Фильтр публикаций


የዓለም ሀገራት ትናንት ትራምፕና ዘለንስኪ ያደረጉትን ሀይለ ቃል የተሞላበት ውይይት ተከትሎ አስተያየታቸውን እየሰጡ ይገኛሉ።

ፈረንሳይ፦ ፕሬዝዳንት ማክሮን "ወራሪ አለች ሩሲያ፣ ተጎጂ አለች ዩክሬን" በማለት ለዩክሬን ያላቸውን ድጋፍ አሳይተዋል።

"ከሶስት አመት በፊት ዩክሬንን መርዳታችንና ሩሲያ ላይ ማዕቀብ መጣላችን ልክ ነበር" ያሉት ፕሬዚዳንቱ ይህ እርምጃ ወደ ፊትም ይቀጥላል ብለዋል።

ዩናይትድ ኪንግደም፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታርመር "መከባበር የተሞላበት ዲፕሎማሲ ለሰላም ወሳኝ ነው። የአውሮፓ መከፋፈል የሚጠቅሙ ሩሲያን ነው" ያሉት ስታርመር የትኛውም የሰላም ስምምነት ዩክሬንን ያሳተፈ ሊሆን እንደሚገባ አብራርተዋል።

ኖርዌ፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ጆናስ ስቶሬ፣ "ከነጩ ቤተመንግሥት የተመለከትነው ነገር ልብ የሚሰብር ነው" ብለዋል። ትራምፕ ዘለንስኪን "በሶስተኛው የአለም ጦርነት እየተጫወትክ ነው ያሉት ንግግር ምክንያታዊ አይደለም" በማለት ተችተዋል።

ፖላንድ፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶናልድ ተስክ፣ "የተከበሩ ዘለንስኪ፣ የተከበራችሁ የዩክሬን ወዳጆች ብቻችሁን አይደላችሁም" ሲሉ አጋርነታቸውን አሳይተዋል።

ጀርመን፦ አዲሱ ፕሬዝዳንት ሜርዝ፣ "በጥሩውም ሆነ በመጥፎው ጊዜ ከዘለንስኪና ከዩክሬን ህዝብ ጎን እንቆማለን" ብለዋል።

ሩሲያ፦ ምንም እንኳን በመንግሥት በኩል ይፋዊ አስተያየት ባይሰጥም ከፍተኛ ባለሥልጣናት ግን ብዙዎችን ላስቆጣው ውይይት አድናቆት ሰጥተውታል።

የቀድሞው ፕሬዝዳንትና የአሁኑ የሩሲያ ደህንነት ምክርቤት ምክትል ሀላፊ ድሜትሪ ሜድቬዴቭ፣ "ትራምፕ ትክክል ናቸው፤ የኪቭ አገዛዝ በሶስተኛው የአለም ጦርነት እየቀለደ ነው" ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አስፍረዋል። #foxnews#independent#theglobeandthemail

@ThiqahEth


"በሶስተኛው ዓለም ጦርነት ቁማር እየተጫወትክ ነው፤ አንተ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግ ፍላጎት የለህም፣ በሚሊዮኖች ህይወት እየቀለድክ ነው" - ትራምፕ

"ፑቲንን መቼ አወራኸው ? ምን አለህ ? 25 ጊዜ የፈረመውን ስምምነት የጣሰው ራሱ" - ዘለንስኪ

"በሚዲያ ፊት ከምትከራከር ስህተትህን አምነህ ተቀበል" - ጄይዲ ቫንስ

የትራምፕና የዘለንስኪ ውይይት ያለስምምነት ተጠናቀቀ።

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮለድሚር ዘለንስኪ በሩሲያ ጋር ስለሚደረገው ስምምነት ለመነጋገር ወደ አሜሪካ ያደረጉት ጉዞ ውጤታማ አለመሆኑ ተገልጿል።

ፕሬዝዳንት ትራምፕ ፕሬዝዳንት ዘለንስኪን "የሚሰማንን ስሜት አንተ አትነግረንም" በማለት ከተለመደው የመሪዎች ንግግር ወጣ ባለ መልኩ ኃይለ ቃል ሲለዋወጡ ተደምጠዋል።

ይህን ተከትሎ ዘለንስኪ የማዕድን ስምምነት ፊርማ አለመፈረማቸው ተዘግቧል።

ትራምፕ፣ "በሶስተኛው የአለም ጦርነት ቁማር እየተጫወትክ ነው: አንተ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግ ፍላጎት የለህም፡ በሚሊዮኖች ህይዎት እየቀለድክ ነው" ሲሉ ተናግረዋል።

ዘለንስኪ በበኩላቸው፣ "ፑቲንን መቼ አወራኸው ? ምን አለህ ? 25 ጊዜ የፈረመውን ስምምነት የጣሰው ራሱ" ሲሉ ተደምጠዋል።

በነጩ ቤተመንግሥት በተደረገው ውይይት የአሜሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ጄጂ ቫንስ ዘለንስኪን፣ "ለአሜሪካ ህዝብ አክብሮት ሊኖርህ ይገባል" በማለት በስሜት ተናግረዋል።

"በሚዲያ ፊት ከምትከራከር ስህተትህን አምነህ ተቀበል" ሲሉም ተደምጠዋል። #startribune#kyivpost#thenational#scotsman#buenosairestimes

@ThiqahEth


#አዲስአበባ

የካቲት 23 ቀን በሚከበረው 129ኛው የዓድዋ ድል በዓል የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይኖር ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን ይፋ አድርጓል።

በዚህም መሰረት፡-

- በቸርችል ጎዳና በቴዎድሮስ አደባባይ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ባንኮ ዲሮማ መብራት፣

- ከአራት ኪሎ በራስ መኮንን ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ራስ መኮንን ድልድይ፣

- ከመነን አካባቢ እና የካቲት 12 ሆስፒታል በአፍንጮ በር ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ አፍንጮ በር፣

- ከእሪ በከንቱ በኤሌክትሪክ ህንፃ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ደጎል አደባባይ፣

- ከአዲሱ ገበያ በሰሜን ሆቴል ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ሰሜን መብራት፣

- ከመርካቶ በአቡነ ጴጥሮስ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ደጃዝማች ሀብተጊዮርጊስ ድልድይ፣

- ከእንቁላል ፋብሪካ በቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ዮሐንስ መብራት የሚወስዱት መንገዶች ከየካቲት 22 ቀን 2017 ዓ/ም ከምሽቱ 6 ሰዓት ጀምሮ እስከ የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 7 ሰዓት ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚደረጉ ፓሊስ አስታውቋል።

ተሽከርካሪዎች አማራጭ መንገድ እንዲጠቀሙም ተመልክቷል።

@ThiqahEth


ኢትዮጵያ 2,500 ወታደሮችን እንደምታሰማራ ተገለጸ፡፡

የአፍሪካ ህብረት በሶማሊያ በሚያሰማራው አዲሱ የሰላም አስከባሪ ኃይል ሀገራት የሚያዋጧቸውን ወታደሮች ቁጥር ይፋ አድርጓል፡፡

በዚሁ መሰረት ከአምስት የአፍሪካ ሀገራት ማለትም ከኢትዮጵያ፣ ግብጽ፣ ኡጋንዳ፣ ጅቡቲና ኬንያ የተውጣጡ በድምሩ 11,195 የሰላም አስከባሪ ኃይሎች እንደሚሰማሩ ህብረቱ አስታውቋል፡፡

ኡጋንዳ 4,500 ወታደሮችን በማሰማራት ቀዳሚ ናት፤ 2,500 ወታደሮችን የምታሰማራው ኢትዮጵያ ደግሞ ሁለተኛ ይዛለች፡፡

ጅቡቲ 1,520፣ ኬንያ 1,410 እንዲሁም ደግሞ ግብጽ 1,091 የሰላም አስከባሪዎችን ወደ ስፍራው ይልካሉ፡፡

አዲሱ የሰላም አስከባሪ ኃይል በዋና ከተማዋ ሞቃዲሾ፣ ጆውሀርና ባይዶዋ እንደሚሰፍር ህብረቱ ገልጿል፡፡
#voa    #aupkm

@ThiqahETH


ቱኒዚያ ከአይ.ኤም.ኤፍ ያላትን ግንኙነት አቋረጠች።

ሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር ቲኒዚያ ''በኢኮኖሚ ጉዳዬ ላይ ጣልቃ እየገባ ነው'' ካለችው  ከአለማቀፉ የገንዘብ ተቋ አይ ኤም ኤፍ ጋር ያለትን ግንኙነት አቋርጣለች፡፡

የቱኒዚያ ፋይናንስ ሚንስትር "አይ. ኤም. ኤፍ የቱኒዚያን ትክክለኛ ፍላጎትና ተግዳሮቶች የተረዳ አይመስለኝም''  ብሏል።

ፋይናንስ ሚንስቴሩ፣ በጉዳዩ ላይ ባወጠው መግለጫ አይ. ኤም. ኤፍ መንግስት ድጎማን እንዲያቋረጥ፣ ግብር እንድጨምርና የመንግስት ሰራተኛ ደመወዝን እንዲቀንስ ጠይቋል ብሏል፡፡

ይሁን እንጂ ተቋሙ ያቀረባቸው እርምጃዎች ሀሳቦች ከፍተኛ የኑሮ ውድነት የነገሰባትና የስራ አጥ ቁጥር በጨመረባት ቱኒዚያ ድህንት እንዲስፋፋና ማህበራዊ አለመረጋጋት እንዲፈጠር ያደርጋል ብለዋል፡፡ 

የካዒስ ሰይድ መንግስት ከተቋሙ የሚያገኘውን ብድር በሌላ ለመተካት አማራጮችን እየፈለገ እንደሚገኝ ሚንስቴሩ አመላክቷል፡፡
#africaintelligence   #northafricapost

@ThiqahEth


"የአንካራው ስምምነት ቴክኒካል ውይይት ተጠናክሮ ይቀጥላል"  - ኢትዮጵያና ሶማሊያ 

ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃመድ በሞቃዲሾ ውይይት ካደረጉ በኋላ የጋራ መግለጫ አውጥተዋል፡፡

መሪዎቹ በመግለጫቸው፣ "የጋራ ጥቅሞች ላይ ትብብራችንን ለማጠናከር ተስማምተናል" ሲሉ ገልጸዋል፡፡ አቢይና ሀሰን ሼክ በመግለጫቸው አክለውም በተከታዮቹ ጉዳዮች መምከራቸውን አስታውቀዋል፡፡

መሪዎቹ በመግለጫቸው፦

"ኢትዮጵያና ሶማሊያ በህዝቦቻቸው መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነትና የሚጋሩት ድንበር ለግንኙነታቸው ያለውን ጥቅም እውቅና ሰጥተናል።

በድፕሎማሲያዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ትብብር አማካኝነት መተማመን ለመፍጠር ተስማምተናል።

ሁለቱ ሀገራት የሚጋሯቸው የጋራ ራዕይ እንዳሏቸው ገልጸው፤ ለቀጠናዊ መረጋጋትና ብልጽግና በጋራ ለመስራት መክረናል።

ለዚህም ይረዳ ዘንድ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እና የሶማሊያ ብሄራዊ ጦር ቀጠናዊ ሰላም ለማስጠበቅ የሚስችላቸውን ስምምነት አድርገዋል።

የመሰረተ ልማት ፕሮጄክቶችን ለማሻሻልና ህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶችን ለማጠናከር ተወያይተናል። የአንካራውን ስምምነት በተመለከተ ገንቢ ውይይቶች መደረጋቸውን ይቀጥላሉ።

በአጠቃላይ በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ጸጥታን ለማስፈንና የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን ለማጠናከር ለመስራት ከስምምነት ላይ ደርሰናል" ሲሉ ገልጸዋል፡፡
#pmo #villasomalia

@ThiqahEth


ኢትዮጵያ አንድ ቢሊየነር አስመዘገበች።

ቢሊየነርስ አፍሪካ በኢትዮጵያ ውስጥ 10 እጅግ የናጠጡ ሀብታሞችን ዝርዝር ይፋ አድርጓል፡፡

መፅሔቱ ግብፅ፣ ናይጄሪያና ደቡብ አፍሪካ በቢሊዮን የሚቆጠር ሀብት ያላቸው ባለሀብቶችን ማፍራት የቻሉ ቢሆንም ኢትዮጵያ ግን ያላት ቢሊየነር አንድ ብቻ ነው፡፡ እሳቸውም ሼክ መሀመድ አልአሙዲ ናቸው፡፡

በመከተል በአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ተፅእኖ መፍጠር የሚችሉ በርካታ ሚሊየነሮች በኢትዮጵያ እንዳሉ ዘገባው አስረድቷል፡፡

አልአሙዲ በቁጥር አንድነት የተቀመጡ ሲሆን፣ የሀብታቸው መጠን 9.56 ቢሊዮን ዶላር መሆኑ ተገልጿል፡፡ በሁለተኛ የተቀመጡት በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩትና የሳንሻይን ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሳሙኤል ታፈሰ ናቸው፡፡

በቢሊየነርስ አፍሪካ ዝርዝር በሶስተኛነት የተቀመጡት የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ ባለቤት አቶ በላይነህ ክንዴ ናቸው፡፡

በአራተኛ ደረጃ የተቀመጡት ደግሞ ከሀይል አቅርቦት እስከ ሸቀጣ ሸቀጥና ሪል ስቴት ዘርፍ ባሉ ስራዎች ላይ የተሰማሩት አቶ ቴዎድሮስ አሸናፊ ናቸው፡፡

መፅሄቱ በአምስተኛ ደረጃ ያስቀመጣቸው በዋሽንግተን ዲሲና ኒውዮርክ ከተሞች በርካታ የነዳጅ ማደያዎች ያላቸውና በቨርጂኒያ የሪል ስቴት ዘርፍ ላይ የተሰማሩትን አቶ ኢዮብ ማሞ ነው፡፡

አቶ ከተማ ከበደ ስድስተኛ፣ አቶ አለማየሁ ከተማ ሰባተኛ፣ አቶ ብዙአየሁ ቢዘኑ ስምንተኛ፣ አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ዘጠነኛ እንዲሁም የአቪየሽን ባለሙያው አቶ ግርማ ዋቄ አስረኛ ሁነው አጠናቀዋል፡፡  
#billionairesafrica

@ThiqahEth


በሱዳን የሟቾች ቁጥር 46 ደረሰ፡፡

በትናንትናው ዕለት በኦምዱርማን ግዛት አንቶኖቭ ወታደራዊ አውሮፕላን ተከስክሶ ጉዳት ደርሷል፡፡

የሱዳን ጤና ሚኒስቴር የሟቾች ቁጥር አሁንም እየጨመረ በመሆኑ፤ በግልጽ መናገር እንደሚያስቸግር አስታውቆ 10 ሰዎች ግን ጉዳት ደርሶባቸው ህክምና እየተከታተሉ ነው ብሏል፡፡

አደጋው በደረሰበት አካባቢ የሚገኙ መኖሪያ ቤቶች ላይ ጉዳት ደርሶባቸዋል ተብሏል፡፡

የሀገሪቱ ጦር የአደጋው መንስዔ ምን እንደሆነ እስካሁን ድረስ አልገለጸም፡፡ 
#ashraqalawusat

@ThiqahEth


ዩክሬን የመሬት ስር ማዕድኗን ለአሜሪካ ለመስጠት ተስማማች፡፡

ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኪቭ በጦርነቱ ከአሜሪካ የተደረገላትን ድጋፍ ለማካካስ ማዕድኗን መስጠት እንዳለባት ባቀረቡት ሀሳብ መሰረት ዛሬ ተፈጻሚ መሆኑን ነጩ ቤተመንግስት አስታውቋል፡፡

17 አይነት ናቸው የተባሉት ማዕድናቶቹ 500 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ይገመታሉ ተብሏል፡፡

ማዕድናቶቹ ለኤሌክትሪክ መኪና ምርት፣ አውሮፕላን ሞተር፣ የህክምና ቁሳቁስ፣ ለነዳጅ ማጣያና ሌሎች የሚሳዔልና ራዳር ምርት እንደሚያገለግሉ ተገልጿል፡፡  
#france24

@ThiqahEth



Показано 10 последних публикаций.