TIKVAH-MAGAZINE


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን +251913134524

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


''በርካታ የልብ ታማሚዎች ወረፋ ሳይደርሳቸው ህይወታቸውን ያጣሉ '' - ዶክተር ፈቀደ አግዋር

በኢትዮጵያ የልብ ህክምና በተሟላ ሁኔታ እየተሰጠ የሚገኘው አዲስ አበባ ከተማ በመሆኑ ወረፋ ሳይደርሳቸው ህይወታቸው የሚያልፉ የልብ ታማሚዎች መኖራቸው ይነገራል።

ዶክተር ፈቀደ አግዋር በኢትዮጵያ የልብ ህክምና ማዕከል ''የልብ ቀዶ ጥገና'' ሀኪም ናቸው። 800 የልብ ቀዶ ጥገና አድርገዋል። በሂሊንግ ቫልቭስ ኢትዮጵያ ደግሞ (HVE) 25 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ነፃ የልብ ቀዶ ጥገና ለ30 ታዳጊዎች ሰርተዋል። በተጨማሪም "የልብ ጠጋኙ ማስታወሻ" የተሰኘ መጽሐፍም ለአንባቢ አበርክተዋል።

ዶ/ር ፈቀደ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሰሀራ በርሀ በታች ባሉ ሀገሮች ላይ በአሁኑ ሰዓት በተደጋጋሚ በሚከሰት ቶንሲል ምክንያት የሚፈጠር የልብ ህመም ከህፃናት እስከ አዋቂዎች ድረስ በከፍተኛ ሁኔታ ለልብ ህመም መፈጠር ምክንያት እንደሆነ ይናገራሉ።

በቅርቡ በሂሊንግ ቫልቭስ ኢትዮጵያ (HVE) የነጻ ህክምና ተጠቃሚዋ መሆን የቻለችው የ18 አመቷ ታዳጊም የልብ ህመሟ በቶንሲል ምክንያት የተከሰተ ሲሆን 4 ሰዓታት በፈጀው አንድ የግራ ልብ በር ቀዶ ጥገና በቶንሲል ምክንያት ክፋኛ የተጎዳው የታዳጊዋ የልብ በር በመቀየር የተሳካ ህክምና አድርጋለች።

የልብ ቀዶ ጥገና ህክምና የሚሰጠው ደረት ተከፍቶ፣ ልብና ሳንባ ቁሞ፣ የደም ዝውውር ለማሽን ተሰጥቶ በመጨረሻም ልብ ተከፍቶ ህክምናው እንደሚሰጥና በዚህም ብዙ የህክምና ሂደቶችን እንደሚያልፍ ዶ/ር ፈቀደ ያስረዳሉ።

የልብ ህመም በተፈጥሮ ሊከሰት የሚችል ሲሆን በዓለም ላይ ''ከ1 ሺ ሰው 10 ሰው'' በተፈጥሮ የልብ ችግር ይኖርበታል ተብሎ ይታሰባል።

በሌላ በኩል ደግሞ በደም ግፊት፣ በስኳር በሽታ ምክንያትም የልብ ህመም እንደሚከሰት የልብ ሀኪሙ ዶክተር ፈቀደ ገልፀዋል።

አሁን ላይ ኢትዮጵያ ውስጥ የልብ ህክምና በተሟላ ሁኔታ የሚሰጠው በአዲስ አበባ በመሆኑ ለታማሚዎች ፈተና እየሆነ መምጣቱን ገልጸዋል።

"በሽዎች እሚቆጠሩ ሰዎች ወረፋ ይጠብቃሉ፣ወረፋ ሳይደርሳቸው በርካቶችም ህይወታቸውን ያጣሉ'' ብለዋል።


በመጨረሻም ተሳክቶላቸው ወረፋ ሲደርሳቸው በጣም ያረፈዱና የተወሳሰቡ ህክምና እንድንሰጥ እንገደዳለን ሲሉ ዶ/ር ፈቀደ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀዋል።

"ለአንድ የልብ ህመምተኛ ህክምና ለመስጠት በርካታ ባለሙያዎች፣ ብዙ ማሽን ጥቅም ላይ ይውላላል ከዚህ አንፃር በአሁኑ ሰአት በኛ ሀገር የልብ ህክምና ገና ጅማሮ ላይ ነው ማለት እንችላለን" ብለዋል።


እንደ መፍትሔ . . .

በኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት ሁሉንም ነገር ያሟላ የልብ ህክምና የሚሰጠው ተቋም የኢትዮጵያ የልብ ህክምና ማዕከል እንደሆነ ዶ/ር ፈቀደ አግዋር ይናገራሉ።

ይህን ማዕከል አሳድጎ ትምህርት ቤት በማረግ ብዙ የልብ ህክምና ባለሙያዎችን በማፍራት በየከተማው፣ በየክልሉ እንዲሄዱ በማረግ ችግሩን መፍታት የሚቻልበት መንገድ ቢፈጠር ሲሉ ኃሳባቸውን ያቀርባሉ።

በተጨማሪም አሁን ላይ ማዕከሉ ያለውን አቅም አሳድጎ ብዙ የልብ ቀዶ ህክምናዎችንም እንዲሰራ ቢደረግ ለበርካቶች መድረስ እንደሚቻልም ገልፀዋል።

በኢትዮጵያ የልብ ቀዶ ህክምና እና በደም ስር ገብቶ የሚሰራ የልብ ህክምና የሚሰጡት ቅዱስ ጳውሎስ፣ ጥቁር አንበሳና ኢትዮጵያ የልብ ህክምና ማዕከል መሆናቸውን ከኢትዮጵያ የልብ ህክምና ባለሙያዎች ማህበር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethmagazine

19.9k 0 24 17 139

በ6 ወሩ የፎረንሲክ ምርመራ ከተካሄደባቸው ሰነዶች ውስጥ 73 በመቶው ሀሰተኛ ናቸው ተባለ።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በ2017 በጀት ዓመት ስድስት ወራት ከቀረቡለት 191 የወንጀል ጉዳዮች እና 167 ከፍታብሔር ጋር የተያያዙ የምርመራ ጥያቄዎችን ከፖሊስና ከፍርድ ቤት ተቀብሎ በፎረንሲክ ምርመራ ማጣራቱን ገልጿል።

በዚህም የፎረንሲክ ምርመራ ከተካሄደባቸው 358 ሰነዶችን ውስጥ 73 በመቶ የሚሆኑት ሀሰተኛ መሆናቸውን አረጋግጫለሁ ሲል አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባደራጀው የምርመራ ላብራቶሪ በሰነዶች ላይ የሚፈፀሙ ፊርማዎችን፣ በቲተሮችና በማህተሞች፣ በባንክ ቼኮች፣ በፖስፖርቶች፣ በተለያዩ ሀገር ገንዘቦች ላይ የተፈፀሙ ድልዝና ስርዞችን፣ በፅሁፎች እና በቁጥሮችን ይመረምራል።

በተጨማሪም ከውርስ ጋር የተያያዙ ሰነዶችን እና ከቦታ ካርታ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በመመርመር ትክክለኛ እና ሀሰተኛ መሆናቸውን የማረጋገጥ ሥራም ይሰራል።

በሀገራችን የፀረ-ሙስና አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 23 ሥር መንግሥታዊ እንዲሁም ሕዝባዊ ድርጅት ሰነዶችን በማስመሰል በሙሉ ወይም በከፊል የለወጠ፤ ያሻሻለ፤ የቀነሰ፤ የጨመረ ወይም በማጥፋት ወደ ሀሰተኛነት የለወጠ እንደ ወንጀሉ ክብደት እስከ እድሜ ልክ ጽኑ እስራት ያስቀጣል።

ኅብረተሰቡም ማንኛውም ዓይነት ውሎችን ሲዋዋል፣ Online ግብይቶች ሲያደርግና ሲፈርም በአጠቃላይ ከሰነድ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በሚገባ ማየትና ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡

@tikvahethmagazine


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
📢📢📢 እንዳያመልጦት

የመጨረሻው እና ሶስተኛዉ የሱቅ ሺያጭ በ ፒያሳ (አድዋ 00 )ፊትለፊት  

💥 ከ 3,9 ሚሊዮን ጠቅላላ ክፍያ ጀምሮ በ 900ሽ ቅድመ ክፍያ

💥 እንዲሁም  ፒያሳ ሊሰ ገብረ ማርያም ት/ቤት ጀርባ

💥 ከባለ 1መኝታ ጀምሮ እስከ ባለ 3 መኝታ ዘመናዊ አፓርትመንቶችን

💥 ከ 3,900,000 ሙሉ  ክፍያ ጃምሮ

💥 በተጨማሪ  ግንባታየው ከ 75% በላይ የተጠናቀቁ አፓርትመንቶች

📍 በአያት 1(አንድ) (በካሬ 61 ሺ ብር)
📍በአያት 2(ሁለት ),(በካሬ 69 ሽብር )
📍ሱማሌ ተራ (በካሬ 95 ሺ ብር)
ለሽያጭ አቅርበናል

ለበለጠ መረጃ
               ☎️0944201554
               ☎️0987076900 ይደውሉ


የሊፍት አደጋ!

የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ባለፉት ቅዳሜና እሁድ በአዲስ አበባና አካበቢዋ ወደ 5 አደጋዎች ደርሰው በሰውና በንብረት ላይ ጉዳታ ማድረሳቸውን አስታውቋል።

ከእነዚህ አደጋዎች መካከል በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ዋሪት አካባቢ'' የፍሊንት ስቶን ሆምስ የመኖሪያ ህንፃ ሊፍት ላይ የደረሰው አደጋ አንዱ መሆኑን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ንጋቱ ማሞ ጠዋት ላይ ሰይፉ ሾው ለመቄዶንያ ባዘጋጀው የቀጥታ ሥርጭት የገቢ ማሰባሰቢያ ላይ መረጃውን አጋርተዋል።

አደጋው የደረሰው የህንጻውን ሊፍት ተጠቅመው ከ6ተኛ ፎቅ ወደ ግራውንድ ለመውረድ ሲሞክሩ በነበሩ 14 ሰዎች ላይ እንደሆነ አስረድተዋል።

በዚህም ሊፍቱ ተበጥሶ አደጋ መድረሱን ገልጸው በዚህ አደጋ የ7 አመት ህፃን ልጅን ጨምሮ 8ቱ ላይ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ህክምና ተቋማት ለህክምና መላካቸውን አስረድተዋል።

ሊፍቱ ከሚይዘው ሰው ቁጥር በላይ ሊፍት ውስጥ ባለመግባት ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ ያሳሰቡት አቶ ንጋቱ በተመሳሳይ አደጋ ከዚህ ቀደም ህይወታቸውን ያጡ ዜጎች እንዳሉም ለአብነት ጠቅሰው አስረድተዋል።

በየህንፃው የሊፍት ባለሙያ እንዲኖር በማረግ መሰል አደጋዎችን መከላከል እንደሚቻልና  ኮሚሽኑም ሁሉንም ማዳረስ ባይችል የክትትል ሥራ እንደሚሰራ አስረድተዋል።

በተመሳሳይ በትላንትናው ዕለት ታዋቂው ድምጻዊ አብዱ ኪያር በተመሳሳይ አደጋ ጉዳት ደርሶበት እንደነበረና በተደረገለት ህክምናም አሁን ላይ በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል።

@tikvahethmagazine

42.5k 0 158 21 204

በማሊ ህገ-ወጥ የወርቅ ማዕድን ማውጫ ላይ በደረሰ አደጋ 48 ሰዎች ሞቱ

ከአፍሪካ ወርቅ በማምረት ግንባር ቀደም በሆነችው በማሊ ህገ-ወጥ የወርቅ ማዕድን ማውጫ ላይ በደረሰ የመሬት መንሸራተት 48 የሚቆጠሩ ሰዎች መሞታቸውን የአካባቢው ባለስልጣናት ገልፀዋል።

የአካባቢው ባለስልጣናት በአደጋው ​​አብዛኞቹ ሴቶች በሆኑበት ቢያንስ 48 ሰዎች መሞታቸውን ገልጸው የሟቾች ቁጥር ግን ሊጨምር እንደሚችል ተናግረዋል።

በጉዳዩ አሳሳቢነት ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የአካባቢው ባለስልጣን “ሁኔታው በጣም አሳሳቢ ነው፤ አሁንም በህይወት ሊኖሩ የሚችሉትን ለማዳን የምንችለውን ሁሉ እያደረግን ነው” ብለዋል።

ከዚህ በፊት በጃንዋሪ 30፣ በደቡብ ምዕራብ ማሊ በኩሊኮሮ በምትገኘው ዳንጋ መንደር ውስጥ መደበኛ ባልሆነ የማዕድን ማውጫ ላይ በደረሰ የመሬት መንሸራተት ቢያንስ 15 ሴቶች ህይወታቸው አልፎ ነበር።

ኢትዮጵያን ጨምሮ በሌሎችም አፍሪካ ሀገት ወርቅ ለማውጣት በሚደረግ ጥልቅ ቁፋሮ አማካኝነት በሚደርስ አደጋ በርካታ ዜጎች ህይወታቸው ያልፋል።

@tikvahethmagazine


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
📢📢📢 እንዳያመልጦት

የመጨረሻው እና ሶስተኛዉ የሱቅ ሺያጭ በ ፒያሳ (አድዋ 00 )ፊትለፊት  

💥 ከ 3,9 ሚሊዮን ጠቅላላ ክፍያ ጀምሮ በ 900ሽ ቅድመ ክፍያ

💥 እንዲሁም  ፒያሳ ሊሰ ገብረ ማርያም ት/ቤት ጀርባ

💥 ከባለ 1መኝታ ጀምሮ እስከ ባለ 3 መኝታ ዘመናዊ አፓርትመንቶችን

💥 ከ 3,900,000 ሙሉ  ክፍያ ጃምሮ

💥 በተጨማሪ  ግንባታየው ከ 75% በላይ የተጠናቀቁ አፓርትመንቶች

📍 በአያት 1(አንድ) (በካሬ 61 ሺ ብር)
📍በአያት 2(ሁለት ),(በካሬ 69 ሽብር )
📍ሱማሌ ተራ (በካሬ 95 ሺ ብር)
ለሽያጭ አቅርበናል

ለበለጠ መረጃ
               ☎️0944201554
               ☎️0987076900 ይደውሉ


በባህርዳር 2 ህጻናት ተጣብቀው ቢወለዱም ህይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም።

በአማራ ክልል በባህርዳር ከተማ በጥበበ ግዮን እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የካቲት 5/ 2017 ዓ.ም ተጣብቀው የተወለዱት ህፃናት በትናንትናው እለት ሂወታቸው ማለፉን ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገልፀዋል።

የተወለዱት ሕጻናት ከደረታቸው በላይ ሁለት ሰው፤ ከደረታቸው በታች ደግሞ የአንድ ሰው አካል ይዘው እንደተወለዱ ለማወቅ ተችሏል።

ለመረጃው ቅርበት ያላቸው ምንጮች እንደገለፁት ከሆነ እናቲቱ ከመውለዷ በፊት የእርግዝና ክትልል በዱርቤቴ ጤና ጣቢያ ስታደርግ እስከ ሰባት ወሯ  መቆቷ ተገልጿል።

በክትትሉ ወቅት ነፍሰ ጡሯ ከዚህ በፊት በእርግዝና ወቅት አይታው የማታውቀው ነገር ስለገጠማት የህክምና ባለሙያዎችን በማናገር ወደ ጥበበ ግዮን እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በመምጣት ምርመራ ያካሄደች ሲሆን ፅንሱ ትክክል እንዳልሆነ ተረጋግጦ ነበር ተብሏል።

ይሁን እንጂ ፅንሱ ሰባት ወር ስለሞላው ግደታ የመወለጃቸው ቀን መድረስ ስለነበረበት በቀኑ በኦፕራሲዎን እንድትወልድ ተደርጓል ብለዋል።

በመሆኑም በአገራችን እንደዚህ አይነት አፈጣጠር በስፋት ታይቶ የማይታወቅ እና ያልተለመደ ነገር ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ልጆቹ ከተወለዱ በኋላ ወላጅ እናትን ጨምሮ ቤተሰቦችም ልጆቹን ለማየት እንኳ ፍቃደኛ እንዳልነበሩ ምንጮቹ ጠቁመዋል።

የሆስፒታሉ የህክምና ባለሙያዎች ልጆችን በሂወት ለማቆየት ያደረጉት ጥረት ሳይሳካ እንደቀረ ምንጮቹ ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ደግሞ በክልሉ የሚስተዋለው ግጭት የጥበበ ግዮን እስፔሻላይዝድ ሆስፒታልን ክፉኛ በመጎዳቱ አሁን ላይ 10 በመቶ ብቻ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑ ተነግሯል።

በተጨማሪም ተጣብቀው ለተወለዱት ህፃናት እጥጋቢ ወይም በቂ የህክምና አገልግሎት በሆስፒታሉ በኩል ማግኘት እንዳልቻሉ  ተጠቁሟል።

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሐረርጌ ዞን ሂርና ከተማ በ2014 ዓ.ም ከደረታቸው በታች የተጣብቁ  ህፃናት መወለዳቸው ይታወሳል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethmagazine


🔈#የነዋሪዎችድምጽ

🟢  ''ለፈረሰው ቤታችን ግብር ክፈሉ እየተባልን የቴክስት መልዕክት እየተላከልን ነው'' ቅሬታ አቅራቢዎች

🟢 '' አቅራቢያው ወደሚገኙ ወረዳ ላይ ባሉ ቢሮዎቻችን ጉዳዩን በማስረዳት ችግሩን መፍታት ይችላል '' ገቢዎች ቢሮ


የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ቤታችን ፈርሶብን ወደሌላ ቦታ የተዘዋወርን ሰዎችን በፈረሰው ቤት ስም የቤት ግብር እንድንከፍል የቴክስት መልዕክት እየላከላቸው መሆኑን ቅሬታ አቅራቢዎች ተናግረዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎች በጉዳዩ ዙሪያ እንደተናገሩት:-

"ቤቴ ካዛንችስ ነበር፣ ቤቴም ሰፈሩም ከፈረሰ 3 ወራት አልፎታል በፈረሰው ቤት ስም የቤት ግብር እንድንከፍል የቴክስት መልዕክት የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ እየላከልን'' ነው ሲሉ ተናግረዋል።

አክለውም '' በአሁን ሰአት ከነቤተሰቤ ቱሉ ዲምቱ ኮንዶሚንየም ተከራይተን እየኖርን ሳለ ታድያ ላፈረሱት ቤቴ እንዴት ግብር ክፈል እንባላለን''
ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም በጉዳዩ ዙሪያ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የኮምኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለን ጠይቀናቸው በሰጡን ምላሽ:-

እንደሚታወቀው '' የቤትና ቦታ ግብር ያለ ቅጣት እሚከፈልበት ጊዜ እስከ የካቲት 30 ድረስ''ነው።

ግብር ከፍዩ ከዚህ አንፃር እንዳይዘናጋ በየጊዜው በኤስ ኤም ኤስ በመጠቀም መረጃ የማድረስ ስራ እንሰራለን
ብለዋል

ምናልባት '' በመጀመሪያ ይኖሩበት በነበረው አካባቢ ቀደም ብሎ ተመዝግቦ ባለ ስልክ ቁጥር ግብር ክፈሉ የሚል የፅሁፍ መልዕክት ለግብር ከፍዩ ደርሶ ሊሆን'' ይችላል።

ግብር ከፋዩም '' ቤቱ ፈረሶበት በማይኖርበት ቤት ግብር ክፈል እሚል የአጭር የፁሁፍ መልዕክት ደርሶት ከሆነ አቅራቢያው ወደሚገኙ ወረዳ ላይ ባሉ ቢሮዎቻችን ጉዳዩን በማስረዳት ችግሩን መፍታት ይችላል'' ሲሉ አቶ ሰውነት አስረድተዋል።

በተለይ ከቤትና ቦታ ግብር ጋር በተያያዘ ግብር ከፍዮች በተለያየ ምክንያት እንዳይዘናጉ፣ ቅጣት፣ ወለድ እንዳያጋጥማቸው ከማሰብ አንፃር አጭር የፅሁፍ መልዕክት በመላክ ግብር ከፍዩን የማስታወስ ስራ ቢሯቸው እየሰራ መሆኑን አቶ ሰውነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ጥቆማዎችን በ @tikvahmagbot ላይ ማድረስ ይችላሉ

#TikvahEthiopia

@tikvahethmagazine


ኢትዮጵያ ከዓለም በሙስና በስንተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች?

ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል በተለያዩ ሀገራት ያለውን የሙስና ደረጃ በመገምገም በሰጠው ነጥብ ኢትዮጵያ በ2024 37 ነጥብ በማግኘት ከዓለም 180 ሀገራት 99ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።

በድርጅቱ መረጃ መሰረት ኢትዮጵያ በ2022 በ38 ነጥብ 94ኛ እና በ2023 በ37 ነጥብ 98ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣ ነበር።

ኢትዮጵያ በ2024 37 ነጥብ በማግኘት ከአለም ከ180 ሀገራት በሙስና 99ኛ ደረጃን መያዟን ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል አስታውቋል።

ከሰሃራ በታች ካሉ ሀገራት ኤርትራ በ13 ነጥብ፣ ሶማሊያ በ9 ነጥብ እንዲሁም ደቡብ ሱዳን በ8 ነጥብ ዝቅተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ሀገራት ናቸው።

በአለምአቀፍ ደረጃ ዴንማርክ 90 ነጥቦችን አስመዝግባለች በዚህም እንደ ባለፈው አመት አንደኛ ሆናለች እሷን ተከትሎ ፊንላንድ እና ሲንጋፖር ከፍተኛ ውጤት አስመዝግበዋል።

@tikvahethmagazine


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
📢📢📢 እንዳያመልጦት

የመጨረሻው እና ሶስተኛዉ የሱቅ ሺያጭ በ ፒያሳ (አድዋ 00 )ፊትለፊት  

💥 ከ 3,9 ሚሊዮን ጠቅላላ ክፍያ ጀምሮ በ 900ሽ ቅድመ ክፍያ

💥 እንዲሁም  ፒያሳ ሊሰ ገብረ ማርያም ት/ቤት ጀርባ

💥 ከባለ 1መኝታ ጀምሮ እስከ ባለ 3 መኝታ ዘመናዊ አፓርትመንቶችን

💥 ከ 3,900,000 ሙሉ  ክፍያ ጃምሮ

💥 በተጨማሪ  ግንባታየው ከ 75% በላይ የተጠናቀቁ አፓርትመንቶች

📍 በአያት 1(አንድ) (በካሬ 61 ሺ ብር)
📍በአያት 2(ሁለት ),(በካሬ 69 ሽብር )
📍ሱማሌ ተራ (በካሬ 95 ሺ ብር)
ለሽያጭ አቅርበናል

ለበለጠ መረጃ
               ☎️0944201554
               ☎️0987076900 ይደውሉ


🔊 #የሠራተኞችድምጽ

🟢 "ቅሬታችን በአስቸኳይ ምላሽ የማያገኝ ከሆነ ከየካቲት 15/2017 ዓ.ም ጀምሮ ሥራ እናቆማለን"- የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሰራተኞች

🟢 "ለክልሉ መንግስት ቅሬታውን አቅርበናል። ነገር ግን ለቀረበለት ጥያቄ ምላሽ መስጠት አልቻለም " - የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የሰው ኃብት አስተዳደር

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሰራተኞች በሀገር አቀፍ ደረጃ ጥቅምት አንድ ተግባራዊ የተደረገው አዲሱ የደመወዝ ማሻሻያ ጭማሪ እስካሁን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ተግባራዊ  ባለማድረጉ ለከፋ ችግር ተጋልጠናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

በተጨማሪም የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሸን ለሁሉም ሲቪል ሰርቫንት የኑሮ ውድነት መደጎሚያ ያደረገውን ጭማሪ እስካሁን አልተጨመረንም ብለዋል።

ሰራተኞቹ  የተለያዩ ጥያቄዎችን ለክልሉ ገቢዎች ቢሮ   ማቅረባቸውን የገለፁ ሲሆን ጥያቄያችን በቀጠሮ  የታጀበ የአመታት ችግር ሆኖ ቀጥሏል ብለዋል።

"የክልሉ መንግስት የተቋሙን ሰራተኞች ድካም እና መስዋዕትነት የተረዳው አይመስለንም " ። እኛ " ተስፋ ቆርጠናል ፣ የሚሰማን አካል የለም ፣ እየታገትን እና እየተገደልን ነው  ፣ከማህበራዊ ሂወት ተገለናል ብለዋል።

አክለውም "እንደሰው መቆጠር ናፍቆናል ፣ ችግሮቻችን በዝተዋል ፣  ችግሮችን የሚፈታልን የለም ፣ እባካችሁ የሚሰማን አካል ካለ የሁለት አመት ቅሬታችን ይሰማ " ሲሉ የነበሩበትን የችግር ግዝፈት ተናግረዋል።

አያይዘውም ሰራተኞቹ  መጋቢት 5 / 2015 ዓ.ም ይወክሉናል ያሏቸውን ተወካይዮች በመምረጥ ለክልሉ ገቢዎች ቢሮ ፣ ለበጀትና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እና ለብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት አመራር እንዲሁም ለርዕሰ መስተዳድሩ ልዩ አማካሪ ቅሬታቸውን እንዳቀረቡ ገልፀዋል።

ሰራተኞቹም በሰዓቱ ለአመራሮቹ ያቀረቧቸው ጥያቄዎች በርካታ መሆናቸውን የገልፁ ሲሆን ከጥያቄዎቻቸው መካከል የገቢ ተቋሙ ሰራተኛ በልዩ ሁኔታ በጥናት ላይ የተመሰረተ ልዩ ጥቅማጥቅም ይደረግልን፣ የእርከን ጭማሪ በአደረጃጃትና በመመሪያ ደረጃ የወረደ ቢሆንም በአፈጻጸም ተግባራዊ ይደረግ እና የሰራተኛውን ጥቅም የሚመለከት ጥናት ሲጠና እስከ ታችኛዉ መዋቅር ያለ ባለሙያ ተሳታፊ ይደረግ የሚሉ እና መሰል ጥያቄዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል።

በመሆኑም በሰዓቱ አመራሮቹ በምላሻቸው  ጥያቄው ተገቢነት ያለው የባለሙያውን ሮሮና ብሶት ያዘለ ስለሆነ በቀጣይ የተሻለ ገቢ ለመሰብሰብ ይህንን አካል የግድ ማትጋትና ማበረታታት አስፈላጊ ስለሆነ ጥያቄውን እንፈታለን ብለውን ነበር ብለዋል።

ይሁን እንጂ ቅሬታችንን ሰምቶ የፈታልን አካል የለም ያሉ ሲሆን አሁንም ለከፋ ችግር ተጋልጠን እንገኛለን ሲሉ አክለዋል።

በሌላ በኩል ደግሞ ሰራተኞቹ የክልሉን የገቢዎች ቢሮ የሰው ሀብት አስተዳደር ቅሬታችንን ፍቱልን ብለን ጠይቀን ነበር ያሉ ሲሆን ሀላፊውም በምላሻቸው " ቅሬታችሁ ከአቅማችን በላይ ነው። በአስቸኳይ ምላሽ ይሰጣቸው ስንል ለክልሉ መንግስት ጥያቄ አቅርበናል እስካሁን ግን መልስ የለም " የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል።

አክለውም እንደተቋም በቀን እስከ 200 ሚሊየን ገቢ የሚሰበስብ ሰራተኛ አንድ ቀን ስራ ቢያቆም እንኳ ምን ሊፈጠር እንደሚችል መገመት ቀላል መሆኑን ጠቁመዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ በዝርዝር ምን አሉ?

ከደሴ ኮምቦልቻ የደወለልን ባለሙያ " ስራችን ከማህበረሰቡ ሂወት ነጥሎናል፣ ከነጋዴዎች አራርቆናል፣ ደመወዝ ሲያልቅብን እንኳ ከነጋዴዎች መበደር አንችልም፣ ቤት ለመከራየት ስንጠይቅ ገቢዎች ቢሮ ከሆነ የምትሰሩት አናከራይም እያሉን ነው፣ አሁን ላይ ችግሮችን መቋቋም አቅቶናል "  ሲል ተናግሯል።


ስሙን መጥቀስ ያልፈለገው የደባርቅ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ሰራተኛ ደግሞ " የደረጃ እርከን እየተሰራልን አይደለም " 2012 ዓ.ም የደመወዝ ጭማሪ እንደተደረገ እስካሁን አልተጨመረንም " በስራ አጋጣሚ ሂወታቸውን የገበሩ ጓዶች  አሉ " የክልሉን መንግስት ታግሰናል" አሁን ላይ ግን ኑሮ ከብዶናል " ሲል ገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም የሰራተኞቹን ቅሬታ በመቀበል ለአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የሰው ሃብት አስተዳደር ሀላፊ ለአቶ ሽመልስ አዱኛ ቅሬታቸውን ያቀረበ ሲሆን እርሳቸውም በምላሻቸው እንድህ ብለዋል።

" የሰራተኞቹ ቅሬታ ተገቢ ነው። በኛ በኩል ቅሬታውን እናውቃለን ። ለክልሉ መንግስት ቅሬታውን አቅርበናል። ነገር ግን ለቀረበለት ጥያቄ ምላሽ መስጠት አልቻለም "በዚህ ጉዳይ የተለየ መረጃ ልሰጥ አልችልም " ብለዋል።

ቲክቫህ የባለሙያዎችን ቅሬታ በተመለከተ የክልሉን መንግስት እና የኮሚኒኬሽን ባለሙያ እንዲሁም የክልሉን ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ በስልክ አግኝቶ ምላሻቸውን ለማካተት ያደረገው ጥረት ባለመሳካቱ ምላሻቸውን ማካተት አልተቻለም።

በመጨረሻም ሰራተኞቹ ቅሬታችን በአስቸኳይ ምላሽ የማያገኝ ከሆነ ከየካቲት 15/2017 ዓ.ም ጀምሮ  ስራ የምናቆም መሆኑን እንገልፃለን ብለዋል።

( ቲክቫህ ጉዳዩን እስከመጨረሻው ተከታትሎ መረጃውን የሚያደርሳችሁ ይሆናል )

#TikvahEthiopia

@tikvahethmagazine


ኢቦላን ለመቆጣጠር ተጨማሪ 2 ሚሊዮን ዶላር መለቀቁን ተገለፀ

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም በኡጋንዳ ውስጥ የተከሰተውን የኢቦላ ወረርሽኝ ለመቆጣጠር ተጨማሪ 2 ሚሊዮን ዶላር መለቀቁን ገልጸዋል።

በኡጋንዳ አዲስ በተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ አንድ ሰው የሞተበት እና ቢያንስ ስምንት ሰዎች በበሽታው የተያዙበት ነው።

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም በኡጋንዳ ኢቦላ ወረርሽኝ ለመቆጣጠር እሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ ከWHO የአደጋ ጊዜ ፈንድ ተጨማሪ 2 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ መደረጉን ገልፀዋል።

WHO በሆስፒታሎች፣ በሕክምና ማዕከላት፣በምርምር መስኮች ክትትል፣ ላቦራቶሪዎች፣ ሎጂስቲክስ፣ የኢንፌክሽን መከላከል እና ቁጥጥርን እየደገፉ መሆኑን ዶክተር ቴዎድሮስ X ማህበራዊ ገፃቸው ላይ ገልፀዋል።

Credit: Reuters

@tikvahethmagazine


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
📢📢📢 እንዳያመልጦት

የመጨረሻው እና ሶስተኛዉ የሱቅ ሺያጭ በ ፒያሳ (አድዋ 00 )ፊትለፊት  

💥 ከ 3,9 ሚሊዮን ጠቅላላ ክፍያ ጀምሮ በ 900ሽ ቅድመ ክፍያ

💥 እንዲሁም  ፒያሳ ሊሰ ገብረ ማርያም ት/ቤት ጀርባ

💥 ከባለ 1መኝታ ጀምሮ እስከ ባለ 3 መኝታ ዘመናዊ አፓርትመንቶችን

💥 ከ 3,900,000 ሙሉ  ክፍያ ጃምሮ

💥 በተጨማሪ  ግንባታየው ከ 75% በላይ የተጠናቀቁ አፓርትመንቶች

📍 በአያት 1(አንድ) (በካሬ 61 ሺ ብር)
📍በአያት 2(ሁለት ),(በካሬ 69 ሽብር )
📍ሱማሌ ተራ (በካሬ 95 ሺ ብር)
ለሽያጭ አቅርበናል

ለበለጠ መረጃ
               ☎️0944201554
               ☎️0987076900 ይደውሉ


200 ካሬ በሆነ የእርሻ መሬት ላይ የካናቢስ ዕጽ ሲያመርቱ የነበሩ ተጠርጣሪዎች ተያዙ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ጎርካ ወረዳ ላንቴ ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ በእርሻ ማሳ ካናቢስ የተባለውን አደንዛዥ ዕፅ ሲያመርቱ የነበሩ ግለሰቦችን ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የዞኑ ፖሊሲ መምሪያ አስታዉቋል።

የኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ የመረጃና ኢንተለጀንስ ዲቪዥን ኃላፊ ዋና ሳጅን ሙሉቀን ጋሞ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት ተጠርጣሪዎቹ አቶ በላቸው በረሱ እና እልኩ ደፋር የተባሉ ግለሰቦች ሲሆኑ እጹን ሲያመርቱ የተገኙትም በጎርካ ወረዳ ጎልቤ ቀበሌ ላንቴ ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ እንደሆነ ጠቅሰዋል።

ተጠርጣሪዎቹ፥ 10 በ 20 በሆነ የእርሻ መሬት ላይ ዕፁን ሲያመርቱ ከሕብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ አስፈላጊዉን  ክትትል በማድረግ ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ማዋላቸዉንም ተናግረዋል።

ከምርመራና ክስ ሂደቱ ጎን ለጎን ከግሌሰቦቹ ጋር በዕፅ ዝዉዉሩም ሆነ የአቅርቦት ተስስር ግንኘነት ያላቸዉን ሰዎች የመከታተልና በሕብረተሰቡም ዘንድ ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራዉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ሀይሌ በበኩላቸው አንድ ኩንታል ካናብስ በቲቢኤስ ሞተር ሳይክል ተጭኖ በቁጥጥር ሥር መዋሉን ጠቅሰዋል።

እስከ እርሻ ማሣ በተደረገው ኦፕሬሽንም '' አራት ክምር በአጠቃላይ እስከ 120 ኪ.ግ  የሚመዘን ካናብስ አደገኛ ዕፅ በመያዝ የምርመራ ሂደት እየተጣራ '' መሆኑን አብራርተዋል።

የፌደራል ፖሊስ መረጃና ደህንነት፣ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት እንድሁም የኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ መረጃና ኢንቴለጄንስ ዲቪዥን በጋራ በመቀናጀት አደንዛዥ ዕፁን ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ማዋል እንደተቻለ ኮማንደር አሸናፊ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።

ይህ ህገ ወጥ ተግባር በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ክሳራ የሚያስከትልና ወጣቶችን ወደ አላስፈላግ ወንጀል የሚመራ በመሆኑ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ እንድያደርግ አሳስበዋል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethmagazine


Addis Abeba's top and luxury apartment for sale
Bole - infront Bole Metemiya - (ቦሌ ማተሚያ)

👉  City View luxury apartments   
                        
👉  Built on Bole Main Road with Radisson Blu international hotel standard

We are offering more than 90% completed fully finished 2 bedroom and 3 bedroom apartments for sale.

📌 The apartment includes:

👉 Each house has a private parking lots
👉 Each apartments got digital carta
👉 4 modern elevators
👉 Standby electric generator
👉 Underground water is available and big capacity water tank ..etc

And many more luxury amenities ...

‼️ DON'T MISS THIS OUT ‼️

For more information :

0920224609  |   @Tsedalproperties


በሥጋ ቤቶች ላይ ያለው የደረሰኝ ቁጥጥር ተጠናክሮ ይቀጥላል።

በየካቲት ወር ቀጣይ15 ቀናት በከተማዋ በሚገኙ ስጋ ቤቶች ላይ ደረሰኝ በመቁረጥ ላይ ትኩረት አርጎ በመሥራት መንግስት ማግኘት ያለበትን ገቢ እንዲያገኝ እንደሚሰራ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ አስታውቋል።

@tikvahethmagazine

40.9k 0 79 26 133

በኡጋንዳ በኢቦላ የተያዙ ሰዎች ወደ ዘጠኝ ከፍ ማለቱ ተገለፀ

በኡጋንዳ በኢቦላ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ወደ ዘጠኝ ከፍ ያለ ሲሆን 265 ሌሎች ሰዎች ደግሞ በኳራንቲን ውስጥ ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን የጤና ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።

ስምንት ታካሚዎች “የሕክምና ክትትል እየተደረገላቸው ሲሆን በጥሩ ሁኔታ ላይ ናቸው” ሲል የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ገልጿል።

ከእነዚህ ውስጥ ሰባቱ በዋናው የህዝብ ሆስፒታል በካምፓላ ሲገኙ አንዱ በምስራቃዊ ምባሌ አውራጃ ውስጥ እየታከመ ነው ሲል ሚኒስቴሩ ገልፀዋል።

ካምፓላ ወደ 4 ሚሊዮን የሚጠጋ ከፍተኛ ተንቀሳቃሽ ህዝብ ያላት ሲሆን ባለሥልጣናት አሁንም የወረርሽኙን ምንጭ እየመረመሩ ነው።

እስካሁን አዲስ በተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ ከተያዙ ዘጠኝ ሰዎች ውስጥ የአንድ ሰው ሞት ተመዝግቧል።

Credit: AP News

@tikvahethmagazine


#Update

በምስራቅ ወለጋ ዞን ጉደያ ቢላ ወረዳ "ኢፋ ቢያ" በተባለው ቦታ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሟቾች ቁጥር 26 አልፏል ሲል ኤፍ ኤም ሲ አፋን ኦሮሞ ዘግቧል።

የዞኑን የትራፊክ ቢሮ ጠይቆ በሰራው ዘገባ 42 ሰዎች ከፍተኛ የአካል ጉዳት ደርሶባቸው በህክምና ላይ እንደሚገኙ ጠቅሷል።

የቢሮው ኃላፊ ኢኒስፔክተር አስናቀ መስፍን የሟቾች ቁጥር ከዚህም ከፍ ሊል እንደሚችል አስረድተዋል።

@tikvahethmagazine


አሳዛኝ አደጋ 🕯️

በምስራቅ ወለጋ ዞን ጉደያ ቢላ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ 40 ሰዉ ህይወት ማለፉ ተሰምቷል።

አደጋው ከሻምቡ ወደ አዲስ አበባ እያመራ ያለ ታታ መኪና ላይ መድረሱን ከአከባቢው ያሉ ምንጮች እየገለጹ ነው።

ስለ አደጋው ይፋዊ መግለጫ እስካሁን አልተሰጠም።

@tikvahethmagazine

34.4k 0 11 19 180
Показано 19 последних публикаций.