Фильтр публикаций


አሜሪካ ኢትዮጵያን ጨምሮ ዜጎቿ ወደ 23 ሀገራት እንዳይሄዱ አስጠነቀቀች፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሜሪካውያን ወደ አፍሪካና ላቲን አሜሪካ ሀገራት እንዳይሄዱ ማስጠንቀቂያ አስተላልፏል፡፡

አሜሪካውያኑ ከመሄዳቸው በፊት ጉዟቸውን እንዲያጤኑበት አሳስቧል ተብሏል፡፡

አሜሪካውያን እንዳይሄድባቸው ከተባሉት ሀገራት ውስጥ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ፣ ባንግላድሽ፣ ቻድ፣ ኒካራጉዋ፣ ሁንዱራንስ፣ ሞሪታኒያና ኡጋንዳ ይጠቀሳሉ፡፡   
#miamiherald

@ThiqahEth


ፕሬዜዳንት ሳልቫኪር ማያርዲት ሦስት ሚኒስትሮችን ከስልጣን አባረሩ፡፡

ሳልቫኪር የፍትህና ህገመንግስታዊ ጉዳዮች ሚኒስትር ሩበን ማዶል አሮንን አንስተው ዌክ ማሜር ኮልን ተክተዋል፡፡

በተመሳሳይ መልኩ የትምህርት ሚኒስትሩን አወት ደንግ አኩልን በኩዮክ አቦል ተክተዋል፡፡

ሳልቫኪር ጠንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትሩን ጆሴፍ ሙም ማጃክን በአቶንግ ማንያንግ ተክተዋል፡፡

በፖለቲካ አለመረጋጋት ውስጥ የምትገኘው ደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንቱ ሚኒስትሮቹን ከስልጣን ያነሱበት ምክንያት በግልጽ አልተነገረም፡፡
#anadoluagency

@ThiqahEth


የቀድሞው የፊሊፒንስ ፕሬዝዳንት ሮድሪጎ ዱቴርቴ በቁጥጥር ስር ዋሉ።

አለማቀፍ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ዱቴርቴ በፈጸሙት ወንጀልና በህገወጥ እፅ ዝውውር እንዲያዙ ባስተላለፈው ውሳኔ ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።

ፕሬዝዳንቱ "በሰብዓዊነት ላይ በተፈጸመ ወንጀል" ተጠያቂ እንደሚሆኑ ተገልጿል።

ዱቴርቴ ከሆንክ ኮንግ ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ ማኒላ አለማቀፍ አየር መንገድ ውስጥ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
#toi

@ThiqahEth


የሶርያ ሽግግር መንግስት የሰሞኑ ግጭት ማቆሙን አወጀ።

በሽር አላሳድን በኃይል ያስወገደውና በአህመድ አልሻራ የሚመራው የወቅቱ የሶሪያ መንግስት ላለፉት አምስት ቀናት ከአሳድ ደጋፊዎች ጋር ግጭት ውስጥ ቆይቷል።

ከ1000 መብለጡን ንጹሐን በግጭቱ መገደላቸው መገለጹ ይታወሳል።

የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ መንግስት በሶሪያ የአልዋይቲ ክርስቲያኖች ላይ የደረሰውን ግድያ አውግዟል።
#newarab #apnews #shafaqnew

@ThiqahEth


ኢጋድ በደቡብ ሱዳን አለመረጋጋት ዙሪያ ለመምከር አስቸኳይ ስብሰባ ሊያደርግ መሆኑን አስታወቀ።

የምስራቅ አፍሪካ በይነ መንግስታት (IGAD) ስለደቡብ ሱዳን ይመክራል የተባለውን 43ኛውን ልዩ ጉባዔ በመጪው  ረቡዕ እንደሚያካሂድ ባወጣው መግለጫ ይፋ አድርጓል።

አስቸኳይ ጉባዔው በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች አማካኝነት በበይነ መረብ እንደሚካሄድ ተጠቁሟል።

የወቅቱ የኢጋድ ሊቀመንበር የጅቡቲው ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጉሌህ፣ ስብሰባው እንድካሄድ በደብዳቤ ማሳወቃቸውን መግለጫው ጠቅሷል።  
#sudanpost

@ThiqahEth


"83% የሚሆኑት የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት (USAID) ፕሮግራሞች ተሰርዘዋል" - ማርክ ሩቢዮ

በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ ቢሊዮን ዶላሮችን ያስወጡ 5,200 ኮንትራቶች መሰረዛቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርክ ሩቢዮ ተናግረዋል።

በዚህም፣ "83% የሚሆኑት የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት (USIAD) ፕሮግራሞች ተሰርዘዋል" ብለዋል።

ሩቢዮ፣ "አድነነዋል" ያሉትን ወጪ "የአሜሪካ ብሄራዊ ጥቅም ማዕከል ነው" ነው ብለውታል።

የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት (USAID) ፕሮግራሞችን ለመከለስ ስድስት ሳምንት የፈጀ ውይይት መደረጉንም አብራርተዋል።
#pbsnews

@ThiqahEth


በአዲስ አበባ የባቡር ትራንስፖርት ትኬት ሽያጭ በዲጂታል መልኩ ሊጀመር ነው።

የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅት ከወረቀት ትኬት ሽያጭ ወደ ዲጂታል ሽያጭ አገልግሎት ሊሸጋገር መሆኑን ገልጿል።

የዲጂታል ትኬት ሽያጩ ለጊዜው በተመረጡ ቦታዎች ማለትም በሀያት፣ጦርሀይሎች ዳግማዊ ሚኒሊክና ቃሊቲ ጣቢያዎች እንዲሁም በስታዲየም የሽያጭ ቁጥጥር በማድረግ የሚተገበር ይሆናል ተብሏል፡፡

የክፍያ ሥርዓቱ በቴሌ ሱፐር አፕና በዩኤስ ኤስዲ (USSD) ኮድ አማካኝነት መቁረጥ የሚያስችል ነው። More፥
@tikvahethmagazine

@ThiqahEth


ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀስላሴ ለሁለት የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የባለሙሉ ስልጣን አምባሳደርነት ሹመት ሰጡ።

ፕሬዚዳንቱ፣ ለአምባሳደር ምስጋኑ አርጋና ለአምባሳደር ሱለይማን ደደፎ የባለሙሉ ስልጣን አምባሳደርነት ሹመት ሰጥተዋል።

በህገ መንግስቱ አንቀጽ 71 ንዑስ አንቀጽ 3 መሰረት ለሁለት የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የባለሙሉ ስልጣን አምባሳደርነት ሹመት መሰጠቱ ታውቋል። #ENA

@ThiqahEth


የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ገቡ።

በዚህም ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሃመድ እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

አቶ አወል ዛሬ በጅግጅጋ የሶማሌና አፋር ወንድም ህዝብ በጋራ የሚያፈጥሩበት ኢፍጣር ለአብሮነትና ለሰላም መርሐ ግብር ላይ ይታደማሉ፡፡

በመርሐ ግብሩ የሃይማኖት አባቶች፣ የሃገር ሽማግሌዎችና የፌደራል መንግስት ተቋማት ኃላፊዎች እንደሚገኙም የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

@ThiqahEth


"ካናዳ በምንም ዓይነት መልኩ የአሜሪካ አካል አትሆንም" - የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር

ካናዳ "በዘመኗ ከፍተኛ ቀውስ" ውስጥ ትገኛለች ሲሉ የሀገሪቱ ገዥ ሊበራል ፓርቲ መሪ ሆነው የተመረጡት ማርክ ካርኒ ተናግረዋል፡፡

ተመራጩ የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ "ያልተገባ ቀረጥ" ካናዳ ላይ በመጣል ኢኮኖሚዋን ለማዳከም እየጣሩ ነው ብለዋል።

ከዚህ ቀደም የካናዳ ባንክ ገዥ በመሆን ያገለገሉት ማርክ ካርኒ፣ ጀስቲን ትሩዶን ተክተው የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን በትላንትናው እለት ተሾመዋል።
#sputnik

@ThiqahEth


#Chagni

ከ490 በላይ የሽሻ ማስጨሻ ዕቃዎች ተወገዱ ተባለ

ይህን ያለው በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር የቻግኒ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽሕፈት ቤት ነው።

በዚህም በተለያዩ ጊዜ የተያዙ ከ490 በላይ የሽሻ ማስጨሻ ዕቃዎችን ማስወገዱን ገልጿል።

@ThiqahEth


#Update

32 ኢትዮጵያዊያን ከታይላንድ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ።

በማይናማር ታግተው ከቆዩ በኋላ ከሳምንታት በፊት ወደ ታይላንድ ተሻግረው ከነበሩት በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን መካከል 32ቱ ዛሬ አዲስ አበባ ገቡ።

32 ኢትዮጵያውያን ዛሬ ጠዋት አዲስ አበባ መድረሳቸውን ከተመላሾቹ አረጋግጠናል።

የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ፣ 32 ኢትዮጵያውያን መመለሳቸውን አስታውቋል።

ተመላሾቹ እንደሚሉት ከሆነ፤ የታይላንድ መንግስት አልቀበላችሁም ያላቸው ወደ 300 የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን ከማይናማር ካምፕ ገና አልወጡም።

ከማይናማሩ እገታ ወጥተው ወደ ታይላንድ ከተሻገሩት መካከል ደግሞ ወደ 5 ልጆች ተመልሰው ተወስደዋል።

ወደ 29 የሚሆኑ ኢትዮጵውያን ደግሞ ማይናማር ውስጥ "ዋልዋይ" የሚባል ቦታ የከፋ ግፍ እየተፈጸመባቸው ይገኛሉ።

ታይላንድ የሚገኙ ኢትዮጵያውያኑ በበኩላቸው፣ "ሌሎች በርካቶች በሌሎች ካምፓች ስቃይ እየደረሰባቸው ነው" ብለዋል።

@ThiqahEth


ትራምፕ ላይ የግድያ ሙከራ ሊፈፅም ነበር የተባለ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ።

የአሜሪካ ሚስጥራዊ አገልግሎት (USSS) አንድ አጥፍቶ ጠፊ ወጣት በዋሽንግተን ከተማ ሲንቀሳቀስ ተይዟል ሲል አስታውቋል።

አገልግሎቱ፣ ጥቃቱን ሊፈፅም የነበረው ግለሰብ የህንድ ዜግነት እንዳለውና በቅርቡ ወደ አሜሪካ መግባቱን ገልጿል።

ግለሰቡን በቁጥጥር ስር ለማዋል በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ጉዳት ደርሶበት ሆስፒታል ገብቷል ተብሏል። 
#theweek

@ThiqahEth


የአሜሪካ ጤና ቢሮ ስራቸውን በገዛ ፍቃዳቸው ለሚለቁ ሰራተኞች 25,000 ዶላር እሰጣለሁ አለ።

በጤናና ሰብዓዊ አገልግሎት ዲፓርትመንት የሚሰሩ ከ80,000 የሚልቁ የፌዴራል ሰራተኞች ስራቸውን ከለቀቁ የካሳ ክፍያው ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተገልጿል።

የቢሮው ውሳኔ የፕሬዝዳንት ትራምፕ፣ "ወጭ መቀነስ" እርምጃ አካል ነው ተብሏል።

ሰራተኞቹ እስከመጪው ሳምንት አርብ ውሳኔያቸውን እንዲያሳውቁ ተነግሯቸዋል ነው የተባለው።

ይህ እርምጃ በአሜሪካ የጤናው ዘርፍ ላይ የሰው ኃይልና የበጀት እጥረት ሊያመጣ ይችላል የሚል ስጋት አስከትሏል።
#theeconomictimes

@ThiqahEth


#Update

ሶሪያ!

"የሟቾች ቁጥር ከ1000 በልጧል" -  ስይሪያን ኦብዘርቫቶሪ

በሶሪያ በተፈጠረው ግጭት የሟቾች ቁጥር ከ70 ወደ 600 ከፍ ማለቱ ትላንት መዘገቡ ይታወሳል።

የስይሪያን ኦብዘርቫቶሪ የዛሬ መረጃ እንደሚያስረዳው ደግሞ የሟቾች ቁጥር ከ400 በላይ አሻቅቧል።

በሶሪያ ከቀናት በፊት የጀመረው ግጭት ተባብሶ መቀጠሉን መቀመጫውን እንግሊዝ ያደረገው ስይሪያን ኦብዘርቫቶሪ አስታውቋል።

እስካሁን ድረስ 745 ንጹሃን ሰዎች፣ 148 የአሳድ ታማኝ ወታደሮችና 125 የሽግግር መንግሥቱ ወታደሮች ህይወታቸው ማለፉን ተቋሙ ገልጿል።

"ታጣቂዎች በግጭቱ ወቅት ቤቶችን አቃጥለዋል፣ ተሽከርካሪዎችን ሰርቀዋል" ተብሏል። #outlookindia

@ThiqahEth


"ሁለት ስደተኞች ሙተዋል፤ 186ቱ እስካሁን ድረስ አልተገኙም"  - IOM

ዓለማቀፍ ስደተኞች ድርጅት (አይ ኦ ኤም) ስደተኞችን ጭነው ሲጓዙ የነበሩ 4 ጀልባዎች መገልበጣቸውን አስታውቋል።

ድርጅቱ ስደተኞቹ 57 ሴቶችን ጨምሮ አብዛኛዎቹ ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ገልጿል።

IOM ባለፈው የፈረንጆች አመት 2024 ውስጥ 558 ስደተኞች ከምስራቅ አፍሪካ ተነስተው ጅቡቲና የመንን ለማቋረጥ ሲሞክሩ ህይወታቸው ማለፉን አመላክቷል።  
#thedailytribunenewsofbahrain #vaticannews

ThiqahEth

Показано 16 последних публикаций.