💛 የ መዝሙር ግጥሞች 💛


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


🇪🇹 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን  አስተምህሮ ና ስርአትን የጠበቁ ቆየት ያሉና አዳዲስ👇👇
👏 የቸብቸቦ መዝሙራት 🎻 የበገና መዝሙራት  
👑 የቅዱሳ መዝሙራት ⛪️ የንግስ መዝሙራት
💍 የሠርግ መዝሙራት 🌦 ወቅታዊ መዝሙራት መገኛ

📢ለ ማስታወቂያ ስራዎች @Miki_Mako

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций


🙏 በማርያም ይሄን ቻናል ሳታዩ እንዳታልፉት ✅JOIN✅ የምትለውን ብቻ ይንኳት።🙏


✞እኔ ግን በምህረትህ ብዛት✞

እኔ ግን በምሕረትህ ብዛት
እኔ ግን በይቅርታህ ብዛት
ወደ ቤትህ እገባለሁ
አመልክሃለው እዘምርልሃለሁ

በሕይወቴ ዘመን አንዲት ነገር ሻትኩኝ
በቤትህ ተጥዬ መኖሬን መረጥኩኝ
ከኃጢአት ድንኳን የአንተን ደጅ ይሻላል
እረፍቴ ጌታዬ እቅፍህ ይሞቃል(፪)
አዝ= = = = =
የክብርህን ሥፍራ ማደርያ ወደድኩት
መቅደስህ ቀደሰኝ ዙፋኔን ጠላሁት
ከዚህች ለምለም ስፍራ ወዴት እወጣለሁ
የተሰበረ ልብ ይዤልህ እመጣለሁ
አዝ= = = = =
በመከራዬ ቀን የተናገርኩትን
ከደጅህ መጥቼ ከንፈሮቼ ያሉትን
ስዕለቴን ልፈፅም ማልጄ እነሣለሁ
የአምልኮ መስዋዕቴን እሰዋልሃለው(፪)
አዝ= = = = =
እንደ ሰብአ ሰገል ይዤ ወርቅ ዕጣኔን
አምሃ አኮቴት መባዬን ከርቤዬን
ልቤን አየሰዋሁ እሰግድልሃለው
ኦሜጋ አልፋ ነህ እቀኝልሀለው

        መዝሙር
  ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ

"እኔ ግን በምሕረትህ ብዛት ወደ ቤትህ እገባለሁ፤ አንተን በመፍራት ወደ ቅድስናህ መቅደስ እሰግዳለሁ።"
መዝ፭፥፯
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


✞ና ና አማኑኤል✞

ና ና አማኑኤል ና መድኃኒቴ
ጽድቅህን አልብሰኝ ይቅር መራቆቴ

የምህረት አባት - - አማኑኤል
የቸርነት ጌታ - - አማኑኤል
ፊትህ የተመላ - - አማኑኤል
ሁሌ በይቅርታ - - አማኑኤል
ካለው ፍቅር በላይ - - አማኑኤል
አባት ለአንድ ልጁ - - አማኑኤል
አምላክ ይወደናል - - አማኑኤል
አይጥለንም ከእጁ- -  አማኑኤል
አዝ= = = = =
መድኃኒቴ ልበል - - አማኑኤል
ድኛለው በሞትህ - - አማኑኤል
ቁስሌ ተፈውሷል - - አማኑኤል
በቁስልህ በሞትህ - - አማኑኤል
ስሸጥህ አቀፍከኝ - - አማኑኤል
ስወጋህ አይኔ በራ - - አማኑኤል
በፍቅርህ አወጣኸኝ - - አማኑኤል
ከዚያ ከመከራ - - አማኑኤል
አዝ= = = = =
አንተ ከኔ ጋር ነህ - - አማኑኤል
አዎ ከኔ ጋራ - - አማኑኤል
ድል አርገህልኛል - - አማኑኤል
የጭንቄን ተራራ - - አማኑኤል
በጉባኤ መሃል - - አማኑኤል
አፌ አንተን አወጀ - - አማኑኤል
የከበረ ደምህ - - አማኑኤል
ነፍሴን ስለዋጀ - - አማኑኤል
አዝ= = = = =
የድንግሏ ፍሬ - - አማኑኤል
የብላቴናዋ - - አማኑኤል
የቤቴ ምሰሶ - -  አማኑኤል
የነፍሴ ቤዛዋ - - አማኑኤል
መሰረቴ አንተ ነህ - - አማኑኤል
ያሳደገኝ እጅህ - - አማኑኤል
አትተወኝም አንተ - - አማኑኤል
ስለሆንኩኝ ልጅህ - - አማኑኤል

መዝሙር
ሲስተር ሕይወት ተፈሪ

"እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።"
                 ኢሳ፯፥፲፬
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


💍የጋብቻ ዓላማ💍

ይህ ምስጢር ታላቅ ነው እንዳለው መጽሐፍ
መኝታውም ንጹሕ የለበትም እድፍ(፪)

እውቀትን ጥበብን ጎናጽፎት ለአዳም
ሁሉን እንዲገዛ አሰልጥኖት በዓለም
ከጎኑ አጥንት ወስዶ በረቂቅ ምስጢሩ
አስማምቶ ፈጠራት ሔዋንን ለክብሩ(፪)
አዝ= = = = =
ዘርን ለመተካት ትውልድ እንዲቀጥል
በትዕዛዘ አምላክ ከአብራክ የሚከፈል
በሕግ እና ሥርዓት በቤቱ ለኖሩት የተሰጠ ጸጋ የምሥጢር አንድነት (፪)
አዝ= = = = =
በጸሎት ለመትጋት በአንድነት ተባብሮ መንግሥቱን ለመውረስ ሕጉንም አክብሮ
ከዝሙት እርቆ ሕይወትን ለመምራት
ፈጣሪ ለሰው ልጅ ያበጀው ሥርዓት(፪)
  አዝ= = = = =
በምድራዊ ኑሮ በመውጣት መግባቱ
እየተረዳዱ በአንድ እንዲበረቱ
የቤተክርስቲያንን ሥርዓት ጠብቀው
ለክብር እንዲበቁ የተሰጠ ሕግ ነው(፪)
አዝ= = = = =
ዘወትር ይታወጅ የጋብቻ ዓላማ
ሙሽሮች ልበሱ ፍቅርን እንደ ሸማ
የነፍስ ዋጋን ትተን ለሥጋ በማድላት
ከመንገድ እንዳንርቅ እንትጋ ለጸሎት(፪)

      መዝሙር
  በማኅበረ ቅዱሳን

"...ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል ከሚስቱም ጋር ይተባበራል ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ።ይህ ምሥጢር ታላቅ ነው፥"
ኤፌ ፭፥፴፪
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


#ተጋብኡ
ተጋብኡ በቅጽበት ለግንዘተ እሙ ቅድስት
ብጹአን(፭)ሐዋርያት
#ትርጉም
ቅድስት እናቱን ለመገነዝ ብጹአን ሐዋርያት በቅጽበት ተሰበሰቡ



#ጊዜ_እረፍታ
ጊዜ እረፍታ(፪) ለሶልያና
ወረደ ወልድ(፬)ወልድ እም ዲበ ልዕልና
#ትርጉም
በማርያም እረፍት ጊዜ ወልድ ከሰማይ ወረደ



#ለዛቲ_ድንግል
ለዛቲ ድንግል(፪)
ወአግአዛ(፪)ለዛቲ ድንግል(፪)
#ትርጉም
ድንግልን ከዓለም ድካም ነጻ አወጣት



#ዘድንግል
ዘድንግል መናስግተ ኢያርኂዎ
ኢያርኂዎ ዘኪሩቤል ኢርእዮ(፪)
#ትርጉም
ኪሩብ በማይመረምረው ምስጢር የድንግል ማህተመ ድንግልናን ሳይከፍት



#አንጺሆ_ሥጋሃ
አንጺሆ ሥጋሃ ቀዲሶ ኪያሃ
ወረደ(፬) ሃደረ ላዕሌሃ
#ትርጉም
ስጋዋን አንጽቶ/ ከሃጢአት ጠብቆ እሷን ለይቶ/አክብሮ ከሷ  ሰው ሆነ።



#እስመ_እም_ዘርዐ_ዳዊት
እስመ እም ዘርዐ ዳዊት ዘመጽአ
በቤተልሄም ዘይሁዳ(፪)
#ትርጉም
ከዳዊት ዘር በይሁዳ እጣ በምትሆን በቤተ ልሄም ሰው ሁኗልና..

╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


#ወልድኪ_ይጼውአኪ
       
ወልድኪ ይጼውአኪ(፪)
ውስተ ሕይወት ወመንግሥተ ክብር (፪)
ልጅሽ ይጠራሻል(፪)
ወደ ሕይወትና ወደ ክብር መንግሥት(፪)

╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


✞አይዞህ ዶኪማስ✞

አይዞህ ዶኪማስ ሆይ ቢያልቅም ወይን ጠጁ
እድምተኛው ቢጎርፍ ቢሞላ በደጁ
ንግሥቷ ስላለች በእድምተኛው መሃል
ያለቀው መጠጥህ ይጨመርልሃል

ወይኑ አለቀ ብለህ ስትጨነቅ በእፍረት
ሰውም ቢስቅብህ ቢያደርግህ ለተረት
የጠራኻት  ንግሥት ልጇ ጋር ያለችው
ከእፍረት አዳነችህ ጋኑን እስሞላችው
አዝ= = = = =
ስድስቱ መጥመቂያ ተሟጥጦ ከስሩ
ዶኪማስ ደንግጦ ሲጓዝ በግንባሩ
የአማኑኤል እናት የክብር እንግዳ
አትረፈረፈችው ያለቀውን ጓዳ
አዝ= = = = =
የጓዳህ ስብራት  ተጠግኖልሃል
ጎዶሎህ በሙሉ ዳግም ሞልቶልሃል
ተትረፈረፈልህ በደስታ ላይ ደስታ
ሠርግህ ላይ ስላለ የሠራዊት ጌታ
አዝ= = = = =
የተራቆታችሁ ጸጋችሁ ያለቀ
የሕይወታችሁ ወይን ዛሬም የደረቀ
የልባችሁ ስፍራ ይደልደል ይዘርጋ
ክፈቱ እና አስገቧት ንግሥቷን ልጇ ጋ

መዝሙር
በኮምቦልቻ ደብረ ምሕረት ቅ/ገ/ሰ/ት/ቤት
ዘርዓይ ደርቤ እና ብዙአየሁ ተክሉ

ዮሐ፪፥፩-፲፭
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


Репост из: 💛 የ መዝሙር ግጥሞች 💛
"በሦስተኛውም ቀን በገሊላ ቃና ሰርግ ነበረ፥ የኢየሱስም እናት በዚያ ነበረች፤
ኢየሱስም ደግሞ ደቀ መዛሙርቱም ወደ ሰርጉ ታደሙ።
የወይን ጠጅም ባለቀ ጊዜ የኢየሱስ እናት። የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም አለችው።
ኢየሱስም። አንቺ ሴት፥ ከአንቺ ጋር ምን አለኝ? ጊዜዬ ገና አልደረሰም አላት።
እናቱም ለአገልጋዮቹ። የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ አለቻቸው።
አይሁድም እንደሚያደርጉት የማንጻት ልማድ ስድስት የድንጋይ ጋኖች በዚያ ተቀምጠው ነበር፥ እያንዳንዳቸውም ሁለት ወይም ሦስት እንስራ ይይዙ ነበር።
ኢየሱስም። ጋኖቹን ውኃ ሙሉአቸው አላቸው። እስከ አፋቸውም ሙሉአቸው አላቸው። እስከ አፋቸውም ሞሉአቸው።
አሁን ቀድታችሁ ለአሳዳሪው ስጡት አላቸው፤ ሰጡትም።
አሳዳሪውም የወይን ጠጅ የሆነውን ውሃ በቀመሰ ጊዜ ከወዴት እንደ መጣ አላወቀም፤ ውኃውን የቀዱት አገልጋዮች ግን ያውቁ ነበር፤ አሳዳሪው ሙሽራውን ጠርቶ።
ሰው ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን የወይን ጠጅ ያቀርባል፥ ከሰከሩም በኋላ መናኛውን፤ አንተስ መልካሙን የወይን ጠጅ እስከ አሁን አቆይተሃል አለው።
ኢየሱስ ይህን የምልክቶች መጀመሪያ በገሊላ ቃና አደረገ፤ ክብሩንም ገለጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ።

ዮሐ ፪፥፩-፲፩
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
    @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


#ክርስቶስ_ተጠመቀ

ክርስቶስ ተወለደ ተጠመቀ ክርሰቶስ
ዳግመኛ ወለደን ከውሃ ከመንፈስቅዱስ(፪)


ዮሐ ፫፥፭


መዝሙር
የናዝሬት ደብረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ሰ/ት/ቤት

╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯




Репост из: 💛 የ መዝሙር ግጥሞች 💛
⛪️ መልካም የ ጥምቀት በዓል ያድርግልን ⛪️
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯




ከሰማያት ወርዶ
                
            ● ጸሐፌ ትዕዛዝ
    ♡ዲ/ን ታዴዎስ ግርማ
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


​​✞ከሰማያት ወርዶ✞  
                
ከሰማያት ወርዶ ከድንግል ተወልዶ        
ተገኘ በበረት ራሱን አዋርዶ       
       
የነገሥታት ንጉሥ - - - ተገኘ በበረት       
ቤዛ ኲሉ ዓለም - - - ተገኘ በበረት    
መድኅን ተወለደ - - - ተገኘ በበረት      
በቤተልሔም - - - ተገኘ በበረት   
አራቀልን ከእኛ - - - ተገኘ በበረት    
ቁጣን በትዕግስቱ - - - ተገኘ በበረት    
ታላቅ ነው ከሁሉ - - - ተገኘ በበረት     
የጌታ ልደቱ - - - ተገኘ በበረት   
    አዝ= = = = =   
ለቅዱሳን ክብር - - - ተገኘ በበረት     
ጸጋን ሊያለብሳቸው - - - ተገኘ በበረት     
መጣ ወልደ አምላክ - - - ተገኘ በበረት    
ከመካከላቸው  - - - ተገኘ በበረት
የጠፋው አዳምን - - - ተገኘ በበረት 
ከቦታው መልሶ - - - ተገኘ በበረት      
የተገፈፈውን - - - ተገኘ በበረት     
ጸጋውን አልብሶ - - - ተገኘ በበረት    
በበረት ተገኘ - - - ተገኘ በበረት    
ኮባ ቅጠል ለብሶ - - - ተገኘ በበረት    
  አዝ= = = = =      
የጠፋ አዳምን - - - ተገኘ በበረት       
ከውድቀት ሊያነሣ - - - ተገኘ በበረት    
ተገኘ አምላካችን - - - ተገኘ በበረት    
በቤተ እንስሳ  - - - ተገኘ በበረት     
መላእክት መጡ - - - ተገኘ በበረት    
እረኞች ዘመሩ  - - - ተገኘ በበረት         
የአጋንንት ሰራዊት - - - ተገኘ በበረት    
በሙሉ አፈሩ - - - ተገኘ በበረት
   አዝ= = = = =
ከልዑል መንበሩ - - - ተገኘ በበረት         
ከዙፋኑ ወርዶ  - - - ተገኘ በበረት     
ትሕትናን ሰበከ - - - ተገኘ በበረት    
በበረት ተወልዶ      - - - ተገኘ በበረት    
ቁጣ ሞትን ሽሮ  - - - ተገኘ በበረት    
ጽድቅን አበሰረ  - - - ተገኘ በበረት     
ሰይጣን ድል ተነሣ   - - - ተገኘ በበረት      
መርገምም ተሻረ - - - ተገኘ በበረት    

       ጸሐፌ ትዕዛዝ
  ዲ/ን ታዴዎስ ግርማ
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


#አሰርግዉኒ

አሰርግዉኒ ሥላሴ በቀጠንተ ምጽዋት ሠናይ
እምነ ልማዱ ብሉይ ለነዌ ጊጉይ
እንዘ በዴዴሁ ይግእር አልአዛርን ነዳይ

ሥሉስ ቅዱስ  ሸልመኝ መልካሙን የርኅራኄ ሃር
እንደ ነዌ አርጅቷል ቆልፎ የልቡናውን በር
በደጃፉ ቆሞ ሲማጸን ሲለምን አልአዛር

╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
  @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

"ከሁሉ አስቀድመን በአካል ልዩ በክብር አንድ የሆነውን ሦስትነቱን እንሰብካለን
እነሱም አብ ወልድ መንፈስቅዱስ ናቸው።"

     ሃይማኖተ አበው ዘጎርጎርዮስ ...

✞መቅድመ ኲሉ✞

መቅድመ ኲሉ ንሰብክ ሥላሴ ዕሩየ
ወንዌጥን ሎቱ አኮቴተ ዕሩየ
የዝማሬ አልፋ የአገልግሎት መቅድም
ሥላሴን ማወደስ ብለን አንድም ሦስትም

መሠረተ ሃይማኖት እርሱም በኩረ  አእማድ
ምስጢረ ሥላሴን ማጉላት በአበው ልማድ
ተምረናልና በየ መጻሕፍቱ
ወጠነ ስብሐተ በስመ ሠለሥቱ
አዝ= = = = =
በስም በአካል በግብር በከዊን ሦስት ብለን
ወእንዘ ሠለሥቱ አሐዱ ነው አሚን
አይደርስበት ጠቢብ የተመራመረም
ብሎ ያደንቃል እንጂ ትትነከር ትትረመም
አዝ= = = = =
ንግበር ሰብአ ብለው በአርአያ በአምሳል
መልክአ ሥላሴ በማኅጸን ሲሳል
የሰው ልጆች ሆነን የተፈጠርን ሁሉ
ንበል ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ይደሉ
አዝ= = = = =
አድባራቱ መምሬ ድንኳን ሆኖ መቅደስ
አብርሃም ካህኑ እንዳገኘ ሞገስ
አሐዱ አብ ሲባል ተገለጥ ሥላሴ
በረከትህን ላክ በጊዜ ቅዳሴ

በገነተ ኢየሱስ ገነተ ማርያም
መሠረተ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


Репост из: 💛 የ መዝሙር ግጥሞች 💛
​​በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

በዓለ ግዝረት

ከርእሰ ደብር ብርሃኑ አካል

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅድመ ዓለም በህሊና ያሰበውን፤ ድኅረ ዓለም በነቢያት ያናገረውን ለመፈጸም ሰው ሆነ፣ ሥጋ ለበሰ፤ ሕግ ጠባያዊን ሕግ መጽሐፋዊን እየፈጸመ በጥቂቱ አደገ። ሕግ ጠባያዊ፤ አበ፣ እመ ማለት፣ ለዘመድ መታዘዝ፣ በየጥቂቱ ማደግ ነው። "ወልህቀ በበኅቅ እንዘይትኤዘዝ ለአዝማዲሁ ወለይእቲ እሙ"እንዲል።

ሕግ መጽሐፋዊ በስምንት ቀን ቤተ ግዝረት በአርባ ቀን ዕጉለ ርግብ ዘውገ ማዕነቅ ይዞ ቤተ መቅደስ መግባት የመሳሰሉት ናቸው፤ በማለት የመጻሕፍተ ሐዲስ ኪዳን ሊቃውንት በሐዲስ ኪዳን ትርጓሜ መግቢያ ላይ ያመሰጥራሉ፣ ያስተምራሉ።

ቅዱስ ሉቃስ በጻፈው የጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል ምዕራፍ ፩ ቁጥር ፶፱ ላይ ዘግቦልን እንደምናገኘው፤ በዘመነ ብሉይ ወንድ ልጅ በተወለደ በስምንተኛው ቀን ሲገረዝ ስም ይወጣለት ነበር።በመሆኑም ግዝረት የሥጋ ሸለፈት መቆረጥን ያመለክታል።

የግዝረት ሥርዓት ዝም ብሎ የመጣ ሳይሆን እግዚአብሔር ለአብርሃም የሰጠው የቃል ኪዳኑ ምልክት ነው። ዘፍ፲፯ ፥ ፯-፲፬

በሙሴ የመሪነት ዘመንም ለእስራኤል ህዝብ ምልክትና መለያ ነበር።
ዘፀ ፲፪፥፵፫

ፈሪሳውያን ግን ከአብርሃም የመጣ መሆኑን ሳይረዱ በሙሴ እንደተሰጠ ሕጋዊና ሕዝባዊ ምልክት አድርገው ያምኑ ነበር።የሐዋ፲፭፥፲-፭

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ግን፤ መጀመሪያ ራሱ የሰጠው ለአብርሃም እንደነበርና መንፈሳዊ ምልክትም እንደሆነ አስረድቷቸው ነበር።ዮሐ ፯፥፳፪

የሚከተሉት ሦስት ነጥቦች የግዝረት ዋና ዋና ዓላማዎች ናቸው።

፩.እግዚአብሔር የተገረዘውን ሰው ለራሱ መርጧልና አምላኩ ነው። ዘፍ ፲፯፥፰

፪.የተገረዙት የእግዚአብሔር ህዝቦች ናቸውና ክፋትንም ከህይወታቸው ማስወገድ አለባቸው። ዘጸ፲፥፲፮

፫.እግዚአብሔር በእምነት ስለተቀበላቸው የጽድቃቸው መሠረት ነው። ሮሜ፬፥፲፩

ሆኖም በሐዲስ ኪዳን ሥርዓት ሣይሆን፤ የሚያድነው የእግዚአብሔር ህግ መሆኑን ቅዱስ ጳውሎስ ያብራራል።
ሮሜ፪፥፳፭

ዋናው ነገር የሥጋ ሸለፈት መገረዝ ሳይሆን የልብ መለወጥና በእግዚአብሔር ማመን ሕጉንም መፈጸም ነው፣ ሲል ቅዱስ ጳውሎስ ምዕመናኑን በመንፈስ የተገረዙ መሆናቸውንም ጨምሮ አብራርቷል።ፊሊጵ ፫፥፴

በተለይም ህዝብና አህዛብ ማለትም ትንቢት የተነገረላቸው፣ ተስፋ የተነገራቸው እስራኤላውያን እና ከአህዛብ ወገን የመጡት ሁለቱም የክርስትና አማኞች በግዝረት ምክንያት ያስነሱትን አለመግባባት አስመልክቶ በጻፈው መልእክቱ በሐዲስ ኪዳን ዘመን ጥምቀት በግዝረት ፋንታ መተካቱን ያስረዳል።ቆላ፪፥፲፩

ግዝረትም አሁን አይጠቅምም ይለናል። ገላ ፭፥፮

ወደ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ግዝረት ስንመለስ ደግሞ፤ በመግቢያው እንደተገለጸው ኦሪትና ነቢያትን ልፈጽም እንጂ ልሽራቸው አልመጣሁም እንዳለ፤ ለስም አጠራሩ ክብር ይግባውና እርሱ ራሱ ሥርዓቱን ለመፈጸም ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በተወለደ በስምንተኛው ቀን እናቱ ወደ ቤተ መቅደስ ወስዳው ሊገረዝ በታሰበ ጊዜ በፍጡራን እጅ አልተገረዘም።

ምላጩ በገራዡ እጅ እንዳለ ውኃ ሆኖ ተገኝቷል (መጽሐፈ ስንክሳር ጥር ስድስት)።ይህም በመለኮታዊ ኃይሉ ነው። እርሱም በግብር መንፈስ ቅዱስ ተገርዞ ተገኝቷል።ይህንንም ያደረገው ሰውን ንቆ ስርዓቱንም ጠልቶ ሳይሆን ደመ መለኮቱ ያለ ዕለተ ዓርብ የማይፈስ ስለሆነ እርሱ ባወቀ ይህን አደረገ ስሙንም አስቀድሞ በመልአኩ እንደተነገረ ኢየሱስ አሉት። ሉቃ፪ ፥፳፩

በዚህም ምክንያት ቅድስት ቤተክርስቲያናችንም የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የግዝረት በዓል በየዓመቱ ጥር 6 ቀን ታከብራለች (መጽሐፈ ስንክሳር ጥር ስድስት)።

ስታከብርም በግዝረቱ እለት የተፈጸሙትን ተአምራት በማስተማርና በማሳወቅ ነው።

ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ክብርና ምስጋና  ይሁን!

አሜን!!!

የአሜሪካ ማዕከል - በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ - ማኅበረ ቅዱሳን

╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯


✞ ድንግል ሆይ ወደ እኔ ትመጪ ዘንድ ✞


ደንግል ሆይ ወደ እኔ ትመጪ ዘንድ
ድንግል ሆይ ወደ እኔ ትመጪ ዘንድ እንዴት ይሆናል
እመቤቴ ወደ እኔ ትመጪ ዘንድ እንዴት ይሆናል ደካማ ነኝ እኔ ምግባር ይጎድለኛል (2x)
ወደ ተራራማው ይሁደ ከተማ
ፈጥነሽ ስትመጪ ድምፅሽ የተሰማ
የኤልሳቤጥ ዘመድ የዘካርያስ
ድምፅሽን አሰሚኝ ባንቺ ልቀደስ



በማኀፀንሽ ይዘሽ የሰማይ እንግደ
አንዴት ትመጫለሽ ከታናሽዋ ጓደ
አንዴት ልቀበልሽ እምላኬን ይዘሽ
መንፈስ ቤቴን ሞላው ሲሰማ ድምፅሽ
አዝ= = = = =
በሥጋዊ ሳይሆን በመንፈስ ዓይኖቼ
ለማየት አሻለሁ ከልቤ ጓጉቼ
ሥራዬ የከፋ መሆነን እውቀስሁ
ድምፅሽን ለመስማት አጅግ አፈራለሁ
አዝ= = = = =
አንቺ ቡርክት ነሽ ቡሩክ ያንቺ ፍሬ
ላመንሽዋ ብፅዕት ትዘምር ከንፈሬ
ፅንሰን ደስ አሰኘ የድምፅሽ ሰላምታ
ለዚህ ታላቅ ነገር ይገባል አልልታ
አዝ= = = = =
በሁሉ የሞላው ዙፋኑ ቢያደርግሽ
የመላእክት መዝሙር ተሰማ ከሆድሽ
ሁስተኛ ሰማይ ድንግል ማርያም
ባንቺ ድንቅ አድርጓል መድኀኔዓለም

የአእላፋት ዝማሬ መዝሙር
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯


✞ሳር ቅጠሉ ሰርዶው✞

ሳር ቅጠሉ ሰርዶው ሰንበሌጥ ቄጤማው
በዚያች ቀን በዚያች ወር ለምልሞ የነበረው
በእልልታ ዘመሩ በደስታ ተሞልተው
ጌታ መወለዱን የምስራች ሰምተው


እልል በይ ቤተልሔም ሃሌ ሃሌሉያ
የፍቅር የሰላም ነሽና ገበያ(፪)


እረኝነት ትንሽ የወራዳ ግብር
ብሎ ሰው በልማድ ደንግጎ ነበር
የብዙ ሰው ራስ መሆኑን እረኛ
ክርስቶስ ሲወለድ ተረዳነው እኛ
አዝ= = = = =
የተነበዩለት ነቢያት በሙሉ
ጌታ ተወለደ የምሥራች በሉ
ሰውን በመውደዱ ሰማያዊው ንጉሥ
ይኸው ተወለደ እኛን ለመቀደስ
አዝ= = = = =
የሩቅ ምስራቅ ሰዎች ሰብአ ሰገል ሰምተው
ሊሰግዱለት መጡ በኮከብ ተመርተው
ዕጣንና ከርቤ ወርቁንም አመጡ
እንደየ ስርአቱ እጅ መንሻ ሰጡ
አዝ= = = = =
ስለተወለደ መድኅን የእኛ ተስፋ
በደል ተወገደ ኃጢአትም ጠፋ

መዝሙር
ዲያቆን መገርሳ በቀለ

"አንቺም ቤተ ልሔም ኤፍራታ ሆይ፥ አንቺ በይሁዳ አእላፋት መካከል ትሆኚ ዘንድ ታናሽ ነሽ፤ ከአንቺ ግን አወጣጡ ከቀድሞ ጀምሮ ከዘላለም የሆነ፥ በእስራኤልም ላይ ገዥ የሚሆን ይወጣልኛል።"
ሚክ ፭፥፪
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


✞ልቤ በእግዚአብሔር ጸና✞

ልቤ በእግዚአብሔር ጸና(፪)
አፌን አላቀኩኝ ለስሙ ምስጋና

በጠላቶቼ ላይ አፌ ተከፈተ
ማዳኑን አይቼ ልቤ ተደሰተ
እንደ እግዚአብሔር ያለ ረዳት ማን አለ
ደካማ ባርያውን ስለተቀበለ
አዝ= = = = =
ጠግበው የነበሩ እንጀራን ተራቡ
ተርበው የሚያድሩት እረኩ ጠገቡ
መች ጎድሎብኝ ያውቃል አንተን ተደግፌ
በእጆችህ በረከት ተሞልቷል መዳፌ
አዝ= = = = =
እግዚአብሔር ይገድላል እንዲሁም ያድናል
የኃይለኞችን ቀስት ሰብሮ ይታደጋል
መካኒቱ ሃና ወለደች ሰባት
ሥራህ ይደንቀኛል በቀን በሌሊት
አዝ= = = = =
ምስኪኑን ከጉድፍ ያነሳል ከምድር
ይዘረጋለታል የክብርን ወንበር
ተመከረ ልቤ ሐናን ተመልክቶ
እግዚአብሔር ለጋስ ነው ለጠበቀው ከቶ
     
             መዝሙር
       ዲ/ን ወንድወሰን በቀለ

"ሐናም ስትጸልይ እንዲህ አለች። ልቤ በእግዚአብሔር ጸና፥ ቀንዴ በእግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ፤ አፌ በጠላቶቼ ላይ ተከፈተ፤"
      ፩ሳሙ ፪፥፩

╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯

37k 0 232 119
Показано 20 последних публикаций.