ያሲን ኑሩ️️ YASIN NURU


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Блоги


የ ያሲን ኑሩ ሐዲሶች
Yasin Nuru
"ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የሰራውን ሰው ያህል አጅር ያገኛል" ረሱል (ﷺ)
"የበጎ ስራ ምላሹ በጎ እንጂ ሌላ አይደለም "  
የብናኝ ክብደት ያክልም መልካምን የሰራ ሰው ያገኘዋል :>> { አል -ዘልዘለህ 7}
This is not official
ለአስተያየት👇👇
@Hasabbbbot

ሀዲሶችን ከፈለጋችሁ👇👇
@yasin_nuru_hadis

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Блоги
Статистика
Фильтр публикаций


🍂ዕረፍት

☞ስንቅ የፈለገ አላህን መፍራት ይበቃዋል።

◾️ልዕልና የፈለገ እስልምና ይበቃዋል።

☞ፍትህን የፈለገ የአላህ ፍርድ ይበቃዋል።

◾️አጫዋች የፈለገ አላህን ማስታወስ ይበቃዋል።

☞መካሪን የፈለገ ሞት ይበቃዋል።

◾️ሐብትን የፈለገ መተናነስ ይበቃዋል።

☞ጌጥን የፈለገ እውቀት ይበቃዋል።

◾️ቁንጅናን የፈለገ ጥሩ ፀባይ ይበቃዋል።

☞ዕረፍትን የፈለገ አኺራ ይበቃዋል።
"ይህ ሁሉ ያልበቃው እሳት ይበቃዋል"

@yasin_nuru @yasin_nuru

4k 0 58 31 203

የረመዷን ተናፋቂ ወርን በተሻለ የኢማን ከፍታ እና አንድነታችን በሚያጎላ መንፈሳዊ ክዋኔ ለመፆም «ቁርዓን የእውቀት እና የሰላም ምንጭ» በሚል መሪ ቃል መጋቢት 07/2017 በአብዮት አደባባይ ከኢፍጣራችን ጋር ከፍተኛ የመንግስት ሀላፊዎች፣ የአገር ሽማግዎች፣ ድፕሎማቶች፣ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች እና የተከበረው ህዝባችን በተገኙበት በድምቀት ለማከናወን እየተዘጋጀን እንደሆነ መግለፃችን ይታወቃል።

ውደድሩ የክልል እስልምና ጉዳዮች ክልላቸውን ወክሎ የሚወዳደረውን ተወዳዳሪ  የሚያቀርቡበት ሂደት ስለሆነ  ምዝገባም ሆነ የማጣሪያ ውድድር የሚካሄደው  በክልሎችና በከተማ አስተዳደር እንደሆነ በመረዳት በመርከዝ ደረጃም ሆነ በግል ለመወዳደር የምትፈልጉ በየክልላችሁ ወይም በከተማ አስተዳደር ተወዳድራችሁ በውጤታችሁ መሰረት ለአሸናፊዎች አሸናፊ ወደ ፌደራል እስልምና ጉዳይ በውጤታችሁ መሰረት የምትመጡ ይሆናል። 
አንድ ክልል ወይም ከተማ አስተዳደር አወዳድሮ የሚልከው በክልሉ ወይም ከተማ አስተዳደሩ በወንድ 1ኛ እና 2ኛ የወጣውን ሲሆን በሴት 1ኛ የወጣችውን በድምሩ 3 ተወዳዳሪ በመላክ  የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር ላይ እንዲወዳደር ይደረጋል። 

አዲስ አበባ ላይ  በሚደረገው የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር ላይ መጨረሻ ለሚኖሩት አሸናፊዎች፡-
·    
👉በሁለቱም ፆታ 1ኛ ለሚወጡ ተወዳዳሪዎች የመኪና ሽልማት፤
·      
👉ውድድሩን በ2ኛ ደረጃነት ለሚያጠናቅቅ ወንድ ተወዳዳሪ የሐጅ ዕድል እንዲሁም ለሴት ተወዳዳሪ ብር 500,000.00 (አምስት መቶ ሺህ ብር)፤
·      
👉3ኛ ደረጃ የሚወጡ ወንድም ሴትም ተወዳዳሪዎች ለእያንዳዳቸው ብር 300,000.00 (ሶስት መቶ ሺ ብር) ሽልማት ያገኛሉ። 

እድሜና እና ፆታ በማይወስነው በዚህ የቁርዓን ውድድር ላይ በክልላችሁ ወይም ከተማ አስተዳደር የእስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት አማካኝነት ተጨማሪ መረጃዎችን የምናሳውቅ ሲሆን  በዚህ ወር ከቁርአን በላይ ቅድሚያ የሚሰጠው ነገር ባለመኖሩ እሁድ መጋቢት 7 ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በአብዮት አደባይ በመገኘት የዝግጅቱ ታዳሚ እንድትሆኑ ተጋብዛችኋል።

@yasin_nuru @yasin_nuru

6.1k 0 13 7 113

የባህርዳር፣አሶሳ፣ሻሸመኔ፣መቀሌ፣ሐረር፣ጅግጅጋ፣መቱ፣ጅማ፣አዲስ_አበባ፣ድሬዳዋ የረመዳን ወር የሰላት ሰዓት

@yasin_nuru @yasin_nuru


ጾመኛ ሆነህ ያለ አግባብ ሊያልፉህ የማይገቡ ③ ወቅቶች‼
=================================

①) የቀኑ የመጀመሪያ → ከፈጅር ሶላት በኋላ፦

በርግጥ ሌሊት ተነስቶ ሰሑር የበላና ተሃጁድ የሰገደ ሰው ከፈጅር በኋላ ከባድ እንቅልፍ የሚያስቸግረው ቢሆንም፤ ግና ያንን ወቅት ጸሐይ እስክትወጣ ድረስ እንደምንም ተቋቁሞ በዚክርና በዒባዳህ ማሳለፍ ወሳኝ ነው።

አል-ኢማም አ-ን'ነወዊይ (አላህ ይዘንላቸውና) በ"አልአዝካር" ኪታባቸው ላይ «በቀኑ ክፍለ ጊዜ እጅግ በጣም በላጩ የዚክር ወቅት ከፈጅር በኋላ ያለው ነው!» ብለዋል።

«የፈጅርን ሶላት በጀማዓህ የሰገደ፣ ከዚያም ጸሐይ እስክትወጣ ድረስ አላህን እያወሳ የተቀመጠ፣ ከዚያም 2 ረከዓህ የሰገደ ሐጅና ዑምራ እንዳደረገ ነው!» የሚል ሐዲሥ አለ።


አስበው ደግሞ ምንዳ እጥፍ ድርብ በሚደረግበት የረመዿን ወቅት ሲሆን!
*
②) የቀኑ የመጨረሻ ጊዜ → ከመጝሪብ በፊት፦
ለኢፍጣር በምንዘጋጅበት በዚህ ወቅት አላህን መለመን ዱዓእን ተቀባይ ያደርገዋል።
*
③) በሰሑር ወቅት → ከፈጅር በፊት፦
ይህ ወቅት አላህ ወደ ዱንያ ሰማይ ወርዶ «ማነው ምህረትን የሚጠይቀኝ → የምምረው፣ ማነው የሚለምነኝ ልመናውን የምቀበለው …» የሚልበት ወቅት ስለሆነ ይህን ወቅት በአግባቡ መጠቀም ያስደልጋል።


ታዲያ ያውም በረመዿን ምን ትጠብቃለህ ያ ዐብደ-ል'ሏህ⁉️

አላህ ያግራልን!

@yasin_nuru @yasin_nuru

6.4k 0 73 29 190

በምናፈጥር ጊዜ የሚባል ዱአ

ﺫﻫﺐ ﺍﻟﻈﻤﺄ ﻭ ﺍﺑﺘﻠﺖِ ﺍﻟﻌﺮﻭﻕ ﻭﺛﺒﺖ ﺍﻷﺟﺮ ﺇﻥ ﺷﺎﺀ ﺍﻟﻠﻪ
ጥም ተወገደ፣ ጉሮሮዎችም (የደም ስሮች) ረጠቡ፣ በአሏህ ፍቃድ አጅሩም ፀደቀ።"

📚 ﺻﺤﻴﺢ ﺍﻟﺠﺎمع) [(4678)

@yasin_nuru @yasin_nuru

7k 0 64 12 193

ለጾመኛ ሰው የሚወደዱ 40 ተግባራት‼️
=============================

1) ለሙስሊሙ ኡማ ዱዓ ማብዛት
2) ሰላምታን ማብዛት
3) ዝምድናን መቀጠል
4) መልካም ነገርን ማብዛት
5) ሶደቃ ማብዛት
6) ወንድምን በፈገግታ መገናኘት
7) ለጎረቤት መልካም መዋል
8) ለሚስኪኖች፣ ለአቅመ ደካሞችና ለየቲሞች መልካም መዋል
9) መልካም ንግግርን መናገር
10) አላህን ማውሳት (ዚክር) ማብዛት
11) ወደ አላህ መመለስን፣ ኢስቲጝፋርን ማብዛት
12) ኢማንን ማደስ፣ "ላ ኢላሃ ኢለልሏህ!" የሚለውን ቃል ማብዛት
13) "ላ ሐውለ ወላ ቁወተ ኢላ ቢልላህ!" የሚለውን ቃል ማብዛት
14) "ሱብሐነልላህ ወቢ ሐምዲህ፣ ሱብሐነልሏሂል ዓዚም!" የሚለውን ቃል ማብዛት
15) በነብያችን ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ላይ ሶለዋት ማብዛት
16) እውቀትን ፍለጋ ማብዛት
17) ወደ አላህ መጣራትን ማብዛት
18) ለቤተሰብ ስጦታ መስጠት
19) ውዱዕን መጠበቅ (ቂርኣትና ሶላት ላይ ባንሆንም በስራ ቦታ ሁሉ ብንሆንም)
20) ሲዋክ መጠቀም
21) ጥሩ ሽታ መኖር (ንጽህናን መጠበቅ)
22) ከመጝሪብ በፊት ሁለት ረከዓ መስገድ
23) በሱንና ሶላቶች ላይ መበራታት
24) ቤት ውስጥ የትርፍ ሶላቶችን ማብዛት
25) ወደ አወለ ስሶፍ (የመጀመሪያው ረድፍ) መጣደፍ
26) ከአንድ ሶላት በኋላ ቀጣዩን ሶላት በጉጉት መጠበቅ
27) በጁሙዓ ቀን በወቅቱ መገኘት
28) የሌሊት ሶላትንና ግዜን መጠበቅ
29) መስጅድ ውስጥ መቆየት ማብዛት
30) አላህን ከሚያወሱ መልካም ሰዎች ጋር መቀመጥ ማብዛት
31) የጧትና የማታ አዝካሮችን መጠበቅ
32) ቁርኣንን መማር፣ መቅራት፣ ድምጽ በማሳመር መቅራት፣ ሱጁዱ ቲላዋ መውረድ፣ ቁርኣንን ለማኽተም መጓጓት፣ ሲያኸትሙ ዱዓ ማድረግ
33) ዛሂድ መሆን
34)  ስናፈጥር መቸኮል
35) ሌላን ሰው ማስፈጠር
36) ሱሕር መመገብ፣ ሱሕርን ማዘግየት (ባይሆን ወቅቱ እንዳያልፍ)
37) የታመመን መጠየቅ
38) ቀብርን መዘየር (ለወንድ)
39) አኺራን፣ ሞትን፣ ጀነትንና እሳትን ማስታወስ
40) የአላህ ታዕምሮችን እያስተዋሉ ማስተንተን

እና ሌሎችም መልካም ተግባራት!!

*
አላህ ያግራልን።
||
[ከሸይኽ ሙሐመድ ኢብኑ ዐብዱል ወህ'ሃብ አል-ወስ'ሷቢይ ሐፊዘሁልሏህ

7.4k 0 99 6 118



ፆም የሚያበላሹ ነገሮች
~
1- የግብረ ስጋ ግንኙነት መፈፀም፣

2- የዘር ፈሳሽን ሆን ብሎ ማውጣት፣

3- መብላትና መጠጣት፣

4- በአፍ መድሃኒት መዋጥ፣

5- ሲጋራና መሰል ነገሮችን ማጨስ፣

6- የወር አበባ ወይም የወሊድ ደም መምጣት፣

7- ፆምን የማቋረጥ ቁርጠኛ ውሳኔ ላይ መድረስ (ባይበላም ባይጠጣም)

እነዚህ ነገሮችን ፆምን የሚያበላሹት የሚያፈርሱ እንደሆነ እያወቀ፣ አስታውሶ እና በምርጫው በቀኑ ክፍለ ጊዜ ከፈፀማቸው ነው።

* የሚያፈርሱ መሆናቸውን ሳያውቅ ቢፈፅም ፆሙ አይበላሽም። ልክ እንደዚሁ ያልነጋ መስሎት ወይም ፀሐይ የገባ መስሎት ቢፈፅምም ፆሙ አይበላሻም።

* የሚያፈርሱ መሆናቸውን እያወቀ ነገር ግን ረስቶ ቢፈፅም ፆሙ አይበላሽም።

* የሚያፈርሱ መሆናቸውን እየወቀ ግን ተገዶ ቢፈፅም ፆሙ አይበላሽም።

@yasin_nuru @yasin_nuru

7.5k 0 58 19 218

•አዎ አሁንም ቢሆን ዝም አትበሉ፣ አትዘናጉ፡፡  ያሳሰባችሁን ማንኛዉም ነገር ሁሉ ለፈጠራችሁ አምላክ ለአላህ ሱብሐነሁ ወተዓላ ንገሩት፡፡ እሱ ጉዳያችሁን ይፈታል፣ አይቻልም ተብሎ የሚታሰበዉን ሁሉ ያገራል፡፡

አንዳንድ ጉዳዮች የናንተን እጅ ማንሳት ብቻ እየጠበቀ ይሆናል፡፡ እጃችሁን ወደ አላህ አንሱ አትፍሩ፣ አትፈሩ፣ አታመንቱ፣ አመቺ ጊዜ አትጠብቁ፡፡አንድ ሰው ብዙ እንዲሳኩለት የሚፈልጋቸው ሓጃዎች እያሉት እንዴት ይሰንፋል! እንዴት እጁን አጣጥፎ ይቀመጣል!!፡፡ 

ብቸኝነት ያደከማችሁና  መልካም ትዳር የምትናፍቁ፣ ጉዳያችሁ ከዓመት ዓመት መልስ ሳያገኝ የተንከባለለ አሁንም ወደ አላህ ተጠጉ፣ ከአላህ ጋር አውሩ፡፡ ሪዝቅ የጠበባችሁ፣ ድህነት ያዋረዳችሁ አላህ ሆይ ሪዝቄን አስፋ በሉት፡፡ ያሳሰባችሁን ማንኛዉንም ነገር ሳትፈሩ ሳታፍሩ ለምኑት፣ ጠይቁት፣ ተማፀኑት፡፡
©

እንግዳችንን በታላቅ የመልካም ስራ ድግስ እንቀበለው…የኢስቲጝፋር፣ ተውበት፣ ሰላት፣ ዚክር፣ ሰደቃ፣ ዘካና ሌሎችም ብዙ የኸይር አይነቶች የተሰበሰቡበት ቡፌ ያለው ድግስ የተደገሰበት ረመዻን መጥቶልናል ፤ እንኳን አደረሳችሁ እንኳን አደረሰን አላህ ፆመው ከሚጠቀሙት ባሮቹ ያድርገን።
ረመዿን ሙባረክ

https://t.me/asdajlahh

7.6k 0 43 32 156

በረመዳን ቁርኣንን ለማክተም‼️
========================
1) አንድ ግዜ ለማክተም፥
~~~
ፈጅር (ሱብሒ) ላይ 4 ገጽ መቅራት፣
ዝሁር ላይ 4 ገጽ መቅራት፣
አሱር ላይ 4 ገጽ መቅራት፣
መጝሪብ ላይ 4 ገጽ መቅራት፣
ዒሻእ ላይ 4 ገጽ መቅራት፣

2) ሁለት ግዜ ለማክተም፥
~~~
ፈጅር (ሱብሒ) ላይ 8 ገጽ መቅራት፣
ዝሁር ላይ 8 ገጽ መቅራት፣
አሱር ላይ 8 ገጽ መቅራት፣
መጝሪብ ላይ 8 ገጽ መቅራት፣
ዒሻእ ላይ 8 ገጽ መቅራት፣

3) ሶስት ግዜ ለማክተም፥
~~~
ፈጅር (ሱብሒ) ላይ 12 ገጽ መቅራት፣
ዝሁር ላይ 12 ገጽ መቅራት፣
አሱር ላይ 12 ገጽ መቅራት፣
መጝሪብ ላይ 12 ገጽ መቅራት፣
ዒሻእ ላይ 12 ገጽ መቅራት፣

4) አራት ግዜ ለማክተም፥
~~~
ፈጅር (ሱብሒ) ላይ 16 ገጽ መቅራት፣
ዝሁር ላይ 16 ገጽ መቅራት፣
አሱር ላይ 16 ገጽ መቅራት፣
መጝሪብ ላይ 16 ገጽ መቅራት፣
ዒሻእ ላይ ገጽ 16 መቅራት፣

5) አምስት ግዜ ለማክተም፥
~~~~
ፈጅር (ሱብሒ) ላይ 20 ገጽ መቅራት፣
ዝሁር ላይ 20 ገጽ መቅራት፣
አሱር ላይ 20 ገጽ መቅራት፣
መጝሪብ ላይ 20 ገጽ መቅራት፣
ዒሻእ ላይ 20 ገጽ መቅራት!!
||


ረመዳን የቁርኣን ወር ነው።
ከአምስት ግዜ በላይ ብናከትምም በጣም ተወዳጅ ነው።

ምናልባት ይህ ፕሮግራማችን አንድ ቀን ወይም በሆነ ሰአት ላይ በተለያዬ ምክንያት ቢያልፈን፣
ከሌላኛው ቀን ወይም ግዜ ማካካስ መቻል አለብን።

"ረመዳን ገጥሞት ሳይጠቀምበት ምህረት ሳያገኝ የሄደበት ሰው በአፍጢሙ ጀሀነም ይደፋ!"፡ ጂብሪል(ዐሰ)፤ አሚን በል ሲላቸው
ነብዩ(ሰዐወ) "አሚን"ብለዋል! ጠንቀቅ እንበል አደራ!!

@yasin_nuru    @yasin_nuru   

9.2k 0 206 22 235

🚨🌙 በሳውዲ አረቢያ ጨረቃ መታየቷን ተከተሎ የታላቁ የረመዳን ፆም ነገ ይጀመራል።


ረመዳን ሙባረክ 🌙

#RAMADAN1446

@yasin_nuru

11.2k 0 244 92 378

አንዳንድ ሃገሮች ነገ ነው ብለዋል የሳኡዲን እንጠብቃለን!

@yasin_nuru


Репост из: ISLAMIC SCHOOL️
በሳኡዲ አረቢያ ጨረቃን ለማየት በፍለጋ ላይ!

21/6/2017 
29 ሻዕባን 1446

@islam_in_school

7.8k 0 15 14 122

Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ልጆቻችሁን እንዲህ ነው ማረግ ያለባችሁ😂😂

ካሁን ቡኋላ በረመዳን መስጅድ ውስጥ ኢሻ እና ተራዊህ ላይ የሚረብሽ ካለ ወላጅ ነው ተጠያቂው😂😂

@yasin_nuru     @yasin_nuru

9.5k 0 55 19 214

ጁመዓ ጨረቃ ከታየች ቅዳሜ ረመዷን 1 ይሆናል።

አላህ ከቤተሰቦቻችን፣ከዘመዶቻችን፣ከጓደኞቻችን ጋር በሰላም አድርሶን በዚክር በኢባዳ ረመዳንን የምናሳልፍ ያድርገን።

@yasin_nuru @yasin_nuru

10.9k 0 65 153 588

❤️ፍቅር ማለት …❤️

✍ ቢላል ረዲሏሁ አንሁ ነብዩ ከሞቱ በኃላ አዛን ማድረግ ማቆማቸው ነው ፤

✏ ፍቅር ማለት … ✍ ቢላል ረዲሏሁ አንሁ ነብዩ ከሞቱ በኃላ መዲና መኖር አለመቻላቸው ነው ፤

✏ፍቅር ማለት … ✍ ቢላል የነብዩን መስጅድ ከዘየሩ ጊዚያት ተቆጠረው የአላህ መልክተኛ በህልማቸው መጥተው አንተ ! ቢላል ምነው አስቻለህ ? ሲሏቸው እያለቀሱ ለዚያራ መዘጋጀታቸው ነው ፤

✏ ፍቅር ማለት… ✍ ቢላል ረዲሏሁ አንሁ ወደ መዲና መጥተው ሀሰንና ሁሴን የሱብሂን አዛን እንዲያደርጉ አዘዋቸው የመዲና ህዝብ አዛናቸውን ሲሰሙ በእንባ መራጨታቸው ነው፤

✏ ፍቅር ማለት … ✍ ቢላልን ዑመር አልፋሩቅ ረዲሏሁ አንሁ 'ሻም' ላይ አዛን እንዲያደርጉ አዘዋቸው በማልቀስ ብዛት ' አሽሀዱ አንነ ሙሀመድ ረሱሉላህ ' ማለት ተሰኗቸው ሁሉንም ማስለቀሳቸው ዑመርም ይበልጥ ማለቀሳቸው ነው ፤

✏ ፍቅር ማለት … ✍ ቢላል ረዲሏሁ ዐንሁ ሊሞቱ እያሉ ' ነገ ወዳጄ ሙሀመድንና ባልደረቦቹን እገናኛለሁ ' ማለታቸው ነው

✏ምርጥ ህዝቦች አልፈዋል እኛንም የነርሱ ተከታይ ያድርገን اللهم صلي ال محمد

👍ሼር ማድረጋችንን አንርሳ


ረመዳን 2 ወይም 1 ቀን ብቻ ይቀረዋል

ጁመዓ ጨረቃ ከታየች ቅዳሜ ረመዷን 1 ይሆናል።

20/6/2017 
28 ሻዕባን 1446

@yasin_nuru   @yasin_nuru

11.3k 0 107 34 190

ያስለመደው ፆም ካልሆነ በቀር…

ረሱል (🤍) እንዲህ ብለዋል፦

﴿لا تَقَدَّمُوا رَمَضانَ بصَوْمِ يَومٍ ولا يَومَيْنِ إلَّا رَجُلٌ كانَ يَصُومُ صَوْمًا، فَلْيَصُمْهُ.﴾

“ከናንተ ውስጥ ማንም ቢሆን ከረመዳን አስቀድሞ አንድም ቀን ቢሆን ወይንም ሁለት ቀን እንዳይፆም። ነገር ግን ያስለመደው ፆም ካለ መፆም ይችላል።”

📚 ቡኻሪ (1914) ሙስሊም (1082) ዘግበውታል

ሼር አርጉት ብዙ ሰው ለመፆም ያሰበ አለ❗️

@yasin_nuru @yasin_nuru

10.1k 1 51 11 136

🍂ስንቶቻችን የረሱልን (ሰዐወ) ዘር እናውቃለን??

እስካሁን ባናውቀውም ኢንሻአላህ ከአሁን በሁዋላ ሀላችንም እናውቀዋለን…

➡️እስከ አድናን ያለው የረሱል ሰዐወ ዘር...

1 ሙሀመድ(ሰዐወ)ኢብን🥰🥰

2 አብዲላ ኢብን🩵🩵

3 አብዲል ሙጠሊብ ኢብን💙💙

4 ሀሺም ኢብን🤎🤎

5 አብዲ መናፍ ኢብን🤍🤍

6 ቁሰይ ኢብን💓💓

7 ኪላብ ኢብን🩶🩶

8 ሙር ኢብን💛💛

9 ከዓብ ኢብን🩷🩷

10 ሉዓይ ኢብን❤️‍🔥❤️‍🔥

11 ጋሊብ ኢብን🩶🩶

12 ፈኸር ኢብን💜💜

13 ማሊክ ኢብን🩵🩵

14 ነዝር ኢብን💟💟

15 ኪናና ኢብን💚💚

16 ኩዘይማ ኢብን💞💞

17 ሙድሪካ ኢብን💕💕

18 ኢሊያስ ኢብን💓💓

19 ሙደሪብ ኢብን💗💗

20 ዛር ኢብን💖💖

21 መዓድ ኢብን💟💟

22 አድናን💝💝

💞💞💞💞💞💞💞💞💞💞💞💞

ረመዳን 3 ወይም 2 ቀናቶች  ብቻ ይቀረዋል🔥🔥

19/6/2017 
27 ሻዕባን 1446

@yasin_nuru   @yasin_nuru

10.3k 0 136 15 147

በአክሱም 159 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሒጃብ ለብሰው ወደ ትምህርት ቤት እንዳይገቡ በሚል ላለፉት አንድ መቶ ቀናት ከትምህርት ገበታቸው ውጪ መሆናቸው ተነገረ

በትግራይ ክልል አክሱም የሚገኙ 159 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሒጃብ ለብሰው ወደ ትምህርት ቤት እንዳይገቡ ተከልክለዋል በሚል ላለፉት አንድ መቶ ቀናት ከትምህርት ገበታቸው ውጪ መሆናቸው ተገለጠ ።

በትግራይ ክልል በዋነኝነት በሴቶች መብት ጉዳይ ዙርያ የሚሠሩ ስድስት ሲቪክ ተቋማት ሕገወጥ ያሉትን ይህን የትምህርት ክልከላ ተቃውመዋል ። የአክሱም ከተማ ትምህርት ጽሕፈት ቤት በዚህ ጉዳይ ዙርያ ምላሽ መስጠት አልቻለም ።

ሒጃብ ለብሰው ወደ ትምህርት ቤት እንዳይገቡ በሚከለክል የአክሱም ከተማ ትምህርት ቤቶች መመርያ ምክንያት ካለፈው ጥቅምት ወር ጀምሮ እስካሁን 159 ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ከትምህር ገበታ ውጪ ሆነው እንዳለ  የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት ይገልፃል ።

ጉዳዩን አስመልክቶ የትግራይ ትምህርት ቢሮ ተማሪዎቹ ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመለሱ መመርያ አስተላልፎ የነበረ ቢሆንም ይህ መመርያ በትምህርት ቤቶች መጣሱን፣ ከዚህ በተጨማሪ የፍርድ ቤት ውሳኔም ጭምር አለመተግበሩን የእስልምና ጉዳዮች ምክርቤቱ ይገልፃል።

በዚህ በአክሱም የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ርምጃ ምክንያትም ሴት ተማሪዎች ከትምህርት ውጭ መሆናቸው ተገልጿል። 

    #DW

@yasin_nuru   @yasin_nuru

10k 0 7 14 140

የተክሪት ሀገረ ግዛት አስተዳዳሪ የሆነው ነጅሙ ዲን ለረጅም አመታት ያለ ሚስት ቆይቷል። (525 አ.ሂ)

«ወንድማለም ለምን አታገባም?» ብሎ ጠየቀው ወንድሙ።
«ምትሆነኝን አላገኘሁማ!» አለው፤ እንደዘመናችን ወንዶች።
«ታድያ እኔ ልጭልሃ!» ወንድማዊ እዝነት።

«ማንን» ብሎ ጠየቀው።
«የንጉሰ ነገስቱን ምክትል ጠቅላይ አስተዳዳሪ ልጅ የሆነችውን ልጭልህ» ሲል ተማፀነው ወንድማለም።

«አይ አትሆነኝም ስልህ» ብሎ አሻፈረኝ አለው።
በአግራሞት እና በወንድማዊ እዝነት እየተመለከተው፦ «ትድያ ላንተ ማን ናት ምትሆንህ?»

«ለኔ ምትሆነኝ ምርጥ መልካም የሆነች ሚስት፤ እኔን እጄን ይዛ ወደ ጀነት የምትሄድ እና ከኔ ጀግና ልጅ ወልዳ በመልካም አስተዳደግ አሳድጋ ልጄንም አጀግና ያ ጀግና ልጇም በይተል መቅዲስን ለሙስሊሞች የሚያስረክብ ከሆነ ነው።» ህልሙን ነገረው።

ወንድም ንግግሩ ምንም አልጣመውም፤ ከባድ ህልም ነው ማይታሰብ።
«ታድያ እንዲህ ያለች ሚስት ከየት ነው ሚመጣልህ?» ጠየቀው።
«ኒያውን ለአላህ ያጥራራ፤ አላህ ይለግሰዋል» ብሎ መለሰለት።

ያ ቀን አለፈ።

ከዕለታት አንድ ቀን አስተዳዳሪው ነጅሙ ዲን ከመስጅዱ ቁጭ ብሎ ከአንድ ሸይክ ጋ እያወጉ ሳለ ድንገት ከመጋረጃው ጀርባ አንዲት እንስት መጥታ ሸይኩን ጠራችው።

ሸይኩ አስተዳዳሪውን አስፈቅደውት ልጅቱን ሊያገኟት ጠጋ አሉ። ሸይኩ ከሷ ጋ ሲያወጉ ድምፃቸው ለአስተዳዳሪው በግልፅ ይሰማ ነበር።

«ልጄ ትናንት እንዲያገባሽ ቤታችሁ የላኩትን ወጣት ለምን እንቢ ብለሽ መለሽው? »

«ኡስታዝ ልጁ ቆንጆ፣ ሀብታም እና መልከ መልካም ነው፤ ግና ለኔ አይሆነኝም» ብላ ትመልስላቸዋለች።

«ታድያ ምን አይነት ነው አንች ምትፈልጊው!» ሸይኩ ይጠይቋታል።
«ኡስታዝ! እኔ ምፈልገው ባል እጄን ይዞ ወደ ጀነት የሚመራኝ፣ ጀግና ልጅን ከሱ የምወልደውን፣ ልጁም ጎርምሶ ሲጀግን በይተል መቅዲስን ለሙስሊሞች የሚያስረክብ ሲሆን ነው» ፈላጊ እና ተፈላጊ ግጥምጥም አሉ።

«ኧረ ኡስታዝ እችን ልጅ ለኔ ይዳሩኝ» አላቸው።
«ይህች እኮ የከተማው ድሃ ልጅ ናት» አሉት፤ የግዜው ንጉሳን የድሃ ልጆችን እንደማያገቡ ስለሚያውቁ።

«አይይይይ...እኔ ምፈልጋት በቃ ይች ናት» ሙጥኝ አለ።

የሀገረ ግዛቱ አስተዳዳሪ ነጅሙ ዲን ልጅቱን አገባት። በመቀጠልም አንድ ቆንጅዬ ልጅ ወልደው ልጁ ሲጎረምስ ለዘመናት ከሙስሊሞች እጅ ተነጥቆ የቆየውን በይተል መቅዲስን ወደ ሙስሊሞች እጅ አስመለሰላቸው።

ይህ ሰው ☞ ሰላሁዲን አል አዩቢ ነው።


#ረመዳን_4_ቀናቶች_ይቀሩታል።
18/6/2017 
26 ሻዕባን 1446

@yasin_nuru   @yasin_nuru

10.8k 0 84 26 204
Показано 20 последних публикаций.