( የመጨረሻ ክፍል)
ክፍል 18
============================
#sex_is_life_part_18
.
"ያኔ እንደዛሬው ከጌታዬ ጋር ሳንጨካከን
በፊት እንዲያስተወኝ ብዙ ጊዜ ፀልያለሁ ፤ ግን
አልቻልኩም። ይባስ ብሎ ምን ባደርግ ጥሩ
ነው?........ተደብቄ ፣ በእፈረት ተሞልቼ
ማድረጌ ሳያንስ አደባባይ ላይ ፣ ሰው በበዛበት
ቦታ ሁሉ ከራሴ ጋር ማድረግ ያምረኝ ጀመር።
ወንዴ ይሄ ታሪክ እንኳን በጣም ብዙ ነው።
ምክንያቱም ደም ዕንባ እስካነባ ድረስ
ተሰቃይቼበታለሁና!.... ..." ለረዥም
ደቂቃዎች ዝም አለችኝ። ዓይኖቿ ላይ እንደ
አራስ ልጅ ንፁህ የሆኑ ዕንባዎች ግጥም አሉ።
ወሬ ማስቀየስ እንዳለብኝ ገባኝና ወደ ዋናው
ጉዳዬ ዘው ብዬ ገባሁ.......
"ሙና ከእናትሽ ጋርስ ከዛ በኋላ እንዴት
ሆናችሁ?"
"..........ወንዴ ሰው ላይ ክፉ ካደረክ ይዘገያል
እንጂ የወርደትህ ቀን መምጣቱ አይቀርም።
ያኔም ይሄ የሀይማኖት መፅሐፍት ላይ የተፃፉት
ገሀነም ና ሲኦል ገብተህ የእቶን ባህር ላይ
አትዋኝም። ሲኦልም ገነትም ያሉት እዚችው
ምድር ላይ ነው። እየታወቀን ላይሆን ይችላል
እንጂ ሁሉም እንደየስራው የእጁን
እየተከፈለው እየኖረ ነው ያለው....."
አቋረጥኳት
"አንቺ ታዲያ ምን በድለሽ ነው እንዲህ የሰቆቃ
ህይወት የምትኖሪው?"
"ወንዴ ደግሞ ብዙ ስታነብ ኮ ብዙ ነገር
የምታውቅ ይመስለኝ ነበረ ፣ ለካ አንተም
እንደሌላው ትላልቅ እውቀቶችን ፍለጋ
ስትማስን ምድር ላይ ፍጥጥ ብለው የሚታዩ
ጥቃቅን የሚመስሉ መሠረታዊ ዕውነታዎችን
ረስተሀቸዋል። ለምሳሌ አንዳንድ ቀን ብዙ
እሰራለሁ ብለህ አቅደህ ፣ አንዱንም ሳትሰራው
ውለህ ታውቃለህ?"
"በጣም ብዙጊዜ ነዋ!"
"አየህ እነዛ ቀናቶች ምን ብታደርጋቸው ካንተ
ቁጥጥር ውጪ የሆኑ የማይለወጡ ለመባከን
የተፈጠሩ ቀናቶች ናቸው። ልክ እንደዛ ሁሉ
እኔና እኔን መሰሎች ደግሞ ለመባከን
የተፈጠሩ ነፍሶች ነን።......ምነው ይሄን ጥቁር
ፊትህን አገለባበጥከው?......
..አልተዋጠልህም አይደል?!......... ......አሁን
አንዳንድ ሰዎች ገጥመውህ አያውቁም ፣
ሁሌም ከሰው በላይ ይለፋሉ። ሳንቲም
ለማጠራቀም ላባቸውና ደማቸው
እስኪቀላቀል ይሰራሉ ፣ ግን ኑሮአቸው ፈቀቅ
ብሎ አያውቅም። ያንተ እናትስ ዕድሜ ልኳን
ጉሊት ቸርቻሪ ነበረች አላልከኝም። ከዚህ
በላይ ምን ማረጋገጫ ትፈልጋለህ? በቃ አንተ
ፍልስፍና የሚመስልህ ኦሾ የፃፈው ብቻ ነው
አይደል? አይንህን በደንብ ገለጥ አድርገህ
ዙሪያህን ተመልከት ዓለምን የሚቀይሩ
ሀሳቦችን እግርህ ስር ወድቀው ነው
የምታገኛቸው ፤ እዚሁ ድድ ማስጫ ላይስ
ስንቷ የሰፈር ልጅ በየአረብ ሀገሩ የወገቧ ውሀ
ልክ እስኪዛባ 18 ሰርታ 8 ዘጠኝ 10 ዓመት
ስትፈጋ ቆይታ ይኸው እያየናቸው አይደል
ዱምቡሎ ሳይዙ እየመጡ ሞራላቸው እየላሸቀ
የቤተሰባቸው ሸክም ሲሆኑ! ታዲያ እነዚህ
ስላልፈጉ ይመስልሀል ያልተለወጡት?
አይምሰልህ ለመባከን የተፈጠርን ሰዎች
ስላለን ነው። ሀበሻ ወዶ አይደለም
የሚለው
፤ይሄን የመሰለ ፍጥጥ ያለ ፍልስፍና ከወዴት
ይመጣል። አየህ ግን ችጋር እንዴት
እንደሚያራቅቀን! ይሄ ህዝብ ግን
አይገርምህም ዓለም ባንቀላፋችበት ሰዓት ነቄ
ሆኖ ኖሮ ዓለም በተራዋ መንቃት ስትጀምር
ደግሞ ፉዞ ሆኖ ቀረ!
.
"እናልህ የእናቴም የውርደት ቀን ብዙም
ሳይቆይ ሳላስበው ጆሮዬ ውስጥ ዘው ብሎ
ገብቶ እሷ ላይ ሒትለርን እንድሆን አደረገኝ።
እዛው ሾላ በፍራሽ ተራው ጋር ወደ ቁጭራ
ስትገባ አንድ የእናቴ የልብ ጓደኛዋ የሆነች ሸሌ
ነበረች። እሷም በኤድስ ነው የሞተችው ፣
ነፍሷን ይማረውና.........እ ናልህ ከናቴ ጋር
ሲገናኙ ከምርቃና እስከ ቅምቀማ ድረስ
የማያወሩት ጉድ የለም። ዕድለ ጎዶሎ
አይደለሁ። እናቴ አዝናልኝ ነው ያስደገመችብኝ
ብዬ እሷን ለማስደሰት ትምህርቴን ካቋረጥኩ
በኋላ ያለእረፍት ጉሊት እነግድ ነበር።
እንደልማዴ አምሽቼ ወደ ቤት ስመጣ እናቴና
ጓደኛዋ ፣ ጫታቸውን ጨርሰው ደረቅ ጅን
እየጠጡ ሁለቱም ሰክረው ልፍድድ ማለት
ጀምረዋል ፤ ስለእኔ ሲያወሩ ሰማኋቸው.....
'አንቺ ግን በጣም ክፉ ነሽ....' እያለች ጓደኛዋ
ትስቅላታለች
'እና ታዲያ ሳትታሰብ ተወልዳ ፣ ወጣትነቴን
ማጨለሟ ሳያንስ ፣ አንድ ቀንም ሳትጦረኝ
ልሞት ነው። አሁን እያረጀሁ ነው ፣
በሽታውም እየጎዳኝ ነው። እኔ ደግሞ ቶሎ
መሞት አልፈልግም። ኧረ እንደውም ጭራሽ
መሞት አልፈልግም። ከመሞት ምን
ይገኛልና ልሙት?!.......... መኖር ካለብኝ
ደግሞ የሚያኖረኝ ሰው እፈልጋለሁ።
ሳያቋርጥ እኔን ብቻ የሚደጉም! እኔ ደግሞ
ከሙና ውጪ ማንም የለኝም! እሷ ደግሞ
እንኳን እንዲሁ በዘራችንም ቅንዝራሞች ነን
ቁላ ከለመደች ርግፍ አድርጋ ነው የምትረሳኝ
፣ ስለዚህ ያ ሙጣምጢያምን 2 ቀን በነፃ
ስበዳለት ገድግዱን ሰራልኝ። ይኸው
ታኖረኛለች......... ...'
........አናቴ ላይ ዕብድ የሚያክል ድንጋይ
የወደቀብኝ መሰለኝ......በቅፅበት ውስጥ ሁለ
ነገሬ ፍርክስክስ አለ......ወንዴ አታምነኝም
አይኖቼ እያዩ ድንዝዝ አሉ ፣ ሁሉ ነገር ድቅድቅ
ሆነብኝ......እጆቼ የት እንደሆኑ የማውቀው
ነገር የለም.........እግሬ ቄጤማ
ሆነብኝ......የስሜት ህዋሶቼ በሙሉ መስራት
አቆሙ......ራሴን ስቼ ወደኩ......ለስንት ቀን
እንደተኛሁ አላውቅም።
የነቃሁ ቀን ግን ወሰንኩ። እዚች ዓለም ላይ
ያሉ ክፉዎችን በአቅሜ መቀነስ እንዳለብኝ።
ወሰነኩና አደረኩት።
.
"እናቴ እየታመመች ስትሄድ የቤት ኪራይ
መክፈል ስላቃታት ከቁጭራ ተባረርን ፣
ከዛም በቅናሽ ብር ከሚካኤል ጀርባ ጨረቃ
ሰፈር......አሁን ሚሊኒየም ፓርክ እንሰራለን
ብለው እነ አጅሬ ሚሊዮን ብር የዛቁበት ሰፈር
ላይ በርካሽ ቤት ተከራይቼ ገባሁ። እናቴን ቶሎ
እንዴት መግደል እንዳለብኝ አሰብኩ።
ወዲያው እንዲህ አደረኩ። በሽታዋ ሞቷን
እያፋጠነላት ስለነበር ፤ እኔ ደግሞ ምግቧን
ነፈኩዋት። ቀስ ቀስ እያልኩ በሴራዬ አነኳት።
በቀን አንዴ እሰጣት የነበረውን ምግብ
እየተውኩት መጣሁ......በሶስተኛው ሳምንት
አጥንቷ ብቻ ቀርቶ ሞተች። ሰፈርተኛው
ተባብሮ የካ ሚካኤል ጓሮ ቀበራት። እኔ
የተከራየሁበትን ቤት ሳልስትም ሳልቀመጥ
ትቼ ወጣሁ። እናቴ በመሞቷ አሁን ምንም
አይሰማኝም ፣ ለግዜር ስራ ያቃለልኩለት ነው
የሚመስለኝ። ፍትህ ነው የሰጠሁት!
ፍትህ..........."
ምንም አልመለስኩላትም ፣ ህመሟ
ይገባኛል። ዓለም ላይ ብቻዋን ተነጥላ
የምትኖር ሴት ሆናለች። የሷ ጫማ ውስጥ
አልቆምኩኝምና ልፈርድባት አልችልም! ቶሎ
እንድትረሳው ሌላ ጨዋታ ጀመርኩ። አመሻሹ
ላይ ከቤቷ ልወጣ ስል.......እጄን ያዘችኝ......ዞር
ብዬ አየኋት........ዓይኖ ቿ ላይ የማይነበቡ ግን
የሚገቡ የስሜት ፊደሎችን አነበብኩ........ከን
ፈሯን አየሁት ይንቀጠቀጣል........ .ከንፈሬን
በምላሴ አረጠብኩት......... .......
ተፈጸመ
https://t.me/yewesib_tarikochhh