ርዕሰ :- ቅባት
መነሻ ጥቅስ
(መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ ምዕ. 16)
12፤ ልኮም አስመጣው፤ እርሱም ቀይ፥ ዓይኑም የተዋበ፥ መልኩም ያማረ ነበረ። እግዚአብሔርም። ይህ ነውና ተነሥተህ ቅባው አለ።
13፤ ሳሙኤልም የዘይቱን ቀንድ ወስዶ በወንድሞቹ መካከል ቀባው። የእግዚአብሔርም መንፈስ ከዚያ ቀን ጀምሮ በዳዊት ላይ በኃይል መጣ። ሳሙኤልም ተነሥቶ ወደ አርማቴም ሄደ።
*ዳዊት በእናት እና አባቱ የተረሳ ሰው ቢሆንም እንኳ እግዚአብሔር የሚያውቀው ሰው ነበር።
*ዳዊት ከተቀባ በውኋላ ተራ ሰው መሆን አይችልም።
*"ቅባትን የሚሰጥ እግዚአብሔር ነው!"
*እንደ ሳሙኤል የሚቀባው ኤልያብ ቢመስለውም የእግዚአብሔርን ልብ የማረከው ግን ዳዊት ነበር።
*ዳዊት ከተቀባ እና ጎልያድን ከገደለ በኋላ የገባው ምድረበዳ ነበር፤ግዜው ሲደርስ ግን ወደ ንግስና መጣ።
*ምንም እንኳን ምድረበዳ ቢሆንም እንኳን ከተማው ያወራ የየነበረው ስለእርሱ ነበር።
*ዳዊት ቅባት ምን እንደሆነ ጠንቅቆ የሚያውቅ ሰው ነበር።
*የዳዊት የስኬት ምስጢር እግዚአብሔር ነበር!
*እግዚአብሔር የጠራንን ጥሪ እና ተልእኮ በራሳችን ችሎታ ልንሰራው አንችልም፤ቅባት ያስፈልገናል!
*የእግዚአብሔር ቅባት ማለት ለተጠራንበት ጥሪ የሚሆን የእግዚአብሔር ሀይል ማለት ነው።
*ቅባቱ ሲመጣ ዘመን ተሻጋሪ ስራ እንሰራለን!
*ክርስቶስ ማለት የተቀባ ማላት ነው!(Christ the anointed one)
*በዚህ ምድር ላይ ያለ ተልዕኮ እግዚአብሔር ያመጣው ሰው የለም!
*አንድ ሰው የእግዚአብሔር ቅባት በሃይል በእርሱ ላይ መስራት ሲጀምር ያ ሰው የእግዚአብሔር መለኮታዊ አሰራር ማስተላለፊያ ይሆናል።
*ሳውል ያሳደደው ሐዋርያትን ነቀር ጌታ ኢየሱስ ግን ስለምን ታሳድደኛለህ አለው!(የተቀባን ሰው ስትነካ እርሱን ሳይሆን የእግዚአብሔርን አሰራር ነው ነክቶ የነበረው)
*ቅባት በላያችን ላይ የሚፈስ ዘይት አይደለም!
*ያለ ቅባቱ ባዶ መሆናችን ሊገባን ይገባል!
*ቅባት ቀንበርን ይሰብራል!
*ዳዊት ወደ ጎልያድ ሊገድለው ሲሮጥ ራሱን አይቶ ሳይሆን እግዚአብሔርን አይቶ ነው!
*ቅባት ድፍረት ይሰጥሃል፤ቅባቱ ሲመጣ ድፍረት ይዞ ይመጣል።
*ቅባት ሲመጣ ፍላጎትህን ይቀይራል፣አስተሳሰብህን ይቀይራል፣ሰዎች ፊት ያለህንም ተቀባይነት ይቀይራል!
*ቅባት በህይወትህ ሲመጣ ይታወቃል!
*የመጨረሻው ዘመን ቅባት በኢየሱስ ስም ያግኝህ/ሽ።
*ተጨማሪ ጥቅስ: ሉቃስ 4:-17-19
2ቆሮንቶስ 1:-21-22
ኢሳይያስ 10:27
ሐዋርያት ስራ 10:38
@ChristJesusTV@ChristJesusTV@the_annointing