ሙጀሲማን በማክፈር ዙሪያ በኡስታዝ ፈኽሩዲን እና በጀምዒያው ኡስታዝ አብዱሏህ ጎበዜ መካከል የተደረገ ውይይት
በውይይቱ ————
👉 ከኛ በኩል ቀጣይ ነጥቦች ተነስተዋል :-
# የአሽዐሪያ ሚዛን የሚደፋው ቀውል ሙጀሲሞችን በሁለት ከፍሎ መመልከት ሲሆን እነርሱም ሙጀሲም ሙሶሪህና ገይሩ ሙሶሪህ ይሰኛሉ
# ሙጀሲም ሙሶሪህ ( ተጅሲምን ከነ መልለያዎቹና መግገለጫዎቹ ) ለአሏህ የሚያፀና ሰው በመክፈሩ ላይ ልዩነት እንደሌለ
# ሙጀሲም ገይሩ ሙሶሪህ
አሏህ ጂስም ነው ግን እንደጂስም ያልሆነ የሚል እንዲሁም ጂስም የሚለውን ቃል ለአሏህ ከተጠቀመ በኃላ የተጅሲምን መግገለጫዎች ውድቅ ያደረገ ሰው በመክፈሩ ላይ በዑለሞች መካከል ልዩነት እንዳለና ከትላልቅ የዐቂዳ ዑለሞቻችን የመጣው እንዲህ አይነት ሰዎችን አለማክፈር ነው ።
# ሙጀሲማን በደፈናው ስለማክፈር የመጡ የዑለሞቻችን አቋሞች ሙጥለቅ እንደሆኑና “ ሙጀሲም ሙሶሪህን “ እንደፈለጉበት እኚህን አቋሞች ያስተላለፋልን ዑለሞች ግንዛቤ እንደሚያስይዝ
# ውይይቱ መመርኮዝ ያለበት በኛ የግል ግንዛቤ ሳይሆን በዑለሞቻችን ግንዛቤ እንደሆነ
👉
ከጀምዒያ በኩል # የጂስምን ትርጉም እያወቀ ለአሏህ ጂስም የሚለውን ቃል የተጠቀመ ሰው ይከፍራል ፤ ከዚህ ቃል ሌላ ትርጓሜ ፈልጌበት ነው ቢል ቦታ አንሰጠውም ( አረቦች ሆነው ለአሏህ ጂስም የሚለውን ስያሜ የተጠቀሙት ከራሚያዎችን ያላከፈሩትን ታላቁን የኢማም ራዚንና የሌሎች ዑለሞችን አቋም ረድ ማድረግ አልቻሉም)
💢 ርእሱ “ ሙጀሲማን በማክፈር “ ዙሪያ ሆነ ሳለ ልክ እኛ ተጅሲምን ለአሏህ ማፅናት እንደሚቻልና ምንም ችግር እንደሌለው አድርገን እንደምናስተምር አድርጎ ረዥም ስብከት በማድረግ ከአውድ መውጣት
💢 የዑለሞችን ንግግሮች በዑለሞች ግንዛቤ ከመረዳት ይልቅ የራስን ግንዛቤ አስቀድሞ አንድ ሀሳብ ላይ ክችች ማለት ወዘተ ይገኙበታል
♦️
ማጠቃለያ እንደሚታወቀው በጀምዒያዎች አቋም መሰረት “ ሙጀሲማን ያላከፈረ እንደውም ለማክፈር የተጠራጠረ እንኳን እርሱ ይከፍራልና “ ፤ ኡስታዝ አብዱሏህ ሙጀሲሞቹን ከራሚዮችን ሙነዚህ ናቸው ብለው እነርሱን ከማክፈር ሲሸሹ በመርሀቸዉ መሰረት ራሳቸውን ያከፍሩ ይሆን ⁉️⁉️
https://t.me/sufiyahlesuna