TIKVAH-ETHIOPIA


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


#NationalExam

" ፈተናው ስታንዳርዱን ፣ ደህንነቱንና ሚስጢራዊነቱን ጠብቆ በመዘጋጀት ላይ ይገኛል " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሁሉም ተማሪዎች በተማሩበት ሥርዓተ ትምህርት ይዘት እየተዘጋጀ እንደሆነ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

አገልግሎቱ ፤ " የ2017 ዓ.ም ተፈታኝ ተማሪዎች ከ9ኛ - 10ኛ በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት፣ ከ11ኛ - 12ኛ ደግሞ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ናቸው " ብሏል።

" ነገር ግን በ2015 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ በናሙናነት በተመረጡ ት/ቤቶች የስርዓተ ትምህርት የሙከራ ትግበራ ላይ የተሳተፉ ት/ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች 10ኛ ከፍልን በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ናቸው " ሲል ገልጿል።

በአማራ ክልል በ2016 የትምህርት ዘመን መፈተን ሲገባቸው በጸጥታ ችግር ምክንያት ሳይፈተኑ የቀሩና የ11ኛ ክፍልን በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ት/ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች በ2017 ዓ.ም የሚፈተኑ እንዳሉም ጠቁሟል።

በዚህም " የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ከላይ የተገለጹትን ሶስቱንም ነባራዊ ሁኔታዎች ከግምት ውስጥ ባስገባ እና ሁሉንም የዘመኑን ተፈታኝ ተማሪዎች በማከለ መንገድ ስታንዳርዱን ፣ ደህንነቱንና ሚስጢራዊነቱን ጠብቆ በመዘጋጀት ላይ ይገኛል " ሲል አሳውቋል።

የፈተና ዝግጅቱ፡-

1) ከ9ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከነባሩ ሥርዓተ ትምህርት፣

2) ከ10ኛ ክፍል በነባሩና በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ላይ ተመሳሳይ ይዘቶች፣

3) ከ11ኛ ከፍል በነባሩና በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ላይ ተመሳሳይ ይዘቶች፣

4) ከ12ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት የሚዘጋጅ እንደሆነ ተገልጿል።

ከላይ የተዘረዘረው የዝግጅት ሂደት በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ላይ እንደተጠበቀ ሆኖ የኢኮኖሚክስ የትምህርት ዓይነት ግን በስርዓተ ትምህርቱ አዲስ የተጀመረ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በ12ኛ ክፍል ይዘት ላይ ብቻ ተመስርቶ የሚዘጋጅ እንደሆነ ተመላክቷል።

በአጠቃላይ ሁሉም ተማሪዎች ከ9ኛ -12ኛ ክፍል በየተማሩበት የሥርዓተ ትምህርት ይዘት ላይ መመስረት ፈተናው እንደሚዘጋጅ አውቀው ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ አገልግሎት መ/ቤቱ አሳስቧል።

ተማሪዎች አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ወላጆች፣ መምህራንና መላው የትምህርት ማህበረሰብ ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ተላልፏል።

የዘንድሮ ሀገር አቀፉ የ12ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና መቼ እንደሚሰጥ እስካሁን የተወሰነ ነገር የለም።

@tikvahethiopia

69k 2 408 247

#MoE

" በዚህ ዓመት 150 ሺህ የሚደርሱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናቸውን በበየነ መረብ (ኦንላይን) ይወስዳሉ " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

ባለፈው ዓመት ወደ ተግባር የገባው የኦንላይን ብሔራዊ ፈተና ዘንድሮም እንደሚቀጥል ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በዚህ ዓመት 150 ሺ የሚደርሱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናቸውን በበየነ መረብ (ኦንላይ ) እንዲወስዱ ቅድመ ዝግጅ እየተደረገ መሆኑን አሳውቀዋል።

ይህንን ያሉት የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምክክር መድረክ ላይ ነው።

ከዚህ ባለፈ በመድረኩ  " ሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥራት ያለው ትምህርት በማግኘት ረገድ እኩል እድል እንዲኖረው ፤ በድሃና ሃብታም መካከል ያለውን ልዩነት የሚያጠብ ሥራ መስራት አለብን " ብለዋል።

" ይችን ሀገር መለወጥ የሚቻለው የትምህርት ሥርዓቱን መቀየር ሲቻል " ነው ሲሉም ገልጸዋል።

በመንግስት ትምህርት ቤቶች የተሻለ የመማር ማስተማር እንዲኖር ማድረግ ላይ መሥራት እንደሚገባና ' በትምህርት ለትውልድ ' የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል የተጀመረው ንቅናቄ ግለቱን ጠብቆ እንዲሄድ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

በሌላ በኩል ፤ የመምህራንን አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ከተመረቁ  ዜጎች ውስጥ ልዩ የማስተማር ሙያ (pedagogy) ስልጠና እንዲወስዱ በማድረግ ወደ ሙያው እንዲገቡ እንደሚደረግ ይፋ አድርገዋል።

#MoE

@tikvahethiopia


🔊 #የጤናባለሙያዎችድምጽ

🔴 “
የጸጥታ አካላት ሆስፒታል ድረስ በመምጣት ድብደባ ፈጽመዋል፣ ዘጠኝ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላትን አስረዋል ” - የሆስፒታሉ ሠራተኞች

➡️ “ እነርሱ ጋ ብቻ አይደለም ያልተከፈለው፤ ከ2000 በላይ ሠራተኞች እንደ ዞን ያልተከፈላቸው አሉ ”  - የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ

በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ከተማ፣ የይርጋጨፌ ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎችና የአስተዳደር ባለሙያዎች “ በጸጥታ አካላት ድብደባና እስራት ተፈጽሞባቸዋል ” ሲሉ ሠራተኞቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።

ተፈጽሟል ስላሉት እስራትና ድብደባ ምክንያት ምን እንደሆነ ሲገልጹ፣ እንደ ሀገር የተደረገው የደመወዝ ጭማሪ ክፍያ ባለመፈጸሙ የሥራ ማቆም አድማ መደረጉን ተከትሎ መሆኑን ሠራተኞቹ አስረድተዋል።

የአራት ወራት የደመወዝ ጭማሪ ክፍያ ከ150 በላይ ለሚሆኑ የሆስፒታሉ ሠራተኞች አለመፈጸሙን፣ እስከ የካቲት 10 ቀን 2017 ዓ/ም እንዲፈጸምላቸውና እስከተጠቀሰው ጊዜ ድረስ ካልተፈጸመላቸው ሥራ የማቆም አድማ ለማድረግ እንደሚገደዱ በደብዳቤ ጭምር ማሳወቃቸውን ገልጸዋል።

በመሆኑም ክፍያው ባለመፈጸሙ የሥራ ማቆም አድማ እንዳደረጉ፣ የተወሰኑት ሥራ ማቆም አድማ ያላደረጉ ሰራተኞች ቢሮ ባሉበት “ አድማ አስመትታችኋል ” በሚል እስራትና ድብደባ እንደተፈጸመባቸው በመግለጽ አማረዋል።

በዚህም፣ “የካቲት 10 እና 11 ቀን 2017 ዓ/ም ሥራ አልገባንም። በቀን 12/2017 ዓ/ም ደግሞ ሙሉ ፓትሮል ፓሊስ መጥቶ በሥራ ላይ የነበሩ የማኔጅመንት አባላትን ይዘው ወጡ ” በማለት ተናግረዋል።

አክለው፣ “ ከየቤቱ ያሉት ሠራተኞችም መረጃው ደርሷቸው ‘ካሰራችሁ ሁላችንንም እሰሩን የሁላችንም ጉዳይ ነው’ ብለው እስሩ ከተፈጸመበት ፓሊስ ጣቢያ ድረስ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተዋል ” ሲሉ ሁነቱን አስረድተዋል።

የታሰሩት ምን ያክል ግለሰቦች ናቸው? ስንል የጠየቅናቸው ሠራተኞቹ በሰጡት ምላሽ፣ “የታሰሩት የሆስፓታሉ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላት ናቸው፡፡ የጸጥታ አካላት ሆስፒታል ድረስ በመምጣት ድብደባ ፈጽመዋል፣ 9 ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላትን አስረዋል ” ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሠራተኞቹን ቅሬታ በመያዝ፣ ድርጊቱ ለምን እንደተፈጸመ የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ቢሮን ምላሽ የጠየቀ ሲሆን፣ እስራቱ መፈጸሙን እና ደመወዙ አለመከፈሉን አምኖ ምላሽ ያለውን ሰጥቷል።

የመምሪያው ኃላፊ አቶ አንዱዓለም ማሞ በዝርዝር ምን መለሱ ?

“ ባለሙያዎቹ የካቲት 7 መጥተው ነበር። ከኛ ጋ ውይይት አድርገዋል፡፡ ውይይት ካደረግን በኋላ ፕሮሰስ እያደረግን ለማክሰኞ ጠዋት ክልል ቀጠሮ እንደነበረ ገልጸንላቸው ነበር፡፡ ማክሰኞ ሂደን ዘጠኝ ሰዓት ላይ ምላሽ ታገኛላችሁ ብለናቸው ነበር፡፡

እነሱ ጋ ብቻ አይደለም ክፍያው ያልተከፈለው ከ2000 በላይ ሰራተኞች እንደ ዞን ያልተከፈላቸው አሉ፡፡ እንደ ዞንም ሶስት ሆስፒታል ላይ ነው ክፍያው ያልተከፈለው፡፡ የተለያዩ የጤና ባለሙያዎችም በወረዳ ደረጃ ያልተከፈላቸው አሉ፡፡

በሦስቱ ሆስፒታሎች ነው ያልተፈጸመው። ግን ሁለቱ ሆስፒታሎች የስራ ማቆም አድማ አላደረጉም፡፡ እነርሱ ግን ለማክሰኞ ቀጥረናቸው እያለ ቀጠሮውን አንቀበልም ብለው ሙያዊ ሥነ ምግባር በማይፈቅድ መንገድ ስራ የማመጽ ነገር አድርገው ነበር።

ግን የተወሰኑ ልጆች ደግሞ ስራ ገበታ ላይ ተገኝተው ነበር፡፡ ስለዚህ ኦሬዲ ድስከስ አድርገን ጉዳዩን ፈተን ልጆቹ ስራ ጀምረዋል አሁን፡፡ ስራ ላይ ናቸው ሁሉም ” ብለዋል።

ታሰሩ የተባሉት የሆስፒታሉ ባልደረቦች ሳይፈቱ እንዴት ሁሉም ስራ ላይ ሊገኙ እንደቻሉ ምላሽ የጠይቅናቸው ኃላፊው፣ “እነርሱ ያልተገባ አካሄድ የሄዱ አሉ፡፡ ከስነ ስርዓት ውጭ ያልተፈቀደ ሰልፍ የወጡበት ሂደትም አለ፡፡ እንግዲህ ከእስር እንዲወጡ እየተሰራ ያለበት ሂደት አለ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ሠራተኞቹ ቅሬታ ያቀረቡት የአራት ወራት ገደማ ደመወዝ አለመጨመሩን ተከትሎ ነውና የመብት ጥያቄ በመቅረቡ እስርና ድብደባ መፈጸም አግባብ ነው? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ጥያቄ አቅርቧል።

አቶ አንዷለም በሰጡት ማብራሪያ፣ “ሠራተኞቹና ባለሙያዎቹ፣ ‘የፈጸምናቸው ድርጊቶች ትክክል አይደሉም ህዝቡን በድለናል ብለው’ ይቅርታ ጠይቀው ወደ ስራ ገብተዋል፡፡ ከአጠቃላይ ሰራተኞች ውይይት ተደርጎ ጤናማ ስራ ጀምረዋል አሁን” ሲሉ አስተባብለዋል።

ይቅርታ የጠየቁት ማን ናቸው? ሰራተኞቹ ወይስ አሳሪዎቹ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም  ኃላፊው፣ “ሰራተኞቹ ” ሲል የመለሰ ሲሆን፣ ታስረው እያለ እንዴት ይቅርታ ይጠይቃሉ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ በድጋሚ ጥያቄ አቅርቧል።

እሳቸውም፣ “ሙያዊ ክብር በጣሰ መልኩ ሰልፍ የወጡትም ይቅርታ እየጠየቁ ነው ያሉት አሁን፡፡ ‘እነርሱ ናቸው ጥፋተኛ’ በሚል ልከውልናል ቤተሰቦቻቸው” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

የተወሰኑት ሠራተኞች የስራ ማቆም አድማ አድርገው ነበር፤ በአንጻሩ ደግሞ የተወሰኑት ደግሞ ስራ ላይ ተገኝተው ነበር፤ ነገርግን ‘ሌሎቹን አሳምጻችኋል’ በሚል ስራ የገቡትም ናቸው የታሰሩት። ሥራ ላይ እያሉ ታስረው ሳለ “ይቅርታ ጠይቀዋል” መባሉ ምን ማለት እንደሆም በድጋሚ ምላሽ ጠይቀናል።

አቶ አንዷለም በምላሻቸው፣ “ነገሩ እንግዲህ እንደዚሁ ነው። አሁን ውይይት ላይ ነን፡፡ እነርሱ የሰሩት ጥፋት ስለነበረ ነው የተጠየቁት። አሁን ይቅርታ ጠይቀው ውይይት ላይ ነን ችግሩን ለመፍታት” ነው ያሉት፡፡

እንዳጠቃላይ ችግሩን ለመፍታትስ ምን እየተሰራ ነው? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም፣ “አሁን በጀቱ እውቅና አግኝቷል፡፡ ለሰራተኞች የጸደቀላቸው በጀት እጃችን ላይ ገብቷል፡፡ የክፍያ ሂደት ለማመቻቸት ጥረት እየተደረገ ነው” ብለዋል።

“ከክልል ፋይናንስ ገንዘብ እንድለቀቅ ሂደት ላይ እንደሆነና ያው ከዚያ እንደተለቀቀ ክፍያ እንደሚከፈል ተግባቦት ላይ ተደርሷል” ሲሉም አክለዋል፡፡

(ጉዳዩን እስከመጨረሻ የምንከታተለው ይሆናል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia


#UPDATE

" ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ ወደ ማንወጣው ቀውስ እንደምንገባ የቅርብም የሩቁም ሊገነዘበው ይገባል " - የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር

" ሃይል በመጠቀም የመንግስት መዋቅር ለማፍረስ የሚደረግ ህገ-ወጥ እርምጃ ተቀባይነት የለውም " አለ የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ። 

ጊዚያዊ አስተዳደሩ ዛሬ የካቲት 13
/2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ፤ በትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ሰሓርቲ ወረዳ አዲስ አለም ቀበሌ ገበሬ ማህበር የትግራይ ኃይል አባላት በነዋሪ አርሶ አደሮች ላይ ያደረሱትን ጥቃት አውግዟል።

" የተወሰኑ የትግራይ ሰራዊት አመራሮች የጊዚያዊ አስተዳደሩ መዋቅር ለማፍረስ ሲንቀሳቀሱ እየታዘብን ነው " ያለው መግለጫው " በሰሓርቲ ወረዳ የተከሰተው አሳዛኝ ተግባር እንደ አንድ ማሳያ መውሰድ ይቻላል " ብሏል።

" ሰራዊቱ የህዝብ ህልውና ለመጠበቅ እንጂ የአንድ ቡድን የስልጣን ጥማት ለማርካት የተሰለፈ አይደለም " ያለው ጊዚያዊ አስተዳደሩ " ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ ወደ ማንወጣው ቀውስ እንደምንገባ የቅርብም የሩቁም ሊገነዘበው ይገባል " ሲል አስጠንቅቋል።

" ማንኛውም የህግ ወይም የአስራር ክፍተት ሲኖር የሚሊሻና የፓሊስ ሃይል ከህዝባቸው በመተባበር የሚፈቱት እና የሚያርሙት እንጂ ሰራዊት ወደ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ማሰማራት የሚያስገድድ ሁኔታ ፈፅሞ እንደሌለ የለም " ሲል ገልጿል።

" ይህንን ህገ-ወጥ አካሄድ የሚያበረታቱ እና የሚያግዙ ፓለቲከኞች እና የሰራዊት አመራሮች አደብ እንዲገዙ " ሲልም አስጠንቅቋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            


" አንዳንዴ ቀን ሙሉ የሰራነውን ገንዘብ ያለ አንዳች ጥፋት ተቀጥተን ባዶ እጃችንን ቤታችን እንገባለን ! " - አሽከርካሪዎች

በአዲስ አበባ በርካታ አሸከርካሪዎች ከትራፊክ ቁጥጥር ጋር በተያያዘ ወቀሳ እና ቅሬታ ያቀርባሉ።

ለአብነትም ፤ አንዳንድ የትራፊክ ፖሊስ አባላት ያለ አንዳች ምክንያት እየሄደ ያለን ተሽከርካሪ ማስቆም ፤ ጥፋት ሲያጡ ጥፋት ወደ መፈለግ መግባት ከዛ የቅጣት ወረቀት ላይ መፃፍ ስራቸው ያደረጉ አሉ።

ከዚህ ባለፈ ለዜጎች ክብርን ያለመስጠት ፤ ዝቅ ብሎ አለማገልገል፣ አሽከርካሪዎችን መናቅ ፣ ምንም የምታመጡት ነገር የለም ማለት፣ በስርዓት አለማናገር፣ ጥፋትን አለማስረዳት ... የመሳሰሉ ባህሪዎችም ይታይባቸዋል።

አንዳንድ ትራፊክ ፖሊስ አባላት የትራፊክ ሁኔታውን ማሳለጥ ሲገባቸው እንቅፋትም ይሆናሉ።

መሃል መንገድ ላይ፣ አደባባይ ላይ ሳይቀር የትራፊክ እንቅስቃሴን በሚያውክ መልኩ ተሽከርካሪ አስቁመው መንገድ እንዲዘጋጋም ያደርጋላ።

በተለያየ ጊዜ ቃላቸውን አሽከርካሪዎች ቁጥጥር መኖሩን ግዴታ ቢሆንም በአግባቡ እና በስርዓት መሄን እንዳሚገባው ያነሳሉ።

" ቅጣቱ ለተላለፈ ደንብ መቅጫ ሳይሆን ከዜጎች ገንዘብ መሰብሰቢያ ሆኗል " የሚሉት የሜትር ታክሲ አገልግሎት የሚሰጡ አሽከርካሪዎች " ቀን ሙሉ የሰራነውን አንዳንዴ ያለ አንዳች ጥፋት ተቀጥተን ባዶ እጃችንን ቤታችን እንገባለን " ብለዋል።

" በተለይ የቅጣት ብሩ ከጨመረ ወዲህ በሆነው ባልሆነው መኪና እያስቆሙ መቅጣት ተበራክቷል " ሲሉም ገልጸዋል።

በተላይ አዳዲስ በተሰሩ የመንገድ ዳሮች ማቆም ስላማይቻል ስራቸውን ለመስራት እንደተቸገሩ ሆኖ ሳለ ያለ አግባብ በትራፊክ ፖሊስ እና የትራፊክ ተቆጣጣሪዎች የሚጣለው ቅጣት ቀን ሙሉ ለፍተው ማታ ባዶ እጃቸውን ወደ ቤት እንዲገቡ እያስገደደ መሆኑን አመልክተዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia


#AddisAbaba

🚨" ባለፉት 6 ወራት ብቻ ከ1 ሚሊየን 293 ሺህ በላይ አሽከርካሪዎች በትራፊክ ፖሊስ አባላት ብቻ  ተቀጥተዋል !! "

እንደ ሸገር ሬድዮ ዘገባ ፥ በአዲስ አበባ በየቀኑ በአማካይ 7,183 አሽከርካሪዎች በትራፊክ ደንብ መተላለፍ በትራፊክ ፖሊስ ብቻ ይቀጣሉ።

ይህ በሌሎች የትራፊክ ደንብ ታላፊዎችን የሚቀጡትን አይጨምርም።

ባለፉት በ6 ወራት ውስጥ በተለያዩ የደምብ መተላለፍ ጥፋቶች ከ1 ሚሊየን 293 ሺህ በላይ አሽከርካሪዎች በትራፊክ ፖሊስ አባላት ብቻ  ተቀጥተዋል፡፡

ይህም በየቀኑ 7,183 አሽካርካሪዎች መቀጣታቸውን ያሳያል፡፡

በሌላ በኩል " የታጠፈ የደበዘዘ የተፋፋቀ እና በአጠቃላይ ለዕይታ ግልፅ ያልሆነ ሰሌዳ ለጥፈው በሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር አደርጋለሁ " ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ተናግሯል፡፡ 

ባለፈው በጥር ወር ብቻ ለዕይታ ግልፅ ያልሆነ ሰሌዳ ለጥፈው በሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ላይ በተደረገ ቁጥጥር ከ2,100 በላይ አሽከርካሪዎች ተቀጥተዋል ተብሏል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ በየጊዜው እየተባባሰ ለመጣው የመንገድ ትራፊክ አደጋ ልዩ ልዩ የደምብ መተላለፍ ጥፋቶች እንደ ምክንያትነት የሚገለጹ ቢሆንም ለእይታ ግልፅ ያልሆኑ የተሽከርካሪ ሰሌዳዎች መበራከት ለአደጋ ብቻ ሳይሆን የወንጀል ስጋት እየሆኑ መምጣታቸውን ፖሊስ አስረድቷል፡፡

በየጊዜው የታጠፈ የደበዘዘ እና የተፋፋቀ ሰሌዳ ለጥፈው በሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ እየተወሰደ ቢሆንም በሚፈለገው ደረጃ ችግሩን መቅረፍ አልተቻለም ያለው ፖሊስ አሁንም ጠንካራ የቁጥጥርና አደርጋለሁ ብሏል፡፡

ለዕይታ ግልፅ ያልሆነ ሰሌዳ ለጥፈው በሚንቀሳቀሱ አሽከርካሪዎች ላይ ጥፋቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሆነ 1500 ብር ያስቀጣል፡፡

መረጃው የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።

@tikvahethiopia


#ችሎት

" ንብረታችሁ ሊወረስ ነው " በማለት ባለሃብቱን አስፈራርተው በቼክ ገንዘብ ሲቀበሉ በፀጥታ አካላት የተያዙ 4 ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀረቡ።

ተጠርጣሪዎቹ በብሔራዊ መረጃ ደህንነትና በፌደራል ፖሊስ ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።

አዲሱ የንብረት ውርስ አዋጅ ወደ ስራ ባልገባበትና በፖሊስ ምርመራ ባልተጀመረበት ሁኔታ ላይ ተጠርጣሪዎቹ " የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት እና የፋይናንስ ደህንነት ሰራተኞች ነን " በማለት አንድን ባለሃብት አስፈራርተው 5 ሚሊየን ብር ጉቦ ተደራድረው የ1 ሚሊየን ብር ቼክ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል ተብሏል።

ተጠርጣሪዎቹ በተለያዩ መዝገቦች ፍ/ቤት ቀርበው ጉዳያቸው ታይቷል።

በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት የቀረቡት ተጠርጣሪዎች ፦

1ኛ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በሞጆ ደረቅ ወደብ የጥበቃ ኃላፊ ኢኒስፔክተር ሰለሞን ካሳ፤

2ኛ በግል ስራ የሚተዳደሩት ተስፋ ሀታኡ ገምቴሳ፣

3ኛ ጁዋር አወል ጀማል

4ኛ በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የአይቲ ባለሙያ ረ/ኢ/ር ኩሉሌ ጉዮ ቦሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ናቸው።

አዲሱ የንብረት ውርስ አዋጅ ወደ ስራ ባልገባበት፣ በፖሊስ ምርመራ ባልተጀመረበትና በጋዜጣ ባልታወጀበት ሁኔታ ላይ ተጠርጣሪዎቹ " ደዘርት ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር " ለተባለው ድርጅት ባለቤት አቶ ቢኒያም ሀደር እና ወኪላቸው ስራ አስኪያጅ መሐመድ እስማኤል አሊ ለተባሉት ግለሰቦች ስልካቸው ላይ ይደውላሉ።

ጥር 05 ቀን 2017 ጀምሮ ደግሞ በተለያዩ ቀናት ባለሃብቶቹን በአካል በማግኘት " የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት እና የመረጃ ደህንነት ሠራተኞች ነን " በማለት ይተዋወቃሉ።

" በአዲሱ ንብረት ማስመለስ አዋጅ መሰረት በንብረታችሁ ላይ እና የባንክ የሂሳብ እንቅስቃሴዎች ላይ ምርመራ ተደርጎ ንብረታችሁ ይወረሳል፤ የባንክ ሂሳብ እንቅስቃሴ እናግዳለን " በማለት ሲያስፈራሩ እንደነበረ በጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ላይ ተብራርቷል።

በተለይ መንግስት ሃብታቸውን እንዳይወርስባቸው እንደሚያደርጉ በመግለጽ ለዚህ ማስፈጸሚያነት የሚውል 5 ሚሊየን ብር በመደራደር በቅድሚያ 20 ሺህ ብር በባንክ ሂሳብ እንዲሁም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቦሌ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ቦሌ ሚካኤል አኑዋር ምግብ ቤት ውስጥ አንድ ሚሊየን ብር የተዘጋጀ ቼክ ከደርጅቱ ወኪል ከሆነው ከአቶ ማሐመድ እስማኤል አሊ እጅ ሲቀበሉ በክትትል ላይ በነበሩ ጸጥታ ኃይሎች መያዛቸውን የፌደራል ፖሊስ መርማሪ አሳውቋል።

መርማሪ ፖሊስ በዚህ መልኩ ተጠርጣሪዎቹ የሙስና ወንጀል የምርመራ ማጣሪያ ስራ እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን ከእነዚህ ተጠርጣሪዎች መካከል ኢኒስፔክተር ሰለሞን ካሳ በሚመለከት የምርመራ መዝገቡን ለዐቃቤ ህግ ማስረከቡን ለጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ፖሊስ አስታውቋል።

በፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሪክቶሬት ዐቃቤ ህግ በጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርቦ የምርመራ መዝገቡን ከዐቃቤ ህግ መረከቡን ጠቅሷል።

ዐቃቤ ህግ የምርመራ መዘገቡን ተመልክቶ በተገቢው ሁኔታ ክስ ለመመስረት እንዲያስችለው የ15 ቀን የክስ መመስረቻ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።

በተጨማሪም ዐቃቤ ህግ በወንጀል ድርጊት ሊገኝ ከታሰበው የገንዘብ መጠን ወይም የደረሰው ጉዳት አንጻር ሲታይ ከ10 ዓመት በላይ የሚያስቀጣና ዋስትና የሚያስከለክል መሆኑን ጠቅሶ ፤ የተጠርጣሪው ዋስትናው ታልፎ ክስ እስኪመሰረት ባሉበት በእስር እንዲቆዩ እንዲፈቀድለት ጠይቋል።

ተጠርጣሪው የዐቃቤ ህግ ክስ መመስረቻ ጥያቄን በመቃወም ዋስትና እንዲፈቀድለት ጠይቋል።

የግራ ቀኝ ክርክሩን የመረመረው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ የተጠርጣሪውን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ በማድረግ ለዐቃቤ ህግ የዘጠኝ ቀናት ክስ መመስረቻ ጊዜ ፈቅዷል።

መረጃው የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ነው።

@tikvahethiopia


#Tigray

ትናንተ የካቲት 12 /2017 ዓ.ም በትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ሰሓርቲ ወረዳ አዲስ አለም ቀበሌ በነዋሪዎችና በአከባቢው በሚገኘው የትግራይ ኃይል አባላት መካከል ግጭት ተከስተዋል።

በግጭቱ ምክንያት በ20 የቀበሌው ነዋሪዎችና ቁጥራቸው ባልታወቀ የትግራይ ኃይል አባላት ላይ ጉዳት ደርሷል።

ያጋጠመ ሞት የለም።

ግጭቱ እንዴት እና በምን ምክንያት አጋጠመ ? 

በአዲስ አለም ቀበሌ ሁለት አስተዳዳሪዎች አሉ። አንዱ የቆየ ሲሆን ሌላው ደግሞ በጊዚያዊ አስተዳደሩ የተሾመ ነው።

ሁለቱም ማህተም ይዘው በየፊናቸው " እኔ ነኝ ህጋዊ የቀበሌው አስተዳደር " በማለት ህዝቡን ለሁለት መክፈላቸው ነዋሪዎች ይናገራሉ።

ከዚህ ጋር በተያያዘ " ህዝቡ አማርሮ እንድንታደገው ጠይቆናል አዛዦቻችንም ይህንን እንድንፈፅም ልከውናል" ያሉ 9 የሰራዊት አባላት ወደ ቀበሌው ደርሰው ሁለቱ አስተዳዳሪዎች ማህተም እንዲያስረክቡ ይጠይቃሉ።

" ታስረክባላችሁ አናስረክም " በሚል እልህ በነዋሪዎች እና የትግራይ ኃይል አባላት መካከል ግጭት ይነሳል። ነዋሪውም ደንጋይ መወርወር ይጀምራል። የትግራይ ኃይል አባላትም ጥይት ይተኩሳሉ።

በዚህ መካከል በተተኮሰ ጥይት አንድ ሰው እጁ ላይ ተመትቶ ሆስፒታል ሲገባ ሌሎች 20 ሰዎች ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል። በትግራይ ኃይል አባላት ላይም ጉዳት የደረሰባቸው አሉ። 

የወረዳው አስተዳደር ለክልሉ የሰላም እና የፀጥታ ቢሮ የካቲት 11/2017 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ 13 ታጣቂዋች ወደ ወረዳው አስተዳደር በመምጣት የጊዚያዊ አስተዳደር ማህተም እና የፅህፈት ቤት ቁልፍ እንዲያስረክቡዋቸው መጠየቃቸውን እና ይህንን ህገ-ወጥ ተግባር እንዲቆም ጠይቋል።

ከህወሓት ወደ ሁለት መሰንጠቅ በኋላ የክልሉ ዋና ከተማ መቐለ ጨምሮ በተለያዩ የገጠር እና የከተማ አስተዳደሮች ተመሳሳይ ስልጣን ያላቸው ሁለት አሰተዳዳሪዎች መስማት የተለመደ ነው።

በአንዳንድ ዞኖች ያሉ ወረዳዎች በጊዚያዊ አስተዳደሩ እና የደብሪፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት የተሾሙ አስተዳዳሪዎች ለሁለት ተከፋፍለው ይተዳደራሉ።

የትግራይ መሪዎች በተለይም የህወሓት አመራሮች ከዚህ መሰል ህዝብ የሚከፋፍል አደገኛ ተግባራቸው እንዲቆጠቡ የሚመክሩ አስተያየት ሰጪዎች ፤ የትግራይ ኃይል አባላት አንዱን ቡድን ደግፈው ሌላው ቡድን ማውገዝ ተጨማሪ ቀውስ እና ጥፋት ስለሚያስከትል የገለልተኝነት ሚናቸው እንዱወጡ አበክረው እያሳሰቡ ናቸው።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia 


#DStvEthiopia

የሳምንቱ ምርጥ ጨዋታ !

ማን ሲቲ በኢመሬትስ ስታዲዩም ከሊቨርፑል ጋር ይጫወታል!
⚽️ ከ60 ጨዋታዎች 26ቱን ሊቨርፑል ሲያሸነፍ 12ቱን ማን ሲቲ ድል ማረግ ችሏል! 22 ጨዋታዎችም አቻ ወጥተዋል!

61ኛውን ጨዋታዎቸውን የሚያደርጉት ሁለቱ ቡድኖች ማን 3 ነጥብ ማሸነፍ ይችላል?

🏆 ሊቨርፑል ከአርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ማስፋት ይችላል?
👉 ይህንን ድንቅ ፍልሚያ ጨምሮ ሌሎች የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን በቀጥታ በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ይመልከቱ።

🎊 እስከ መጋቢት 22 ባሉት ቀናት አሁን ካሉበት ጎጆ ፓኬጅ የቀጣዩን ቤተሰብ ፓኬጅ፣ የአንድ ወር ሙሉ ክፍያ ሲከፍሉ፣ ዲኤስቲቪ ደግሞ የሜዳ ፓኬጅን ፓኬጅ በነፃ ከፍ ያደርጎታል
ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh

#ሁሉምያለውእኛጋርነው


“ብዙ ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆኑ ነገሮች ይኖራሉ። ነገር ግን ሁሉም ነገር በትክክል ከተካሄደ ሊበቃን ይችላል” - ምክትል ኮሚሽነር ሒሩት ኃ/ስላሴ

ከቀናት በፊት አንድ አመት ተጨማሪ የሥራ ጊዜ በፓርላማ የተሰጠው የ3 አመታት የሥራ ዘመኑን ነገ ይጠናቅቅ የነበረው የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የ3 አመታት ክንውንና የቀጣይ አቅጣጫውን በተመለከተ ዛሬ በስካይ ላይት ሆቴል መግለጫ ሰጥቷል።

በዚህም ኮሚሽኑ የተሰጠው ተጨማሪ ጊዜ በቂ ነው? አጠቃላይ ሥራውስ መቼ ይጠናቀቃል? በሚል ከጋዜጠኞች ለቀረላቸው ጥያቄ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገብረ ስላሴ፣ “ብዙ ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆኑ ነገሮች ይኖራሉ። ነገር ግን ሁሉም ነገር በትክክል ከተካሄደ ሊበቃን ይችላል” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

"ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆኑ ነገሮች አሉ” ያሉት፣ ምክትል ዋና ኮሚሽነሯ ይህን ይበሉ እንጂ ከቁጥጥር ውጪ ስለሆኑ ነገሮችን በዝርዝር አልገለጹም። 

11 ኮሚሽነሮች እንዳሉና ሥራውን ተባብሮ ለመስራት እንደሚቻል ገልጸው፣ "ተጨማሪ አንዳንድ ሥራዎችን የሚያቃልሉ ነገሮች በመንግስትም ሆነ በሌሎች ከተፈጠሩልን ስራችንን ያጣድፋል" ብለዋል።

“ምክክር በዚህ ሰዓት ውስጥ ተመካክራችሁ በዚህ ጊዜ ውስጥ ውሳኔ ስጡ የሚባልበት አይደለም። ህዝቦች ቁጭ ብለው ጊዜ ውስደው ተመካክረው የሚወሰኑት ሂደት ስለሆነ በቀላሉ የሚወሰኑ አጀንዳዎች ይኖራሉ። ጊዜ የሚፈጁም ሊኖሩ ይችላሉ” ሲሉም አስረድተዋል።

አክለው፣ “በዚህ ምክንያት በትክክል በዚህ ጊዜ ውስጥ ያልቃል ለማለት ያስቸግራል” ብለው፣ ሆኖም ግን ኮሚሽኑ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሥራውን ለመጨረስ ጥረት እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

የተወሰኑ ፓርቲዎች ባልተሳተፉበት የምክክሩ ሂደቱ ሙሉ ይሆናል? በሚል ለቀረበው ጥያቄም፣ ፓርቲዎች በምክክሩ እንዲሳተፉ ጥረት መደረጉን ገልጸው፣ “ዳተኛ ሆነው” ያልገቡት እንዲገቡ ደግሞ ንግግር እንደተደረገ፣ አሁንም ጥረቱ እንደሚቀጥል አስረድተዋል። 

ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር) በበኩላቸው፣ በመግለጫው ባደረጉት ንግግር በሕጋዊ ከተመዘገቡ ወደ 70 ፓርቲዎች 57 የሚሆኑት ከኮሚሽኑ ጋር እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

ከታጣቂዎች ጋር ንግግር ተደርጎ እንደሆን ከጋዜጠኞች ጥያቄ ቀርቦላቸው በሰጡት ማብራሪያ ዋና ኮሚሽነሩ፣ የፋኖ ታጣቂዎችን እንዳነጋገሩ፣ “ሊከፋፍለን ነው” በሚል ስማቸው እንደሚነሳ አስታውሰው ተከታዩን ብለዋል።

ምን አሉ?

“ሀገራዊ ምክክሩ ማንንም መከፋፈል አይመኝም። የሚመኘው፣ መደረግ አለበት ብሎ የሚያምነውም ሁሉም ተሳታፊ እንዲሆን ነው።

እኔ ፋኖ መሆናቸውን አላውቅም አንድ ታጣቂ ቡድን ራሳቸው ደውለውልኝ ‘የምክክር ኮሚሽኑን ሥራ ተገንዝበናል። ‘በዚህ መሠረት ወደ ትግሉ የገባንበትን አጀንዳ ወደ እናንተ አምጥተን ወደ ውይይት የሚቀርብ ከሆነ መሳሪያችንን ለማስቀመጥ ዝግጁ ነን’ የሚል በቀጥታ በግሌ አቅርበውልኛል። ይሄን ሰው በተደጋጋሚ አግኝተዋለሁ። 

እዛ ላሉትም የደኅንነት፣ አካላት በስልክ አግኝቼ እነዚህ ሰዎች በአግባቡ መሠረት ሰላማዊ ጥበቃ ተደርጎላቸው አጀንዳቸውን የሚያመጡበት መንገድ እንዲመቻች ይሄን አስተላልፌያለሁ። 

ይህን ሳደርግ ለሀገራዊ ምክክር ጉባዔ በማሳወቅ ነው። እንጂ የፋኖ ናቸው ብዬ የተናገርኩት አንድም የለም” ብለዋል።

በሌላ በኩል በዛሬው መግለጫ የኮሚሽኑ የ3 አመታት ክንውኖች በኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር) በዝርዝር የቀረቡ ሲሆን፣ ይህንኑ ሪፓርት ከቀናት በፊት አድርሰናችሁ ነበር።

(ተጨማሪ ዘገባ በቀጣይ የምናቀርብ ይህናል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia


#ትግራይ

🚨“ በአንድ አመት ውስጥ ከ40 በላይ ሰዎች ሞተዋል” - በአይደር ሆስፒታል የዲያሌሲስ ዩኒት

➡️ “ ጳውሎስ ሆስፒታል 400 ብር የሚሸጠውን መድኃኒት እኛ 1200 ብር ነው የምንገዛው ” - የትግራይ ክልል ኩላሊት ህሙማን ማኀበር

በትግራይ ክልል ያሉ የኩላሊት ህሙማን ወገኖች በመድኃኒት እጥረት ሳቢያ የዲያሌሲስ ክትትል ለማድረግ በመቸገራቸው ለሞት መዳረጋቸውን የክልሉ ኩላሊት ህሙማን ማኀበርና አይደር ሆስፒታል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።

በሆስፒታሉ የዲያሌሲስ ዩኒት አስተባባሪ አቶ ጥዑም መድኅን በሰጡን ቃል፣ “ ህሙማኑ ከውጪ ፋርማሲ ነው መድኃኒት የሚገዙት። ከመንግስት ፋርሚሲ አይገኝም ” ብለዋል።

አቶ ጥዑም መድኅን በዝርዝር ምን አሉ ?

“ በአንድ ዓመት ውስጥ ከ40 በላይ ሰዎች ሞተዋል። ብዙዎቹ የሚሞቱት የህክምና ክትትል ባለማድረጋቸው ነው። ክትትል የማያደርጉት ደግሞ የገንዘብ እጥረት ስላለባቸው ነው።

ችግሩ ብዙ ነው። በትግራይ ክልል ደረጃ አንድ የዲያሌሲስ ሴንተር ብቻ  ነው ያለው በአይደር ሆስፒታል። ለዛውም መንግስት ምንም ድርሻ የለውም መድኃኒት አያቀርብም።

በ2013 ዓ/ም ጦርነት ከተጀመረ በኋላ በጣም ሰፊ ችግር ነው ያለው። በጦርነቱ ወቅትም ብዙ ሰዎች ናቸው የሞቱት። አሁንም የመድኃኒት እጥረት አለ ሰላም ቢሆንም።

መድኃኒት በትግራይ አይገኝም። ብዙ ጊዜ ከውጪ፣ በብላክ ማርኬት ከአዲስ አበባ ነው የሚገዙት። ዋጋውም ውድ ነው። ለአንድ እጥበት 3900 ብር ነው ከሌሎች መድኃኒቶች ወጪ ውጪ።

በሆስፒታሉ 44 ህሙማን አሉ ክትትል የሚያደርጉ። ከ44ቱ ወደ 4 የሚሆኑት ‘አንችልም’ ብለው አቁመዋል። 40ዎቹ አሉ። 

ግን በሳምንት ሦስት ጊዜ ኩላሊታቸውን መታጠብ ቢኖርባቸውም የገንዘብ አቅም ስለሌላቸው በሳምንት አንድ ጊዜ፤ ሁለት ጊዜ፣ ቀሪ ስምነቱ ደግሞ የባሰ የገንዘብ እጥረት ስላለባቸው በሁለት ሳምንት ይታጠባሉ ”
ብለዋል።

የትግራይ ክልል ኩላሊት ህሙማን ማኀበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ሐፍቶም አባዲ በበኩላቸው “ አርቲፊሻል ኪዲኒ ዲያላይዘርን ከ8 እስከ 10 ጊዜ ነው እያጠብን ነው ስንጠቀም የነበረው በጦርነቱ ጊዜ” ነው ያሉት።

“ በዚያ ምክንያት የፕሪቶሪያ ስምምነት እስከሚፈረም ድረስ በሁለት ዓመት ከ100 በላይ ህሙማን ሞተዋል። ከ100 በላይ የማኀበሩ ታካሚ ህሙማን ውስጥ 14 ሰዎች ብቻ ነበሩ በእድል የቀሩት ” ሲሉም አስታውሰዋል።

የማኀበሩ ሥራ አስኪያጅ አክለው ምን አሉ ?

“ አንድ ታካሚ ለአንድ ዲያሌሲስ ከ35,000 እስከ 40,000 ነው በወር የሚያወጣው ለዲያሌሲስ ብቻ። ለዚህም አቅም የለውም ሰው። ኮስቱ በጣም ከፍተኛ ነው።

ህክምናው የጀመሩ ህሙማንም አቅም ስለሌላቸው ትንሽ ተከታትለው አቋርጠው ነው የሚሄዱት። ዲያሌሲስ ካቋረጡ ደግሞ የሚጠብቃቸው ሞት ነው።

ከፕሪቶሪያ ስምምነቱ በኋላ ብዙ ሰዎች ሞተውብናል። ሦስት ጊዜ ማድረግ ሲጠበቅባቸው በገንዘብ እጦት በሳንምት አንድ ጊዜ ዲያሌሲስ የሚያደርጉ አሉ። በዚሁ ምክንያት ብቻ እኔኳ የማውቃቸው ወደ 5፣ 6 ሰዎች ሞተዋል።

ኮስቱ እንዳለ ታካሚው ላይ ነው ያረፈው። ታካሚው ካለው ይከፍላል ከሌለው ያው የሚጠብቀው ሞት ነው። መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ለዲያሌሲሱ ድጋፍ ያድርግልን። 

ለምሳሌ ፦ እነ ጳውሎስ፣ እነ ሚኒሊክ ሆስፒታሎች ኮስታቸው በጣም ፌር ነው መንግስት ስለሚደግፋቸው።

እኛ ግን የግል ሆስፒታሎች ከሚከፍሉት በላይ ነው እየከፈልን ያለነው በመንግስት ሆስፒታል ላይ ሆነን። መንግስት መደገፍ ያለበትን ራሳችን ወጪ እያደረግን ነው የምናደርገው።

ጳውሎስ ሆስፒታል 400 ብር የሚሸጠውን መድኃኒት እኛ 1200 ብር ነው የምንገዛው። በመንግስት ሆስፒታሎች የሚገኙትን መድኃኒቶች መንግስት ያቅርብልን”
ሲሉ ተናግረዋል።

ከሰሜኑ ጦርነት በፊት የመድኃኒት ድጋፍ ሲያደርግላቸው የነበረው ሱዳናዊ ድርጅት በጦርቱ ሳቢያ ውሉና ድጋፉ እንደተቋረጠ፣ ከሁለት አመታት በላይ የህክምና የሚደረገው ከህሙማኑ በሚሰባሰብ ገንዘብ መሆኑን ማኀበሩና ሆስፒታሉ አስረድተዋል።

እስከ ጥር 2017 ዓ/ም መጀመሪያ ድረስ መድኃኒት የሚገዛው ከህሙማኑ በሚዋጣ ገንዘብ እንደነበር፣ አሁን አንድ መድኃኒት አቅራቢ ድርጅት ውል ገብቶ በሆፒታሉ በኩል የመድኃኒት አቅርቦት እንደጀመረ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia


" ምርጫ ማሸነፌ እንደወንጀል ታይቶ 1 ዓመት ለሚጠጋ ጊዜ ያለአግባብ ታስሪያሁ " - አቶ አማንያስ ጉሹና

ከሰሞኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤዉን አካሂዶ ነበር።

በዚህም ጉባኤ ላይ የኢዜማው ተመራጭ ጉባኤ እንዳይሳተፉ መደረጋቸውን ገልጸዋል።

በክልሉ የዘይሴ ብሔረሰብ ተመራጭ የሆኑት አቶ አማንያስ ጉሹና " ያለአግባብ 4 ወራት ከታሰርኩ በኋላ ያለመከሰስ መብቴ ተነስቶ ለተጨማሪ 7 ወራት በእስር ላይ እንዲቆይና በምክር ቤት ጉባኤ እንዳልሳተፍና ከመንግስት ስራም እንዲሰናበት ተደርጌያለሁ " ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

አቶ አማንያስ ፤ " ብሔረሰቡ ያለዉን የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና የመዋቅር ጥያቄ በተለያዩ ጊዜያት ሲጠይቅ የቆዬ ቢሆንም ተገቢዉን ምላሽ ባለማግኘቱ በ6ኛ ሀገራዊ ምርጫ የኢዜማ ፓርቲን በመምረጡ ከምርጫዉ ማግስት ጀምሮ በፓርቲው በአባላትና አመራሮች ላይ የእስርና የማሳደድ ተግባር በይፋ ማካሄድ ተጀምሯል " ብለዋል።

" በአሁኑ ሰዓት ከ2 መቶ በላይ የፓርቲዉ አባላትና አመራሮች በጊዜ ቀጠሮ ፍርድ ቤት እየተመላለስን ነዉ " ሲሉ አስረድተዋል።

" ተወዳድረን ምርጫ ማሸነፋችን ሃጥያት ባልሆነበት በገዢዉ ፓርቲ አመራሮች በግልም ሆነ በብሔረሰቡ ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ እየደረሰብን ነዉ " የሚሉት አቶ አማንያስ " ለአብነትም የደቡብ ክልል ምክር ቤት ሰሞኑን ባካሄደዉ 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ የዜይሴ ብሔረሰብ ያለተወከለበት እና ከሌሎች ብሔሮች ጋር በክልላዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከሌሎች ተሳታፊዎች ጋር ያልተሳተፈበት ጉባኤ ነዉ " ሲሉ ወቅሰዋል።

" በዚሁ የፖለቲካ ተፅእኖ ምክንያት ሀገሬን ለ17 ዓመታት ካገለገልኩበት የመምህርነት ሙያ እንድሰናበት ተደርጌያለሁ " ያሉት አቶ አማንያስ " ወደ ስራ ገበታዬ እንዲመልሱኝ ደጋግሜ ብጠይቅም 'ያለመከስ መብትህ ሳይነሳ መመለስ አትችልም' የሚል ምላሽ ከትምህርት አስተዳደር መዋቅሮች ተሰጥቶኛል " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የኢዜማ ፓርቲ የሕግና አባላት ጉዳይ ደህንነት መምሪያ ኃላፊ አቶ ስዩም መንገሻን በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገራቸዉ ሲሆን " በዘይሴ ብሔረሰብ የሕዝብ ተመራጭ አቶ አማኒያስ ጉሹና ላይ የተፈፀመዉ ጉዳይ ኢ-ሕገመንግስታዊ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

በወቅቱ ያለመከሰስ መብታቸዉ ሳይነሳ ታስረዉ መቆየታቸዉንና በአካባቢዉ ያለዉን የሰብአዊ መብት ረገጣና የፖለቲካ ተፅእኖ ለኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በፅሑፍ ማሳወቃቸዉንና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት ግብረ ሃይል ተቋቁሞ ወደአከባቢዉ ማቅናቱንና የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ ስለመሆኑ አንስተዋል።

" ከስራ የተሰናበቱበትና ወደ ስራ እንዳይመለሱ የሚደረግበት አግባብ ከፍተኛ የፖለቲካ ተፅእኖ ያለበት ነዉ " ያሉት አቶ ስዩም ፤ የኢዜማ ፓርቲ በአከባቢው ያለዉን የፖለቲካ ጫናና ተያያዥ ጉዳዮችን ለኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በጽሑፍ አቅርቦ ባለድርሻ አካላት የተካተቱበት ግብረሃይል ተዋቅሮ ቦታዉ ድረስ በመሄድ በሰጠዉ አቅጣጫ መሠረት አቶ አማንያስ በዋስ እንዲፈቱ መደረጉን ተናግረዋል።

አቶ አማንያስ " ወደ ስራ ገበታዬ እንዲመልሱኝ በተደጋጋሚ ብጠይቅም የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤትና የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ' ያለመከሰስ መብትህ እስካልተነሳ ድረስ መመለስ አንችልም ' ተብያለሁ " በሚል ላነሱት ቅሬታ ከከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ጽ/ቤትና ከጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ ለጊዜው አልተሳካም።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia


" ዜለንስኪ ጥሩ የነበረበት ብቸኛው ነገር ባይደንን ማታለል ብቻ ነበር " - ፕሬዜዳንት ትራምፕ

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሊድሚር ዘለንስኪን " ትሁትና ውጤታማ ኮሜዲያን ነው " ሲሉ ወረፏቸው።

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትሩዝ በተባለው የማህበራዊ ትስስር ገጻቸው የዩክሬኑን ፕሬዝዳንት ቮሊድሚር ዘለንስኪን " ያለ ምርጫ የተቀመጠ አምባገነን ነው " ብለዋል።

ትራምፕ ዩክሬን ከአሜሪካ ያገኘችውን ድጋፍ በውድ ማዕድናት እንድትከፍል እንደሚፈልጉ ተናገሩ
ትራምፕ " ትሁቱና ውጤታማ ኮሜዲያን ዘለንስኪ አሜሪካን 350 ቢሊየን ዶላር በማስውጣት መጀመር ያልነበረባቸው እና የማያሸንፉት ጦርነት ውስጥ ገብተዋል " ብለዋል።

" ዩክሬን ጦርነቱን ያለ አሜሪካ እና ትራምፕ በፍፁም መቋቋም አትችልም " ሲሉም ገልጸዋል።

ዜለንስኪ ከላክንለት ገንዘብ ግማሹ " የጠፋ " መሆኑን አምኗል ያሉት ትራምፕ " ምርጫ ለማድረግ ፈቃደኛ አይደለም፣ በዩክሬን የሕዝብ ዘንድ ያለው ተቀባይነት በጣም ዝቅተኛ ነው " ብለዋል።

" ዜለንስኪ ጥሩ የነበረበት ብቸኛው ነገር ባይደንን ማታለል ብቻ ነበር " ሲሉም ገልጸዋል።

" ያለ ምርጫ የተቀመጠ አምባገነን ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ በፍጥነት መንቀሳቀስ ይኖርበታል፤ ካልሆነ ግን የሚያተርፈው ሀገር አይኖርም " ብለዋል።

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አክውም " ዩክሬንን እወዳለሁ፣ ነገር ግን ዘለንስኪ አስከፊ ስራ ሰርቷል፣ ሚሊዮኖችም ያለምክንያት ሞተዋል እየሞቱም ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሊድሚር ዘለንስኪ " ዶናልድ ትራምፕ የሀሰት መረጃ ውስጥ እየኖሩ ወይንም በሀሰት መረጃ እየተነዱ ነው " ብለዋል።

ዩክሬን ከሩስያ ጋር ጦርነቱ ውስጥ እንዳለች ይታወቃል።

መረጃው የአል አይን ኒውስ ነው።

@tikvahethiopia


ልጆች በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ማንበብ እንዲማሩ የሚያግዝ አዝናኝ እና አሳታፊ ጨዋታ!

ኪዩሪየስ ሪደር ልጅዎ የተለያዩ ሀገርኛ ቋንቋዎችን ልክ እንደ አማርኛ፣ ኦሮምኛ፣ ሶማልኛ እና ትግረኛ በቀላሉ ማንበብ እና ማወቅ እንዲችሉ በጨዋታ እና በተረት መልክ እያዋዛ ፊደላትና ቃላቶችን የሚያስተምር መተግበሪያ ነዉ!

ከ”Play Store” ካወረዱ በኋላ ቋንቋ በመቀያየር ልጅዎን ከተለያዩ ሀገርኛ ቋንዎች ጋር ያስተዋውቋቸው!!

እነዚህን ሊንኮች በመጠቀም መተግበሪያውን በነጻ አሁነኑ አውርደው ከልጅዎ ጋር ይማሩ!

ይሄን ይንኩት 👉🏼 አማርኛ
ይሄን ይንኩት 👉🏼 ኦሮምኛ
ይሄን ይንኩት 👉🏼 ሶማልኛ
ይሄን ይንኩት 👉🏼 ትግረኛ


#ለልጅዎ #ከፊደል_ይጀምሩ

Показано 14 последних публикаций.