TIKVAH-MAGAZINE


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።
ያግኙን +251913134524

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ባስጀመረው የንባብ ዘመቻ በበርካታ ሰዎች የተጠቆሙት መጻሕፍት የትኞቹ ናቸው ?

ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬድዮ ከየካቲት 17 እስከ ግንቦት 27 /2016 ዓ.ም ለ100 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የንባብ ዘመቻ ማስጀመሩ ይታወሳል። እስካሁን የመጻሕፍት ምርጫቸውን በማሳወቅ ጥቆማ የሰጡ ሰዎች ሰላሳን ተሻግረዋል።

የመጻሕፍት ጥቆማቸውን ይፋ ባደረጉት የጀመሪያዎቹ 30 ሰዎች ዘንድ የትኞቹ መጻሕፍት በተደጋጋሚ ተመረጡ ?

1) የሀዲስ አለማየሁ "ፍቅር እስከ መቃብር" በ 9 ሰዎች የንባብ ጥቆማ ዝርዝር ውስጥ ተካትቷል።

2) የሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን " እሳት ወይ አበባ "  በ5 ሰዎች የንባብ የንባብ ዝርዝር ውስጥ መግባት ችሏል።

3) የሀዲስ አለማየሁ " ትዝታ " በ 3 ሰዎች፤

4) የቀዳማዊ አፄ ሀይለስላሴ " ሕይወቴ እና የኢትዮጵያ እርምጃ " በ 3 ሰዎች፤

5) የበዓሉ ግርማ " ኦሮማይ " በተመሳሳይ በ3 ሰዎች የንባብ ምርጫ ውስጥ መካተት ችሏዋል።

የሚከተሉት 6 መጻሕፍት ደግሞ እያንዳንዳቸው በ 2 ሰዎች የንባብ ጥቆማ ዝርዝር ውስጥ መካተት ችለዋል።

1)  የፊዮዶር ዶስቶቭስኪ " ወንጀል እና ቅጣት "

2) የእጓለ ገ/ዮሐንስ " የከፍተኛ ትምህርት ዘይቤ"

3) የተመስገን ገብሬ " ሕይወቴ "

4)  የፋሲካ ሲደልል " የሻምላው ትውልድ "

5) የመርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ " የሐያኛው ክፍለ ዘመን መባቻ "

6) የዳኛቸው ወርቁ " አደፍርስ "

@TikvahethMagazine


በሰሜን ኢትዮጵያ ያሉ አሳሳቢ የጤና ችግሮችን ለመፍታት የሚውል 1.8 ሚሊዮን ዶላር እንደምትሰጥ ጃፓን አሳወቀች

በሰሜን ኢትዮጵያ የጤናና ስነ ምግብ አገልግሎትን ማጠናከርን ጨምሮ አሳሳቢ የጤና ችግሮችን ለመቅረፍ ይረዳል ያለውን 1.8 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ ለኢትዮጵያ እንደሚሰጥ የጃፓን መንግስት አሳውቋል።

በዚህም የገንዘብ ድጋፉ የጃፓን ኤምባሲ እና የአለም ጤና ድርጅት የኢትዮጵያ ቢሮ በጋራ በመሆን በኢትዮጵያ በትግራይ፣ አፋር እና አማራ ክልሎች የኮሌራ፣ የኩፍኝ እና የወባ ወረርሽኞችን ለመቆጣጠር ለሚሰሩት ስራ እንዲሁም የተመረጡ የጤና ተቋማትን መልሶ ለማቋቋም እንደሚውል ተነግሯል።

@TikvahethMagazine


ዜጎች የብሔራዊ መታወቂያ ካርድ በኦንላይን ተመዝግበው ባሉበት እንዲመጣላቸው የሚያስችል አገልግሎት ተጀመረ

ብሔራዊ መታወቂያ ካርድን በኦንላይን ተመዝግቦ በኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት በኩል ካርዱን ካሉበት ሆነው በማዘዝ ባሉበት የማድረስ ሥራ መጀመሩን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ማስታወቁን ኢፕድ ዘግቧል።

የብሔራዊ መታወቂያ ካርድ የሕትመት ሥራ በኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ሲከናወን የቆየ ሲሆን የብሔራዊ መታወቂያ ካርዱን ማግኘት የሚፈልጉ ዜጎችም አገልግሎቱን ለማግኘት በአካል መገኘት ይኖርባቸው ነበር። አሁን ግን ዜጎች አገልግሎቱን በቀላሉ ማግኘት እንዲችሉ የኦንላይን ምዝገባ የተጀመረ ሲሆን የክፍያ ሥርዓቱም በቴሌ ብር እና በባንክ መክፈል እንደሚቻል ተጠቁሟል።

የብሔራዊ መታወቂያ ካርድ ማግኘት የሚፈልጉ ዜጎች card-order.fayda.et ድረ ገጽ ላይ በኦንላይን መመዝገብ እንደሚችሉ ሲገለፅ ፥ በኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት በኩል ካርዱን ባሉበት ቦታ እንዲመጣላቸው ማዘዝ ይችላሉ ተብሏል። ዜጎች ምዝገባ ከማድረጋቸው በፊት የፋይዳ ቁጥራቸውን የሚገልጽ የጽሑፍ መልዕክት በስልካቸው ስለመላኩ ማረጋገጥ እንደሚኖርባቸውም ነው የተገለፀው።

@TikvahethMagazine

27k 0 506 123

የኬንያ አየር መንገድ ከሰባት አመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ 80 ሚሊዮን ዶላር ትርፍ ማግኘቱ ተነገረ

የኬንያ አየር መንገድ በ2018 የማስፋፊያ ፕሮጀክት በመጀመር የብድር እዳ ውስጥ ከገባ በኋላ በተጠናቀቀው የፈረንጆቹ 2023 አመት ለመጀመሪያ ጊዜ 80 ሚሊዮን ዶላር ትርፍ ማግኘቱ ተነግሯል።

አየር መንገዱ 178 ሚሊዮን ሽልንግ አጠቃላይ ገቢ ማግኘቱ ሲነገር ይህም በ 2022 ከነበረው አጠቃላይ ገቢ ጋር ሲነፃፀር የ53 በመቶ ጭማሪ ያለው ነው ተብሏል። የተጓዦች ቁጥርም 35 በመቶ መጨመሩ ሲነገር በቀጣይ ወደ ለንደን ከተማ የበረራ አድማሱን እንደሚያሰፋ ተገልጿል።

@TikvahethMagazine


አዲስ የኤሌክትሪክ ኃይል ታሪፍ በተያዘው ዓመት ተግባራዊ ሊደረግ ነው ተባለ

በ2014 ዓ.ም. ተጀምሮ የነበረው አዲስ ኤሌክትሪክ ኃይል የታሪፍ ማሻሻያ ጥናት ተጠናቆ፣ በተያዘው ዓመት ተግባራዊ ሊደረግ መሆኑን ሪፖርተር ዘግቧል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና አገልግሎት በጋራ በዓለም ባንክ ድጋፍ በውጭ አማካሪ ድርጅት ያስጀመሩት ጥናትና የተዘጋጀው አዲሱ የታሪፍ ፖሊሲ የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ካፀደቁት በኋላ፣ በተያዘው ዓመት ሦስተኛው ሩብ ዓመት ላይ ተግባራዊ ሊያደርጉት እንደሚችሉ ዘገባው ጠቅሷል።

በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚሸጥበት ታሪፍ ወጪን ያላማከለና በኢነርጂ ዘርፉ መዋዕለ ንዋይ ለሚያፈሱ ባለሀብቶች በቂ ክፍያ የማያስገኝ ነው ያለው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኢትዮጵያ ለመኖሪያ ቤት የሚደጎመው የኤሌክትሪክ ኃይልም ዋጋ በኪሎ ዋት ሰዓት (kWh) 0.035 ዶላር እንደሆነና በጎረቤት አገሮች ከዚህ ከፍ የሚል መሆኑ ተጠቅሷል።

እነዚህንና መሰል የታሪፍ ልዩነት ችግሮችን ለመቅረፍ በዓለም ባንክ አጋዥነት የውጭ አማካሪ ኩባንያ በመቅጠር ጥናት የተደረገ ሲሆን በአጥኚ ድርጅቱ የተዘጋጀውን የታሪፍ ፖሊሲ ማሻሻያ ለኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን በመላክ ማፅደቅ ቀጣይ ሥራ እንደሆነም ነው የተገለፀው።

@TikvahethMagazine


ነጋዴ ነዎት?
ቀጥታ ከውጭ ሀገር እቃ ማስመጣት ይፈልጋሉ?
ቋንቋ ባለመቻልዎ ምክንያት የደላላ ጣልቃ ገብነትስ መሮዎታል?
ወይስ ውጭ ሀገር ሔደው መስራት ይፈልጋሉ?

ሀሳብዎ ይህ ከሆነ የኛም ፍላጎት እርሶዎን ማስደሰት ነው። እንግሊዘኛ፣አማርኛ፣አፋን ኦሮሞ እና አረብኛ ቋንቋን ባሉበት ሆነው በኦንላይን ልናስትምርዎ እጅግ የላቀ ልምድ ያላቸውን መምህራን አዘጋጅተን እየጠበቅነወት ነው።

@Bright_Training_Center1

@brightregisteral
ለመመዝገብ በእነዚህ ስልኮች በዋት ሳፕ፣ በኢሞ፣በቴሌግራም ያገኙናል
0933666662
0932878889


ሲዝንስ የአእምሮ ጤና ማእከል ልምድ ባላቸው የስነ አእምሮ ባለሙያዎች (Psychiatrists) ፤ የስነ ልቦና ባለሙያዎች (Clinical Psychologists) እንዲሁም ጠቅላላ ሃኪሞች (General Practitioners) ዘመናዊ ንድፈ ሀሳቦችን በመጠቀም የንግግር እና የመድሃኒት ህክምና እና ክትትል እየሰጠ ይገኛል፡፡ አገልግሎቱን በአካል በመምጣት አሊያም በቤትዎ ሆነው በስልክ ማግኘት ይችላሉ፡፡ ከሃገር ውጪ ላሉ ደምበኞቻችን ከስልክ በተጨማሪ በ What’s app ከባለሙያዎቻችን ጋር በቪዲዮ ወይም በድምጽ ቆይታ ማድረግም ይችላሉ፡፡ በተጨማሪም የአእምሮ አድገት ውስንነት ላላቸው ህፃናት ራስን የመቻል ልምምድ እና ስልጠናም በ Special needs psychology ባለሙያ በሳምንት 1 ቀን እየሰጠን እንገኛለን፡፡
ለተጨማሪ መረጃ ወይም ቀጠሮ ለማስያዝ የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
ስልክ +251963400957
+251962689650
ኢ-ሜይል - seasonsmedicaloffice@gmail.com




የኬንያ ፖሊስ በሞያሌ አቅራቢያ ተጨማሪ 7 ኢትዮጵያውያን ማዕድን አውጪዎችን መያዙን አስታወቀ

የኬንያ ፖሊስ በሞያሌ ድንበር መርሳቤት አውራጃ ማዕድን ሊያወጡ እየተጓዙ የነበሩ ተጨማሪ 7 ኢትዮጵያውያንን መያዙን ዘ ስታር ጋዜጣ ዘግቧል።

ሰባቱ ኢትዮጵያውያን በቁጥጥር ስር የዋሉት ከቀናት በፊት የኬንያ ፖሊስ ወርቅ ማውጣት በተከለከለበትና የማዕድን ማውጫው በተዘጋበት ሞያሌ አካባቢ በሚገኝ የዳባሌ ወርቅ ማዕድን ማውጫ ፥ ወርቅ ለማውጣት ሲሞክሩ የነበሩ 5 ኢትዮጵያውያን በተያዙ ማግስት ነው ተብሏል።

@TikvahethMagazine


ቀደም ሲል በውስን የክፍያ አማራጭ ሲደረግ የነበረው የነዳጅ ግብይት ሁሉንም ባንኮች ሊያካትት ነው ተባለ

ቀደም ሲል በቴሌ ብር፣ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክና በኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ሲደረግ የነበረው የነዳጅ ግብይት ዲጂታል የክፍያ አማራጮችን ለማስፋት ሌሎች ተጨማሪ የፋይናንስ ተቋማትን በተለይም ሁሉም ባንኮች እንዲካተቱ ሊደረግ መሆኑን ሪፖርተር አስነብቧል፡፡

አሁን በሥራ ላይ የሚገኙት የክፍያ አማራጮች ውስን በመሆናቸው ምክንያት፣ አንዳንድ ባንኮችና ተገልጋዩ ማኅበረሰብ ቅሬታ ሲያቀርቡ መቆየታቸውን የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ገልጿል።

በዚህም ደንበኛው በተመቸው የክፍያ አማራጭ አገልግሎቱን እንዲያገኝ ለማስቻል፣ የነዳጅ ማስተግበሪያ ሥርዓት ተዘጋጅቶ በቀጣዮቹ ሁለትና ሦስት ወራት ሥራው ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ወደ ትግበራ ለመግባት መታቀዱ ተጠቁሟል፡፡

@TikvahethMagazine


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
🔥ደማቁ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ወደ ሜዳ ሊመለስ ነው🔥

አንድ ቡድን መርተው ቢያውቁም ፔፕ ጋርዲዮላ እና ሚካኤል አርቴታ ባላንጣ ሆነው ሊሰለፉ ግድ ሆኗል

🏆አስተማሪው ከ ተማሪው ጋርለዓመቱ የመጨረሻ ጊዜ ይገናኛሉ!

🎉ዛሬውኑ ፓኬጅዎን ያሳድጉ ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃትእስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት ይከታተሉ!

🎉ከጥር 6 እስከ መጋቢት 22 ደንበኝነትዎን ሲያሳድጉ... እኛም ቀጣዩን ፓኬጅ ለአንድ ወር እንጋብዝዎታለን!

የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ!
https://mydstv.onelink.me/vGln/eth2

#PremierLeagueAllonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #DStvSelfServiceET #StepUp


#update

" ዓቃቢ ህግ በፍርድ ቤቱ በኩል ውሳኔ ከተላለፈ በኃላ ይግባኝ በመጠየቅ ክሱ በዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በኩል እንዲታይ ተደርጓል" - የወምበራ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት

" ይህንን የፍርድ ዉሳኔ የሰጠዉ ዳኛ ከስራና ከደመወዝ ታግዶ እንዲቆይና ጉዳዩ በኮሚቴ ተጣርቶ እንዲቀርብ ትእዛዝ ተሰጥቷል " - የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት

በወምበራ ወረዳ ፍ/ቤት ከዚህ ቀደም ስሙ ያልተጠቀሰው ' ተክለአብ ገለታ ' የተባለው ተከሳሽ የ5 አመት ህጻን ልጅ በመድፈር ወንጀል ተከስሶ #በ6ወር እስራት እንዲቀጣ መወሰኑ ይታወሳል።

ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የወረዳው ፍርድ ቤት ያስተላለፈው ውሳኔ አግባብ አለመሆኑንና አስተማሪነቱን ባለመቀበል ዓቃቢ ህግ በፍርድ ቤቱ በኩል ውሳኔ ከተላለፈ በኃላ #ይግባኝ መጠየቁን የወምበራ ወረዳ ፍትህ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መልካሙ አመንቴ ገልፀዋል።

ጉዳዩን አስመልክተው ለወረዳው ኮሚዩኒኬሽን ማብራሪያ የሰጡት የፅህፈት ቤቱ ሃላፊ የወረዳው ፍርድ ቤት ባስተላለፈው የቅጣት ውሳኔ ከተፈፀመው ወንጀል ጋር ተመጣጣኝና አስተማሪ ባለመሆኑ ይግባኝ ተጠይቆ ክሱ በዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በኩል እየታየ መሆኑን  አስረድተዋል።

ይህንን ተከትሎ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት የመዝገቡን የክስ ሂደት ማጣራትና ማስተካከያ እርምጃ እንዲወሰድ ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት ወደ መተከል ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ኮሚቴ በመላክ ጉዳዩ በአስቸኳይ እንዲጣራ ኮሚቴ መላኩን አሳውቋል።

ጠቅላይ ፍ/ቤቱ " ይህንን የፍርድ ዉሳኔ የሰጠዉ ዳኛ ከስራና ከደመወዝ ታግዶ እንዲቆይና በኮሚቴዉ ጉዳዩ  ተጣርቶ ሲቀርብ ቀጣይ በዲስፕሊን ታይቶ በክልሉ ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ተገቢውን የእርምት እርምጃ ይወሰዳል " ብሏል።

የተፈፀመው የወንጀል ድርጊት ቅጣት ማነስ ጋር በተያያዘ ጉዳዩ በመተከል ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት በይግባኝ እየታየ መሆኑን ያረጋገጠው የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት የሚሰጠውን ዉሳኔ በቀጣይ መረጃዉን ይፋ እንደሚያደርግ አሳውቋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከወምበራ ኮሚኒኬሽን እና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት እንዳገኘው ያሳውቃል።

@TikvahethMagazine


#AddisAbaba

የአንበሳ እና ሸገር ከተማ አውቶቡሶች የመገልገያ ትኬት ከነገ ጀምሮ የሚቀየር መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት አስታወቀ።

ትኬቶችን የመቀየር ስራ የመዲናዋ የትራንስፖርት ቢሮ በኪሎ ሜትር ባወጣው የትራንስፖርት ታሪፍ መሰረት ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑን አስታውቋል። በመሆኑም አውቶቡሶቹ ከዚህ ቀደም ሲጠቀሙበት የነበረው ትኬት በባለ 5፣ 10፣ 15፣ 20 እና ባለ 25 ብር ይቀይራል ብሏል፡፡

በዚህም መሰረት የካቲት 19 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በሁለቱም ድርጅቶች የተቀየረው አዲስ ቲኬት ሙሉ በሙሉ ሥራ የሚጀምር ሲሆን በአዲስ መልክ ስራ ላይ የሚውለው ትኬት ከነባሩ የተለየ ቀለም፣ ወጥ የሆነ ዋጋ፣ ምስጢራዊ መለያ ያለው መሆኑን የዘገበው ኢዜአ ነው።

@TikvahethMagazine


በህዳሴ ግድብ ዙሪያ የሚሰራው ሰው ሰራሽ  ሀይቅ 70 ደሴቶች ይኖሩታል ተባለ

በህዳሴ ግድብ ዙሪያ በሚኖረው ሰው ሰራሽ  ሀይቅ በግድቡ ዙሪያ የሚጠራቀመው ውሃ እየሰፋ ሲሄድና ግድቡ ሲጠናቀቅ 70 ደሴቶች እንደሚኖሩት ሸገር ኤፍ ኤም ዘግቧል።

በግድቡ ዙሪያ የተንጣለለው ዉሃ 246 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሰው ሰራሽ ሀይቅ እንደሚፈጥር ሲገለፅ ይህም የጣና ሀይቅን በ 3 እጥፍ እንደሚበልጥ መገመቱን ተነግሯል፡፡

በሚፈጠረው ሰው ሰራሽ ሀይቅ ለመጓጓዣነት የሚያገለግሉ ብዙ ጀልባዎችም ያስፈልጋሉ የተባለ ሲሆን የግድቡ የህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት፤ የህዳሴ ግድብ የተጀመረበት 13ኛ ዓመትን የፊታችን መጋቢት 24 እንደሚያከብር ገልጿል።

@TikvahethMagazine


በአሜሪካ የሚኒሶታ የሀይማኖት ተቋማት ፆታ የሚቀይሩ ሰዎችን የመቅጠር የህግ ግዴታ እንዳይጣልባቸው ጠየቁ

በአሜሪካ ሚኒሶታ የካቶሊኮች፣ ሉተራኖች፣ አይሁዶች እና ሙስሊሞች የሃይማኖት ጥምረት ቡድን የሃይማኖት ድርጅቶች እና ትምህርት ቤቶች ሀይማኖታዊ እሴቶችን የሚጥሱ ጾታ ቀያሪ ግለሰቦችን ከመቅጠር ግዴታ ነፃ እንዲሆኑ የሚያደርገውን የሚኒሶታ የሰብአዊ መብት ድንጋጌ እንዲሻሻል ጠይቀዋል።

ባለፈው አመት ህግ አውጪዎች የሚኒሶታ የሰብአዊ መብት ድንጋጌ ላይ በፆታ ማንነት ላይ የተመሰረተ መድልዎን የሚከለክል ህግ ማውጣታቸው ሲገለፅ የሀይማኖት ተቋማቱ ግብረ ሰዶማውያንን በተቋሞቻቸው የመቅጠር ግዴታ እንዳይኖርባቸው ቢደረግም ፆታን የሚቀይሩ ዜጎች ላይ የተቀመጠ አመልካች ህግ አልነበረም።

አሁን ላይ እንዲፀድቅ የተጠየቀው አዲስ ድንጋጌ ሁሉም የሃይማኖት ድርጅቶች እና ተቋማት ከፆታ ማንነት ጋር በተገናኘ ጾታ ቀያሪዎችን በግዴታ የመቅጠር ፖሊሲውን ከመከተል ነፃ ለማድረግ ያለመ ነው ሲባል የሀይማኖት ተቋማቱ ያለ ህዝባዊ የመብት ሙግት ጾታ ቀያሪ ሰዎችን መቅጠር መተው እንደሚፈልጉ ተነግሯል።

@TikvahethMagazine


በኢትዮጵያ ባለፉት 15 አመታት በተደረገ የአሰሳ ጥናት ከ517 ቶን በላይ የወርቅ ክምችት መገኘቱ ተረጋገጠ

በኢትዮጵያ ካለፉት 15 ዓመታት ጀምሮ በተደረገው የወርቅ ማዕድን ክምችት የዳሰሳ ጥናት ከ517 ቶን በላይ የወርቅ ክምችት መገኘቱን የማዕድን ሚኒስቴር ገልጿል በማለት ኢፕድ ዘግቧል።

የወርቅ ክምችቱ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ጋምቤላ፣ ኦሮሚያና ትግራይ ክልሎች መገኘቱ ሲገለፅ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በኢትዮጵያ ትልቁና የመጀመሪያ የሆነው የወርቅ ኩባንያ ፋብሪካ እየተገነባ መሆኑንና በወለጋ፣ በጉጂ፣ በጋምቤላ እና ትግራይ ተጨማሪ የወርቅ ማውጫ ኩባንያዎች ይገነባሉ ተብሏል፡፡

@TikvahethMagazine


#ኢትዮ_ኢስታንቡል_አጠቃላይ_ሆስፒታል

የሕክምና ባለሙያዎችን ወደ ኢትዮጵያ በማስመጣትና ሀገር ውስጥ የማይታከሙ ህመሞችን በቱርክ ሆስፒታሎች ለማከም እንዲሁም የኦክስጅን ማምረቻ ፕላንት ለመግጠም የሚያስችል 3 ስምምቶች መፈረራሙን ኢትዮ-ኢስታንቡል አጠቃላይ ሆስፒታል አስታወቀ።

ኢትዮ-ኢስታንቡል አጠቃላይ ሆስፒታል በቱርክ ሀገር ከሚገኙ አሲባዳም እና ሚዲፖል ሆስፒታሎች ጋር የሕክምና ባለሙያዎችን ወደ ኢትዮጵያ በማስመጣት ውጭ ሀገር የሚያስኬዱ ሕክምናዎችን እዚሁ ለማከም የሚያስችልና በሀገር ውስጥ ጨርሶ ሊታከሙ የማይችሉ እንደካንሰር፣ የኩላሊት ንቅለ ተከላና መሰል ሕመሞች በተመጣጣኝ ዋጋ በቱርክ ሆስፒታሎች ለታካሚዎች ለማስገኘት የሚያስችል ስምምነት መፈረሙን ገልጿል።

በተጨማሪም ሆስፒታሉ የኦክስጅን ማምረቻ ፕላንት ለመግጠም ወርልድ ኦክስጅን ኩባንያ ጋር በኢትዮጵያ ብቸኛ ወኪል እንዲሆን የሚያስችለውን ስምምነት ፈጽሟል። የኦክስጅን ማምረቻ ፕላንት መግጠም የሚፈልጉ ሆስፒታሎች ኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል በመመዝገብ አገልግሎቱን ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።


ሲዝንስ የአእምሮ ጤና ማእከል ልምድ ባላቸው የስነ አእምሮ ባለሙያዎች (Psychiatrists) ፤ የስነ ልቦና ባለሙያዎች (Clinical Psychologists) እንዲሁም ጠቅላላ ሃኪሞች (General Practitioners) ዘመናዊ ንድፈ ሀሳቦችን በመጠቀም የንግግር እና የመድሃኒት ህክምና እና ክትትል እየሰጠ ይገኛል፡፡ አገልግሎቱን በአካል በመምጣት አሊያም በቤትዎ ሆነው በስልክ ማግኘት ይችላሉ፡፡ ከሃገር ውጪ ላሉ ደምበኞቻችን ከስልክ በተጨማሪ በ What’s app ከባለሙያዎቻችን ጋር በቪዲዮ ወይም በድምጽ ቆይታ ማድረግም ይችላሉ፡፡ በተጨማሪም የአእምሮ አድገት ውስንነት ላላቸው ህፃናት ራስን የመቻል ልምምድ እና ስልጠናም በ Special needs psychology ባለሙያ በሳምንት 1 ቀን እየሰጠን እንገኛለን፡፡
ለተጨማሪ መረጃ ወይም ቀጠሮ ለማስያዝ የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
ስልክ +251963400957
+251962689650
ኢ-ሜይል - seasonsmedicaloffice@gmail.com


በኢትዮጵያ ባለፈው የካቲት ወር ብቻ 705 ሺ ሰዎች በወባ ተይዘው 764 ሰዎች መሞታቸው ተገለፀ

በኢትዮጵያ ባለፈው የካቲት ወር ውስጥ ብቻ 705 ሺ ሰዎች በወባ በሽታ ተይዘው፥ 764 ሰዎች መሞታቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (OCHA) ባወጣው ሪፖርት አስታወቀ።

በሪፖርቱ መሰረት በኢትዮጵያ በወባ በሽታ ተይዘው የተመዘገቡ ሰዎች ቁጥር ወደ 5.2 ሚሊዮን ከፍ ሲል፥ የሟቾች ቁጥርም በጥር ወር ከነበረነት 611 በየካቲት ወር ወደ 764 ጨምሯል። በዚህም የሟቾች ቁጥር በ25 በመቶ መጨመሩን ሪፖርቱ አመልክቷል።

በወባ በሽታ ​​የተያዙት ሰዎች አብዛኞቹ በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ ሲሆኑ የአማራ፣ ደቡብ ምዕራብ እና ደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች በቅደም ተከተል ከፍተኛውን በወባ በሽታ የተያዙ ሰዎች ቁጥር አስመዝግበዋል። የጋምቤላ ክልል ደግሞ ከ100,ሺ ሰዎች መካከል ከፍተኛውን በወባ የተያዙ ሰዎች ቁጥር እንዳስመዘገበ ተጠቁሟል።

@TikvahethMagazine


ኢትዮጵያ ማዳበሪያ ከውጭ ለማስገባት የኬንያን ላሙ ወደብ ልትጠቀም ነው ተባለ

ኢትዮጵያ በኬንያ ላሙ ወደብ በኩል ከውጭ ማዳበሪያ ለማስገባት ከሳምንት በፊት ሁኔታውን እንዲገመግሙ ልዑካን ቡድኗን ወደ ኬንያ መላኳን ካፒታል ዘግቧል።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታው ደንጌ ቦሩ “ወደቡን በቅርቡ እንጠቀማለን” ያሉ ሲሆን ልዑካን ቡድኑ ያገኘውን ውጤት ለትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር እንደሚያቀርብና በእቅዱ መሰረት ከፊሉ የማዳበሪያ ጭነት በላሙ ወደብ በኩል እንደሚጓጓዝ ተገልጿል።

ኢትዮጵያ ከህዳር ወር ጀምሮ በቀይ ባህር እና በኤደን ባህረ ሰላጤ ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት የጅቡቲ ወደብን መጠቀም እክል እንደሆነባት ተገልጿል። ይሁን እንጂ ከጅቡቲ ወደብ ጋር ሲወዳደር ኢትዮጵያ ልትጠቀመው ያቀደችው አማራጭ የኬንያ ወደብ ከርቀቱ አኳያ የሚያስወጣው ዋጋ ውድ እንደሆነ ተነግሯል።

@TikvahethMagazine

Показано 20 последних публикаций.