ደብረ ዘይት ሚዲያ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


ቤተክርስቲያን ሆይ ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ ።

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций


#ዘወረደ_አራት_ነገሮች_ይነገሩበታል 👇
1.የአዳም ከገነት ወደ ምድረ ፋይድ መውረድ
2.የወረደውን ለመመለስ የአካላዊ ቃል ከሰማይ መውረድ
3.ከሰማይ የወረደው ጌታ የተሰቀለበት የዕፀ መስቀል ከኢየሩሳሌም ወደ ፋርስ መውረድ
4.ክርስቶስ የወረደለት የእኛ ሰውነት ከጽድቅ ከቅድስና ወደ ኃጢአት መውረድ በሥጋ ወደ መቃብር በነፍስ ወደ ሲኦል ይነገርበታል!

ለአራቱም ከፍታ/መመለስ/ትንሣኤ/ዕርገት አላቸው 👇
1.አዳም ወደ ገነት ተመልሷል
2.ክርስቶስም ወደ ሰማይ ዐርጓል
3.ዕፀ መስቀሉም በንጉሠ ሮም ኅርቃል አማካይነት በምእመናነ ኢየሩሳሌም ጾምና ጸሎት በ 614 ዓ.ም ወደ ኢየሩሳሌም ተመልሷል
4.እኛም በንስሐ እናርጋለን (ወደ ጽድቅ ወደ ቅድስና እንመለሳለን)

አጠቃላይ የጾሙ ምሥጢርም ይኸው ነው
ከፍታ የሚነገርበት በይቅርታ እግዚአብሔርን የምንመስልበት የሥጋ ሳይሆን የመንፈስ ለውጥ የምናሳይበት ነው!
👉ጾም ዕድል ነው
• የመለወጥ እድል
• ንስሓ የመግባት ዕድል
• የመቁረብ ዕድል
• ራስን የማየትና የማዳመጥ
• የጽሙና የፀጥታና የመረጋጋት ዕድል
• የጸሎትና የስግደት
• የማስቀደስ ...ከመላእክት ጋር ከቅዱሳን ከጻድቃን ከሰማዕታት ጋር የማመስገን ዕድል
• በአጠቃላይ የእግዚአብሔርን የምሕረት ፊት የማየት ዕድል ነው!!!

ጾሙን ለምሕረትና ለበረከት ድል ለመንሣት ያድርግልን🙏

ሠናይ ዐቢይ ጾም!

መጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ ከፍያለው

ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
ዩቱብ
https://www.youtube.com/@12Samual

ቴሌግራም
https://t.me/tsidq

ቲክ ቶክ
https://vm.tiktok.com/ZMkpyjd6h




ኹለት ጉዳዮች...
በሊቀ ሊቃውንት ስሙር አላምረው
1ኛ፦
ነገረ ማርያም፥ እንኳን የአዳምን መርገም የተፈጥሮን ሕግ የሻረ ነው።
አሮጌው ክርክር በቤታችን እንደ አዲስ ባይነሣ ጥሩ ነበር።

ለማንኛውም፥
አምጦ መውለድ የመርገም ውጤት ነበር።
“ለሴቲቱም አለ፦ በፀነስሽ ጊዜ ጭንቅሽን እጅግ አበዛለሁ፤ በጭንቅ ትወልጃለሽ።” እንዲል
ዘፍጥረት 3፥16።
ጌታችን ክርስቶስ ይኽን ቀዳማዊ(አበሳ ዘጥንት) መርገምንና ኀጢኣትን ከደመሰሰልንም በኋላ፥በሰማንያ ቀን ተጠምቀው ከእግዚአብሔር ለተወለዱ እናቶችም በምጥ መውለድ አልቀረም።
እንግዲህ ሴቶች በምጥ ስለወለዱ፥ የወደቀ ሥጋ ስለያዙ ነው እንላለን?? አንልም።

እንዲኽ የምንል ከኾነማ የክርስቶስ ቤዛነት ከመርገም ከፍሎ ያስቀረው አለ ያሰኝብናል።
ነገረ ማርያም፥ የተፈጥሮን ሕግ እንኳ የሻረ መኾኑ፥ ሰይጣን እንኳ ያወቀው ፀሓይ የሞቀው ዕውነት ነው።
ለዚኽም ምስክራችን ብዙ ነው።አንዱን ብንጠራ እንዲኽ ይለናል።
"ወሊድ ዘእንበለ መወልዲት ወዘእንበለ ሕማም፤
ያለ አዋላጅ ያለ ሕመም መውለድ"። እያለ ይደነቃል ኤራቅሊስ።

ጌታችን ክርስቶስ ከመሰቀሉ አስቀድሞ የውድቀት ውጤት የኾነው ምጥ በወሊድ ጊዜ ካላገኛት
የመርገም ምልክት የነበረ መስቀልን የድል ምልክት አድርጎት የኀጢኣት ውጤት የነበረ ሞትን በሞቱ ክቡር አድርጎት ሳለ፥ የእመቤታችን ሞት እንዴት የውድቀት ምልክት ይኾናል?አይኾንም።
ሲጠቃለል
ነገረ ማርያም፥ እንኳን የአዳምን መርገም የተፈጥሮን ሕግ የሻረ ነውና ዕፁብ ብለን ማለፍ ይሻለናል።

2ኛ፦
በማኅበራዊ ሚዲያ ብዙ ወጣት ከሚሰማቸው አንዱ ወንድማችን፥ አገልግሎቱን ለጊዜው እንዳቆመ ሰማኹ። እኔ ግን እላለኹ። አገልግሎቱን ከምታቆም አቋምኽን አስተካክል። ምን ማለት ነው? ዕይታኽ ከውስጥ ወደ ውጭ ይኹን።
እና ደግሞ በአብነት ትምህርት ወይም በነገረ መለኮት ትምህርት ቤት የሚነሱ አከራካሪ ጉዳዮችን በማኅበራዊ ሚዲያ አታንሣ።
የጥብርያዶስ ቀለም ለዮርዳኖስ አይኾንም። ቦታው አይደለምና።

ወንድማችን ላይ ጥርጣሬ ያለን ሰዎች፦
ከመቶ ዘጠና ያመጣውን ተፈታኝ ከትምህርት ማባረር አግባብ አይደለም። ሙሉ በሙሉ ፈተናውን እንዲያልፍ ከተፈለገ እንዲያነብብ ያነበበውን በውስጣዊ ዐይን እንዲረዳ ማድረግ ነው ትርፍ። ማባረር ኪሳራ ነው።

ውስጣዊ ዐይን የምለው ምኑን መሰላችኹ?
ኹሉም የሊቃውንት መጻሕፍት ትርጓሜዎች ናቸው። ለምሳሌ የቄርሎስ የዮሐንስ... መጻሕፍት ሃይማኖተ አበውን ጨምሮ ራሳቸው ሊቃውንቱ ሲጽፏቸው በትርጓሜ መልክ ነው።
የእኛ ሊቃውንት ደግሞ ትርጓሜውን ተረጎሙት። ዐውድ እንዳንስት በሀገርኛ ምሳሌ አብራሩት። የሊቃውንት መጻሕፍት የትርጓሜ ትርጓሜ ናቸው። ውስጣዊ ዐይን ያልኩት ይኽ ነው።

Edited
"የወደቀ ሥጋ ማለት ሞት የሚስማማው ማለት ነው" የሚል መልስ እያየኹ ነው፡፡ መልካም፡፡
አዳም ከመውደቁ በፊት ሞት የሚስማማው እንጂ የማይስማማው አልነበረምኮ፡፡ ስለኾነም "የወደቀ ሥጋ" ማለትና ሞት የሚስማማው ማለት፥ እንዴት አንድ እንደሚኾን ለሚነግረኝ ሰው እርማቴ ፈጣን ነው፡፡

መጭው ዐቢይ ጾም የፍቅር ጾም ይኹንልን።






እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና
የሐዋርያት ሥራ 4-12


1 በገና በ437,000 ብር በጨረታ ተሽጧል።

በዕለተ ሰንበት የመቄዶንያ ገቢ ማሰባሰብ ዘመቻ ከኤማን የዜማ መሳሪያ ማሰልጠኛ የተበረከተው ይህ በገና ለጨረታ ቀርቦ ነበር።

ከአሜሪካ ሜሪላንድ በአንድ እህታችን አማካኝነት በ437,000 የኢትዮጲያ ብር ተሽጧል።

አሸናፊዋ ስሜ አይጠቀስ ያሉ እህትም በገናው ለመቄዶንያ እንዲሰጥና አንድ ሰው ሰልጥኖ ለአረጋውያኑ እንዲዘምርላቸው እንደሚፈልጉ ነገሩን።

ኤማን ማሰልጠኛም ከመቄዶንያ አንድ ሰው በነጻ እንደሚያሰለጥን ቃል ገብቷል።

ቢኒም አመስግኖ ተቀብሏል።

መስከረም ጌታቸው


በደብራችን የነበረው ልዩ ጉባኤ ሊቀ መዘመራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ




ሲኖርህና ስትኖር ብዙ ሰዎች በዙርያህ ይኖራሉ
ከሌለህና ከሌለህ ወዳጁ ጠላት ዘመድም ባዳ ይሆናል
8/6/2017 ዓ/ም


ተወዳጆች ሆይ! እስኪ ልጠይቃችሁ፦ አንድ ሰው የተጣራ ወርቅ ልሰጣችሁ እመጣለሁና የኾነ ቦታ ላይ ጠብቁኝ ቢላችሁ ምን ታደርጋላችሁ? ወደዚያ ቦታ ለመሔድ አስፈላጊ ነው የምትሉትን ኹሉ አታደርጉምን? ቀኑን ሙሉም ቢኾን ቁጭ ብላችሁ አትጠብቁምን? እግዚአብሔር እሰጣችኋለሁ ያላችሁ ግን አንዲት ወይም ዐሥር ወይም ሃያ ወይም መቶ ወይም አንድ ሺሕ ቅንጣት ወርቅ አይደለም፤ ወይም ምድርን ኹሉ አይደለም፡፡ ከዚህ ኹሉ የምትበልጠው መንግሥተ ሰማያት እንጂ፡፡ ከዚህ የሚበልጥ ስጦታ ታዲያ ምን አለ? ይህን ስጦታ ለማግኘት የማይደክሙ ሰዎችስ እንደምን ያሉ ምስኪናን ናቸው?

የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ ጸልዩ!
ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
ዩቱብ
https://www.youtube.com/@12Samual

ቴሌግራም
https://t.me/tsidq

ቲክ ቶክ
https://vm.tiktok.com/ZMkpyjd6h






በእርግጥም ዮናስ በሽተኛ አክሞ ስለዳነለት የሚበሳጭ ሐኪም ሆነ፡፡ የነነዌ ሰዎች ግን የሰባኪው ማንነት ፣ የስብከቱ ውበት አልባነት ፣ የአነጋገሩ ለዛ ምክንያት ሳይሆናቸው ተስፋ በማይሰጥ ስብከት ተሰብረው ራሳቸውን አዳኑ፡፡ ብዙ ስብከት አልፈለጉም ፤ ክፋትን ለመተው እና ይቅር በለን ለማለት የተሰበረ ልብ እንጂ በእውቀት መሞላት አያስፈልግም፡፡ ኃጢአታችን ከነነዌ ሰዎች ከበለጠ ቆየ ፤ የጋራ ክፋታችንን በጋራ ንስሓ እንጠበው፡፡

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ጾመ ነነዌ 2011 ዓ.ም
አረንዳል ኖርዌይ

ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ!

የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ ጸልዩ!
ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
ዩቱብ
https://www.youtube.com/@12Samual

ቴሌግራም
https://t.me/tsidq

ቲክ ቶክ
https://vm.tiktok.com/ZMkpyjd6h


+ ጣዕም የሌለው ስብከት
በዲያቆን ሄኖክ ሐይሌ

ወደ ከተማችን አንድ ሰባኪ ሊሰብክ መጣ ፣ የመጣው ለመስበክ ፈልጎ አልነበረም፡፡ እኛን ለማዳን ጉጉት አድሮበት ፣ የእግዚአብሔርን ቃል ሊያሰማን ጓጉቶ አልነበረም፡፡ በግድ ተገፍትሮ ፣ ተተፍቶ ፣ ተወርውሮ የመጣ ዓይነት ሰው ነበር፡፡ ወደ መሃል ከተማም አልገባም የከተማችን አንድ ሦስተኛውን ብቻ ከተጓዘ በኋላ ስብከቱን ጀመረ፡፡ የሰበከው ስብከት ሰላምታ የለውም ፣ መግቢያ የለውም ፣ መውጫም የለውም ፣ ማጽናኛም የለውም ፣ ‹ንስሓ ግቡ› የሚል አዋጅ የለውም፡፡ በጩኸት የተናገረው አንድ አስደንጋጭ ዐረፍተ ነገር ብቻ ነበር ‹‹በሦስት ቀን ውስጥ ነነዌ ትገለበጣለች!!›› ከነነዌ ነዋሪዎች አንዱ የነነዌን ታሪክ ቢጽፈው የሚጽፈው እንዲህ ነበር፡፡

የነነዌ ሰዎች እግዚአብሔርን የማያውቁ አሕዛብ ናቸው፡፡ ዮናስ ደግሞ እነርሱ የማያውቁትን አምላክ የሚያመልክ ነቢይ ነው፡፡ ዮናስ ወደ እነርሱ የመጣው የማዳን ተልዕኮ ይዞ አልነበረም፡፡ ወደ አሕዛብ መላኩ አላስደሰተውም፡፡ ዮናስ ወደ ነነዌ የመጣው እንደ ሌላ ሰባኪ በየትኛውም ትራንስፖርት ተጉዞ ሳይሆን በዓሣ አንበሪ ወደ ነነዌ ተተፍቶ ነው፡፡ የተተፋ ሰባኪ እንዴት ደስ ብሎት ይሰብካል? እንኳን ስብከት ይቅርና ማንኛውም ሥራ ያለ ፍላጎት እንዴት ሊሳካ ይችላል? ዮናስ የነነዌ ሕዝብ እንዲድን ፍላጎትም አልነበረውም፡፡ እንዲያውም ከመጀመሪያውም ፍርሃቱ ‹ትጠፋላችሁ› ብሎ ተናግሮ ሳይጠፉ ቢቀሩስ የሚል ነበር፡፡

ዮናስ ወደ ከተማይቱ ዘልቆ ሲገባም በፍላጎት አልሰበከም ፤ የሰበከው ስብከት ተስፋ የሚያስቆርጥ ፣ እንደ ሰይፍ የሚቆራርጥ ነበር፡፡ የነነዌ ሰዎች የማያውቁትን አምላክ እንዲያውቁ ዕድል የሚሠጥ ትምህርት አልተሠጣቸውም፡፡ ዮናስም እንደ ኖኅ ‹ይኼንን ያህል ዘመን ተሠጥቷችኋል ተመለሱ› ብሎ አልሰበከም፡፡ መርከብ ሠርቶ ግቡም አላላቸውም፡፡ ‹በሦስት ቀን ውስጥ ነነዌ ትገለበጣለች› ብሎ ጮኸ፡፡

የነነዌ ሰዎች ግን ‹ማን ነው የሚገለብጣት?› ‹ለምን ትገለበጣለች?› ‹ለመሆኑ አንተ ማን ነህ?› ‹ዝም ብሎ ትገለበጣላችሁ ይባላል? መጀመሪያ ትምህርት አይቀድምም?› አላሉም፡፡ራሳቸውን እንጂ ሰባኪውንና ስብከቱን ለመገምገም ጊዜ አልነበራቸውም፡፡ ‹‹እግዚአብሔርን አመኑ ለጾም አዋጅ ነገሩ ከታላቁ ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ››

አንድ ላይ ኃጢአት መሥራት ቀላል ነው ፤ አንድ ላይ ንስሓ መግባት ግን ይከብዳል፡፡ በሀገር ደረጃ ንስሓ መግባት ግን እጅግ ያስደንቃል፡፡ ‹ነነዌ የምትገለበጥ ከሆነ ሀገር እንቀይር› አላሉም ፤ ሀገር ከመቀየር ይልቅ ራሳቸውን መቀየር እንደሚሻል ተረድተው ነበር፡፡ ሁሉም እኩል ልቡ ተሰበረ ፤ ሁሉም ማቅ ለበሰ፡፡

የሰባኪው ስብከት ጣዕም የለውም ብለው አላማረሩም ፣ ‹ተስፋ የሚሠጥ ስብከት መቼ ሰማን› አላሉም፡፡ ሰባኪው እያዋዛ አላስተማራቸውም ፣ ምሳሌ አልነገራቸውም ፣ ቅኔ አልተቀኘላቸውም ፣ ቅዱስ ኤፍሬም እንዲህ ይላል ‹‹የተላከላቸው ጨካኝ ሐኪም ነበር ፤ የያዘው መድኃኒትም የሚያቃጥል ነበር ፤ እንደ ሰይፍ የሚቆራርጥ ቃል ተናገራቸው ፤ እነርሱ ግን አቁስሏቸው ተፈወሱ››

የነነዌ ሰዎች ንስሓ ከላይ እስከታች ነበር፡፡ ነገሥታቱ ሳይቀር ማቅ ለበሱ፡፡ ‹‹ነነዌ ትገለበጣለች› ብሎ ሲናገር ንጉሡ ወታደሮች ልኮ ዮናስን ማሰር ይችል ነበር፡፡ ‹‹ምን በሀገራችን ላይ ታሟርታለህ?›› ብለው አፉን አላፈኑትም፡፡ መፍትሔውን ንገረን ያለውም የለም ፤ ችግሩ እነርሱ ናቸውና መፍትሔውንም ያውቁታል፡፡ ስለዚህ ራሳቸውን መውቀስ ወደዱ፡፡

ሀገሪቱ በአንድ ልብ አለቀሰች፡፡ ንጉሡ ፡- ሰዎችና እንስሶች አንዳች አይቅመሱ! ብሎ አዋጅ አስነገረ፡፡ ከቤተ መንግሥት ጾም የሚታወጅባት ነነዌ እንዴት የታደለች ናት? ‹‹መኳንንቶችሽ ማልደው የሚበሉ አገር ሆይ ወዮልሽ›› ተብሎ ከተጻፈ መኳንንቶችዋ የሚጾሙላት ሀገር እንዴት የታደለች ትሆን? (መክ. 10፡16) መቼም ሕዝብ ብቻ መጾሙ ነገሥታት ቢበሉ የተለመደ ነው፡፡ ነገር ግን እየበሉ የሚጾምን ሕዝብ መምራት እንዴት ይቻላል? ሲጠጡ እያደሩስ ሲጸልይ የሚያድርን ሕዝብ መምራት እንዴት ይቻላል?

ንጉሥሽ ላንቺ ማቅ ለብሶ ያለቀሰልሽ ፣ እንስሳት ሳይቀር የጾሙልሽ ነነዌ ሆይ ምንኛ የታደልሽ ነሽ? ሕዝብሽ ጾም ሲታወጅ የማያላግጡ ፣ ‹እኔ በፈለግሁበት ጊዜ ነው የምጾመው› ብለው የማይመጻደቁ ፣ እንኳን ከቤተ ክህነት ይቅርና ከቤተ መንግሥት የታወጀን ጾም በትሕትና የሚጾሙብሽ ነነዌ ሆይ ምንኛ የታደልሽ ነሽ? የዋሐን ሕጻናትን ጡት ከልክለው የፈጣሪን ርኅሩኅ ልብ የሚያስጨንቁ ፣ እንስሳትን ከውኃ ከልክለው ለምህላ የታጠቁ የነነዌ ሰዎች ምንኛ ድንቅ ናቸው፡፡

ቅዱስ ኤፍሬም ያቺን ከተማ በዓይነ ሕሊናው በጎበኛት ጊዜ እንዲህ ብሏል ፡-
‹‹የንጉሥ ቤት ግብዣ ተቋረጠ ፣ ንጉሥ ማቅ ለበሰ ፤ ንጉሥ ማቅ ከለበሰ ደግሞ የጌጥ ልብስ ይለብሳል፡፡ በዚያን ጊዜ በነነዌ ወርቃችሁን ብትጥሉ ማንም አይሰርቀውም፤ ሀብታችሁ ያለበትን ቤት ክፍት ትታችሁ ብትሔዱ ማንም ዘው ብሎ አይገባም፡፡ ወንዶች ወደ ሴቶች በምኞት አይመለከቱም ፤ ሴቶችም የሚያያቸውን ለመማረክ ጌጦቻቸውን አላደረጉም፡፡ ከልጆቻቸው ጋር አብረው ወደ መቃብር ሊወርዱ ነውና አረጋውያን በላያቸው አመድን ነሰነሱ፡፡ ወላጆች በልጆቻቸው ጥያቄ ተጨነቁ ፤ አብርሃም ልጁ ይስሐቅ ‹የመሥዋዕቱ በግ ወዴት ነው› ሲለው የተጨነቀው ጭንቀት በነነዌ ወላጆች ተደገመ››

ሶርያዊው የበተ መንግሥቱን ሁኔታም እንዲህ ይሥለዋል፡፡

‹‹የነነዌ ንጉሥ ወታደሮቹን ሰብስቦ እንዲህ አላቸውም ፡- ይህ ድል እንደተጎናጸፍንባቸው ውጊያዎቻችን አይደለም ፤ ከባዕድ ሀገር በተሰማው ዜና ኃያላኖቻችን ሳይቀሩ ተብረክርከዋል ፤ አንድ ዕብራዊ መጥቶ በቃሉ አብረከረከን፡፡የጀግኖች እናት ነነዌ አንድን ለብቻው የመጣ ደካማ ሰው ቃል ፈርታለች፡፡
ስለዚህ ወገኖቼ ፤ የማይፈርስ አጥር እንገንባ ፤ ይህች አጥር ንስሓ ናት ፤ ሥውር ጦርነት ታውጆብናልና ራሳችንን ሥውር መሣሪያ እናድርግ!!››

ዮናስ በነነዌ መመለስ ደስ አልተሰኘም ፤ ትንቢቱ ስለማይፈጸምለት ብቻ አይደለም፡፡ ‹‹የእስራኤል ሽማግሌዎች በሚቀማጠሉባት ሰዓት የነነዌ ሽማግሌዎች ሲያለቅሱ አየ ፤ ጽዮን በዝሙት እንደ ሰም ስትቀልጥ ነነዌ ታነባ ነበር›› እስራኤል ከፈጣሪ በራቁበት ሰዓት አሕዛብ የንስሓ ዕንባ ሲታጠቡ ሲያይ ክብር ከእስራኤል መልቀቁን አይቶ ተከፋ፡፡
ዮናስ እስከመጨረሻው ሰዓት የነነዌን መጥፋት ይጠባበቅ ነበር፡፡ ዮናስ ነነዌ የምትገለበጥበትን ቀን ሲቆጥር ነነዌ ደግሞ ኃጢአትዋን ትቆጥር ነበር፡፡

ዮናስ ስለ ነነዌ እንደ ሙሴ ‹እነርሱን ከምታጠፋ እኔን አጥፋኝ› አላለም ፤ በተቃራኒው ‹እነርሱን ካላጠፋህ እኔን አጥፋኝ› እስከማለት ደረሰ፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም ነነዌን ወከሎ ነቢዩን እንዲህ ይለዋል ፡-
‹‹አንተ ዕብራዊ ሆይ ሁላችን ብንጠፋ ምን ይጠቅምሃል? አንተ ሰባኪ ሆይ በሁላችን መሞትስ ምን የተሻለ ነገር ይገኛል? የማቴ ልጅ ሆይ ወደ መቃብር በጸጥታ ብንወርድ ምን ታገኛለህ? በቃልህ ፈውሰኸን ልናመሰግንህ ስንመጣ ለምን ታዝናለህ? ዕጣህ ነነዌን ተናግሮ ያጠፋት ከመባል ይልቅ ተናግሮ ያተረፋት መባል ቢሆን አይሻልህም? መላእክት በሰማይ ሲደሰቱ አንተ ለምን ታዝናለህ? ዮናስ ሆይ ከእንግዲህ በስምህ የምትጠራ ናትና ነነዌን አመስግናት››


ሰርፀ ፍሬስብሐት መልካም ልደት ይሁንልህ


ወልደ ገብርኤልና ወለተ ገብርኤል መልካም ጋብቻ ይሁንላችሁ




+ እግዚአብሔር ያልተቀየማቸው ተጠራጣሪዎች +

አባ ጊዮርጊስ እንዲህ አለ ፦ አረጋዊው ስምዖን ‘እነሆ ድንግል ትጸንሳለች’ የሚለውን ትንቢት ተጠራጠረ፡፡ ይህ ጥርጣሬው ግን በደል ሆኖ አልተቆጠረበትም ይልቁንም ስሙ አማኑኤል የተባለውን ሕፃን ለማቀፍ አበቃው እንጂ፡፡ [ወኢተኈልቈ ሎቱ ኑፋቄሁ ኀበ ጌጋይ አላ አብጽሖ ኀበ ሑቃፌ ሕፃን ዘስሙ አማኑኤል]

ቶማስም የጌታን ትንሣኤ ተጠራጠረ፡፡ ትንሣኤውን መጠራጠሩ ግን የጌታን ጎን ለመዳሰስ በችንካሩ እጁን ለማስገባት አበቃው፡፡ [ወአብጽሖ ኑፋቄሁ ኀበ ገሢሠ አጽልእቲሁ ለመድኃኔ ዓለም] በእውነት ‘መተላለፉ የቀረችለት ኃጢአቱም የተከደነችለት ምስጉን ነው’ (መዝ 32፡1) እግዚአብሔር የወደደው ሰው ቍስሉ አይመረቅዝም በደሉም አይታሰብም፡፡

ጌታ ሆይ እኔንም ስለ መጠራጠሬ አትቀየመኝ ልደትህን የተጠራጠረው ስምዖንን እንዲያቅፍህ ፈቀድክለት፡፡ ትንሣኤህን የተጠራጠረውን ቶማስ ጎንህን አስነካኸው፡፡ ያኛው ‘ዓይኖቼ ማዳንህን አዩ’ ብሎ ዘመረልህ ይኼኛው ደግሞ ‘ጌታዬ አምላኬ’ ብሎ መሰከረልህ፡፡

ጌታ ሆይ እኔ እምነተ ቢሱንም መጠራጠሬን አትመልከትብኝ፡፡ የሚዋዥቅ ሕሊናዬን አጽናልኝ፡፡ እንደዚያ የልጅ አባት ‘አለማመኔን እርዳው’ እንደ ጴጥሮስ ‘ወደ አንተ እመጣ ዘንድ እዘዘኝ’ በመጠራጠሬ አትቀየመኝ፡፡

መጠራጠሬን አይተህ አትቀየመኝ፡፡ አንድ ትቢያ ቢጠራጠርህ እንደማይጎድልብህ አውቃለሁ:: ስለዚህ ራርተህ እምነትን አድለኝ:: ምናለ ለእኔም ማዳንህን አይቼ እስካምን እንደ ስምዖን ዕድሜ ብትጨምርልኝ? መቼም ላንተ ዘመን አይቸግርህም፡፡ ሺህ ዓመት ለአንተ አንድ ቀን አይደለች? ቢያንስ አምኜ አሰናብተኝ እስክልህ እስከ ቀትር አቆየኝ፡፡ አንተን በእምነት እንዳቅፍህ እርዳኝ እንጂ ስምዖን አሰናብተኝ እንዳለህ እኔም ደስ ብሎኝ አርፋለሁ፡፡ ማዳንህን ሳልረዳ ፣ አንተን በእምነት መዳፍ ሳላቅፍህ መሞትን ግን እፈራለሁ፡፡

"አምላኬ ጌታዬ" ብዬ ብዘምርም እንደቶማስ ካልዳሰስሁህ ሰውነቴ በእምነት አይኮማተርም፡፡ ተጠራጣሪውን የማትንቀው ሆይ ጥያቄው የማያባራ ልቤን ጥርጣሬው የማያልቅ ከንቱ ሕሊናዬን እንደቶማስ ራራለት፡፡ ለእኔ የቆሰልከውን ቁስል በእምነት መዳፍ ካልነካሁ ፤ እጄን ከችንካርህ ካላገባሁ የፍቅርህ ጥልቀት አይሰማኝምና እባክህን ‘ና ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን’ በለኝ፡፡

ሳላውቅህ የኖርኩት ጌታዬ ሆይ እንደዚያ መቶ አለቃ ‘ለካስ የእግዚአብሔር ልጅ ነበረ’ ብዬ ሳልመሰክርልህ አልሙት፡፡ እንደ ሌንጊኖስ ወግቼህ በፈሰሰው በጎንህ ውኃ ዓይኔን አብርተህ ካለማመን ብታወጣኝ ምናለ?
ያላመኑትን የማትንቀው ሆይ ተጠራጣሪዎችን ያልተቀየምከው ሆይ የሚጠራጠርህን ልቤን አትቀየምብኝ፡፡ የሚያስብ የሚጠይቅ አእምሮ ሠጥተህ ለምን ተጠቀምክበት ብለህ አትቀየምምና ስምዖን አቀፈህ ቶማስም ዳሰሰህ!

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ጥቅምት 18 2013 ዓ.ም.

የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ ጸልዩ!
ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
ዩቱብ
https://www.youtube.com/@12Samual

ቴሌግራም
https://t.me/tsidq

ቲክ ቶክ
https://vm.tiktok.com/ZMkpyjd6h/


እርግጠኛ ነኝ በየትኛውም እምነት ውስጥ ብንሆንም አእምሯችን ይጠይቃል።

መልስ ባለማግኘት የተጨነቃችሁ ወይንም ከጓደኛ ወይ ከቤተሰብ የሚመጣ ጥያቄን ለመመለስ የተቸገራችሁ የማኅበረ ቅዱሳን ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ሊቃውንትን መድቧል።

“ሃሎ መምህር” እንዲመለስልዎ የሚፈልጉትን ኃይማኖታዊ ጥያቄዎች በስልክ ቁጥር 0111 55 32 32 በተጠቀሱት በመደዎል ይጠይቁ፡፡

ለጥያቄዎ ማብራሪያ እና መልስ ከመምህራን ያገኛሉ፡፡

Показано 20 последних публикаций.