ሱፊይ አሕለሱና ወልጀመዐህ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Транспорт


╔════◈◉◈════╗
                     أهل السنة والجماعة
            ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⚪️አህለሱና ወልጀመዓህ ስንል የሰለፎችንና የኸለፎችን የግንዛቤ ዘይቤ የሚከተሉ ማለት ነው።
🔴ይህ መንገድ ሌሎች የኢስላም አስተሳሰብ ተከታዮችን አያከፍርም
🔎አመላካች የሰሪን ምንዳ ያገኛልና ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩልን
╚════◈◉◈════╝

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Транспорт
Статистика
Фильтр публикаций


ኢማም አሽሻፊዒይ ረሂመሁሏህ እንዲህ ይላሉ ፦

ዲናዊ ጉዳይም ላይ ይሁን ዱኒያዊ ጉዳይ ላይ መልካም እጣን የታደልንበትን ግልፅም ይሁን ድብቅ ፀጋ ያገኘነው ፤ ሁለቱም ላይ ወይም አንደኛቸው ላይ መከራ የተወገደልን (በነቢያችን) ሙሀመድ ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም አማካኝነት ነው ።

አርሪሳላህ

ኸሚስ ሙባረክ
https://t.me/sufiyahlesuna


💠 አንድ ዐሊም የበቃ ፈቂህ ነው የሚባለው የሚኖርበትን ዘመን ከጀርባው አድርጎ በትላንት ህልም ሲኖር ሳይሆን የሚኖርበትን ዘመን በሚገባ ተረድቶ እንደውም ዘመኑን ቀድሞ ሲገኝና ለዘመኑ አዳዲስ ችግሮች ሸሪዐዊ መፍትሄ ማበጀት ሲችል ነው ።

የፊቅህ ድርሳናትን መማርና መረዳት ብቻ ብቁ ፈቂህ አያደርግም ፣ የግድ መፅሀፍ ላይ የሰፈሩ ህግጋቶችን ከተጨባጩ አለም ጋር ማስተሳሰር ፣ ማብራራትና ፍርድ መስጠት መቻል አለበት ።
https://t.me/sufiyahlesuna


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
አዲስ አበባ ይገኝ የነበረውን የአብሬት ሀድራ የሆነውን ጠቅላይ ቢሮን ማፍረስ ለምን አስፈለገ??
https://t.me/sufiyahlesuna


ተሽከርካሪ ወንበርና ማይክ ምን አይሰራ

የአሁን ማይክና የድሮ ጡሩንባ እውቀት አይፈልጉም ዝም ብለ ተነስተህ ጡጡጡጡጡጡጡጡጥጥ ማለት ብቻ ነው።

✍ዘ.ሐ


ከነ ጭራሹ ክላሲካል አልወድም ማተኩረው ግጥሙ ላይ ብቻና ብቻ ነው። ለ2ደቂቃ ግጥም የ10ደቂቃ ክላሲካል ለምሰማት ሰብር የለኝም።እና በዚህ ሰሞን አዲስ አፕ መቷል ማንኛውም ነገር ስሰማ ከክላሲካል ውጪ ነው። በጣም የገረመኝ ግጥሙ ምንም አልገባም አለኝ ሌላው ተውት ሙሀደራዎችን ሀዲሶችን ስሟቸው ምን እንደሚሉ ግራ ይገባቹሃል።

አፑ ለሁሉ ነገር ይስራ አላውቅም ብቻ እናንተ እንደምንም ብላቹ ተጠቀሙበት በተለይ ተውሂድድድድድድድ ሺርክክክክክክክክክክክክ
ቢደዓዓዓዓዓዓዓዓዓዓዓዓዓዓዓ ሃራምምምምምምምምምምምም ባንክክክክክክክክክክክክክክክክክ
አደባባይ ይይይይይይይይይይይይይይዮ
መጅሊስስስስስስስስስስስስስስስስ
ኒቃብብብብብብብብብብብብብብ
የሚሉ ግጥሞችን ጭራሽ በክላሲካ አታዳምጡ ከክላሲካ ወጣ አድርጋቹ ስሰሙት ሺር ተው ቢደ ረግ ሀራ ባን አደ መጅ ኒቃ የሚል የቻይና ዘፈን ይሰጣችኋል።

መልካም የተመስጦ ጊዜ


ለፈገግታ

ወሀብያውች ከሚመፃደቁበት የሰለፎችን አቂዳ የያዘ ነው እያሉ ከሚሞግቱት ኪታብ ውስጥ ሸርሁ አሱና የብርበሀሪ ኪታብ ነው።

ኪታቡ ቀላል እንዳይምስላቹ ኪታቡ ውስጥ ያለውን አንድ
ፊደል ብታስተባብሉ ትከፍራላቹ ይላል ኪታቡ።

ፈገግ ያስባለኝ ኪታቡ ውስጥ እንዲህ የሚል ታገኛለህ:-
وإذا سمعت الرجل يقول: تكلم بالتوحيد، واشرح لي التوحيد، فاعلم أنه خارجي معتزلي البربهاري شرح السنة

"ስለ ተውሂድ ተናገር ተውሂድን አብራራልኝ የሚል ሰው ከሰማህ ኻዋሪጅ ሙእተዚላ መሆኑን እወቅ"

😁😁😁😁😁ወሀብያውች ይህን ቃል ከካዱ ከፈሩ ፣ እንቀበላለን ካሉ ኸዋሪጅ ሙዕተዚላ ሆኑ
ምርጫው የወሀብያዎች ነው‼️

ሳቁ መሳቅ ዕድሜ ይጨምራል ማልቅስ ሂወትን ያቀላል።

✍ዘ.ሐ
https://t.me/sufiyahlesuna


ከዘመኑ ሰለፊይ ነን ባይ ሸኾች ባህሪ መካከል ትላንት ሀራም ሲሉት የነበረን ነገር እነርሱን የሚጠቅም ሆኖ ሲገኝ ያለምንም ሸሪዐዊ ምክንያታ ዛሬ ላይ ሀላል ማድረጋቸዉ ነዉ ።

ከዚህ በፊትኮ ሀራም ነዉ ብላችሁ ነበር፡ ዛሬ ምን ተገኘ ? ስትላቸው ፤ የዛኔ ስለጉዳዩ አናዉቅም ነበር ይሉሀል ፤ ዋናዉ ችግር እዚህ ጋር ነዉ ፤ የማታዉቁት ጉዳይ ላይ በምን አይነት ድፍረት ፍርድ ሰጣችሁ ?? እንዴትስ አስችሏችሁ ይህ ሸሪዐዊ ብያኔ ነው ብላችሁ አስተማራችሁ ??


የፌስብክና የቲክቶክ ላይኮች ገንዘብ ይሆናሉ ብሎ ማን አስቦ ነበር ???

የዘመኑ ፋቀሃዎች አሏህ ይሁናችሁ


ቁርዓንን መህር ማድረግ

ቁርአንን መህር በማድረግ ላይ ኡለማውች የተለያዩ ሀሳቦችን አንፀባርቀዋል

👉 ኢማሙ አቡ ሃኒፍ ኢማሙ ማሊክ ቁርአንን መህር ማድረግ አይችልም ብለዋል ከሻፍኢ መዝሀብ ኢማሙ ሙዘኒ ይህን ሀሳብ አንፀባርቀዋል።

👉ኢማሙ አህመድ ደግሞ ቁርአንን መህር ማድረግ ይጠላል ብለዋል

👉ኢማሙ ሻፊዒ ደግሞ ቁርአንን መህር ማድረግ ይቻላል ብለዋል

🌜በአጠቃላይ አብዛኛው ኡለማውች ቁርአንን መህር ማድረግ አይቻልም የሚለውን ሀሳብ አንፀባርቀዋል

አላሁ ተዐላ አዕለም

✍ዘ.ሐ


(የውመ ዩክሸፋ ዐን ሳቅ ) የሚለውን አንቀፅ ኢብኑ ዐብባስ (መከራ የሚገለጥበት) ማለት ነው ብለዋል ፤ ሳቅ ወይም በእማሬያው ፍቺው " ባት " የሚለውን ቃል (መከራ ወይም ችግር ) ብለው ታእዊል አድርገውታል ።

ሀፊዝ ኢብኑ ሀጀር ፈትሁል ባሪ ላይ ኢማም አጥጠበሪይ ደግሞ ተፍሲራቸው ላይ ጠቅሰውታል
https://t.me/sufiyahlesuna


የመህር ገንዘብ የማን ነው⁉️

ኢብኑ ከሲር አቢ ሳሊህን ጠቅሰው እንዲህ ይላሉ
ሰውየው ሴት ልጁን ከዳር ከሷ ውጪ መህሯን ይወስዳል አላህም ይህን ከለከለ እንዲህ ሲል

وَآتُوا النِّسَاءَ صَدُقَاتِهِنَّ نِحْلَةً"

"ለሚስቶችም መህራቸውን ግዴታ ሲሆን ስጧቸው "


ሿሿ እንዳትሰሩ አስቀድማቹ አስገንዝቡ ባባ በጣም ይገርምሃል መህር ቁርአን እንዳለው ለሚስት መሰጠት
አለበት ነው ምናምን እያላቹ እንዲሰጣቹ የምርጫ ቅስቀሳ አድርጉ።😂😂😂

መልካም መህር

✍ዘ.ሐ


ንፅፅር

ብዙ የወሀብያ ንፅፅር ኡስታዞች እየሱስ አምላክ ላለመሆኑ ከሚያመጡት ማስረጃ አንዱ የዩሐንስ ወንጌል ምዕራፍ12:15 ነው ወደ ጥቅሱ እንሂድ

"እየሱስ ውርንጭላ (የአህያ ልጅ) አግኝቶ በእርሱ ተቀመጠ"

የወሀብያ ኡስታዞች ጥያቄ አምላክ እንዴት አህያ ላይ ለዛው የአህያ ልጅ ውርንጭላ ይሸከመዋል የሚል ነው? ጥያቄው ትክክል ነው። ይህ ጥያቄ አስቀድመው የጠየቁት ካልተሳሳትኩ ታላቁ አሊም አህመድ ዲዳት ናቸው እውን እየሱስ አምላክ ነው በተሰኘው ድንቅ መፀሐፍቸው ውስጥ።


ጥያቄ ለወሀብያ ኡስታዞች ነው አምላክ በአህያ መቀመጡ ለአምላክ የማይገባ ባህሪ መሆኑን ከተስማማቹ ለእናንተ ከዚህ የባስ ትልቅ ድንገታዊ ስጦታ አለኝ።

ولو قد شاء لاستقر على ظهر بعوضة فاستقلت به بقدرته ولطف ربوبيته، 

.......በእርግጥ (አላህ) ቢፈልግ የትንኝ ክፍ ላይ በተደላደለ እሷም 🦟 በእሱ ችሎታና በጌትነት እዝነቱ በተሸከመችው ነበር..........

ኡስማን ሰኢድ አዳረሚ

ይህን ምን ትሉታላችሁ? ሁለት ሚዛን አላቹ? አምላክ አህያ ይሸከመዋል የሚለውን ከተቃወማቹ ከአምላክነት ባህሪ ጋር እንደማይሄድ ካመናቹ ይህ ማንም ብሎት ከማንም ተሰምቶ የማያታውቅን የአምላክ ክብር ዝቅ ሰለሚያደርገው የሰለፎችን አቂዳ ሰብስቧል ብላቹ የምትመፃደቁበት ኪታብ ውስጥ መኖሩ አታቁም?

ለማንኛውም ክርስቲያን ወገኖች ይህን ቢያቁ
እንዴት እንደምትሞግቷቸው አላውቅም? ለነገሩ ከነሱ ጋር ስትከራከሩ አሻዒራ ሆናቹ ነው።




✍ዘ.ሐ




ማራገቢያ ሻጩ

በከተማው ላይ ማራገቢያ እያዞረ የሚሸጥ ነጋዴ ነበር። አንድ ቀን ንጉሡ ቤተ መንግስት ውስጥ ቁጭ ብለው እየተዝናኑ ሳለ ከውጪ በኩል አንድ ሺህ ዓመት የሚቆይ ማራገብያ እያል የሚጮህ ሰው ስሙ። ንጉሡም በመገርም እስኪ አስገቡት አሉ ነጋዴው ወደ ቤተመንግሥት እንዲገባ ተደረገ ንጉሡም እውን
እንዳልከው 1ሺህ ዓመት ይቆያል? ነጋዴውም በሙሉ እመነት በሚጋባ ንጉስ ሆይ የምትለውን አክል ጊዜ ካልቆየ ግን ፍርድ ከራሴ አሉ ነጋዴውም እንዳሉ ንጉስ ሆይ ይልና ሸጦ ከቤተመንግስት ይወጣል።

ከሳምንት በኃላ ማራገብያው ከጥቅም ውጪ ይሆናል ንጉሡም ነጋዴውን አስጠርተው ከሸንጎው እንዲቀርብ ያደርጉታል 1000ዓመት ይቆያል አላልከኝም ነበር? በትክክል ንጉሰ ሆይ ታዲያ እንዴት በሳምንቱ ከጥቅም
ውጪ ሊሆን ቻለ? ነጋዴውም በተረጋጋ መንፈስ ከአጠቃቀሞት ሊሆን ይችላል ንጉስ ሆይ?ንጉሱም በመገርም እንዴት ነበር መጠቀም የነበረብን በሚሞቀኝ
ጊዜ አራግብበት ነበር ከዛ ውጪ ሌላ አጠቃቀም አለው?ነጋዴውም አው ንጉስ ሆይ 1000ዓመት እንዲቆይ ከተፈለገ ማራገቢያውን ያቆሙትና እርሶ አንገቶትን ያወዛውዛሉ እንዲህ ተጠቅመው 1000ዓመት ካልቆየ የዛኔ ጠይቁኝ አለ።


አብዛኛው የቲቪ ማስታወቂያ ከዚህ የተወሰደ ነው።! የሚያስተዋውቁት ሌላ ስትሄድ የሚሉህ ሌላ። በማስታወቂያ ተታላቹ እቃ አትግዙ በጭራሽ።


✍ዘ.ሐ


በፊት ኢልም በልቦና ነበር አሁን በልብስ ሆኗል
ኢብኑ ሩሽድ


ሚስት

ባል የውጪ ስራ ሲሳራ ሚስት የቤት ስራ መስራት አለባት የቤት ስራ የሚከብዳት ከሆነ ባል አጋዥ መቅጠር አለበት እንጂ በኢስላም ሚስት ሳሰራ ቁጭ ብላ ጥፍሯን እየሞረደች ባል ከስራ ሲገባ ቶሎ ልብሱን ቀይሮ ቤብ ምን ኩክ ላድርግልሽ ምን ትበያለሽ ብሎ ሰርቶ አምጥቶ አብልቶ እሹሩሩ ብሎ የማስተኛት ግዴታ እንደለበት የሚመስል ኢስላማዊ ትምህርት ስህተት ነው።

የትኛውም የሰሀባ ታሪክን አንብቡ ባልና ሚስት ባል የውጪ ስራ ይሰራል ሚስት የቤቱን ስራ ትሸፍናለች አጋዥ ካስፈለገ ይቀጥርላታል።

የእንሴቶች ንግስት የነብዩ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም የአካል
ክፋይ እጇ ውሃ እስኪቋጥር ድረስ ወፍጮ ትፈጭ ነበር።

ኢማሙ ዓይኒ ኡምደቱል ቃሪእ ላይ ይህን ሀዲስ ሲያብራሩ "ይህ ሀዲስ ፍጢማ ትፈጭ እንደነበር ይጠቁማል የፈጨ ደግሞ ያቦካል ይጋግራል ይህ በአጠቃላይ ሚስት በባሏ ቤት ውስጥ ከምትሰራቸው ስራዎች ውስጥ ነው"


ደግሞ ብዙ ሴቶች መወፈር አይፈልጉም ስለዚህ ቀልጠፍጠፍ በይ ቤት ውስጥ ተፍተፍ በማለት።

✍ዘ.ሐ


"ሀኪሞች ፍቅርን ከነፍስ በሽታ ውስጥ ቆጥረውት መድሃኒቱንም ገልፀዋል። እኔ ግን ከፍቅር መዳንን አላህን ከለመንኩኝ አላህ አፊያ አያድርገኝ"

ሊሳኑዲን ኢብኑ ኸጢብ


ሁሉም ለለይላው ያለቅሳል ለይላም ለሌላው ታለቅሳለች

ቀኑ ይለፍ እንጂ ጊዜው ይለፍ እንጂ የሁሉ ለይላ ከደጅ ትጠናለች

#አብሽሩ

✍ዘ.ሐ


እርሳቸዉ ስለዱኒያ ምንም አያውቁም
👉 አስነዋሪ ባህሪ ሲሆን

ዱንያ ላይ እየኖሩ ስለ ዱንያ አለማወቅ የተመሰገነ ባህሪ የሆነው ከመች ጀምሮ ነው ?

እርሳቸዉ ለዱኒያ ምንም ቦታ የላቸውም
👉 ተፈላጊ ባህሪ


Репост из: Dinia islamic channel
ይህን የዓረብኛ አረፍተ ነገር የሚያነብ ሰው ሚስኪንዋ ሚስት የተከበረውን የባልዋ ጫማ ትብላ ብሎ ይተረጉመው ይሆናል። ምን አልባት ለዳዕዋም ተጠቅመውት ይሆናል። የንግግር ፍሬ ሀሳብ ግን ይሄ አይደልም።

ንግግሩ የሚለው ሚስት ከባልዋ ጎን ተቀምጣ መብላትዋ አደብ ነው። አው የተከበሩት ሚስት ከተከበሩ ባለቤታቸው ጎን ቁጭ ብለው መመገብ።

ሐዛእ (حذاء)የሚለው ቃል በዓረብኛ ከጎን ወይም ከቅርብ የሚል ትርጉም አለው

ተከታዩን ተርጉሙ......
يجوز ذبح المرأة يوم عيد الأضحى
https://t.me/Ustaz_ebin_Selman


አልሀምዱሊላህ ተገላግለነዋል

تجميد الحوار

الحديث عن الوحدة والتصدي للأعداء يقودنا للحديث عن العلاقة مع الآخر الديني عموماً، حيث كنتم من العلماء الموقعين على وثيقة تجميد الحوار بين الأزهر والفاتيكان وفي نفس الوقت لكم كتابات عن الديانات الإبراهيمية الشرق أوسطية الثلاث والعامل المشترك بينها مما يسهم في الحوار بينها فما تفسيركم لهذا الموقف الذي قد يبدو متناقضاً لدى عامة الناس؟

ليس هناك تناقض إذا علمنا أن سبب توقيعي مع أكثر من خمسين عالماً من مختلف الدول العربية والإسلامية بتجميد الحوار مع الفاتيكان لعدم جدوى الحوار معه في ظل تكرار الإساءات من بابا الفاتيكان للإسلام ورسوله صلى الله عليه وسلم، ورفضه الاعتذار عن المغالطات التي جاءت على لسانه، وفي نفس الوقت محاولة الفاتيكان التدخل في الشؤون الداخلية في الدول العربية التي بها مسيحيون، لهذا كان لابد من وقفة مع الفاتيكان .

أما بالنسبة للأديان الشرق أوسطية الثلاث اليهودية والمسيحية والإسلام ففيها غنى روحي وأخلاقي قوي وفاعل، ويمكن أن يقودها ذلك إلى تحقيق التفاهم والعمل المشترك للوصول إلى عالم تتحقق فيه العدالة وينعم بالسلام، لكن من المؤسف أن الواقع شيء آخر بسبب استخدام السياسة للدين من أجل السيطرة على الثروات والمصادر الاقتصادية وإشعال الحروب .

Imam Al Bouti’s Firm Stance Against the Vatican

Due to the the previous Pope, Pope Benedict XVI (Josef Ratzinger), insulting Islam (see the 2006 Regensburg speech for example) and the Vatican’s constant interference in Arab Muslim-majority countries that have Christian populations, Imam Al Bouti was one of 50 Muslim scholars who signed a declaration calling for the freezing of dialogue between Al Azhar and Vatican City.

Показано 20 последних публикаций.