Фильтр публикаций


አሜሪካና ኢራን በኑክሌር ፕሮግራም ዙሪያ ውይይት ጀመሩ።

ከሁለቱ ሀገራት የተውጣጡ ከፍተኛ ባለስልጣናት በኦማን ተገናኝተዋል ተብሏል።

በመካከለኛው ምስራቅ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ስቴቭ ዊትኮፍ የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳደር "ግልጽ ቀይ መስመር አስቀምጧል" ሲሉ ተናግረዋል

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ "በቂ ተነሳሽነት ካለ በቀናነት መፍትሄ መፈለግ ይቻላል" ብለዋል።
#ap #thewashingtontimes

@ThiqahEth


የሶማሊያ መንግስት በጦር አውሮፕላኖች አስቸኳይ የጥራት ፍተሻ እንዲደረግ አዘዘ፡፡

የሶማሊያ ትራንስፖርትና ሲቪል አቪየሽን ሚኒስትር ሙሃመድ ፋራህ፣ በሁሉም የጦር አውሮፕላኖች የደህንነት ፍተሻ እንዲደረግ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።

አውሮፕላኖቻችን በትክክል የተፈተሹ፣ የተመዘገቡና የተጠገኑ መሆን ይኖርባቸዋል ያሉት ሚኒስትሩ አውሮፐሰላኖቹ የጥራት ፍተሻ ከተደረገላቸው በኋላ በአዲስ መልክ የምዘና ሰርቲፊኬት እንደሚሰጣቸው አስታውቀዋል፡፡

ፋራህ ይህን ውሳኔ ያስተላለፉት አልሸባብ በዋና ከተማዋ በሚገኘው አየር መንገድ ላይ የሞርታር ጥቃት ካደረሰ ከአምስት ቀን በኋላ ነው፡፡ 

ይህን ጥቃት በመፍራት የግብጽ እና የቱርክ አየር መንገዶች ወደሶማሊ የሚያደርጉትን በረራ አቋርጠዋል፡፡
#sonna   #chaviation

@ThiqahEth


#Update

"125% ታሪፍ የጣልነው ተናጠላዊ የጉልበት እርምጃ ስለተወሰደብን ነው" - የቻይና ገንዘብ ሚኒስቴር

የቻይና ገንዘብ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ "በጉልበትና አስገዳጅነት የተጣለብን ታሪፍ የአጸፋ እርምጃ እንድንወስድ አስገድዶናል" ብሏል፡፡

የአጸፋ እርምጃውን በተመለከተም፣ "125% ታሪፍ የጣልነው ተናጠላዊ የጉልበት እርምጃ ስለተወሰደብን ነው" ነው ያለው።

ሚኒስቴሩ በመግለጫው፣ ትራምፕ ታሪፍ መጣላቸውን ከቀጠሉ የአሜሪካ ምርቶች ከቻይና ገበያ ሊወጡ ይችላሉ ሲል አስጠንቅቋል፡፡

አሁን ባለው የታሪፍ ሁኔታ ምክንያት የአሜሪካ ምርቶች በቻይና ያላቸው ተቀባይነት ቀንሷል
መባሉን #Upi ተዘግቧል።

ቻይና ከቀናት በፊት፣ "በቻይና እና በአሜሪካ መካከል በተፈጠረው የንግድ ጦርነት ሳቢያ የደህንነት ችግሮች ሊፈጠሩ ይችላሉ" ማለቷን #thestreetstimes መዘገቡ ይታወሳል።

በዘገባው መሠረት፣ አሜሪካ ለጣለችባት የ67% ታሪፍ በአጸፋው በአሜሪካ ምርቶች ላይ የ84% ታሪፍ እንደምትጥል ነበር ቻይና ያስታወቀችው።

@ThiqahEth


በህንድና በኔፓል ድንገት የጣለው ከባድ ዝናብ የ100 ሰዎችን ህይወት ቀጠፈ፡፡

ዝናቡ ረቡዕ ጀምሮ መጣሉን የገለጸው የህንድ ሜትሮሎጂ ድፓርትመንት (IMD) የጥንቃቄ መልዕክቶችን አሰራጭቷል።

በምሥራቅ እና ማዕከላዊ ህንድ መብረቅ መከሰቱንም ዲፓርትመንቱ አመላክቷል፡፡

በተመሳሳይ መልኩ ብሄራዊ የአደጋ ጊዜ ባለስልጣን በከባድ ዝናብ ሰዎች መሞታቸውን ገልጾ፤ ተጎጅዎችን የማገዝ ስራ እየተሰራ ነው ብሏል፡፡
#asiaone

@ThiqahEth


የቀድሞው የትግራይ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ሚኒስትር ሆኑ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሚያዝያ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የቀድሞውን የትግራይ ጊዜያዊ አስታዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳን የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አድርገው ሾመዋል።

@ThiqahEth


#Update

"እያንዳንዱ ሰው መትረፉንም ሆነ መሞቱን እስከምናረጋግጥ እዚህ እንቆያለን" - ጁዋን ሜንዴዝ

በዶሚኒካን ሪፐብሊክ የሟቾች ቁጥር 218 ደረሰ።

የአደጋ ምርመራ ዳይሬክተር ጁዋን ሜንዴዝ፣ "189 ሰዎችን በህይወት ማትረፍ ችለናል ግን አስቸጋሪ ሁኔታ ገጥሞናል" ብለዋል።

"በህይወት የተረፉትን ማዳን ተስፋ አስቆራጭ ሆኗል" ያሉት ዳይሬክተሩ፣ "እያንዳንዱ ሰው መትረፉንም ሆነ መሞቱን እስከምናረጋግጥ እዚህ እንቆያለን" ሲሉ ተናግረዋል። #aljazeera

@ThiqahEth


"ከ150 የሚበልጡ የቻይና ዜጎች በጦርነቱ ተሳትፈዋል" - ዘለንስኪ

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮለድሚር ዘለንስኪ ቻይናውያን ከሩሲያ በኩል ተሰልፈው መገኘታቸው ቤጂንግ በዚህ ጦርነት ተሳታፊ መሆኗን ያሳያል ብለዋል።

ዘለንስኪ ሩሲያ የውጭ ተዋጊዎችን በመመልመል ጦርነቱን ለማራዘም ያላትን ፍላጎት ያመላከተ መሆኑንም ገልጸዋል።

ፕሬዝዳንቱ የዩክሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማብራሪያ መጠየቁን አብራርተዋል። #hindustantimes

@ThiqahEth


"ዋሽንግተን እና የእስያ አጋሮቿ የሚጠነስሱት ሴራ እውን እንደማይሆን ግልጽ ነው" - ዮ ኡንግ

የኪም ጆንግ ኡን እህት የኑክሌር ፕሮግራምን ማስቆም "የቀን ቅዥት" ስትል አጣጣለች፡፡

የሰሜን ኮሪያው ፕሬዝዳንት ታናሽ እህት ኪም ዮ ኡንግ ሀገራቸው የኑክሌር ፕሮግራምን መቼም ቢሆን የማቆም እቅድ የላትም ብለዋል፡፡

ዮ ኡንግ፣ "ዋሽንግተን እና የእስያ አጋሮቿ የሚጠነስሱት ሴራ እውን እንደማይሆን ግልጽ ነው" ሲሉ ተናግረዋል፡፡

አሜሪካ፣ ጃፓንና ደቡብ ኮሪያ ከቀናት በፊት በነበራቸው የሶስትዮሽ ውይይት ሰሜን ኮሪያ የኑክሌር ፕሮግራሟን እንድታቆም የጋራ ስምምነት አድርገዋል፡፡

ከፕሬዝዳንቱ በመቀጠል በሰሜን ኮሪያ ፖለቲካ ተጽዕኖ ፈጣሪ እንደሆነች የሚነገርላት ዮ ኡንግ ስምምነቱን ጸብ አጫሪ በማለት ተችተዋል፡፡   
#irishexaminer

@ThiqahEth


"በቻይና እና በአሜሪካ መካከል በተፈጠረው የንግድ ጦርነት ሳቢያ የደህንነት ችግሮች ሊፈጠሩ ይችላሉ" - ቻይና

ቻይና ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ዜጎቿ ጥንቃቄ እንድያደርጉ አሳስባለች፡፡

በዚህም የቻይና የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ "ዜጎች ከጉዟቸው በፊት አደጋዎችን ማጤን አለባቸው" በማለት አስጠንቅቋል፡፡

ሚኒስቴሩ ባወጣው ይፋዊ ማሳሰቢያ፣ "በቻይና እና በአሜሪካ መካከል በተፈጠረው የንግድ ጦርነት ሳቢያ የደህንነት ችግሮች ሊፈጠሩ ይችላሉ" ብሏል፡፡

ቻይና አሜሪካ ለጣለችባት የ67% ታሪፍ በአጸፋው በአሜሪካ ምርቶች ላይ የ84% ታሪፍ እንደምትጥል አስታውቃለች፡፡ 
#thestreetstimes

@ThiqahEth


"ተላልፈው ተሰጥተውናል፤ በኛ ቁጥጥር ስር ናቸው"  - የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር

ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በመፈንቀለ መንግስት ተጠርጥረው በእስር የነበሩ ሶስት አሜሪካውያን መልቀቋን አስታወቀች፡፡

አሜሪካውያኑ ከአንድ አመት በፊት "በፕሬዝዳንት ፍሊክስ ስሼኬድ መንግስት ላይ መፈንቀለ መንግስት ለመፈጸም ተንቀሳቅሰዋል" በሚል ወንጀል ተከሰው የእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባቸው ነበር፡፡

ሆኖም የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ታሚ ብሩስ ደግሞ፣ "ተላልፈው ተሰጥተውናል፤ በእኛ ቁጥጥር ስር ናቸው" ሲሉ ተናግረዋል፡፡

እስረኞቹ መለቀቃቸው የተሰማው በአሜሪካ የአፍሪካ ልዩ መልዕክተኛ ማሳድ ቦውሎስ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረግ መጀመራቸውን ተከትሎ ነው፡፡

በእስር ላይ የነበሩት አሜሪካውያን ቤንጃሚን ሩበን፣ ማርሴል ማላንጋና ታለር ቶምሰን ናቸው፡፡ "thenational  
#associatedpress

@ThiqahEth


"ቢያንስ 7 ጋዜጠኞች በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው ተይዘዋል" CPJ

በግል በሚተዳደረው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ሳተላይት (EBS) መንግስት ሀሰተኛ ዶክመንተሪ ተሰርቷል በሚል ወንጀል መያዛቸውን አለማቀፉ የጋዜጠኖች ጥበቃ ኮሚቴ (CPJ) አስታውቋል፡፡

ጋዜጠኞቹ የታሰሩት ብርቱን ተመስገን የተባለች ግለሰብ በአዲስ ምዕራፍ ፕሮግራም ቀርባ ተማሪ በነበረችበት ወቅት የደረሰባትን የመደፈር ወንጀል በመናገሯ ነው ብሏል፡፡

ሲ ፒ ጄ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ሳተላይት (EBS) ከኢትዮጵያ ሚዲያ ባለስልጣን "አስተዳደራዊ ማዕቀብ ፈተና ተጋርጦበታል" ሲል ገልጿል፡፡

የፍርድ ቤት የክስ ዶክመንት እንደደረሰው የገለጸው ተቋሙ ጋዜጠኞቹ በአማራ ክልል ከሚገኙ ጽንፈኛ ቡድኖች ጋር ተባብራችኋል የሚል ክስ እንደቀረበባቸውም አስታውቋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ህገመንግስቱን ለመናድ እና መንግስትን ለመጣል አሲራችኋል በሚል ክስ ቀርቦባቸዋል ብሏል፡፡

በፍርድ ቤት ከሚገኙት መካከል ነብዩ ጥኡመልሳን፣ ታሪኩ ሀይሌ፣ ህሊና ታረቀኝ፣ ንጥር ደረጀ፣ ግርማ ተፈራ፣ ሄኖክ አባተ እና ሀብታሙ አለማየሁ መሆናቸውን አስታውቋል፡፡

@ThiahEth


#Update

በዶሚኒካን ሪፐብሊክ የሟቾች ቁጥር 113 መድረሱ ተገለጸ፡፡

በአንድ የምሽት ክለብ ላይ የደረሰው የመደርመስ አደጋ 155 ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸው ሆስፒታል መግባታቸውን ባለስልጣናት አስታውቀዋል፡፡

ከፖርቶሪኮ እና ከእስራዔል የተውጣጡ 400 የአደጋ ጊዜ ፈጥኖ ደራሽ ባለሙያዎች አደጋው ወደደረሰበት ስፍራ ተልከዋል ተብሏል፡፡ 

የሟቾችን አስክሬን ለማፈላለግ ውሾች፣ ድሮኖች እና ሌሎች መሳሪያዎች ጥቅም ላይ መዋላቸው ተገልጿል፡፡
#yenisafaq

@ThiqahEth


የግብፅ ደህንነት ኃላፊ ከሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ጋር ተወያዩ።

የደህንነት ቢሮ ኃላፊው ሀሰን ረሻድ ከጄኔራል አብዱል ፈታህ አልቡርሃን ጋር በፖርት ሱዳን መገናኘታቸው ተዘግቧል።

ውይይቱ በሱዳን ሰላምና መረጋጋትን ለመመለስ ያለመ ነው ተብሏል።

ረሻድ ከአልሲሲ የተላከ ደብዳቤ ለአልቡርሃን መስጠታቸው ተገልጿል።

የሱዳን ጦር ቤተመንግስቱን እና አየር ማረፊያውን ከተቆጣጠረ በኋላ የተደረገ የመጀመሪያ ውይይት ነው ተብሏል።  
#suna #alqahera #ahramonline

@ThiqahEth


በዶሚኒካን ሪፐብሊክ ህንፃ ተደርምሶ ቢያንስ የ27 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ፣ 160 የሚሆኑት ተጎዱ።

በናይት ክለብ ላይ በደረሰው አደጋ 160 ሰዎች ተጎድተው ሆስፒታል ገብተዋል ተብሏል።

የአደጋ ምርመራ ማዕከል ኃላፊ ጁዋን ሜንዴዝ፣ "በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች እያፈላለግን ነው"ም ብለዋል።

ሜንዴዝ የአደጋውን መንስኤ ከመናገር ተቆጥበዋል።
#bowenislandundercurrent

@ThiqahEth


የቀድሞው የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁን አወገዙ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ኦልመርት የወቅቱን የእስራዔል ጠቅላይ ሚኒስትር ኒታንያሁን "በፍልስጥኤማውያን ላይ ወንጀል ፈጽመዋል" በማለት ከሰዋል።

ዌስት ባንክን ጨምሮ በፍልስጥኤም ግዛቶች ላይ ግፍ ተፈጽሟል ብለዋል ኦልመርት።

የእስራኤል መንግስት መጠለያ ካምፕ ላይ በሚገኙ ንጹሐን ዜጎች አሰቃቂ ግድያ መፈጸሙ ሊወገዝ የሚገባ እርምጃ ነው ሲሉም ገልጸዋል።
#aa

@ThiqahEth


"ደቡብ ሱዳን ዝግጁ ከሆነች ውሳኔቻችንን የምንከልስበት እድል ይኖራል"  - ማርክ ሩቢዮ

አሜሪካ ለደቡብ ሱዳን ዜጎች የቪዛ እገዳ ጣለች።

ዋሽንግተን ጁባ ዜጎቿን ለመመለስ ፍቃደኛ ባለመሆኗ የቪዛ ክልከላ ማድረጓን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርክ ሩቢዮ አስታውቀዋል።

የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በህገወጥ መንገድ የሚኖሩ ስደተኞች ወደሀገራቸው እንድመለሱ መወሰናቸው ይታወቃል።
#gulftoday

@ThiqahEth


ከ50 በላይ ሀገራት በቀረጥ ዙሪያ ከትራምፕ መንግስት ጋር ንግግር  እንዲጀመር ጠየቁ።

የፕሬዝዳንቱ የምጣኔ ሀብት አማካሪ፣ "የተጣለው ታሪፍ አሜሪካ ከገጠማት የኢኮኖሚ ቀውስ የምታግምበት ስትራቴጂ አካል ነው" ብለዋል።

የአሜሪካ ብሄራዊ የኢኮኖሚ ምክር ቤት ዳይሬክተር ኬቪን ሀሴት የትራምፕ ውሳኔ የሀገር ውስጥ ኢንቨስተሮችን ለማበረታታት የወሰዱት እርምጃ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

አክለውም ትራምፕ እየጣሉት ያለው ታሪፍ ተፅዕኖ አሳድሮብናል ያሉ ሀገራት ውይይት እንድደረግ ማመልከታቸውን ገልጸዋል።

ከእነዚህ መካከል የታይዋን ፕሬዝዳንት ላይ ቺንግ ቴ የንግድ መዛባት እንዳይፈጠር በማሰብ ከአሜሪካ የሚገቡ ምርቶች ከቀረጥ ነፃ እንድገቡ መወሰናቸውን ተናግረዋል።
#reuters #timeslive

@ThiqahEth



Показано 18 последних публикаций.