ያሲን ኑሩ️️ YASIN NURU


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Блоги


የ ያሲን ኑሩ ሐዲሶች
Yasin Nuru
"ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የሰራውን ሰው ያህል አጅር ያገኛል" ረሱል (ﷺ)
"የበጎ ስራ ምላሹ በጎ እንጂ ሌላ አይደለም "  
የብናኝ ክብደት ያክልም መልካምን የሰራ ሰው ያገኘዋል :>> { አል -ዘልዘለህ 7}
This is not official
ለአስተያየት👇👇
@Hasabbbbot

ሀዲሶችን ከፈለጋችሁ👇👇
@yasin_nuru_hadis

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Блоги
Статистика
Фильтр публикаций


ነገ ጠዋት ከማለዳው 12:30 ጀምሮ አዲስ አበባ

ነገ እሁድ በአዲስ አበባ ስታዲየም የቁርኣንና የአዛን ውድድር ይካሄዳል።

እንዳትቀሩ!

@yasin_nuru

3.2k 0 21 38 279

#በጣም_ልብ_የሚነካ_ታሪክ_ነው

☞በአረብ አለም የሚኖር አንድ የአሥር አመት ታዳጊ ነው

ይህ ታዳጊ የሰራው ነገር ግን ሠውን አጃኢብ አስኝቷል።

ነገሩ እንዲህ ነው: ይህ የአስር አመት ህፃን ዘውትር በሠላት ወቅቶች ከመሥጂድ ይታደማል

ሠላቱም በጀመዓ ይሠግዳል ድምፅ ከፍ ተደርጎ በሚሰገድባቸው ሦስት ሠላቶች ላይ ታዲያ ኢማሙ ፋቲሀን ቀርቶ ሲጨርስ ማለትም ወለዷ ሊን ሲል ሠጋጁ በአንድነት አሚን ሢል ይህ ልጅ ድምፁን ከፍ አድርጎ ከጀመዓው ተነጥሎ ብቻውን አሚን ይላል....

ይህ ነገር በመደጋገሙ ኢማሙን እጅግ ያበሳጨው ነበር ቢያየው ቢያየው ልጁ ሊያቆም ስላልቻለ አንድ ቀን ከመግሪብ ሠላት በኃላ ንዴቱን መቆጣጠር ያቃተው ኢማም ይህን ልጅ እንቅ አድርጎ አንጠልጥሎ ያምባርቅበታል!

ለምንድነው ምትረብሸው ከጀመዓው ጋር አብረህ ለምን አሚን አትልም እና መሰል ነገሮችን ይህን ህፃን ልጅ ተናገረው😡😡

ይህ ታዳጊ በፍርሃት በተሸበሸቡት ልብሶቹና
ቲማቲም በሚመሥሉ ጉንጮቹ እምባ ያቀረሩ አይኖቹ ያንን ኢማም በሥሥት እየተመለከቱ...

«እኔ ምጮህው አለ......
እኔ ምጮህው እቤታችን መስጂዱ አጠገብ ነው አባቴ ደሞ ሠላት አይሰግድም ምናልባት የኔን ድምፅ ሢሠማ ደስ ብሎት አልያም ተደንቆ ከመጣና ከሠገደ ብዬ ነው ያ ኢማም» ብሎ መለሰለት🥺🥺

ይህን ጊዜ ኢማሙ ሚናገረው ጠፋው ሠውነቱ ተርገፈገፈ😔😔

የአከባቢውን ሠው አፈላልጎ ይህን ለአባቱ አደረሠው አባቱም በልጁ ተግባር እጅግ ተደንቆ ወደ ጌታው እያለቀሰ ተውበት በማድረግ ሠላቱን ጀመረ።

ሰዎችን አይተን ብቻ በችኮላ አንፍረድ። ይህን ለመስራት ያበቃቸው ምን ምክንያት ሊኖር ይችላል ብለን ኡዝር እንፈልግላቸው ምናልባት መጥፎ ሥራ የሚሰሩ መስሎን ሲፈተሽ ግን በጣም የሚደንቅ ሊሆን ይችላል!!   

ሱብሃን አላህ

Darul

@yasin_nuru     @yasin_nuru

4.4k 0 66 26 186

#ልብ_ብላችሁ_ፃፉት

ከሱብሂ ቡኋላ አለመተኛት

#በሳምንት_ሶስት_ቀን_ስፖርት_መስራት

በየቀኑ ግማሽ ጁዝ ቁርዓን መቅራት

#በቀን_ውስጥ_አስር_ፔጅ_ማንበብ

ይሄንን ወደ ሂወታችሁ ማምጣት ትፈልጋላችሁ?

#አድርጉት_በስሜት_ተዋሃዱት

#ከ_21_ቀን_በላይ_ድገሙት

ያኔ ቋሚ ልማዳችሁ መሆን ይችላል።

ቡና ሱስ አስቸግሮሃል? ለ21 ቀን አቁም። እሱን በስሜት ማቆምን ተለማመደው። #ያኔ_ሱስን_ማቆም_ትችላለክ።

#ጫት ማንኛውም ነገር #መጥፎ የምትሉትን ባህሪም ይሁን #ጥሩ የምትሉትን ለመትከል እነዚህ ፕሮሰሶች ያስፈልጋሉ።
#Action #Feeling #Repetition #Habit

#ኡስታዝ_ያሲን_ኑር

ወላሂ ነው የምላችሁ በተለይ በተለይ ከወንጀል ለመራቅ ወረቀት ላይ ከ 1 እስከ 21 ቁጥር ፃፉ አቃለው በጣም ይከብዳል ከዚህ ከወንጀል ከሱስ ለመራቅ አላህን እየለመናችሁ ወንጀል የማትሰሩበትን ቀን (x) እያረጋችሁ ቀጥሉ ከአላህ ጋር ለውጥ ታይበታላችሁ።
አልሃምዱሊላህ እኔም በዚህ በኡስታዝ ያሲን ኑሩ ምክር በጣም መጥፎ ሱስ ከሆነብኝ ወንጀል እየራኩ ነው።

ezk

@yasin_nuru   @yasin_nuru

5.8k 0 84 31 171

Репост из: ISLAMIC SCHOOL️
ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን

የቀሳሞች ጦር መሪ ሙሐመድ ደይፍ ወደማይቀረው አለም መሸጋገሩን አቡ ዑበይዳ በይፋ አስታውቋል።

በሐማስ ስር የሚገኘው ቀሳም የቡድኑ ዋና የጦር አዛዥ ሙሐመድ ደይፍ እና ምክትሉ መርዋን ዒሳን ጨምሮ  የቡድኑ የጦር አመራሮች መሰዋታቸውን ዛሬ ገልጿል።

@islam_in_school

6.1k 0 12 67 290

ከእለታት አንድ ቀን የአላህ መላክተኛ (ሰ ዐ ወ) መንገድ ላይ ሳሉ አንዲት በእድሜ የገፉ ሴት እቃ ተሸከመው ይመልከቱና፤ወደሴትዬዋ ጠጋ በማለት እናቴ እቃውን ላግዞት በማለት ይጠይቃሉ?!

ሴትዮዋም የአላህ መላክተኛ ስለመሆናቸው የሚያቁት ነገር አልነበረም፤እቃው ከራሳቸው ላይ አውርደው ሰጧቸው፤የ አላህ መላክተኛም
(ሰ ዐ ወ) እቃውንም ተሸክመው እስከ በር ድረስም አደረሱላቸው።

ሴትዮዋ ትንሽ ጠብቀኝ ብላቸው ወደቤት ገቡ፤
የአላህ መላክተኛ (ሰ ዐ ወ) ሴትዮዋ እስኪመጡም ጠበቁ፤ ሴትዮዋም ከቤት በመውጣት እንዲህም አሉ፦
ሊጄ ምክር ብሰጥህ ትቀበለኛለህ አሉ?የአላህ መላክተኛም (ሰ ዐ ወ) እንዴት አልቀበልም ሲሉ መለሱ፤ሴትዮዋም ልጄ እኔ አደራ የምልህ
የሙሀመድን እምነት እንዳትከተል ነው አሉ፤
የአላህ መላክተኛም(ሰ ዐ ወ) እንዲህም አሉ እኔ ሙሀመድ ከሆንኩኝስ አሉ?!ሲሉ ጠየቋቸው!

ሴትዮዋም አንተ ሙሀመድ ከሆንክማ ከአላህ ሌላ አምላክ የለም ሙሐመድም የአላህ መላክተኛ መሆናቸውን እመሰክራለው አሉ፤

እንዲህ ነበር የአላህ መላክተኛ (ሰ ዐ ወ)አለምን በፀባያቸው የገዙት!!!

እህት ወንድሞቼ እኛስ እውን ባህሪያችን ስራችን ምን ይመስላል?!!

ነብዩ ሙሐመድ (ሰ ዐ ወ) ለአለም የበሩ ብርሃን ናቸዉ!!

@yasin_nuru @yasin_nuru

7k 0 58 51 231

ረመዷን 30 ቀን ቀረው!😍😍

30 days until Ramadan!

اللهم بلغنا رمضان
@yasin_nuru

7.4k 0 54 118 418

የ2ኛው አለም አቀፍ የቁርአን እና የአዛን ውድድር የመክፈቻ ስነ ስርዓት በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ
♻️♻️♻️♻️♻️♻️♻️
በዘይድ ኢብኑ ሳቢት የቁርአን ማህበር አዘጋጅነት በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የበላይ ጠባቂነት በመጭው እሁድ በአዲስአበባ ስታዲየም የሚካሄደው ሁለተኛው አለም አቀፍ የቁርአን እና አዛን ውድድር የመክፈቻ ስነ ስርዓትና የማጣሪያ ውድድር በዛሬው ዕለት በኢሊሌ ሆቴል እየተካሄደ ይገኛል።

የማጣሪያ ውድድሩ ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ60 የተለያዩ ሀገራቶች የመጡ ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉበት ሲሆን የዛሬውን የማጣሪያ ውድድር ያለፉ ተወዳዳሪዎች በመጭው እሁድ በአዲስአበባ ስታዲየም የፍፃሜ ውድድር ተፋላሚ እንደሚሆኑ ተገልጿል።

በዛሬው ዕለት በኢሊሌ ሆቴል እየተካሄደ በሚገኘው የማጣሪያ ውድድር የመክፈቻ ዝግጅት ላይ የፌዴራል እና የአዲስአበባ መጅሊስ አመራሮች ፣ አለምአቀፍ የቁርአን ውድድር ዳኞች ፣ ከተለያዩ ሀገራት የተጋበዙ ሊቃውንት ፣ኡለማኦች ኡስታዞች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

2ኛው አለም አቀፍ የቁርአን እና የአዛን ውድድር የማጣሪያ ውድድር!

ቀጥታ ስርጭት ከአዲስአበባ

https://www.facebook.com/haruntube/videos/1758213854960067/?app=fbl



@yasin_nuru @yasin_nuru

7.4k 0 16 31 110

🔰ነቢዩ ﷺ ነቢይ ሆነው ከመላካቸው በፊት ትክክለኛው መንገድ ላይ ነበሩ።?🔰

➸ነቢዩ ነቢይ ሆነው ከመላካቸው በፊት በአላሁ ሱብሀነሁ ወተዓላ ጥበቃ አንድም ቀን ለጣዖትም አምልኮ ሰጥተው፣አስካሪ መጠጥ ጠጥተው፣ዝሙት ሰርተው አያውቁም።በወጣትነት ዘመናቸውም ማንኛውም ወጣት
ከሚወድቅባቸው ልዩ ልዩ ፀያፍና ክህደት ነገሮች ጥበቃ አድርጎላቸዋል። አላህ ሱብሀነሁ ወተዓላ እንደዚህ አይነት ፀያፍ ወንጀሎች ነቢዩ ሰላሏሁ ዓለይሂ ወሰለም ዘንድ የተጠሉ ነገሮች እንዲሆኑ አደረገላቸው። በህዝቦቻቸው ሃይማኖት ላይም አልነበሩም።
📚 መጅሙዑል ፈታዋ ቅጽ 13 ገፅ 501
📚 ተፍሲሩል ቁርጡቢይ 18 ገፅ 513
📚 ሶሂህ ኢብኑ ሒባን 49

ነቢዩ በነቢዩላሂ ኢብራሂም ዓለይሂ ሰላም መንገድ ላይ ነበሩ።
(ነቢዩላሂ አብራሂም ደግሞ👇

ما كَانَ إِبْرَاهِيمُ يَهُودِيًّا وَلَا نَصْرَانِيًّا وَلَـٰكِن كَانَ حَنِيفًا مُّسْلِمًا وَمَا كَانَ مِنَ الْمُشْرِكِينَ

📚 (ሱረቱ አሊ-ዒምራን - 67)
ኢብራሂም ይሁዳዊም ክርስቲያንም አልነበረም፡፡ ግን ወደ ቀጥተኛው ሃይማኖት የተዘነበለ ሙስሊም ነበረ፡፡ ከአጋሪዎችም አልነበረም፡፡

ነቢዩ ከሸይጣን ጉትጎታና ትንኮሳ ፍፁም የተጠበቁ በማድረግ እና
የውስጣቸውንም ጤንነት በመጠበቅ በጂብሪል አማካኝነት
ሁለት ግዜ ከልባቸው የረጋ ደም አይነት ነገር በማውጣት ይሄ የሸይጣን ድርሻ ነው በማለት ልባቸውን አጥቦላቸዋል።
በንዲህ አይነት ጥበቃዎች በእነዚህ መልኩ ለነቢይነት ዝግጁ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል።
ነቢዩ ዕድሜያቸው ወደ አርባ ዓመት በተጠጋ ጊዜ ሕዝባቸው የሚገኙበት ተጨባጭ ሁኔታና ዕምነት መረጋጋት ነስቷቸው ብቸኝነትን
እየወደዱ መጡ።
የበሶ እና የውኃ ስንቅ በመያዝ ከመካ ሁለት ማይል ያህል ርቀት በመጓዝ ወደ ሒራ ዋሻ
ይጓዙ ጀመር።

ወደሳቸው የወረደላቸው መመሪያ ህግጋት ባይኖራቸውም በዚያም በነቢዩላሂ ኢብራሂም መንገድ ላይ ሆነው አምላካቸውን አላህን በብቸኝነት
በመገዛት ያሳልፉ ነበር፤

📚 ፈትሁል ባሪ ሸርህ ሶሂህ አልቡኻሪይ ቅጽ 1 ገፅ 54

ይህ የነቢዩ ብቸኝነት መምረጥ ለሚጠብቃቸው ታላቅ
ጉዳይና ከባድ አደራ የመቀበል ከአላህ ዘንድ የተቸራቸው ቅድመ ዝግጅት
አንድ አካል ነበር።

ነቢዩ ዕድሜያቸው አርባ ዓመት በሞላ ጊዜ አላህ ለዓለማት
አብሳሪና አስጠንቃቂ ይሆኑ ዘንድ ላካቸው፤ ጂብሪልም (ዐ.ሰ) ከዓለማት
ጌታ መልዕክት ይዞ.እሳቸው ዘንድ ወደ ሒራ ዋሻ በመምጣት
“አንብብ” 
አላቸው፤ እሳቸውም ማንበብ አልችልም” አሉት። የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ አሉ፦ “ያዘኝና እስከሚጨንቀኝ ድረስ ጨመቀኝ፤ ከዚያም
ለቀቀኝና “አንብብ” አለኝ፤ እኔም “ማንበብ አልችልም” አልኩት፤
በሦስተኛውም እንዲህ አለኝ፦ “አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ
ስም። ሰውን ከረጋ ደም በፈጠረው (ጌታህ ስም)። አንብብ፤ ጌታህ በጣም
ቸር ሲሆን፤ ያ በብዕር ያስተማረ፤ ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲሆን።
አል ቀለም (1-5)፣
📚ሀዲሱን ቡኻሪና ሙስሊም ተስማምተውበታል።
ከዚያ በኃላ ወህይ(ራዕይ) በጂብሪል አማካኝነት ወደ ነቢዩ ለ 23 አመታት ወረደ።

ስለዚህ ነቢዩ በነቢዩላሂ ኢብራሂም ዓለይሂ ሰላም መንገድ ላይ ሆነው አላህን በብቸኝነት ያመልኩ ነበር እንጂ ጣዖታትን አምልከው በፍፁም አያውቁም።
➸ እንደውም በጥቅሉ ሁሉም ነቢያት ነቢይ ሆነው ከመላካቸው በፊት አማኞች ነበሩ።
📚 ተፍሲር አያት አሽከለት ሊብኑ ተይሚያህ ገፅ 181
ስለዚህ ካፊሮች ነቢዩ ሙሽሪክ ነበሩ ብለው  የሚያወሩት ቅጥፈት ነው።

አላህ እንዲህ ይላል
*¶በልም «እውነት መጣ ውሸትም ተወገደ፤ እነሆ ውሸት ተወጋጅ ነውና፡፡»*
{📗 Qur'an17:81}


ከላይ የጠቀሰኳቸውን ማስረጃዎች ከኪታብ በማስረጃ ከፈለጉ ይህንን ይጫኑ👇👇
https://t.me/iwnetlehullu1/413?single

☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️

አላሁመ ሶሊ ዓላ ነቢዪና ሙሐመድ
➤➤አልሃምዱሊላህ ረቢል ዐለሚን➤➤

7.1k 0 21 12 53

ብስክሌት ጠጋኝ የነበረው የአሁኑ
ኮንትራክተር ጓደኛዬ እንዴት ሰለመ ??
===============
T.me//yeyasine_wedaje
ከጓደኝነታችን በፊት ክርስቲያን የነበረው ጓደኛዬ በጣም የሚገርም አስደናቂ ባህሪ እንደ ነበረው ከበፊት ጓደኞቹና ጎረቤቶቹ ሰምቻለሁ ። በፊት የነበረው መልካም ባህሪውና ቆራጥነቱ  ዛሬ ላይ በእስልምና ውስጥ የበለጠ ውበት አጎናፅፎታል ።
_
ይህ ሰው  ከጎረቤቶቹ መካከል አንድ እግረ  ሽባ የሆኑ ሙስሊም ሰው ነበሩ ። እኚህ ሰው ሁሌም ባይሆን ለጁምዓ ሰላት ከመስጅድ አይቀሩም ነበር ።

ይህ ጎረቤቱ አርብ አርብ ሁሌም እየተንፏቀቁ ወደ መስጅድ ሲሄዱና ሲመጡ ሲመለከት በውስጡ ያስጨንቀው ጀመረ ።
_
አንድ ቀን በውስጡ ይህን ሰው በብስክሌቱ ወደ መስጅድ ማድረስና ከሰላት ቡሃላ ጠብቆ መመለስ እንዳለበት ወሰነ ። ይህን ሀሳብ ለሰውዬው ሲያማክራቸው እሳቸውም በጣም በመደሰት ዱዓ አድርገውለት በሀሳቡ ተስማሙ ።
_
የመጀመሪያውን ጁምአ ለሰላት አድርሷቸው ከመስጅድ ቅጥር ግቢ ውጪ ሆኖ ከኹጥባ በፊት በሼኽ ኢብኑ ዩሱፍ የሚደረገውን የኹጥባ ተፈሲርና በኢማሙ እርጋታ የሚነበበውን የአርብኛ ኹጥባ በድምፅ በማጉያ ሲያዳምጥ የማያውቀው ስሜት ልቡን ተቆጣጠረው።
_
የሁለተኛው ጁምዓ እስኪደርስ ጨነቀው ቀኑም ደረሶ የመስማት እድል አግኝቶ አዳመጠ  እንዳባለፈው ጁምዓም የሰማው ነገር ሁሉ ልቡን አሸብሮታል ። ጉዳዩ ወደ ሌላ ምእራፍ ተሻገረ ። ደገመ ደጋገመ ። ደካማን በመርዳት እዝነት የጀመረችው ልቡ የአላህንና የሩሱለላህን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ንግግር ለመስማት በፍቅር ተጠለፈች ።
_
የተወሰነ ሳምንታት ከተመላለሰ ቡሃላ እሱን ወደ መስጅድ እንዲመላለስ ሰበብ የሆኑት ሰውዬ በሁለት ጁምዓ መሃል ወደ አኺራ ሄዱ ።
_
ይህ ሰው ውስጡ ሀዘን ቢኖርም በየጁምዓው ከመስጅድ ቅጥር ግቢ ውጪ በመሆን ውስጡን የማረከውን ኹጥባ ለማዳመጥ መመላለሱን አላቋረጠም ።
_
አንድ ቀን ለይለተል ጁምዓ በመናም በህይወቴ አይቼ ማላውቀው በጣም የሚያምር ሰው እጄን ይዞ መስጅድ አብረን ገባን ኹጥባም ሰማሁ ሰላትም ስግጄ ከመስጅድ እየወጣን ሳለ ከእንቅልፍ ነቃሁኝ  የመጀመሪያው የሱብሂ አዛን  ወአሽሃዱ አነ ሙሀመደን ረሱለላህ እያለ ነበር የነቃሁት ።
_
ታዲያ ይህንን መናም ለማስፈታት ማንም ጋር መሄድ አልፈለገም የጁምዓ ሰላት ወቅትን ጠብቆ እንደበፊቱ ሰው ሊያደርስና ኹጥባ ሊሰማ ሳይሆን ከሙስሊሞች ጋር
የሚቀላቅለውን ሰው ለመፈለግ ነበር የወጣው ።
_
በመጨረሻም ከሰፈራቸው አንድ ሻይ ቤት የነበረው መሀመድ የሚባል ሰው ጋር በመሄድ ወደ መስጅድ  ይዞት እንዲሄድ ሲጠይቀው ሙሀመድም በመጀመሪያ ሸሃዳ
መያዝ እንዳለበት ይነግረዋል ።
_
እሱም ሸሃዳ ምንድነው ቢለው > ብለህ ትመሰክራለህ ሲለው ይህንንማ ማታ ያ ሚያምር ሰው አስብሎኛል ብሎ ማታ ያየውንና የሰማውን  ነገረው ።
_
ሙሀመድም እየተገረመ ወደ መስጅድ በመውሰድ ከኡለሞች ጋር በማገናኘት የነገረውን ሲነግራቸው ኡለሞቹም እኛ ረሱለላህ ያሰለሙትን ሰው ደግመን አናሰልምም ባይሆን ደስ እንዲለን እስቲ ያሉህን ንገረን አሉት ።
_
ጓደኛዬም የመጨረሻውን ምእራፍ እነዚያ ከመስጅድ ቅጥር ግቢ ውጪ ሆኖ በፍቅር ምክራቻውን ሲሰማ ልቡን በፍቅር ያሸበሩትን  ኡለሞችን ፊት ፊታቸውን እያየ የሰማውን ሸሃዳ ለኡለሞች አስደምጦ …………… ገቢ ሆነ ።
_
በሰአቱ ቦታው ላይ የነበሩት ኮሚቴዎች ህዝብ ፊት ቆሞ መስለሙን እንዲገልፅና ህዝቡም  የደስታ መገለጫ ስጦት እንደሚሰጡት ሲነግሩት እሱ ግን መስለሜን መናገር እችላለሁ ። ግን ስጦታ ያላቹትን ግን ማርያምን አለፈልግም ሲል የኮሚቴዎች ሳቅ መልሶ እሱንም አስቆት እስላምን መኖር ከጀመረ ይኸው ሁለት አስር አመታቶች አለፉት ።
==============
_
ረሱለላህ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ሰዎችን ወደ ኢስላም ያስገቡት በዳእዋ ፣ በዱዓ ፣ በኢክራም ፣ በኢኽላስና በአኽላቅ ሲሆን አብዛኛው ሶሀባ ኢስላምን የተቀበሉት በአኽላቃቸው ነበር ።
_
ኢማናችን፣ተቅዋችን ፣ኢኽላሳችን፣እንዲሁም ኢባዳዎቻችንን ለሌሎች አይታያቸውም ነገር ግን  አኽላቃችንን ነው የሚመለከቱት ።

አላህ ያግራልን !!

Jan 31 2020

@yasin_nuru    @yasin_nuru

8.6k 0 55 40 201

🛤በውስጥ መስመር የተላከልኝ ማስታወሻ
- ስሞት አላስብም፣ አልጨነቅም፣

- ገላዬ ፈራሽ ነውና ምን አሳሰበኝ

ሙስሊም ወንድሞቼ መደረግ ያለበትን ሁሉ ያደርጉልኛል፡፡

1- ልብሴን ያወልቃሉ፣

2- ያጥቡኛል፣

3- ይከፍኑኛል፣

4- ከቤቴ ይዘውኝ ይወጣሉ፣

5- ወደ አዲሱ ቤቴ (መቃብር) ይወስዱኛል፣

6- ብዙዎች ጀናዛዬን ለመሸኘት ይመጣሉ፣

7- እኔን ለመቅበር ሥራቸውንና ቀጠሯቸውን ሁሉ ትተው የሚመጡ አሉ፡፡

ቀጠሯቸ መካከል ምናልባት ላንዳፍታ እንኳን ስለኔ አስበው የማያውቁ ብዙ ናቸው፡፡

8- ቤተሰቦቼ እኔን ላለማስታወስ ያለኝን ነገር ሁሉ አውጥተው ይጥሉ ይሆናል፤ አሊያም በኔ ሥም ይመፀውቱ ይሆናል

- ቁልፎቼ 🔑🗝

- መጽሐፎቼ 📚

- ጫማዎቼ 👟

- ልብሦቼ 👖👔…..

በአንድ ነገር ግን እርግጠኛ ሁኑ፡፡

- በመሞቴ ይህች ዱንያ ሐዘኗ አልበዛም፣ አለች አልፈረሠችም፣

- የዓለም 🌍 እንቅስቃሴም ላፍታ አልቆመም፣

- የኢኮኖሚው 💰 ቀውስም አልተፈጠረም፣

- በሥራ ቦታዬ ላይ ሰው ለመቅጠር ማስታወቂያ🧾 ይወጣል፣

- ንብረቴ 💸🏠🚘 የወራሾቼ ይሆናል፣ በትንሽ በትልቁም ኦዲት የምደረገው ግን እኔ ነኝ፣

- ስሞት መጀመሪያ ከኔ የሚገፈፈው ስሜ ነው፡፡ በሥሜ መጠራቴ ይቀራል፤

- ጀናዛው የታለ እባላለሁ፡፡ ጀናዛውን ዉሰዱ፣ አምጡ እንስገድበት፣ ጀናዛውን እንቅበር … ይባላል

- ሥልጣኔ፣ ከተከበረ ቤተሰብ መሆኔ፣ ጎሳዬ … ሁሉ ዋጋ ያጣል፤



ዱንያ ይህን ያህል ቀላልና ተራ ነገር ነች፤ የምንሄድበት ዓለም ግን አቤት ክብደቱ! ማስፈራቱ! …

በሕይወት ያለህ ወዳጄ ሆይ! በመሞትህ ሦስት ዓይነት ሐዘን አለ

1- የሚያውቁህ ዋ ያ ሚስኪን እኮ ሞተ! ይላሉ

2- ባልደረቦችህ ለሰዓታት አለያም ለቀናት ያዝኑና ወደ ሳቅና ጨዋታቸው ይመለሳሉ፣

3- ትልቁ ሐዘን ያለው ቤትህ ነው፣ ቤተሰብህ ጋ … ሁሌም ያስታውሱህ ይሆናል፣

የዱንያ ታሪክህ በዚህ መልኩ አበቃ ፤ የመጨረሻው ዓለም ታሪክህ ተጀመረ

ሁሉ ነገርህ ተወሰደ፣ ፈረሠ፣ አለፈ፣ ጠፋ!!!

1- መልክህ፣

2- ሀብትህ፣

4- ጤናህ፣

5- ልጅህ፣

6- ቪላህ፣

7- ዝናህ፣

8- ሚስትህ/ባልሽ

ካንተ ጋር ሥራህ ብቻ ቀረ

እውነተኛው ሕይወት ተጀመረ፡፡

እዚህ ላይ አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ/ሽ

ለአኺራህ ምን አዘጋጀህ!! እስቲ በጥልቀት አስብ፡፡

እናም በርታ፣ በርቺ እህቴ

1- በግዴታዎች፣

2- በሱንና ነገሮች፣

3- በድብቅ መፅውት፣

4- መልካም ሥራ አብዛ፣

5- ሌሊት ተነስተህ ስገድ፣

ትድን ዘንድ ጠንክር፣ ይሳካልህ ዘንድ በርታ፡፡

መልካም ንግግር ምጽዋት ነው፡፡ ምንም የለኝም አትበል፡፡ ሌላ ነገር ብታጣ ይህችን በእጅህ የገባችውን ፅሑፍ መጽውት፣ ምንም ጉልበትና ጊዜ አይወስድብህምና አታመንታ፡፡

ለወዳጅ ዘመዶ ሼር ሼር ሼር .....✔️

#Copied

@yasin_nuru @yasin_nuru

12.9k 0 386 27 229

ገንዘብ ደስታን አይፈጥርም ብላችሁ ካሰባችሁ



ብሩን ወደ አካውንቴ ላኩልኝ አለ አንዱ😁

ኧረ አልሃምዱሊላህ እንበል

@yasin_nuru @yasin_nuru

9.7k 2 19 84 274

ስለ ቻይና ሙስሊሞች 10 ነገሮች

🔷 ኢስልምናን ለመጀመሪያ ጊዜ ቻይና የደረሰው በዑመር (ረዐ) ኸሊፋነት ዘመን በታላቁ ሰሃባ ‹‹ሰዓድ ኢብን አቢ-ወቃስ›› (ረዐ) እንደሆነ ይነገራል።

🔷 በቻይና የመጀመሪያውን መስጂድ ያሰራውም ሰዓድ ሲሆን ‹‹ሑዓሼንግ›› የሚባልና አሁንም በይዞታ የሚገኝ የ1300 ዓመት የዕድሜ ባለፀጋ መስጂድ ነው።

🔷 በአገሪቱ 80 ሚሊዮን የሚገመቱ ሙስሊሞች እንዳሉ የሚገመት ሲሆን ከህዝቡን 2% ገደማ ይሸፍናሉ።

🔷 ሙስሊሞቹ በብዛት የሚኖሩበት ቦታ ‹‹ዢንጂያንግ›› ሲባል ከአፍጋስታን፣ ፓኪስታን፣ ህንድ፣ ታጃኪስታን እና ሌሎች ጋር የሚዋሰን ሰፊ ግዛት ነው።

🔷 ‹‹ዢንጂያንግ›› ቀድሞ የዑስማያ ኸሊፌት የተርኪስታን ግዛት የነበረ ሲሆን ኸሊፋው ከወደቀ በኋላ በ1949 ቻይና በሐይል ልትወስደው ችላለች። ግዛቱም ከቻይና ሰፊው ሲሆን በማዕድን የበለፀገ ነው።

🔷 ቻይና ውስጥ ሁለት አይነት ነገድ ያላቸው ሙስሊሞች ያሉ ሲሆን ‹‹ሐም›› እና ‹‹ኡግሁር›› ይባላሉ። ሐሞች ቻይናዊ ሲሆኑ ኡግሁር ደግሞ በመልካቸውም የተለዩ የመካከለኛው ኤዥያ ዝርያዎች እንደሆኑ ይታመናል።

🔷 በቻይና ሁሉም ሙስሊሞች መድሎ ቢደርስባቸው ከፍተኛ በደል የሚፈፀምባቸው ግን የኡግሁር ሙስሊሞች ናቸው።

🔷 የኡግሁር ሙስሊሞች ከሌላው በተለየ በደል የሚደርስባቸው አንደኛው በዘራቸው ቻይናዊ ስላልሆኑ ሁለተኛው ደግሞ አካባቢው በማዕድን የበለፀገ ስለሆነ መንግስቱ ህዝቡን የማጥፋት ዕቅድ እንዳለው ይነገራል።

🔷 ቻይና በኡግሁር ሙስሊሞች ላይ ከምትፈፅመው ግፍ መካከል  ወላጅና ልጅን መነጣጠል፣ በማጎሪያ ካምፖች ማሰር፣ አካላቸውን መበለት፣ ሰላት፣ ፆምና ቁርኣን መከልከል፣ አልኮል ማስጠጣት፣ የአሳማና ውሻ ስጋ ማስበላት፣ መግደል እና ሌሎችንም ይፈፅማሉ።

🔷 የቻይና መንግስት ይህን ሁሉ አሰቃቂ ግፍ እየፈፀመ ድርጊቱ ‹‹ሽብርተኝነት›› አልተባለም።

👉 በዑመር (ረዐ) ዘመን የቻይና መንግስት ለፋርስ ንጉስ መጠጊያ እንኳን ለመስጠት ኸሊፋውን በመፍራት እንቢ ማለቱ ይነገራል። ዛሬ የሙስሊም አገራት የኡግሁር ሙስሊሞች አሰቃቂ ግፍ እየተፈፀመባቸው እያዩ ከቻይና ጋር የንግድ እንቅስቃሴያቸውን እንኳን ማቆም አልቻሉም።

‹‹አይሁዶችንና እነዚያን ያጋሩትን ለእነዚያ ለአመኑት በጠላትነት ከሰዎች ሁሉ ይበልጥ የበረቱ ሆነው በእርግጥ ታገኛለህ።››
(ማዒዳህ 82)

© ሰል ማን

@yasin_nuru @yasin_nuru

11.1k 0 41 25 171

ፍቅር

በአንድ ወቅት ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ቢላል ኢብኑ ረባህን ከኃላው በፍቅር ስሜት እቅፍ አድርገው ይይዙትና ድምፃቸውን ቀይረው...

❤️ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) :- "እኔ ማን ነኝ"?

ቢላል (ረ.ዐ) :- ዑመር (ረ.ዐ) ነህ?

❤️ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) :- አይደለሁም

ቢላል (ረ.ዐ) :- አቡብክር (ረ.ዐ) መሆን አለብህ?

❤️ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) :- አሁንም ተሳስተሃል

ቢላል (ረ.ዐ) :- በቃ ዑስማን (ረ.ዐ) ነህ?

❤️ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) :- አላወቅከኝም

ቢላል (ረ.ዐ) :- ዓሊ (ረ.ዐ) ነህ ማለት ነው...
እያለ ያቀፈውን ሰው ማንነት ሲጠይቅ ይቆያል።

ከዚያም ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ለቀቅ አደረጉትና ከፊት ለፊቱ በመምጣት

"ቢላል ሆይ! እውነት እኔ መሆኔን አላወቅክም ነበር እንዴ"? ሲሉ ጠየቁት

ቢላልም "የአላህ መልእክተኛ ሆይ!" በደንብ አውቄዎታለሁኝ ነገር ግን ለረጂም ጊዜ እንድታቅፉኝ ስለፈለኩኝ እንጂ ሲል መለሰላቸው።

❤️ሰለዋቱ ረቢ ወሰላሙ አለይከ ያ ረሱሊላህ❤️

@yasin_nuru @yasin_nuru

11.8k 2 121 103 551

ፈገግታ ሱና ነው😁

አንዱ እኮ ነው መላይካ ውሻ ያለበት ቤት አይገባም ሲባል ሰምቶ



መለከል-መውት ቤቱ እንዳይገባ ውሻ ጊቢው ላይ አስሯል።


ሰሉ ዓላ አሽረፈል-ኸልቅ!!

@yasin_nuru
      

10.5k 0 52 44 321

የሰው   ዘር   መጀመሪያ  የሆኑት  #አደም።

ልዩ  የክብር  ቦታ  የተሰጣቸው  #እንድሪስ።

950   ዓመታት  በማስተማር  የቆዩት  #ኑህ

ወደዓድ  ህዝቦች  የተላኩት    #ሑድ።

ድንጋይ  ተፈልቅቆ  ግመል  የወጣችላቸው  #የሰሙዱ ሳሊህ።

የኑምሩድን  እሳት ድል  በማድረግ  የወጡት  #ኢብራሒም።

መላእክት በእንግድነት  ወደቤቱ  የገቡት  #ሉጥ።

በካዕባ ግንባታ የተሳተፉት  #ኢስማኢል።

የአባታቸው  የኢብርሂም ልድ #ኢስሐቅ።

የ12  ወንድ  ልጆች  አባት የሆኑት  #ያዕቆብ።

እጅግ ታጋሹና  ጥበበኛው    #ዩሡፍ።

መከራን  ቻዩና  ጸሎተኛው      #አዩብ።

የሁለት  ሴቶች አባት  የሆኑት  የመደኑ #ሹዓይብ።

ባህር  የተሰነጠቀላቸው  የኢምራን  ልጅ #ሙሳና  ወንድማቸው #ሐሩን

በዓሣ  ሆድ  ውስጥ  ዚክር  ያደረጉት  የነይነዋው #ዩኑስ።

ብረት እንደጭቃ  የሚለዝብላቸው ድምጻዊው  #ዳውድ።

ንፋስን  እንደፈለጉ  የሚያዙት  ንጉሱ  #ሱለይማን።

ቁርኣን  ስማቸውን  እንጅ  ያላስዋወቀን አልየሰእ፤ #ኢሊያስና  #ዙልኪፍል።

አናጺውና  የመሪየም  አሳዳጊ  #ዘከርያ።

በልጅነታቸው  ነብይነትን የተሰጡት #ያህያ።

ያለአባት  የተወለዱት  ተአምረኛው  የመሪየም  ልጅ  #ዒሣ።

ለተልእኳቸው  የቦታና  የዘመን  ግርዶሽ        የተነሳላቸው  #ሙሐመድ ናቸው።

እንግዲህ  ከአላህ  ጋር  ያለንን  ግንኙነት ለማስተካከል  በተላኩት  ነቢያት  በሙሉ  ያለምንም  ልዩነት ማመን  ይኖርብናል።

@yasin_nuru     @yasin_nuru

13k 2 225 25 295

❤️የኛ ነብይ ﷺ
ዝምታቸው ብዙ ሳቃቸው ትንሽ ነበር።

❤️የኛ ነብይ ﷺ በህፃናት ጎን ሲያልፉ ሰላም ይሏቸው ነበር።

❤️የኛ ነብይ ﷺ ለሰው ልጆች ለእንስሳት ሳይቀር ያዝኑ ነበር።

❤️የኛ ነብይ ﷺ ሰዎችን አክባሪና ተናናሽ ኩራት የሚባል ነገር አያውቁም ነበር።

❤️የኛ ነብይ ﷺ ይቅር ባይና ይቅር ማለትን የሚወዱ ነበሩ።

❤️የኛ ነብይ ﷺ የቅርቧ አለም ብልጭልጭ ይልቅ የመጨረሻውን አለም የሚናፍቁ
ዛሂድ ነበሩ።

❤️የኛ ነብይ ﷺ ጌታቸውን አመስጋኝ ሰዎችንም አመስጋኝ ነበሩ።

❤️የኛ ነብይ ﷺ ሷላትን የልቤ እርጋታ እያሉ ለጌታቸው ባጣምም ይሰግዱ ነበር።

❤️የኛ ነብይ ﷺ በፈተናዎች እና በችግሮች ላይ ታጋሽ ነበሩ።

❤️የኛ ነብይ ﷺ ውሸትን በጣም ይጠሉ የነበሩ «ታመኙ-እውነተኛ» ነበሩ።

❤️የኛ ነብይﷺ ስድብንም ሆነ እርግማንን ይጠሉ ነበር።

የኔ ዉድ ነብይ ፤ ሩሔም፣ ገንዘቤም እናቴም፣ አባቴም ለአንቱ ፊዳ ይሁኑሎት..
ሷለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም።

@yasin_nuru    @yasin_nuru

12.7k 2 119 101 354

ፈጣሪህን ብቻ አታስቀይም እንጂ ... ሰዉኮ ብታዝለዉም እግሬ ለምን ተንጠለጠለ... የሚል ፍጡር ነዉ🥺🥺


ትክክል ነው?

የኡመር(ረ.ዐ) እና የአህያው ታሪክ ትዝ አለኝ

@yasin_nuru @yasin_nuru

11.5k 0 21 30 152

ቲክቶክ ላይ ዩትዩብ ላይ አንዳንድ ወንድሞች

አንድ ሰው የተሳሳተ መንገድ ላይ ሆኖ ስታዩት
እሱን ለማተካከል ከፈለጋችሁ አደብ ባለው መልኩ ለብቻው ምከሩት።

እኛ ወንጀላችን አጠገባችን ሰው የማያስቀርብ ሆኖ ሳለ ሌላ ሰውን ግን አጥረግርገን የምንሰድብበት፤ተውበት እንዲያረግ ሳይሆን በወንጀሉ እንዲገፋ በሚያረግ በቁጣ የምንናገራቸው እኛ ማን ሆነን ነው?

ስንመክር በአደብ ለብቻ ይሁን አልመለስም ካሉ እንግዲህ ምንም ማረግ አንችልም በማስገደድ አይሆንም። ነብዩ ሙሳ እንኳ ፊርዓውንን እንኳ እንዴት ነው አናግር የተባሉት እኔ ጌታ ነኝ ያለውን።

ስለዚህ እኛ ከሙሳ በልጠን ነው በአደባባይ ክብራቸውን ዝቅ እያደረግን የምንናገረው🤔 በግድ እንዲ ካልሆናቹ የምንለው? ከልባችሁ ዱዓ አድርጉላቸው

የባሳ ለመበላሸታቸው ሰበብ አትሁኑ ዱአ አድርጉላቸው በየኮሜንቱም እየገባችሁ መጥፎ ነገር የምትፅፉ አላህ እንዲመልሳቸው ዱዓ አድርጉላቸው። ይሄን ማድረግ #ካልቻላችሁ_ዝም_በሉ።

ቲክቶክ ላይ ከእስልምናችሁ ጋር የማይሄድ ነገር የምትሰሩ ይቅርባችሁ ሞት ቢመጣ ዋጋ ያስከፍላቹሃል። የእስልምና እምነት ተከታይ ስለሆናችሁ የእስልምና ወገኖቻችሁ የናንተን ቪድዮ ሲያዩ ይረበሻሉ እና እንተም የዚች አለም ነገር ሳያሳስባችሁ ወደ እስልምናችሁ ተመለሱ አላህ አያሳፍራችሁም የምትፈልጉትን ይሰጣቹሃል ተመለሱ ወደ አላህ።

አላህ ሁላችንንም ወደ እሱ ይመልሰን።

@yasin_nuru    @yasin_nuru

12.8k 2 23 51 159

//ማነው ድሀ ጨዋ አይደለም ያለህ?//

♨አንድ ሀብታም ሰውዬ ወደ አንዲት ሊስትሮ ወደ ምትሳራ ብላቴና ሄደው ጫማ ማስጠረግ ጀመረ

🌻በመጀመሪያ ቀን በንቀት አይኑ እያየ አስጠርጎ ሄደ

🌻በሁለተኛ ቀንም ተመሳሳይ ፈት አሳይቶ ሄደ

🌻ሦስተኛ ቀን ልጅቷ ጫማውን እየጠረገች  በስህተት ትንሽ ቀለም ካልሲ ላይ አደረገች በዚህ የተናደደው ሰውዬ በጣም ተሳድቦ  ይቅርታ እያለችው ጥሏት ሄደ

ከትንሽ ደቂቃ ቡኋላ ተመልሶ መጣ ለካ ስልኩን ጥሎ ሂዶ ነበረ ከዛም ከትህትና ስልክ ጠፍቶብኝ ነው እዚህ ጥዬ ይሆን እንዴ ብሎ ይጠይቃል

ልጅቷ አዎ ስልኩ እዚህ አለ መጥቼ ልሰጥህ ፈልጌ ነበረ ግን የት እንደሄክ አላወኩም ትላለች

ሰውዬውም በልጅቷ ታማኝነት ተገርሞ ሀምሳ ብር ከኪሱ አውጥቶ ይሰጣታል

ልጅቷም እባክህ ጌታዬ አምስት ብር ጨምረህ ስጠኝ ትላለች

ሰውዬውም ያለ ምንም መቅመማት አውጥቶ ሰጣት

ልጅቷም ሀምሳ ብሩን መልሳ ሰጠች ምነው ላንቺ እኮ ነው ለታማኝነትሽ ብዬ ነው ይላታል

የታማኝነት ዋጋ ስንት ነው ትላለች

ሰውዬውም እኔ'ጃ ብሎ መለሰ

ልጅቷም አንተም ታማኝ ለመሆን ሞክር መርዳት ካለብህ ሰው መጀመሪያውኑ እርዳ አምስት ብሩ የሰራውት ብር ነው እኔ ታማኝነትን አልሸጥም ብላ ጥላው ሄደች

ሌላ ቀን መጥቶ ልጅቷን ቤት ብዙ ጫማዎች አሉኝ እቤት እንሂድ ብሏት ይዟት ሄደ

ከዛም እሷ ስራ እየሰራች እሱ ቤት ጥሏት ይሄደል። ቤት ውስጥ ጠረጴዛ ላይ ብዙ ብር አስቀምጦ እመጣለሁ ብሎ ይሄደል

ልጅቷም ብሩን ከጠረጼዛ አንስታ ጥሩ ቦታ ላይ አስቀመጠች

ሰውዬው ከሄደበት ቦታ መጥቶ ብሩን ጠረጴዛ ላይ ተመለከተ ብሩ እዛ አልነበረም ሰውዬውም ልጅቷን ጠርቶ እናንተ ድሆች መቼም ብር አይታችሁ ማለፍ አትችሉም አይደለም ባለፈው ታማኝ ነኝ ብለሽ ነበረ እኮ ብሎ ሰደባት

ልጅቷም አትሳሳት እኔ የድሀ ልጅ ድሀ ነኝ ድሀ የሆነ ሁሉ ሌባ ባለጌ አይደለም ሀብታም የሆነ ሁሉ ደግሞ ጨዋ አይደለም ስለዚህ ሰውን ሰው በመሆኑ ብቻ ቅረብ😡

አንድ ሰው መሆን የሚችለው ራሱን ብቻ ነው
አንድ ሰው ብዙ ሰው መሆን አይችልም
ስለዚህ በአንድ ሰው ስህተት  ብዙ ሰዎችን አትሳደብ ስለ ሁሉም ነገር አመሰግናለሁ።

ብሩን እዚህ መጥፎ ቦታ ላይ አይቼ እዛ ጥሩ ቦታ አስቀምጨልሀለው ብላ ጥለው ሊትሄድ ስትል ሰውዬው መጥቶ ተንበርክኮ ይቅርታ ጠየቀ

ከዛም አብራው እንድትኖር ተማፀነ

ሰውን በልብሱ ወይንም በአቋሙ አይታችሁ አትፍረዱ ልብና ልብስ የተላያዩ ነገሮች ናቸዉ
ልብ የፈጣሪ ስጦታ ሲሆን ልብስ በብር የሚገዛ እቃ ነው ስለዚህ የፈጣሪን ስጦታ በብር ከሚገዛው እቃ ጋር አታወደድሩ

ቅንነት  ለራስ  ነው
ቅንነት  መልሶ  ይከፍላል 

@yasin_nuru @yasin_nuru

12.1k 2 82 21 212

ለፈገግታ😁😁

ሙስሊም ወንድ ታክሲ ውስጥ ሂጃብ የለበሰችን ሴት ሲያይ👀😂

ሙስሊም መሆኑን ለማሳወቅ #በአላህ ፍቃድ ወራጅ አለ😁😁😁😂😂

እስቲ ጨምሩበት😂

@yasin_nuru @yasin_nuru

11.7k 0 86 143 399
Показано 20 последних публикаций.