እንድትጠብቃቸው እንጂ ከዓለም እንድታወጣቸው አልለምንም። እኔ ከዓለም እንዳይደለሁ ከዓለም አይደሉም” (ዮሐ. 17፡15-16)፡፡

ብክለት የአለማችን ችግር ነው፡፡ አየሩ በየዕለቱ በምንናነደው ነዳጅ የተበከለ ነው፡፡ ባሕሩ በየጊዜው በምናራግፍበት ኬሚካና ቆሻሻ የተበከለ ነው፡፡ ምግቡ በማዳበሪያውና በተለያየ ቆሻሻ የተበከለ ነው፡፡ በእነዚህና መሰል የተበከሉ አካባቢዎች ውስጥ እየኖርን በተጽእኖው ስር አለመውደቅ እጅግ ከባድ ሁኔታ ነው፡፡ ከላይ የተመለከትነውም የክርስቶስ ጸሎት ይህንን መሰሉን ስዕል ነው የሚያመለክተን፡፡

ዓለም በተለያዩ ሁኔታዎች የተበከለች ነች፡፡ ይህ ብክለት ወደእኛ የተለያዩ ፈተናዎችን ይዞብን ይመጣል፡፡ የተበከለን አየር ላለመተንፈስ ካስፈለገ ያለን አማራጭ ከዚህ ዓለም መውጣት ነው፡፡ ይህኛውን ምርጫ ግን ክርስቶስ አልመረጠውም፡፡ በዚያው ሆነን እንድንጠበቅ ነው የጸለየልን፡፡

የጌታ የልቡ ፍላጎት በዓለም እንጂ ከዓለም እንዳልሆንን በማወቅ ክብራችንን ጠብቀን በዚህ ዓለም የመመላለስን ሰፊነት እንድንይዝ ነው፡፡ እውነታውን ትንሽ ዘርዘር አድርገን ስንመለከተው የሚከተሉትን ነጥቦች ማጤን እንችላለን፡፡

1. የዚህ አለም ገዢ ፈተና

“የዚህ ዓለም ገዥ ስለሚመጣ ከእንግዲህ ወዲህ ከእናንተ ጋር ብዙ አልናገርም። እርሱም በእኔ ላይ ሥልጣን የለውም” (ዮሐ. 14:30)፡፡

በዚህ ዓለም እስካን ድረስ የዚህ ዓለም ገዢ የሆነው ጠላታችን ዲያቢሎስ ካለማቋረጥ ፈተናውን ይዞ ወደ እኛ ይመጣል፡፡ በዚህ የጠላት አመጣጥ ላይ ድልን የሚሰጠን በክርስቶስ ያገኘነውን ስልጣን በማወቅ መለማመድ ነው፡፡ እኛም ከጌታችን ጋር በማበር “በእኔ ላይ ስልጣን የለውም” በማለት በእምነት ልንሞግተው ይገባናል፡፡

2. የአለም ጥላቻ

“ወንድሞች ሆይ፤ ዓለም ቢጠላችሁ አትደነቁ” (1ዮሐ. 3:13)፡፡

አንዳንድ አማኞች በፍጹም ሊለምዱት ያልቻሉት ሃቅ በተሰማሩበት አካባቢ ሰዎች እነሱን የመጥላታቸውንና ክፋትንና ወጥመድን በእነሱ ላይ ለማድረግ የመሞከራቸውን ሁኔታ ነው፡፡ ለዚህ ነው ጌታ “አትደነቁ” በማለት አዲስ ነገር እንደደረሰብን ማሰብ እንደማይገባን ያሳሰበን፡፡ ደግሞም እንዲህ ብሎናል፡- “ዓለም ቢጠላችሁ፣ ከእናንተ በፊት እኔን እንደጠላኝ ዕወቁ” (ዮሐ. 15:18)፡፡ የዓለም ጥላቻ ክርስቶስን አልደነቀውም፤ መንግስቱም ሆነ አስተሳሰቡ ሰማያዊ ስሆነ ምድራዊው ሊቀበለው አይችልም፡፡

3. የአለም ጉድፍ

“በእግዚአብሔር አብ ፊት ንጹሕና ነውር የሌለበት ሃይማኖት ይህ ነው … ከዓለም ርኵሰት ራስን መጠበቅ ነው” (ያዕ. 1:27)፡፡

ቀደም ሲል እንደጠቀስነው ዓለም በጉድፍ ተሞልታለች፡፡ ፍልስፍናውን፣ ምድራዊውን ጥበብና የኃጢያቱን ጥልቀት ስንመለከተው በቀላሉ ለዚህ ጉድፍ የተጋለጥን እንደሆነ እናስተውላለን፡፡ በዓለም ባለን ስምሪት ውስጥ ከዚህ ጉድፍ ራሳችንን ጠብቀን መኖር ታላቅ ሰፊነት ነው፡፡ በንስሃ፣ ራስን ከክፋት በመለየትና ካለማቋረጥ ሃሳባችንን ከክፉ ሃሳብ፣ እግሮቻችንን ደግሞ ከአልባሌ መንገድ መከልከል የዚህ ሰፊነት ተግባራዊ እርምጃዎች ናቸው፡፡

የሚቀጥለው ትምህርት፡ “ትህትናን ሳይለቁ ምስጋናን የመቀበል ሰፊነት”


@revealjesus


መርህን ሳይለቁ በዓለም የመሰማራት ሰፊነት


ሰላም👋
ዘሬ በአማራ ክልል ስለሚገኘው ስለ
#ወሎ የህዝብ ክፍል እነፀልይ

#ወሎ(አማራ)
ዋና ቋንቋ፡
#አማርኛ
ትልቁ ሀይማኖት፡
#እስልምና

የህዝብ ብዛት: 6,492,000
ክርስቲያን፡ 188,282 (2.90%)
ወንጌላዊ፡ 12,985 (0.20%)

#መጽሐፍ_ቅዱስ፡ ሙሉ መጽሐፍ ቅዱስ አለ
#ኢየሱስ_ፊልም፡- አለ
#የወንጌል_የድምጽ_ቅጂዎች፡- አለ
#የወንጌል_ሬዲዮ፡ የለም

✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
- - - - - - - - - - - - - - - - - -
“ኢየሱስም ይህን ተናግሮ ወደ ሰማይ ዓኖቹን አነሣና እንዲህ አለ፦ “አባት ሆይ፥ ሰዓቱ ደርሶአል፤ ልጅህ ያከብርህ ዘንድ፥ በሥጋም ሁሉ ላይ ሥልጣን እንደ ሰጠኸው፥ ለሰጠኸው ሁሉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸው ዘንድ ልጅህን አክብረው። እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት።”
የዮሐንስ ወንጌል 17:1-3
- - - - - - - - - - - - - - - - - -

#የፀሎት_ረዕስ

#1 አብንና ወልድን አውቀው የዘላለም ህይወት እንዲሆንላቸው
#2 ልባቸውን እግዚአብሔር  ለወንጌል ይከፈት ዘንድ
#3 ሰራተኞችን እንዲልክ ሰራተኛ እኛን አድርጎ እንዲልከን, የተላኩ ሰራተኞች እግዚአብሔር በፍሬ እንዲባርካቸው

#Pray_for_wello ☪️
#Pray_for_wello☪️
#Pray_for_wello ☪️


ዓላማን ሳይለቁ ውጣ ውረዶችን የማስተናገድ ሰፊነት

“በእያንዳንዱ ነገር በነገርም ሁሉ መጥገብንና መራብንም መብዛትንና መጉደልን ተምሬአለሁ። ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ” (ፊል 4፡12-13)፡፡

አንዳንድ ጊዜ አንድን ነገር ጀምረን ገና አንድ እርምጃ ሳንራመድ ውጣውረዶች በሕይወታችን ብቅ ማለት ይጀምራሉ፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ ሰፊነታችን ወሳኝ ነው፡፡

በሚመጡት ውጣውረዶች በመጨናነቅ እነሱ እስከሚወገዱ ዓላማችን ይገታል ወይስ ውስጣችንን ሰፋ አድርገንና ጌታችንን አምነን በዙሪያችን ምንም አይነት ማዕበል ቢነሳ ወደፊት እንገሰግሳለን? ሊመለስ የሚገባው ጥያቄ፡፡

ሐዋርያው ጳውሎስ ምንም እንኳን ሙታንን እስከማስነሳት የደረሰ የምነት ሰው ቢሆንም በተለያዩ ውጣ ውረዶች ማለፍ ነበረበት፡፡ ለእርሱ እምነት ማለት ካለምንም ችግር መኖር ሳይሆን በምንም ነገር ውስጥ ለማለፍ የሚያስችል ኃይል ሊሰጠው የሚችለውን ጌታ ማመን ማለት ነበር፡፡

ልበ ሰፊዎች ከሌሎቹ የሚለዩት በጊዜአዊ ደስታም ሆነ ኃዘን ከጨበጡት ዓላማቸው የአለመነቃነቃቸው ዝንባሌ ነው፡፡ ይህንን ሰፊነት ለመለማመድ ደግሞ ልክ እንደነሱ ልንገነዘባቸው የሚገቡን እውነታዎች ይኖራሉ፡፡

1. የተዛባውን አመለካከት ማስተካከል

“በእኔ ሰላም እንዲኖራችሁ፣ ይህን ነግሬአችኋለሁ። በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ”” ዮሐ. 16፡33

ክርስቶስ እዚህ ጋር ሊያሳስበን የፈለገው እውነታ፣ ሰላማችን ከሚነጥቁ ሁኔታዎች አንዱ በአለም ሳለን ምንም መከራ እንደሌለብን ስንቆትርና መከራው ሲደርስ የሚገጥመን የመናወጥ ሁኔታ ነው፡፡ ለዚህ ነው ሰላም እንዲኖራችሁ በማለት በአለም ያለውን እውነታ የሚነግረን፡፡ ስለዚህም በምንም አይነት ውጣ ውረድ ውስጥ ብናልፍም እንኳን ሳንናወጥ ለመኖር በክርስቶስ እስካለሁ ድረስ ምንም አይደርስብንም የሚለውን የተዛባ አመለካከት ማስተካከል የግድ ነው፡፡

2. የሁኔታዎችን ጊዜያዊነት መገንዘብ

“በክርስቶስ ወደ ዘላለም ክብሩ የጠራችሁ የጸጋ ሁሉ አምላክ፣ ለጥቂት ጊዜ መከራ ከተቀበላችሁ በኋላ እርሱ ራሱ መልሶ ያበረታችኋል፤አጽንቶም ያቆማችኋል” (1ጴጥ. 5:10)፡፡

እውነቱ አጭርና ግልጽ ነው! መከራ ለጥቂት ጊዜ ነው፡፡ መከራው ካለፈ በኋላ ግን መልሶ የሚበረታና እስከመጨረሻው የሚያጸና ጸጋ ይሰጠናል፡፡ በዚህ መለኮታዊ አሰራር ደግሞ ደስ ልንሰኝ ይገባናል፡፡ “ምክንያቱም ቀላልና ጊዜያዊ የሆነው መከራችን ወደር የማይገኝለት ዘላለማዊ ክብር ያስገኝልናል” (2ቆሮ. 4:17)፡፡

3. የችግርን ጥቅም መገንዘብ

“በፈተና የሚጸና ሰው የተባረከ ነው፤ ምክንያቱም ፈተናን ሲቋቋም እግዚአብሔር ለሚወዱት የሰጠውን ተስፋ፣ የሕይወትን አክሊል ያገኛል” (ያዕ. 1:12)፡፡

በምንም አይነት ፈተና ውስጥ ብናልፍ ያንን ለመቋቋም ስንወስን ሽልማትን ከጌታ እንቀበላለን፡፡ ይህ ሽልማት ቀደም ብለን በተመለከትናቸው ትቅሶች መሰረት ምድራዊ ገጽታ ሲኖረው በያእቆብ መልእክት መሰረት ደግሞ ዘላለማዊ ክብርና አክሊል የሚሰጥ ሽልማት ነው፡፡ ይህንን መገንዘብ ይህ ነው የማይባል ሰፊነትን ይሰጠናል፡፡

የሚቀጥለው ትምህርት፡ “መርህን ሳይለቁ በዓለም የመሰማራት ሰፊነት”

@revealjesus


ዓላማን ሳይለቁ ውጣ ውረዶችን የማስተናገድ ሰፊነት


የእግዚአብሔር ጊዜ ከኔ ጊዜ ይለያል 🙏
         
@revealjesus


ሁሉን በማስተናገድ እውነቱ ጋር የመድረስ ሰፊነት

“ሁሉን ፈትኑ መልካሙንም ያዙ” (1ተሰ. 2፡20-21)፡፡

አንዳንድ ሰዎች፣ “ምንም አላይም፣ ምንም አልሰማም፣ ምንም አልሞክርም” በማለት ሁለንተናቸውን ጥርቅም አድርገው መዝጋት ብስለትና ማስተዋል ይመስላቸዋል፡፡ ይህ ሁኔታ ጥንቁቅነት ሊመስል ይችላል፣ ትክክለኛውና ሚዛናዊው መንገድ ግን አይደለም፡፡

በሳል ወደሆነ ሰፊነት አልፈን ስንሄድ ከምን አይነት ሁኔታ መሸሽ እንዳለብንና የትኛውን ደግሞ በማስተናገድ አጣርተን መቀበል እንዳለብን በሚገባ ወደመገንዘብ እንመጣለን፡፡ ስለዚህም፣ የተለያዩ ሃሳቦችን ማስተናገድ ማለት ከተለያዩ ሃሳቦችን በመሸሽ ሳይሆን አውቀናቸው ባመንንበት እውነት የመጽናት ሰፊነት ማለት ነው፡፡

ይህ ሰፊነት ግን ታላቅ ጥንቃቄ የሚጠይቅና አቅምን ማወቅ የሚያስፈልገው ጉዳይ ነው፡፡ የሚከተሉት ነጥቦች ይህንን መርህ እንዳዳብር ሊረዱኝ ይችላሉ፡፡

1. ባመንኩት እምነትና እውነት በሚገባ በመብሰል መደላደል

“እንግዲህ ጌታ ክርስቶስ ኢየሱስን እንደተቀበላችሁት እንዲሁ በእርሱ ኑሩ፤ በእርሱ ተተክላችሁና ታንጻችሁ፣ እንደተማራችሁት በእምነት ጸንታችሁ፣የተትረፈረፈ ምስጋና እያቀረባችሁ ኑሩ” (ቆላ. 2:6-7)፡፡

ወደ እኔ የሚመጣውን ሁሉ በሚገባ በመመዘንና በማጣራት ለመኖር በቅድሚያ በተማርኩበት ትምህርት መጽናት አስፈላጊ ነው፡፡ ክርስቶስን በማመንና በማወቅ መታነጽ፣ መተከልና፣ በተማርነው እምነት መጽናት ወደ እኛ ለሚመጣው ለማንኛውም ነገር ዝግጁ እንድንሆን ያግዘናል፡፡ ለሚነፍሰው የተለያየ የትምህርትና የፍልስፍና ነፋስ ዝግጁ የሆነን መሰረት በመጣል ራሳችንን ለዚህ አይነቱ ሰፊነት ማዘጋጀት እንችላለን፡፡

2. ወደእኔ የሚመጣውን የመለየት ስራ መስራት

“የቤርያ ሰዎች ከተሰሎንቄ ሰዎች ይልቅ አስተዋዮች ነበሩ፤ምክንያቱም ነገሩ እንደዚህ ይሆንን እያሉ መጻሕፍትን በየዕለቱ በመመርመር ቃሉን በታላቅ ጒጒት ተቀብለዋል” (የሐዋ. 17:11)::

የቤሪያ ሰዎች የኖሩበት ዘመን የተለያዩ የትምህርት ነፋሶች የሚነፍሱበትና የግሪክ ፍልስፍና የበዛበት ዘመን ነበር፡፡ እነዚህ ሰዎች ግን በፍርሃት ራሳቸውን አልሸሸጉም፡፡ ወደ እነሱ የሚመጣውን የተለያየ ሃሳብ በመመርመር የቃሉን እውነት ብቻ ጥንፍፍ አድርገው በማውጠት ይቀበሉ ነበር፡፡ እነዚህን ሰዎች ቃሉ አስተዋዮች (ልበ ሰፊዎች) ይላቸዋል፡፡

3. የዘመኑን መንፈስን መመርመር

“ወዳጆች ሆይ፤ መንፈስን ሁሉ አትመኑ፤ ነገር ግን መናፍስት ከእግዚአብሔር መሆናቸውን መርምሩ” (1ዮሐ. 4:1)፡፡

አንዳንድ ሰዎች “ታላቅ ነኝ፣ ተቀብቻለሁ፣ ተልኬያለሁ …” ብሎ ራሱን የሰየመውን ሁሉ ካለምንም ምርመራ የመቀበል የሞኝነት ዝንባሌ አላቸው፡፡ ሆኖም፣ “በኋለኞች ዘመናት አንዳንዶች እምነትን ክደው አታላይ መናፍስትንና የአጋንንትን ትምህርት እንደሚከተሉ መንፈስ በግልጥ ይናገራል” (1ጢሞ. 4:1-2)፡፡ እንደዚህ መሰል ባለንበት ዘመን የሚገኙትን የመናፍስት አሰራር በሚገባ መመርመር አስፈላጊ ነው፡፡ ይህ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል የሚሰራው መናፍስትን የመለየት መለኮታዊ አሰራር በእኛ ሲያድር የዘመኑን መንፈስ እየመረመርን ትክክለናውን መውሰድን እንማራለን፡፡

የሚቀጥለው ትምህርት፡ “ዓላማን ሳይለቁ ውጣ ውረዶችን የማስተናገድ ሰፊነት”


@revealjesus


ሁሉን በማስተናገድ እውነቱ ጋር የመድረስ ሰፊነት


ሰዎችን ከድካማቸው ለይቶ የማየት ሰፊነት

“በሥጋዬም ፈተና የሆነባችሁን ነገር አልናቃችሁትምና አልተጸየፋችሁትም ነገር ግን እንደ እግዚአብሔር መልአክ አዎን እንደ ክርስቶስ ኢየሱስ ተቀበላችሁኝ” (ገላ. 4፡14)፡፡

በቅርባችን የሚገኙ በማንኛውም ደረጃ የምናገናቸው ሰዎች አንድ ድካም ስላገኘንባቸው ብቻ የምንለያቸው ቢሆን ከጥቂት ጊዜ በኋላ ብቻችንን እንደምንቀር ምንም ጥርጥር የለውም፡፡

ይህ የሆነበት ምክንያት ከሰዎች ጋር ጥቂት ካሳለፍን በኋላ አንዳንድ ደካማ ጎናቸውን ማየት ስለምንጀምር ነው፡፡

ሰዎችን ከድካማቸው ለይቶ በመመልከት ማስተናገድ ማለት ድካማቸውንና ማንነታቸውን በማወቃችን ምክንያት ሳንንቃቸውና ሳናቃልላቸው ሰዎቹን የመቀበል ሰፊነት ማለት ነው፡፡

ሐዋርያው ጳውሎስ ይህንን አይነቱን ተቀባይነት ከገላትያ ሰዎች እንዳገኘ ነው ከላይ ባሰፈርነው ክፍል ውስጥ የሚናገረው፡፡ የገላትያ ሰዎች በጳውሎስ ላይ የሚፈትናቸው ሁኔታ እንደነበረ በግልጽ ተናግሯል፡፡

ሆኖም፣ የገላትያ ሰዎች ልክ ምንም ደካማ ባይኖረው ኖሮ ሊቀበሉት በሚችሉበት ሁኔታ ሲቀበሉት እናያለን፡፡

ይህንን እውነታ ለመለማመድ እንድንችል አንዳንድ እውነቶችን ማስታወስ አስፈላጊ ነው፡፡

1. ፍጹም የሆነ ሰው እንደሌለ ማስታወስ

“ጻድቅ ማንም የለም፤ አንድም እንኳ” (ሮሜ 3:10)፡፡

ስፍራ ቢበቃን ኖሮ የመጽሐፍ ቅዱስን ኃያላን ሰዎች በመዘርዘር መመልከት እንችላለን፡፡ ሙሴ በቁጣ ጽላቱን ሰብሯል፡፡ ዳዊት በምንዝርናና በነፍስ ግድያ ተገኝቷል፣ ኤልያስ መሞትን እስከሚመኝ ድረስ ፈርቶ ነበር፡፡ ጴጥሮስ በጳውሎስ እስከሚገሰጽ ድረስ ግብዝ ነበር፣ እንዲሁም ክርስቶስን ክዶ ነበር፡፡

እነዚህና መሰል ታላላቅ ሰዎች ድካማቸውን አልፈው ከተቀበሏቸው ሰዎች የተነሳ አሸንፈው ጌታን አክብረዋል፡፡

2. ደካሞችን መርዳት

“ደካሞችን እርዷቸው” (1ተሰ. 5፡14)፡፡

የዕብራውያን ጸሐፊ “በድካማችን የማይራራልን ሊቀ ካህን የለንምና” (ዕብ. 4፡15) በማለት ክርስቶስ ኢየሱስ የቀደደልን መንገድ ይጠቁመናል፡፡

ስለዚህም፣ ሰዎች ድካም እንዳለባቸው በማወቅ ከእነሱ ፍጽምናን ከመጠበቅ ይልቅ እነሱን የመርዳት ዝንባሌ ሊኖረን እንደሚገባ ያስታውሰናል፡፡

“መንፈስ በድካማችን ያግዘናል” (ሮሜ 8፡26) የሚለውም ቃል ቢሆን በውስጣችን ያደረው የጌታ መንፈስ ድካምን የሚያግዝ መንፈስ እንደሆነና እኛም ያንን መንፈስ የጠጣን ሰዎች ከድካማቸው የተነሳ መተው ሳይሆን በድካማቸው ማገዝ እንደሚገባን ያሳስበናል፡፡

3. የእኛን ደስታ ማዘግየት

“እኛ ብርቱዎች የሆንን፣ የደካሞችን ጉድለት መሸከም እንጂ ራሳችንን ማስደሰት የለብንም” (ሮሜ 15፡1)፡፡

ሰዎችን በድካማቸው ለማገዝ ለጊዜው የእኛን ደስታ ማዘግየትን ይጠይቀናል፡፡ ለምሳሌ በእውቀት አሁን የደረስንበት ደረጃ ከመድረሳችን በፊት እስከሚገባን ድረስ የታገሱንን ሰዎች ማስታወስ ከባድ አይደለም፡፡

አንድን በህመም የደከመን ሰው ለመርዳት ከእርሱ ቀስታ እኩል መራመድና የመፍጠን ፍላጎታችንን መግታት የግድ ነው፡፡ ይህ አመለካከት ግን ሰፊ አመለካከት ያላቸው ሰዎች ብቻ የሚለማመዱት አመለካከት ነው፡፡ “ደካሞችን እመስል ዘንድ፣ ከደካሞች ጋር እንደ ደካማ ሆንኩ” (1ቆሮ. 9:22)፡፡

የሚቀጥለው ትምህርት፡ “ሁሉን በማስተናገድ እውነቱ ጋር የመድረስ ሰፊነት”


ሰዎችን ከድካማቸው ለይቶ የማየት ሰፊነት


ሰላም ለሁላችሁ!

“የታደሰ አእምሮ” በተሰኘው ርእስ ስር ባለፈው የተመለከትናቸው ሃሳቦች “ሰማያዊ አመለካከት”“ንጹህ አመለካከት” እና “ስልታዊ አመለካከት” የሚሉትን ነው፡፡ ከነገ ጀምሮ ለሚቀጥሉት አምስት ቀናት ደግም የምንመለከተው፣ “ሰፊ አመለካከት” የሚለውን ሃሳብ ነው፡፡

ሰፊ አመለካከት

ጠቢቡ ሰሎሞንን በአለም ዙሪያ ታዋቂ ካደረጉት ባህሪዎቹ አንዱ ልበ ሰፊነቱ ወይም የአመለካከቱ ሰፊነት ነው፡፡

“አምላክ ለሰሎሞን ጥበብንና እጅግ ታላቅ ማስተዋልን እንዲሁም በባሕርዳር እንዳለ አሸዋ የልብ ስፋትን ሰጠው” (ምሳ. 4፡29)፡፡

ከዚህ ሰፊነቱ የተነሳ ነበር ከተለያዩ ክፍላተ-አለማት የእርሱን ጥበብና ፍርድ ለማየትና ለማድመጥ ሰዎች ይመጡ የነበረው፡፡ ይህ ሰፊነቱ ከተለያዩ ነገስታት ጋር ላለው የፖለቲካም ሆነ የንግድ ግንኙነት መሰረታዊና አስፈላጊ ነበር፡፡ ይህ ሰፊነቱ በሕዝቡ መካከል በትክክል እንዲፈርድ አስችሎትም ነበር፡፡

በተለያዩ የሕይወት አቅጣጫዎች ከጠባብነት ወጥተን አመለካከታችንን ስናሰፋ የተሳካ ሕይወት ውስጥ እንገባለን፡፡ ይህ የብልሆችና የጥበበኞች መንገድ ነውና፡፡ “ተላላ ከማስተዋል ርካታን አያገኝም፤ የራሱን ሐሳብ በመግለጥ ግን ደስ ይለዋል” (ምሳ. 18፡2)፡፡

ሁል ጊዜ በአንድ ጉዳይ ላይ ግራና ቀኙን በሚገባ ሳንገነዘብ ያቀባበልነውን ሃሳብ ብቻ ለመልቀቅ ከመዘጋጀት የወረደ ሕይወት ወጥተን ወደ አስተዋይነት እንድንገባ ሰፊ አመለካከት ወሳን ነው፡፡

የዚህ ክፍል አላማ አንድ አማኝ ስለ ሰፊ አመለካከት ሊያውቃቸው የሚገባውን መሰረታዊ እውነታዎች መግለጽ ነው፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ የምናጠናቸው አምስት ዋና ዋና እውነታዎች የሚከተሉት ናቸው፡-

1. ሰዎችን ከድካማቸው ለይቶ የማየት ሰፊነት

“በሥጋዬም ፈተና የሆነባችሁን ነገር አልናቃችሁትምና አልተጸየፋችሁትም ነገር ግን እንደ እግዚአብሔር መልአክ አዎን እንደ ክርስቶስ ኢየሱስ ተቀበላችሁኝ” (ገላ. 4፡14)፡፡

2. ሁሉን በማስተናገድ እውነቱ ጋር የመድረስ ሰፊነት

“ሁሉን ፈትኑ መልካሙንም ያዙ” (1ተሰ. 2፡20-21)፡፡

3. ዓላማን ሳይለቁ ውጣ ውረዶችን የማስተናገድ ሰፊነት

“በእያንዳንዱ ነገር በነገርም ሁሉ መጥገብንና መራብንም መብዛትንና መጉደልን ተምሬአለሁ። ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ” (ፊል 4፡12-13)፡፡

4. መርህን ሳይለቁ በዓለም የመሰማራት ሰፊነት

“ከክፉ እንድትጠብቃቸው እንጂ ከዓለም እንድታወጣቸው አልለምንም። እኔ ከዓለም እንዳይደለሁ ከዓለም አይደሉም” (ዮሐ. 17፡15-

5 ትህትናን ሳይለቁ ምስጋናን የመቀበል ሰፊነት

“ሌላ ያመስግንህ እንጂ አፍህ አይደለም ባዕድ ሰው እንጂ ከንፈርህ አይደለም” (ምሳ. 27:2)፡፡

Will See you tomorrow morning!


https://youtu.be/3igcTI9JPd8?si=cgW8UF6iwmfy0PBk

🚀 Best online investment platform for gold🚀
Celebrating Our Members’ Successful Withdrawals!
Join Allied Gold Today – Your Success Story Starts Here!
💡 Online Earnings Made Effortless
💡 Partner with Excellence, Grow with Gold
Why Choose Allied Gold?
✅ Trusted by 100,000+ Investors Worldwide
✅ Secure Gold-Backed Investments with 24/7 Transparency
✅ Instant Withdrawals & Dedicated Support
https://t.me/Allied_Gold
https://www.alliedgoldinvestment.com/?invitation_code=B6897


☝️አንድ የፀሎት ርዕስ => #ነብሳት
☝️የዛሬው የፀሎት ርዕስ => በ
#ፓኪስታን ለሚገኙ ላልተደረሱ #ሰዪድ ነብሳት

✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
- - - - - - - - - - - - - - - - - -
“ውሃ ባሕርን እንደሚሸፍን ሁሉ፣ #ምድርም_የእግዚአብሔርን_ክብር_በማወቅ_ትሞላለችና።”
ዕንባቆም 2:14
- - - - - - - - - - - - - - - - - -

#Pray_for_sayyid ☪️🕋
#Pray_for_sayyid☪️🕋
#Pray_for_sayyid ☪️🕋

Показано 20 последних публикаций.