✞ ጋሜል - የመዝሙር ግጥሞች ✞


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


✟ የኦርቶዶክሳውያን መንፈሳዊ የምስጋና ቤት ✟
ቤተ ክርስቲያንን አንተውም ከቶ
የሰጠንን አምላክ በደሙ መስርቶ
የሰጠንን ጌታ በመስቀሉ ሞቶ
የአምላካችንን ቤት አንተውም ከቶ
ለማስታወቂያ ሥራ➝ @Naolviva
💿 የተዋሕዶ የመዝሙር ግጥሞች 💿
   ✍ / ትምህርቶችን ለማግኘት ✍
👇👇👇
https://t.me/maedot_ze_orthodox

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций


✞ የእኔ መሓሪ ✞

የእኔ መሓሪ ሁሉን መርሻዬ
ሁሉን መርሻዬ
እንደ ሕልም አልፏል ትናንትናዬ
በአንተ ጌታዬ (፪)


    አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
አዳፋው ልብሴ ከነፃ
ከእዳ ከፈታኝ በነፃ
የጽድቁ ባሪያው ሆኛለው
ሳገለግለው ኖራለው
የእንባ ዘለላን ያቀፈው
አይኔም እልልታ ተረፈው
ደልዳዩ መዳፍ ደርሶሎኝ
ተራራው ሜዳ ሆነልኝ
    አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
አይኖቼን ከጉድ ጋርዶልኝ
ክንዶቼን በእጁ ይዞልኝ
ከእግሬ በታች ነው ወጀቡ
አሁን ታይቶኛል ወደቡ
ሰላም ይነፍሳል ዙሪያዬ
እረፍት ሆኖልኝ ጌታዬ
የባረከኝን ባርኬ
ተለወጠልኝ ታሪኬ
    አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ብርሃንህ ገፏል ድቅድቁን
በልቤ ተክሏል ሰንደቁን
ተቆጣጥሮኛል መውደዱ
መንገዴ ሆኗል መንገዱ
ያበቃው ነገር ቀጥሏል
ጭንቄ በሞቱ ተሰቅሏል
የኢየሱስ ሆኜ ምን አጣሁ
ሁሉን በስሙ ተወጣሁ
    አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
   እንደ እኔ ማንን ታግሷል
   ይቅርታ ፍቅሩን አልብሷል
   ማይገባኝን አድርጎ
    ያሳለፈልኝ ሸሽጎ
መልካም ነው ለኔስ መልካም
ፀጋው ያገዘኝ ስደክም
ሞትኩኝ ስል ምሕረት ደርቦ
አቆመኝ በሕይወት አስዉቦ

             መዝሙር|
   ዘማሪ ገ/አምላክህ ደሳለኝ

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE


https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥


ማስታወቂያ
በውጪም ላሉ በስልክ በቴሌግራም ማውራት እንችላን!!!!
🌿🌿ለስንፈተ ወሲብ
🌿🌿ለንግድ ንግድ ጀምረው እንቢ ላላቸው ገና ለሚጀምሩ
🌿🌿ብር ለሚያጠፋ ገንዘብ ለመያዝ
🌿🌿ለውጪእድል እንቢ ላላቸው
🌿🌿ለፍርሀት ሰፊት መቆም መናገር ለሚፈሩ
🌿🌿ለትምህርት እያነበቡ አልያዝ ላላቸው ለማንኛውም ትምህርት
🌿🌿ፍርሀት ጭንቀት አይነጥላ ላለባቸው
ብቻ ያለቦትን ችግር ምንም ቢሆን እንመካከርበትና መፍትሄ እንፈልጋለን።
ይህ መልክት ላላዩ እንዲደርስ ሼር በማድረግ ይተባበሩ። በሀገር ውስጥም በውጪም ላሉ መፍትሄ አለን ይምጡ

🌿መርጌታ በቃሉ የባህል ህክምና መምጣት ለማችሉ እና በአረብ ሀገር ላላችሁ ባላችሁበት ይሰራላችዃል 0912609305
🌿ለመስተፋቅር
🌿ለገበያ
🌿ለወሲብ ስንፈት
🌿ለሀብት
🌿ለቁማር
🌿ነገረ ሚስጥራት(ሚስጥር የሚነግር)
🌿ነገረ ራዕይ(ራዕይ የሚያሳይ)
🌿ለዓቃቤ ርዕስ
🌿ለመክስት
🌿ቡዳ ለበላው
🌿ሰላቢ የማያስጠጋ
🌿ለመፍትሔ ሀብት
🌿ለመፍትሄ ስራይ
🌿ለሁሉ ሠናይ
🌿ለህማም
🌿ለአምፅኦ ብእሲት(ፍቅረኛ ላጣ ወይም ላጣች የሚሰራ)
🌿ለመድፍነ ፀር
🌿ሌባ የማያስነካ
🌿ለበረከት
🌿ለግርማ ሞገስ
🌿ለዓይነ ጥላ
🌿ለሁሉ መስተፋቅር
🌿ጸሎተ ዕለታት
🌿ለታሰረ ሰው እነዲፈታ የሚያደርግ
🌿ለእጅ ስራ (እንዲቀናህ)
🌿ለትዳር የሚሆን የኮከብ ቆጠራ
🌿ለድምፅ
🌿ጋኒን ለያዘው

             መርጌታ በቃሉ
ለጥያቄዎ በ ስልክ 0912609305 ይደውሉ 


✞ ወረት የሌለው ✞

ወረት የሌለው መውደድ
ወረት የሌለው ፍቅር
አንተ ጋር ብቻ ነው
ያለው እግዚአብሔር
(፪)


           አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ዘመን የማይዘው ጊዜ የማይገድበው
የአንተ ፍቅር ብቻ ቀን በቀን አዲስ ነው
ከዴማስ ጋር ስሄድ ትቼው የአንተን መንገድ
ከቶ መች ቀነሰ ለእኔ ያለህ መውደድ
           አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
በአመጽ ብጠፋም ከመንጋህ መካከል
ይመሻል ይነጋል እኔን ስትከተል
እንደወጣ ይቅር ብለህ መቼ ተውከኝ
ሴኬም ድረስ ወርደህ ልጅህን ፈለከኝ
           አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
በዝናዬም ዘመን ባለጸጋ እያለሁ
ቤቴ በወዳጆች ቀን በቀን ሙሉ ነው
እንደ ጤዛ ሲረግፍ ሐብትና ንብረቴ
ያለ አንተ ማን ነበር በፈርሰው ቤቴ
           አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
የታመንኩባቸው ወዳጆች ሲከዱኝ
ሕመሜ ስር ሆነው ደጋግመው ሲወጉኝ
ለአንተ ጊዜ ባጣም ለእኔ ጊዜ አለህ
ገፋህ ክፉ ቀኔን ከእኔ ጋራ አብረህ

             መዝሙር|
ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE


https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥


"በፈጣሪ ልጄን አድኑልኝ" አባት

ይህ ቆንጅዬ ህፃን አሚር የሱፍ  ይባላል! በተወለደ 4ኛ ወሩ ህመም ሲያሰቃየውና እንቅልፍ ሲከለክለው እናትና አባት ወደ ጥቁርአንበሳ ሆስፒታል ይዘውት ይሄዳሉ!
ህፃን አሚር አንድ ወር አልጋ ይዞ ክትትል ካደረገ በኋላ ዶክተሮች "የልብ ክፍተት  ችግር አለበት፣ አስቸኳይ ቀዶ ጥገና ያስፈልገዋል"ተባሉ!

ልጁን ለማሳከም የተጠየቁት 1500000 ብር ነው ከአቅም በላይ ስለሆነ ልጃቸውን ለማዳን እናንተን እየተማፀኑ ነው😭 እባካችሁ #እንድረስላቸው🙏 እናግዛቸው🙏
 "ለመልካም ስራ ረፍዶ አያውቅም"

አካውንት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000304310937-ዩሱፍ ሀምደለ (አባት)
#ስልክ 0705740135

☞አድራሻ ካራ ቆሬ ወታደር ሰፈር
☞ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል


✞ የተሰጠህ ክብር ✞

የተሰጠህ ክብር ግሩም ሐብተማርያም አቡነ
ተማፅነናል በአንተ በእውነት ሐብተማርያም አቡነ
የወንጌል መምህር ጻድቅ አባት ነህ
[፪]


በገድል ብትጸና            ሐብተማርያም
በጾም በጸሎት             ሐብተማርያም
ክብርን ተጎናፀፍክ        ሐብተማርያም
እንደ መላእክት             ሐብተማርያም
ስምህን ስንጠራህ        ሐብተማርያም
በፍቅርህ ተጠምደን      ሐብተማርያም
ጻድቁ አባታችን             ሐብተማርያም
መጥተህ እኛን ባርከን   ሐብተማርያም

         አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ጽድቅ እኮ ነው ምርጫው - ሐብተማርያም
የ ሐብተማርያም              ሐብተማርያም
የፈጸመው ገድል              ሐብተማርያም
ያሳየው ጽናት                   ሐብተማርያም
ለአምላኩ ያለውን             ሐብተማርያም
እውነተኛ ፍቅር                 ሐብተማርያም
ገለጽከው በሕይወት         ሐብተማርያም
በታላቅ እምነት                 ሐብተማርያም

         አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ኢትዮጵያ እልል በይ        ሐብተማርያም
እጅግ ደስ ይበልሽ          ሐብተማርያም
የእግዚአብሔር አገልጋይ - ሐብተማርያም
ጻድቅ አባት አለሽ           ሐብተማርያም
በምልጃው የሚረዳሽ      ሐብተማርያም
በጸሎት ከልሎሽ            ሐብተማርያም
በችግርሽ ጊዜ               ሐብተማርያም
ፈጥኖ የሚያድንሽ          ሐብተማርያም

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE


https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥


✞ በስባረ አፅሙ ✞

በስባረ አፅሙ በገድለ ድካሙ
በፀናበት በአስቦ ገዳሙ
ስድስት ክንፍ አገኘ
ተክለሃይማኖት ምድራዊ መልዐክ ተሰኘ (፪)

 
ትናገር ደብረ አስቦ የተጋደለባት
ተክልዬ በአንድ እግሩ ቆሞ የፀለየባት
በመላዕክት ከተማ ሕብረት የፈጠረ
ከካህናተ ሰማይ መንበሩን ያጠነ
 
         አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
 
ቅዳሴ ቀድሷል ሚካኤል ተራድቶት
ወንጌልን መስርቷል በፅላልሽ ዳሞት
ተክለሃይማኖት ጻድቁ አዲስ ሐዋርያ
ሞገሷ ነህ አንተ ለኢትዮጵያ
 
         አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
 
የመንፈስ ልጆችህ አእላፍ ሆነዋል
በፀሎትህ ታምነው ቤትህን ሞልተዋል
የላመ የጣመ መና በሌለበት
ዳቤው ንፍሮው ውኃው ሆኗቸዋል ውበት

    አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
 
እፁብ ነው ድንቅ ነው የተሰጠህ ፀጋ
ቋጠሮ ቢፈታ ከአንተ የተጠጋ
የጻድቅ ሰው ፀሎት ምልጃው ይፈውሳል
ተክልዬን ያመነ ኧረ ምን ይሆናል

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE


https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥


✞ ቅዱስ ጊዮርጊስ አማለደን ✞

ቅዱስ ጊዮርጊስ አማለደን አማለደን
ከመድኃኔዓለም አስታረቀን
ማረን ይቅር አለን ማረን ይቅር አለን
አማኑኤል ታረቀን


ሹመት ለመፈለግ - - ቅዱስ ጊዮርጊስ
ነገሥታት ዘንድ ሄዶ - - ቅዱስ ጊዮርጊስ
ጣዖት ሲያመልኩ አየ - - ቅዱስ ጊዮርጊስ
አምላኩ ተክዶ - - ቅዱስ ጊዮርጊስ
        አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ክርስቲያን ነኝ የሚል - - ቅዱስ ጊዮርጊስ
በዓለም ሁሉ ጠፍቶ - - ቅዱስ ጊዮርጊስ
እኔ አምናለሁ አለ - - ቅዱስ ጊዮርጊስ
የአምላኩን ስም ጠርቶ - - ቅዱስ ጊዮርጊስ
        አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
የዓለም ግሳንግሷ - - ቅዱስ ጊዮርጊስ
ጸባይዋ ሳይገዛህ - - ቅዱስ ጊዮርጊስ
ስለ ጌታ ፍቅር - - ቅዱስ ጊዮርጊስ
ከእናትህ ተለየህ - - ቅዱስ ጊዮርጊስ
        አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
የመቅጫው መሳሪያ - - ቅዱስ ጊዮርጊስ
በዓይነት ተደቅኖ - - ቅዱስ ጊዮርጊስ
እኔ አልፈራም አለ - - ቅዱስ ጊዮርጊስ
በአምላኩ ተማምኖ - - ቅዱስ ጊዮርጊስ
        አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ተፈጭቶ ተደቅቆ - - ቅዱስ ጊዮርጊስ
ደብረ ይድራስ ሳለ - - ቅዱስ ጊዮርጊስ
እጽዋቱ ሁሉ - - ቅዱስ ጊዮርጊስ
ጊዮርጊስ ጊዮርጊስ አለ - - ቅዱስ ጊዮርጊስ

           መልአከ ሰላም
  ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE

https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥


✞ ተናገራ ✞

ተናገራ እዝራ ተናገራ ዳዊት ዘመራ(፪)

ተናገራ ዳዊት በመሠንቆ ዳዊት ዘመራ
ተናገራ እያጫወታት ዳዊት ዘመራ
    አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ተናገራ ሳታውቀው አለፈ ዳዊት ዘመራ
ተናገራ ያ መልአከ ሞት ዳዊት ዘመራ
    አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ተናገራ ውኆች ቀለም ሆነው ዳዊት ዘመራ
ተናገራ እንጨቶች ብእር ዳዊት ዘመራ
    አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ተናገራ ቢጽፉት አያልቅም ዳዊት ዘመራ
ተናገራ የማርያምን ክብር ዳዊት ዘመራ


✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE

https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥


✞ ሞትሰ ✞

ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ይደሉ/፪/
ሞታ ለማርያም የሐፅብ ለኵሉ (፬) ኧኸ

ሞትማ ለሚሞት ሰው ይገባዋል (፪)
የማርያም ሞት ግን (፪) እጅግ
ያስደንቃል (፬) ኧኸ

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE


https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥


✞ ወልድኪ ይጼውአኪ ✞

ወልድኪ ይጼውአኪ (፪)
ውስተ ሕይወት ወመንግሥተ ክብር (፬)

ልጅሽ ይጠራሻል (፪)
ወደ ሕይወት እና ወደ ክብር መንግሥት(፬)


✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE


https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥


✞ ድንግል ወላድተ ቃል ✞

ድንግል /፪/ ወላድተ ቃል/፪/

አሟሟትሽ በጥር ነሐሴ መቃብር ድንግል
የአንቺስ ለብቻሽ ነው ትንሳኤሽ ሲነገር ድንግል
ስጋሽ በምድር ላይ የት አለ እንደ ፍጡር
አርጓል ወደ ስማይ ከክርስቶስ መንበር

    አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ስጋሽን ሳያሳርጉ መላእክት በስማይ ድንግል
ቶማስ በደመና ሲመጣ መንገድ ላይ ድንግል
መግነዝ ተቀበለ ለሐዋሪያት ሊያሳይ ድንግል
    አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ትንሳኤሽን ሽተው ግራ ሲገባቸው ድንግል
ሐዋርያት ጾመው ተገለጥሽላቸው ድንግል
ተቀብራ አልቀረች በምድር ከደጇ ድንግል
    አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ለማየት ሲጓጉ የድንግልን ትንሳኤ ድንግል
እርገቷን አወቁ በብዙ ሱባኤ ድንግል
እኛም እንጸልይ ደጃችን እንዝጋ ድንግል
ከወላድት አምላክ እንድናገኝ ዋጋ ድንግል

መዝሙር|
|ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE


https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥


✞ አስተርእዮ በሰማይ ኮነ ✞

ሐዋርያት ሁሉ አዘኑ ተከዙ
በስብሐት በማኅሌት ሥጋዋን ገነዙ

   አስተርእዮ በሰማያት ኮነ
   አስተርእዮ አስተርእዮ (፪)

በክብር በስብሐት መላእክት በራማ
እያመሰገኗት በጥዑመ ዜማ

    አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
የማትፈቅጂ ድንግል የኃጥአንን ሞት
በአማላጅነትሽ ለንስሐ አቆዪን ጥቂት

    አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
የምታምር ርግብ ሰሎሞን አለሽ
ሥጋሽን ለመልበስ ወልድ መረጠሽ

    አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ሞትንስ መሞትን ለሁሉም ይገባል
የድንግል መሞት ግን በጣም ያስደንቃል


✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE

https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥


✞ ፀበለ ማርያም ✞

ስሟ የድንግል የማርያም
ሰማዕት ናት ፀበለ ማርያም [፪]


የስሟ ስያሜ .........ፀበለ ማርያም
በወርቅ የተጻፈ.......ፀበለ ማርያም
በመድሃኒአለም...... ፀበለ ማርያም
ተቀምጦ ይኖራል.....ፀበለ ማርያም
በጽርሐ አርያም.......ፀበለ ማርያም

ፀበለ ማርያም ሰማዕቷ
ደረሰልኝ ምልጃና ጸሎቷ [፪]


በጸበለ ማርያም.......ፀበለ ማርያም
በስሟ ያመነ...........ፀበለ ማርያም
ብራናው ሲገለጥ.......ፀበለ ማርያም
ያልተጠራጠረ........ፀበለ ማርያም
ከደዌ ይድናል.......ፀበለ ማርያም
አምኖ የተቀበለ......ፀበለ ማርያም

የማርያም ወዳጅ የድንግል
በጇ አለ ቃለ ወንጌል

የማርያም ወዳጅ የድንግል
በጇ አለ በትረ መስቀል

የማርያም ወዳጅ የድንግል
በጇ አለ ወርቅ መስቀል


የወርቅ መሰላል ነሽ.......ፀበለ ማርያም
የወርቅ መስቀል............ፀበለ ማርያም
ሰይጣንን ድል መንሻ......ፀበለ ማርያም
በክርስቶስ ሐይል......ፀበለ ማርያም
ካጋንንት እስራት.......ፀበለ ማርያም
የማመልጥብሽ.......ፀበለ ማርያም
የእምነት ማሕተቤ.....ፀበለ ማርያም
ሰማዕቷ አንቺ ነሽ......ፀበለ ማርያም

የአማኑኤል ሙሽራ ሰማዕቷ
ደረሰልኝ ምልጃና ጸሎቷ [፪]


የክርስቶስ ወዳጅ.....ፀበለ ማርያም
የአምላክ ሙሽራ......ፀበለ ማርያም
ባሕረ እሳትን.........ፀበለ ማርያም
ልዉጣው ካንቺ ጋራ.....ፀበለ ማርያም
ቃልኪዳንሽ ግሩም.......ፀበለ ማርያም
ምልጃሽም ፈጣን ነው.....ፀበለ ማርያም
አንቺን ያመነ ሰው.........ፀበለ ማርያም
ስሙ ከልዑል ነው........ፀበለ ማርያም
አንቺን የካደ ሰው.........ፀበለ ማርያም
መድረሻው ሲኦል ነው......ፀበለ ማርያም

ስሟ የድንግል የማርያም
ሰማዕት ናት ፀበለ ማርያም [፪]


🌺✞ ጋሜል - ዘ ኦርቶዶክስ ✞🌺


✞ ኢትፍሪ ኢሚ ✞

ኢትፍሪ ኢሚ ነበልባለ እሳት [፪]
ታሪክ ሊቀይር ይችላል በእውነት [፪]

እናቴ አትፍሪ ነበልባሉን እሳት [፪]
ታሪኬን ሊቀይር ይችላል በእውነት [፪]


እየሉጣአ አትፍሪ ፈተናን በዓለም
እግዚአብሔርን አምኖ የሞተ ሰው የለም
መቀየር ይችላል እሳቱን በውኃ
አትፍሪ እናቴ በፈተና እንፅና
ቂርቆስ ሆይ ተመልከት የእሳቱን ወላፈን
እንዴት አልፈራውም ማን ይችላል ይህን
እንግባ ብትለኝ እሺ ብዬሃለው
የምታምነው አምላክ ማዳኑ ድንቅ ነው


          አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ድንገት ይለወጣል የጣቱ ለማታ
በማግኘት በማጣት በሐዘን በደስታ
ሰማሽ ወይ እናቴ የሰውን ፉከራ
በጌታችን ያልፋል ይህ ሁሉ መከራ
አይጠረጠርም ባለ ሙሉ ብርታት
ንጉሥ ይቻለዋል አሳዳጁን መርታት
የጣሉን ከእሳቱ እስከሚገርማቸው
ድነን ስናወድስ ያየናል አይናቸውን

          አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ይኸው ያዜማል አፋችን
ታሪክ ቀይሮ ጌታችን
መልአኩን ልኮ ላዳነን ጌታ
እነሆ እነሆ ቅኔ እልልታ

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE

https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥


​​✞ ዘወይን ዘወይን ✞

ዘወይን ዘወይን ቤተ ቃና ዘወይን(፪)
ቤተ ቃና ዘወይን(፪)


በቃናዋ መንደር  - - - ዘወይን
ሰርግ ተደግሶ - - - ዘወይን
ወይኑ ተሰናድቶ - - - ዘወይን
ዳሱ ተቀድሶ  - - - ዘወይን
ዶኪማስም ጠራ - - - ዘወይን
ደቀ መዛሙርቱን - - - ዘወይን
ኢየሱስንና - - - ዘወይን
ማርያም እናቱን  - - - ዘወይን
     አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ሲበሉ ሲጠጡ - - -  ዘወይን
እጅግ ደስ አላቸው  - - - ዘወይን
ያ መናኛ ወይን  - - -  ዘወይን
እየጣፈጣቸው - - - ዘወይን
እልልታውም ደምቋል - - - ዘወይን
ሙሽራውም ኮርቷል - - - ዘወይን
ሰርጉ ለእንግዶቹ - - - ዘወይን
የበቃ መስሎታል - - - ዘወይን
     አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ወይኑ በመካከል - - -  ዘወይን
አለቀ ከጋኑ - - -  ዘወይን
አፍረው ተደበቁ - - - ዘወይን
አሳላፊው ሁሉ - - - ዘወይን
ማንም ሰው ሳይነግራት - - - ዘወይን
ይህንን ተረድታ - - - ዘወይን
ድንግል ልታማልድ - - - ዘወይን
ሔደች ወደ ጌታ - - - ዘወይን
     አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ጋኖቹን ሙሏቸው  - - -  ዘወይን
ውሃውን ቀድታችሁ - - -  ዘወይን
ብሏችኋል ልጄ - - - ዘወይን
ታዘዙ ታምናችሁ - - -  ዘወይን
ብላ ስትናገር - - -  ዘወይን
አሳላፊዎቹ  - - -  ዘወይን
አምነው ጓዳ ገቡ - - -  ዘወይን
ተሞሉ ጋኖቹ  - - -  ዘወይን
     አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ማድጋው ሲከፈት - - - ዘወይን
መልካም ወይን ሆነ - - - ዘወይን
የክርስቶስ ክብር - - - ዘወይን
በቤቱ ገነነ - - - ዘወይን
የእመ አምላክ ጸሎት - - -  ዘወይን
ታሪኩን ቀየረ - - - ዘወይን
መናኛው በሐዲስ - - - ዘወይን
ይኸው ተቀየረ - - -  ዘወይን
     አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ዛሬም ለደከሙ - - -  ዘወይን
አልጫ ለሆኑ - - - ዘወይን
ለነፍሳቸው ጣፋጭ - - - ዘወይን
አልቆባቸው ወይኑ - - - ዘወይን
ድንግል ትቆማለች - - - ዘወይን
ስለ እነሱ ተግታ - - - ዘወይን
እንዲጣፍጡላት - - -  ዘወይን
ለምና ከጌታ - - - ዘወይን
     አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ልጇም ኤልሻዳይ ነው - - - ዘወይን
ሁሉን አዲስ አርጓል - - - ዘወይን
ጨለማውን ገልጧል - - - ዘወይን
መራሩን አጣፍጧል - - - ዘወይን
ሁሌ ድንቅ አድራጊ - - - ዘወይን
ዛሬም ተአምረኛ - - - ዘወይን
ጋኖቹን እንጠብ - - - ዘወይን
እንመለስ እኛ - - - ዘወይን

   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
    @yemezmur_gexem
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈

10k 0 166 1 44



​​✞ ጥምቀተ ክርስቶስ ✞

በሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ
ጥር ፲ ቀን፳፻፱

ክፍል አምስት (፭)

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሚዜዎችን 'ኵሎ ዘይቤለክሙ ግበሩ፤ ያዘዛችሁን ዂሉ አድርጉ፤' ማለቷ "አንቺ ሴት ከአንቺጋር ምን አለኝ? የሚለው የጌታችን መልስ እሺታን (ይኹንታን) የሚገልጽ ቃል መኾኑን ያስረዳል፡፡

ጌታችንም "ውኃ ቅዱና ጋኖችን ምሏቸው"ባላቸው ጊዜ በታዘዙት መሠረት ውኃውን ቀድተው ጋኖችን ሞሏቸው፡፡ ውኃውንም ክብር ይግባውና በአምላካዊ ችሎታው ወደ ወይን ጠጅ ለወጠው፤ ለአሳዳሪውም ሰጠው፡፡

አሳዳሪው የወይን ጠጅ የኾነውን ውኀ ቀምሶ አደነቀ፤ ከወዴት እንደ መጣ ግን አላወቀም፡፡ ድንቅ በኾነ አምላካዊ ሥራ እንደ ተለወጠም አልተረዳም፡፡ ያን ምሥጢር የሚያውቀው ባለ ሰርጉ፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምና ውኀውን የቀዱ ሰዎች ናቸውና፡፡

ታዳሚዎችም "ሰው ዂሉ የተሻለውን ወይን አስቀድሞ ያቀርባል፤በኋላም ተራውን የወይን ጠጅ ያቀርባል፡፡ አንተስ መናኛውን ከፊት አስቀድመህ ያማረውን ከኋላ ታመጣለህን?"በማለት አደነቁ፡፡

ቀድሞም የአምላክ ሥራ እንደዚህ ነው፤ ብርሃን ከመፍጠሩ አስቀድሞ ጨለማን ፈጥሯል፤ ከጨለማ ቀጥሎ "ብርሃን ይኹን!" በማለት ብርሃንን ፈጥሯል፡፡ መጀመሪያ ብርሃን ተፈጥሮ ኋላ ጨለማ ቢፈጠር ይከብድ ነበርና መጀመሪያ ፳፩ ፍጥረታት ፈጥሯል፡፡

በመጨረሻም በአርአያውና በአምሳሉ የሰው ልጅን ፈጥሯል፡፡ ናትናኤልንም፤- "ከእንግዲህ ወዲህ ከዚህ የሚበልጥ ታያለህ" ብሎታል፡፡ ይህንን ማለቱም የእግዚብሔር ሥራ እየቆየ ውብ፣ ያማረ መኾኑን ያመለክታል፤ ሰው ግን 'የወደዱትን ቢያጡ ያጡትን ይቀላውጡ' እንዲሉ ጥሩ ነው የሚለውን ነገር ያስቀድማል፤ ያ ሲያልቅበት ደግሞ የናቀውን መፈለግ ይጀምራል፡፡

ተራውን ከፊት፣ ታላቁን ከኋላ ማድረግ የእግዚአብሔር ልማዱ ነው፡፡ ለሰው ልጅ በመጀመሪያ የተሰጠው የሚያልፈው ዓለም ነው፤ በኋላም የማያልፈው መንግሥተ ሰማያት ይሰጠዋል፡፡

ሰው መጀመሪያ ይሞታል፤ በመጨረሻ ትንሣኤ አለው፡፡ ሰው መጀመሪያ ሲወለድ ርቃኑን ነው፤ በኋላ የጸጋ ልብስ ይለብሳል፤ ሀብታም ይኾናል፡፡

ሰው ወደዚህ ዓለም ሲመጣ ዓለምን የሚያገኛት፣ የሚተዋወቃት በልቅሶ ነው፤ በኋላ ግን ይደሰታል፡፡ ተመልሶ በኀሣር፣ በልቅሶ ወደ መቃብር ይወርዳል፡፡ በደስታ "መቃብር ክፈቱልኝ? መግነዝ ፍቱልኝ?" ሳይል ይነሣል፡፡ ይህን የአምላክ ሥራም አድንቆ መቀበል እንጂ መቃወም አይችልም፡፡

፪.እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም

"ወሀለወት ህየ እሙ ለእግዚእ ኢየሱስ ክርስቶስ፤ የጌታ እናት ከዚያ ነበረች፤" እንዲል፡፡ የተገኘችውም እንዲያው ዝም ብሎ አይደለም፡፡ በደግ ሰው ልማድ ተጠርታ እንጂ፡፡

ይህም እመቤታችን በማኅበራዊ ሕይወት የነበራትን ተሳትፎ እና በሰዎች ዘንድ የነበራትን ክብር ያመለክታል፡፡

በሌላ መልኩ በቤተ ዘመድ ልማድ ማንኛውም ዘመድ እንደ ተጠራው ዂሉ እርሷም በገሊላ በነበሩት ሰዎች ዘንድ ታላቅና ቤተ ዘመድ በመኾኗ በዚህ ሰርግ ተጠርታ ነበር፡፡ የተገኘችበት ሰው ሰውኛው ምክንያት ይህ ቢኾንም በዚያ ሰርግ ቤት ማንም ሊሠራው የማይችል የሥራ ድርሻ ነበራት፡፡

ይህ በሰዎች ዘንድ የማይታወቅ በእግዚአብሔርና በእርሷ መካከል ያለ አማላጅነት ነው፡፡ ይኸውም የጎደለውን መሙላት ለሚችል ውድ ልጇ የጎደለውን እንዲሞላ ማማለድ ነው፡፡

እመቤታችን ከሰው ልጆች የተለየች ክብርት፣ ቅድስት፣ ንጽሕት፣ ልዩ በመኾኗ የምታውቀው ምሥጢርም ከሰው የተለየ ነው፡፡ "ወእሙሰ ተዐቀብ ዘንተ ኩሎ ነገረ ወትወድዮ ውስተ ልባ፤ ማርያም ግን ይህንንዂሉ ትጠብቀው፣ በልቧም ታኖረው ነበር፤"ሉቃ.፪፥፲፱

የሚለው ቃልም ድንግል ማርያም አምላክን በመውለዷ ከሰው ልጆች የራቀ ምሥጢር እንደ ተገለጠላት ያስረዳል፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም "ጸጋን የተሞላሽ"በማለት የገለጠው ለእርሷ የተሰጠው ባለሟልነት ልዩ መኾኑን ለማስረገጥ ነው፡፡ ከዚህ የተነሣ በሰርጉ ቤት የምትሠራውን ሥራ በውል ታውቅ ነበር፡፡

፫. ቅዱሳን ሐዋርያት

መምህርን ጠርቶ ደቀ መዝሙርን መተው ተገቢ አይደለምና፤ ደቀ መዛሙርቱ ከመምህራቸው ከክርስቶስ ጋር አብረው በሰርግ ቤት ተገኝተው ተአምራቱን ተመልክተዋል፤ በተደረገው ተአምርም አምላክቱን አምነዋል፡፡

ሐዋርያት ከዋለበት የሚውሉ፤ ከአደረበት የሚያድሩ፤ ተአምራት የማይከፈልባቸው፤ ወንጌሉን ለማስተማር የተመረጡ ናቸውና፡፡ ምክንያቱም አየን ብለው እንጂ ሰማን ብለው ቢያስተምሩ
አይታመኑምና፡፡

የሐዋርያት በሰርጉ ቤት መገኘትም ካህናት በተገኙበት ዕለት ሥርዓተ ጋብቻን መፈጸም ተገቢ መኾኑን ያስገነዝባል፡፡

በሰርግ ቤት የካህናት መገኘት እና ቡራኬ መስጠት አስፈላጊ ነውና፡፡ በፍትሐ ነገሥት አንቀጽ ፳፬ የተገለጸውም ይህ ትምህርት ነው፤ "ወማዕሰረ ተዋሰቦሶ ኢይትፌጸም ወኢይከውን ዘእንበለ በሀልዎተ ካህናት ወጸሎት ዘላዕሌሆሙ፤ የጋብቻ አንድነት ካህናት ቢኖሩ እንጂ ያለእነርሱ አይጸናም፡፡ እነርሱ ጸሎት ሲያደርጉ እንጂ ያለ ጸሎት አይፈጸምም፤"እንዲል፡፡

በጥንተ ፍጥረት "ሰው ብቻውን ይኾን ዘንድ መልካም አይደለም ረዳት እንፍጠርለት፤"ዘፍ.፪፥፲፱

በማለት የተናገረ አምላክ ጋብቻ በካህናት ቡራኬና ጸሎት መከናወን እንደሚገባው ሲያስተምረን በቃና ዘገሊላው ሰርግ ቅዱሳን ሐዋርያትን ይዞ ተገኝቷል፡፡

በአጠቃላይ የቃና ዘገሊላ ሰርግ እና በሰርጉ ላይ የታዩ ተአምራት ምልጃዎች ዂሉ ሌላ ምሥጢርንም ያዘሉ ናቸው፡፡ እመቤታችን "የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም" በማለት መናገሯ ሕዝብህን (ምእመናንን) "ደምህን አፍሰህ፣ ሥጋህን ቈርሰህ አድናቸው" ማለቷ ሲኾን፣ ይህም "ወይን" በተባለው የልጇ የክርስቶስ ደም ቤዛነት ዓለም ይድን ዘንድ እመቤታችን ያላትን የልብ መሻት ያስገነዝባል፡፡

"ጊዜዬ ገና አልደረሰም" የሚለው የጌታ ምላሽም ደሙ በዕለተ ዓርብ በመስቀል ላይ የሚፈስበት ጊዜ ገና መኾኑን ያመላክታል፡፡ በሰርግ ቤት የተገኘው በሥጋው መከራ ከመቀበሉ አስቀድሞ ነውና፡፡

የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የእናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት፣ የቅዱሳን ሐዋርያት በረከት አይለየን፡፡
ከበዓለ ጥምቀቱ ረድኤት፣ በረከት ይክፈለን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር፡፡አሜን!!!

ለአባታችን ለሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ ቃለሕይወት ያሰማልን አሜን!!!

ተፈጸመ

   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
    @yemezmur_gexem
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈


​​✞ ጥምቀተ ክርስቶስ ✞

በሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ
ጥር ፲ ቀን፳፻፱

ክፍል አራት (፬)

"ጌትነቱን ገለጠ፤ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ፤"
ዮሐ. ፪፥፲፩

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የበዐላት አከባበር ቀመር ከበዓለ ልደት፣ ግዝረት እና ጥምቀት ቀጥሎ ቃና ዘገሊላ ይከበራል፡፡

ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ልጅ ለማዳን ወደዚህ ዓለም በመጣበት ወቅት ልዩ ልዩ ድንቅ ተአምራትን አድርጓል፡፡

ከእነዚህ መካከልም በቃና ዘገሊላ በሰርግ ቤት ተገኝቶ ያደረገው ተአምር ተጠቃሽ ነው፡፡

ይህንንም ቅዱስ ዮሐንስ በወንጌሉ እንዲህ ጽፎታል፤"በሦስተኛው ቀን በገሊላ ቃና ሰርግ ኾነ፡፡" ምን በተደረገ በሦስተኛው ቀን የሚል ጥያቄ በኹላችንም አእምሮ እንደሚመላለስ አያጠያይቅም፡፡

ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በማየ ዮርዳኖስ በእደ ዮሐንስ ጥር ፲፩ ቀን ተጠምቆ ሳይውል ሳያድር ዕለቱን ገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ ዐርባ መዓልትና ዐርባ ሌሊት ጾሞ፤ ዲያብሎስን ድል ነስቶ፤ መዋዕለ ጾሙን ፈጽሞ፤ ለእኛም ዲያብሎስን ድል የምንነሳበትን መንገድ አሳይቶ ከገዳመ ቆሮንቶስ መልስ ደቀ መዛሙርቱን መረጠ፡፡

ከጥር ፲፩ እስከ የካቲት ፳ ቀን ያለው ጊዜ ፵ ቀን ይኾናል፡፡ ጌታችን መዋዕለ ጾሙን የካቲት ፳ ቀን ፈጽሞ በወጣ በሦስተኛው ቀን በገሊላ አውራጃ ቃና በተባለች መንደር ሰርግ ኾነ፡፡

በዚህ ሰርግ ብዙ ሰዎች መታደማቸውን ወይን ጠጁ ማለቅ ያስረዳናል፡፡ የተጠሩት ሰዎች ብዙ ለመኾናቸው ባሻገር ብዙዎችን መመገብ የሚችል አምላክ በሰርግ ቤት መጠራቱ ልዩ ዕለቱን ያደርገዋል፡፡ በዚህ ሰርግ ከሰዎች በተጨማሪ ሦስት አካላት ተጠርተዋል፡፡

፩.ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ

"ወጸውዕዎ ለእግዚእ ኢየሱስ ክርስቶስ፤ ጌታ ኢየሱስንም ጠሩት"
ዮሐ.፪፥፪

ተብሎ እንደ ተጻፈ እናትን ጠርቶ ልጅን መተው ተገቢ አይደለምና እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ጠርተው ልጇን ኢየሱስ ክርስቶስንም ጠርተውታል፡፡

ይህም ፍጹም ሰው መኾኑን
ያስረዳል።ጌታችን እንደ ሰውነቱ ወደ ሰርግ ቤት ተጠራ፤ እንደ አምላክነቱ ተአምራቱን በማሳየት ጌትነቱን፣ አምላክነቱን ገለጠ፡፡

ከሚደሰቱት ጋር መደሰት፤ ከሚያዝኑት ጋር ማዘን ተገቢ መኾኑን መድኀኒታችን ክርስቶስ በተግባር አስተማረን፡፡

በቃና ዘገሊላ ከሰርግ ቤት እንደ ሔደው በአልዓዛር ቤት ለለቅሶ መገኘቱን ልብ ይሏል፡፡ ወደ ሰርግ ቤት የሔደው በደስታ ነበር፡፡ "ሖረ ኢየሱስ በትፍሥሕት ውስተ ከብካብ እንዘ ይገብር ተአምረ ወመንክረ በውስተ አሕዛብ፤ ኢየሱስ በአሕዛብ ፊት ተአምራትንና ድንቆችንእያደረገ በደስታ ወደ ሰርግ ሔደ፤"በማለት ቅዱስ ያሬድ እንደ ገለጠው፡፡

ጌታችን ወደ አልዓዛር ቤት ሲሔድ ግን በኀዘን ውስጥ ኾኖ ነበር፡፡"ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እርሷ (ማርታ) ስታለቅስ ባየ ጊዜ በልቡ አዘነ፤ በራሱም ታወከ (ራሱን ነቀነቀ – የኀዘን ነው) ዕንባውን አፈሰሰ፡፡ አይሁድም ‹ምን ያህል ይወደው እንደ ነበር እዩ› አሉ፤"
እንዳለ ወንጌላዊው ዮሐ.፲፩፥፴፫-፴፰

ጌታችን "አምላክ ነኝና ከሰርግ ቤት አልሔድም፤ ከልቅሶም ቤትም አልገኝም፤" አላለም፡፡ ከዚህም ጌታችን ከኀጢአት በቀር የሰውነትን ሥራ እንደ ሠራ፤ የሰውን የተፈጥሮ ሕግ እንዳከበረ እና እንደ ፈጸመ እንረዳለን፡፡

በመደሰት እና በማዘን ፍጹም ሰው መኾኑን፤ በሰርጉ ቤት ውኀውን የወይን ጠጅ በማድረግ፤ እንደዚሁም አልዓዛርን ከአራት ቀናት በኋላ ከሞት በማስነሣት ደግሞ ፍጹም አምላክ መኾኑን አስረዳን፡፡

ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ነውና በሰርግ ቤት የጎደለውን መላ፡፡ አምላክ ነውና የሞተውን አልዓዛርን "መግነዝ ፍቱልኝ? መቃብር ክፈቱልኝ? ሳይል" ከሞት እንዲነሣ አደረገ፡፡

"ወሶበ ኀልቀ ወይኖሙ ወትቤሎ እሙ ወይንኬ አልቦሙ፤ የወይን ጠጅ ባለቀባቸው ጊዜም እናቱ (እመቤታችን) 'የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም' አለችው።ዮሐ ፫፥፫

እርሱም "አንቺ ሴት ከአንቺ ጋር ምን አለኝ? ጊዜዬ ገና አልደረሰም፤" አላት፡፡

ይኸውም "ያልሽውን ልፈጽም ነው ሰው የኾንኩት፤ ያልሽኝን እንዳልፈጽም ከአንቺ ጋር ምን ጠብ አለኝ?"ማለት ነው፡፡ ‹ጊዜዬ ገናአልደረሰም› የሚለው ቃልም ጌታችን ሥራውን ያለ ጊዜው እንደማይፈጽመው ያሳያል፡፡

"ለእግዚአብሔር የሥራ ጊዜ አለው፤" እንዲል
መዝ.፻፲፰፥፻፳፮

በሌላ መልኩ "ጊዜዬ ገና አልደረሰም" የሚለው ቃል እግዚአብሔር አምላካችን ይህን አድርግ ብሎ በግድ ማንም ሊያዝዘው የማይቻለውና በራሱ ፈቃድ የወደደውን ዂሉ የሚያደርግ፤ ቢፈልግ የሚያዘገይ፣ ሲፈልግ ደግሞ በዐይን ጥቅሻ በፈጠነ መልኩ መፈጸም የሚችል፤ በራሱ ፈቃድ እንጂ በሰምች ፈቃድ የማይመራ አምላክ መኾኑን ያስተምረናል፡፡

"ፈቃድህ በሰማይ እንደ ኾነችእንዲሁ በምድር ትኹን" ብላችሁ ለምኑኝ ያለውም ለዚህ ነው፡፡

የወይን ጠጁም ሙሉ ለሙሉ አላላቀም ነበር፡፡ ምክንያቱም ጌታችን ያለውን ቢያበረክተው ተአምራቱን አናደንቅም የሚሉ ይኖራሉና ፈጽሞ ጭልጥ ብሎ እስከሚያልቅ ድረስ መጠበቅ እንደሚገባ ሲያስረዳ 'ጊዜዬ ገና አልደረሰም' አለ፡፡

ሰው ቢለምን፣ ቢማልድም እግዚአብሔር በእርሱ ፈቃድ ጊዜው ሲደርስ ነው የሚፈጽመው፡፡ ምልጃው አልተሰማም፤ ተቀባይነት አላገኝም ማለት ግን አይደለም፡፡ ተቀባይነት ያገኘ መኾኑ የሚታወቀው በመደረጉ ነውና፡፡

ተማላጅነት የአምላክ፤ አማላጅነት ደግሞ የፍጡራን መኾኑን ጌታችን በዚህ ሰርግ ቤት አስተምሯል፡፡ ጌታችን በሰርግ ቤት ባይገኝላቸው ኖሮ ሰዎቹ ምን ያህል ኀፍረት ይሰማቸው ይኾን? የእርሱ እንደዚሁም የእናቱ በሰርጉ ቤት መገኘት ለባለ ሰርጉና ለታዳሚዎች ሙላት ነበር፡፡

እርሱ ባይኖር የሰርጉ ቤት ከደስታ ይልቅ በኀዘን ሊሞላ ይችል እንደ ነበር ምንም ጥርጥር የለውም፡፡

አማላጅ ያስፈለገውም እርሱ የማያውቀው ምሥጢር ኖሮ፤ ሥራውን የሚሠራውም በስማ በለው ኾኖ አይደለም፡፡

ለሰው ልጆች ያለው ፍቅር ይታወቅ ዘንድ እና የሰው ልጆችን ከችግር የሚያወጣበት መንገዱ ብዙ መኾኑን ለማስረዳት ነው እንጂ፡፡

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሚዜዎችን 'ኵሎ ዘይቤለክሙ ግበሩ፤ ያዘዛችሁን ዂሉ አድርጉ፤' ማለቷ "አንቺ ሴት ከአንቺ ጋር ምን አለኝ?" የሚለው የጌታችን መልስ እሺታን (ይኹንታን) የሚገልጽ ቃል መኾኑን ያስረዳል፡፡

ጌታችንም "ውኃ ቅዱና ጋኖችን ምሏቸው"ባላቸው ጊዜ...

       ክፍል አምስት ይቀጥላል...
             🙏 ይቆየን 🙏
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
    @yemezmur_gexem
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈


​​ጥምቀተ ክርስቶስ

በሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ
ጥር ፲ ቀን፳፻፱

ክፍል ሦስት (፫)

ጌታችን ጥምቀቱን በውኀ ያደረገው በሌላ ያላደረገው ስለምንድን ነው ቢሉ ትንቢቱ፣ ምሳሌው ሊፈጸም፤

ትንቢት፦"ወእነዝኃክሙ በማይ ወትነጽሑ፤ ጥሩ ውኃንም እረጭባችኋለሁ፤ እናንተም ትጠራላችሁ፤"ተብሎ ተነግሯል ሕዝ.፳፮፥፳፭፡፡

ምሳሌ፦ ውኀ ለዅሉ አስፈላጊ ነው፡፡ ያለ ውኀ መኖር የሚችል የለም፡፡ ጥምቀትም ለዅሉም የሚገባ ሥርዓት ነው፡፡ ያለ ጥምቀት ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት አይቻልምና፡፡ ውኀ መልክ ያሳያል፤ መልክ ያለመልማል (ያጠራል)፡፡ ጥምቀትም መልክዐ ነፍስን ያሳያል፤ መልክዐ ነፍስን ያለመልማልና (ያጠራልና)፡፡

መንፈስ ቅዱስ በአምሳለ ርግብ ወርዶ በራሱ ላይ ሲቀመጥበት አየ፡፡ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል መውረዱም ምሥጢር አለው

ርግብ ኃዳጊተ በቀል ናት፤ መንፈስ ቅዱስም ኃዳጌ በቀል ነውና፡፡ ርግብ በኖኅ ጊዜ 'ሐጸ ማየ አይኅ ነትገ ማየ አይኅ፤ የጥፋት ውኀ ጎደለ' ስትል ቆጽለ ዕፀ ዘይት ይዛ ተገኝታለች፡፡ መንፈስ ቅዱስም ተስፋ መስቀልን ያበሥራልና፡፡

ጥምቀቱን በቀን ያላደረገው በሌሊት ያደረገው ስለ ምን ነው ቢሉ

በቀን አድርጎት ቢኾን መንፈስ ቅዱስ በቁሙ ርግብ ነው በተባለ ነበርና፤ አሁንስ ርግብ አለመኾኑ መንፈስ ቅዱስ መኾኑ በምን ይታወቃል ቢሉ ጌታ የተጠመቀው ከሌሊቱ በዐሥረኛው ሰዓት ነው፡፡ በዚያን ጊዜ ተሐዋስያን ወፎች (ርግቦች) ከየቦታቸው አይወጡምና መንፈስ ቅዱስ መኾኑ በዚህ ይታወቃል፡፡

መንፈስ ቅዱስም መውረዱ ከውኀው ከወጣ፣ ከዮሐንስ ከተለየ በኋላ ነው፡፡

ከውኀው ውስጥ ሳለ ወርዶ ቢኾን ለቀድሶተ ማያት ነው የወረደው ባሉት ነበርና፡፡ ከዮሐንስ ጋርም ሳለ ወርዶ ቢኾን ለክብረ ዮሐንስ ወረደ ባሉት ነበርና፡፡

ረቦ ወርዷል ያሉ እንደ ኾነ አብ ምሉዕ ነው፤ አንተም ምሉዕ ነህ፤ እኔም ምሉዕ ነኝ ሲል፡፡ አሰይፎ ወርዷል ያሉ እንደ ኾነ የብሉየ መዋዕል የአብ ሕይወት ነኝ፤ የአንተም ሕይወት ነኝ፤ እኔም ብሉየ መዋዕል ነኝ ሲል፡፡

ወርዶ ራሱን ቆንጠጥ አድርጎ ይዞታል ቢሉ አብ አኃዜ ዓለም ነው፤ አንተም አኃዜ ዓለም ነህ፤ እኔም አኃዜ ዓለም ነኝ ሲል፡፡ ምሥጢሩም እናንተም ብትጠመቁ መንፈስ ቅዱስ ይወርድላችኋል ለማለት፣ አብነት ለመኾን ነው፡፡

"ወናሁ መጽአ ቃል እምሰማይ ዘይብል ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ዘአፈቅር ዘቦቱ ሠመርኩ፤" ለተዋሕዶ የመረጥኩት በእርሱ ህልው ኾኜ ልገለጥበት የወደድኩት የባሕርይ ልጄ ይህ ነው፤ የሚል ቃል ከወደ ሰማይ ተሰማ፡፡

ይህም አብ የተናገረበት ቃል ያው የሚጠመቀው አካላዊ ቃል ነው እንጂ ሌላ ቃል አይደለም፡፡ የሥላሴ ልብ፣ ቃል፣ እስትንፋስ አንድ ነውና፡፡ አብ ልብ፤ ወልድ ቃል፤ መንፈስቅዱስ እስትንፋስ በመኾን አንድ አምላክ ነውና፡፡ "አብኒ ልቡናሆሙ ለወልድ ወለመንፈስ ቅዱስ ወልድኒ ቃሎሙ ለአብ ወለመንፈስቅዱስ ወመንፈስቅዱስኒ እስትንፋሶሙ ለአብ ወለወልድ፤ አብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ልቡናቸው ነው፡፡ ወልድም ለአብ ለመንፈስ ቅዱስ ቃላቸው ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስም ለአብ ለወልድ ሕይወታቸው ነው፤"በማለት ጎርጎርዮስ ነባቤ መለኮት እንደ ተናገረው፡፡

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተጠመቀውም በሠላሳ ዓመቱ ነው" ሉቃ. ፫፥፳፫፡፡

በሠላሳ ዓመቱ የተጠመቀበት ምሥጢርም
አዳም የሠላሳ ዓመት፤ ሔዋን የዐሥራ አምስት ዓመት ሰው ኾነው ተፈጥረው አዳም በዐርባ ቀን፣ ሔዋን በሰማንያ ቀን ከሥላሴ የተቀበሉትን ልጅነት በምክረ ከይሲ ዕፀ በለስን በልተው አስወስደው ነበረና በሠላሳ ዓመቱ ተጠምቆ መልሶላቸዋል፡፡

በሠላሳ ዓመት የመጠመቁ ምሥጢር ይህ ሲኾን እኛ ዛሬ ወንዶች በዐርባ ቀን፣ ሴቶች በሰማንያ ቀን በዕለተ ዓርብ ከቀኝ ጎኑ በፈሰሰው ማየ ገቦ ተጠምቀን ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ሁለተኛ የምንወለድበት ምክንያትም አዳም በዐርባ ቀኑ፣ ሔዋን በሰማንያ ቀኗ ከሥላሴ ያገኙትን ልጅነት መሠረት በማድረግ ነው።
ኩፋ. ፬፥፱

የምንጠመቀውም በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ነው፡፡ "ወእንዘ ታጠምቅዎሙ በሉ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፤ ስታጠምቋቸውም በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም አጥምቋቸው፤"እንዲል ማቴ. ፳፰፥፲፱

ዛሬም ታቦታቱን ወደ ጥምቀተ ባሕር በማውረድ በዓለ ጥምቀቱን ለሚያከብሩ ክርስቲያኖች በሙሉ ከታቦታቱ ሁለት ሺሕ ክንድ ርቀው መከተል እንዲገባቸው በመጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ተብሎ ተገልጿል፤ "ሕዝቡን የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን ታቦት ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ ከሰፈራችሁ ተነሥታችሁ ተከተሉት፡፡ በእናንተና በታቦቱ መካከል ያለውርቀት በስፍር ሁለት ሺሕ ክንድ ይኹን፡፡ በዚህ መንገድ በፊት አልሔዳችሁበትምና፤ የምትሔዱበትን መንገድ እንድታውቁ ወደ ታቦቱ አትቅረቡ፤።"
ኢያ.፫፥፩–፲፯

ይህ ኃይለ ቃል ዛሬ ታቦታቱ ወደ ጥምቀተ ባሕር ወርደው ለማደራቸው መነሻ ትምህርት ነው፡፡ የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀትም ጌታችን ከተጠመቀበት ከ፴ ዓመተ ምሕረት ጀምሮ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ በየዓመቱ ጥር ፲፩ ቀን ታሪካዊና ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ ሲከበር ይኖራል፡፡

"ጌትነቱን ገለጠ፤ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ፤"
ዮሐ. ፪፥፲፩

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የበዐላት አከባበር ቀመር ከበዓለ ልደት፣ ግዝረት እና ጥምቀት ቀጥሎ ቃና ዘገሊላ ይከበራል፡፡

ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ልጅ ለማዳን ወደዚህ ዓለም በመጣበት ወቅት ልዩ ልዩ ድንቅ ተአምራትን አድርጓል፡፡ ከእነዚህ መካከልም....

       ክፍል አራት ይቀጥላል...
             🙏 ይቆየን 🙏
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
    @yemezmur_gexem
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈


​​✞ ​​ጥምቀተ ክርስቶስ ✞

በሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ
ጥር ፲ ቀን፳፻፱

ክፍል ሁለት (፪)

ያውስ ቢኾን ጥምቀቱን በዮርዳኖስ ያደረገው ስለምን ነው? ቢሉ ትንቢቱን፣ ምሳሌውን ለመፈጸም ነው፤

ትንቢቱ፦"ባሕርኒ ርእየት ወጐየት ወዮርዳኖስኒ ገብአ ድኅሬሁ፤ ባሕር አይታ ሸሸች፤ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ፡፡ … ርእዩከ ማያት እግዚኦ ርእዩከ ማያት ወፈርኁ፤ አቤቱ ውኆች አንተን አይተው ሸሹ፤"ተብሎ ተነግሯል።
መዝ. ፸፮፥፲፮፤ ፻፲፫፥፫/፡፡

ምሳሌው፦ ዮርዳኖስ ከላይ ነቁ (ምንጩ) አንድ ነው፤ ዝቅ ብሎ በደሴት ይከፈላል፤ ከታች ወርዶ ይገናኛል፡፡ ዮርዳኖስ ከላይ (ነቁ) ምንጩ አንድ መኾኑ የሰውም መገኛው (ምንጩ) አንድ አዳም ለመኾኑ፤ ዮርዳኖስ ዝቅ ብሎ በደሴት መከፈሉ እስራኤል በግዝረት፣ አሕዛብ በቍልፈት ለመለያየታቸው፤ ዮርዳኖስ ከታች በወደብ መገናኘቱ በክርስቶስ ጥምቀት ሕዝብና አሕዛብ አንድ ወግን ለመኾናቸው ምሳሌ ነው፡፡

ዳግመኛም አብርሃም ለአምስቱ ነገሥተ ሰዶም ረድቶ አራቱን ነገሥተ ኮሎዶጎሞር ድል ነሥቶ በተመለሰ ጊዜ ደስ ቢለው "በመዋዕልየኑ ትፌኑ ቃለከ ወሚመ ታርዕየኒሁ ኪያሃ ዕለተ፤ በዘመኔ ቃልህን (እግዚአብሔር ወልድን) ትልከዋለህን? ወይስ ያቺን የማዳንህን ቀን በዓይኔ ታሳየኝ ይኾን፤" ብሎ በጠየቀው ጊዜ "ምሳሌውን ታያለህና ዮርዳኖስን ተሻግረህ ሒድ፤" ብሎታል፡፡ አብርሃምም ዮርዳኖስን ተሻግሮ ቢሔድ መልከ ጼዴቅ ኅብስተ አኮቴት፣ ጽዋዓ በረከት ይዞ ተቀብሎታል፡፡

ይኸውም አብርሃም የምእመን፤ ዮርዳኖስ የጥምቀት፤ መልከ ጼዴቅ የካህናት፤ ኅብስተ አኰቴት፣ ጽዋዓ በረከት የሥጋው የደሙ ምሳሌ ነው።
ዘፍ. ፲፬፥፲፫-፳፬/፡፡

ኢዮብና ንዕማን በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠምቀው ከደዌያቸው ድነዋል። ፪ኛነገ.፭፥፰-፲፱/፡፡

ኢዮብና ንዕማን የአዳምና የልጆቹ፤ ደዌ የመርገመ ሥጋ፣ የመርገመ ነፍስ፤ ዮርዳኖስ የጥምቀት ምሳሌ ነው፡፡ ኢዮብ፣ ንዕማን፣ ጌታ የተጠመቁበት ዮርዳኖስ ወደቡ አንድ ነው፡፡

እንደዚሁም እስራኤል ከግብጽ ከወጡ በኋላ በኢያሱ ጊዜ ወደ ምድረ ርስት ሲሔዱ ከዮርዳኖስ ወንዝ ደረሱ፡፡ ታቦቱን የተሸከሙና ልብሰ ተክህኖ የለበሱት ሌዋውያን ካህናት በፊት በፊት ሲጓዙ ታቦቱን የሚያጅቡ ሕዝበ እስራኤል ከታቦቱና ከሌዋውያን ካህናት ሁለት ሺሕ ክንድ ርቀው ዮርዳኖስ ከላይና ከታች ተከፍሎላቸው በየብስ ተሻግረው ኢየሩሳሌም ገብተዋል፡፡ ምእመናንም በማየ ገቦ ተጠምቀው ገነት መንግሥተ ሰማያት ለመግባታቸው ምሳሌ ነው፡፡
ኤልያስም ዮርዳኖስን ተሻግሮ ብሔረ ሕያዋን ገብቷል፡፡

የኤልያስ ደቀ መዝሙር ኤልሳዕ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር በዮርዳኖስ ዳር እንጨትና ሲቈርጡ መጥረቢያው ከውኀው ውስጥ ወደቀ፡፡ ኤልሳዕ የእንጨት ቅርፊት በትእምርተ መስቀል አዘጋጅቶ ምሳሩ ከወደቀበት ላይ ቢጥልበት የማይዘግጠው ቅርፊት ዘግጦ የዘገጠውን ብረት አንሳፎ አውጥቶታል፡፡ እንደዚሁም ዅሉ በባሕርዩ ሕማም ሞት የሌለበት አምላክ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ፣ ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ፣ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ፣ በዮርዳኖስ ተጠምቆ፣ በቀራንዮ በዕፀ መስቀል ተሰቀሎ፣ ከጎኑ ጥሩ ውኀና ትኩስ ደም አፍስሶ በሲኦል የወደቀው አዳምን ለማዳኑ ምሳሌ ነው።
፪ኛነገ. ፮፥፩–፯፡፡

ይህንን ዅሉ ምሳሌ ለመፈጸም ጌታችን በዮርዳኖስ ተጠምቋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ ጌታችን በዮርዳኖስ የተጠመቀበት ምሥጢር ምንድን ነው? ቢሉ ዲያብሎስ በአዳምና በሔዋን የጨለማ መጋረጃ ጋርዶ አገዛዝ ስቃይ አጸናባቸው፡፡ ከዚያም "አዳም ገብሩ ለዲያብሎስ ሔዋን ዓመቱ ለዲያብሎስ፤ አዳም የዲያብሎስ ተገዥ፤ ሔዋንም የዲያብሎስ ተገዥ አገልጋዮች ነን" ብላችሁ ስመ ግብርናታችሁን (የተገዥነታችሁን ስም) ጽፋችሁ ብትሰጡኝ መከራውን አቀልላችሁ ነበር" አላቸው፡፡

እነሱም መከራው የሚቀልላቸው መስሏቸው "አዳም ገብሩ ለዲያብሎስ ሔዋን ዓመቱ ለዲያብሎስ" ብሎ በማይጠፋ በሁለት ዕብነ ሩካም (ዕብነ በረድ) ጽፎ አንዱን በዮርዳኖስ፤ አንዱን በሲኦል ጥሎት ይኖር ነበር፡፡

በዮርዳኖስ የጣለውን ጌታችን ሲጠመቅ እንደ አምላክነቱ አቅልጦ እንደ ሰውነቱ ተረግጦ አጥፍቶልናል፡፡ በሲኦል የጣለውንም በዕለተ ዓርብ በአካለ ነፍስ ወርዶ ነፍሳትን ከዲያብሎስ ባርነት ነጻ ሲያወጣ አጥፍቶልናል፡፡ ጌታችን በዮርዳኖስ የተጠመቀበት አንደኛው ምሥጢርም ይህ ነው፡፡

ጌታችን ጥምቀቱን በውኀ ያደረገው በሌላ ያላደረገው ስለምንድን ነው ቢሉ...

ክፍል ሦስት ይቀጥላል...
🙏 ይቆየን 🙏
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
    @yemezmur_gexem
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈

Показано 20 последних публикаций.