ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


The best fiction is far more true than any journalism
📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ
👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56

https://t.me/AiqemAdsMasterBot
👉 https://www.facebook.com/mik0Man

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


በሐረር ከተማ በተማሪዋ ላይ ድብደባ የፈጸመችዉ መምህር በቁጥጥር ስር ዋለች

በሐረር ከተማ በተማሪዋ ላይ ድብደባ የፈጸመች መምህር በቁጥጥር ስር መዋሏን ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ከሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ሰምቷል።

በሐረር ከተማ ሞዴል ቁጥር አንድ ትምህርት ቤት ዉስጥ ተማሪ የሆነችዉ እሊሊ ናስር  በአካሏ ላይ ዩደረሰባትን ጉዳት የተመለከቱ ወላጆቿ ለፖሊስ ጥቆማ ማድረሳቸዉን በሐረሪ ፖሊስ ኮሚሽን የሴቶችና ህፃናት ምርመራ አስተባባሪ ኢንስፔክተር ህይወት ጌታነህ ነግረዉናል። ይህንን ተከትሎ ፖሊስ ተከሳሽን በቁጥጥር ስር አዉሎ የመምህሯን ቃል ተቀብሏል።

መምህሯ ፤ ተማሪ እሊሊ ናስር በተደጋጋሚ አሳይታለች ባሉት የባህሪ ችግር ምክኒያት ለመቅጣት ሲሉ ድርጊቱን መፈጸማቸውን ለፖሊስ በሰጡት ቃል መናገራቸዉን ኢንስፔክተር ህይወት ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። 

መምህሯ ክስተቱ ስህተት መሆኑን አምነዉ ፖሊስም በዋስ እንደለቀቃቸዉ አክለዋል።

በበረከት ሞገስ
#ዳጉ_ጆርናል


በእነ ክስርስቲያን ታደለ ፣ ዘመነ ካሴ ፣ እስክንድር ነጋ እና ሌሎች 52 ግለሰቦች ላይ የሽብርተኝነት ወንጀል ክስ ተመሰረተ

ዓቃቤ ሕግ ያለመከሰስ መብታቸው በተነሳባቸው የሕዝብ ተመራጮች ክርስቲያን ታደለ፣ ዮሐንስ ቧያለው እና ካሳ ተሻገር ላይ የሽብር ወንጀል ክስ መመስረቱን ዳጉ ጆርናል ሰምቷል። በክስ መዝገቡ ከተካተቱት 52 ተከሳሾች መካከል፣ እስክንድር ነጋ፣ ጫኔ ከበደና ዘመነ ካሴ ይገኙበታል።

ዓቃቤ ሕግ በክሱ፣ ተከሳሾቹ የፖለቲካ ርዕዮታቸውን በኃይል ለማስፈጸም በማሰብ፣ በኅቡዕ የተቋቋመውን የአማራ ፋኖ አንድነት ምክር ቤትን ዓላማዎች ለማስፈጸምና የአማራ ሕዝብ ርሥቶች ናቸው የሚሏቸውን አካባቢዎች በወታደራዊ ኃይል ለማስመለስ የተደራጁ ነበሩ ብሏል።

ዓቃቤ ሕግ፣ ተከሳሾቹ ከ1 ሺህ 100 በላይ ለሚኾኑ የጸጥታ አባላትና ሲቪሎች ሞትና 5 ሺህ 689 በላይ ታራሚዎችን በማስመለጥ ወንጀልም ተጠያቂ አድርጓቸዋል።

#ዳጉ_ጆርናል


የማሊያው ቁጥር በክብር ተቀመጠ!

በድንገት ህይወቱ ያለፈው ወጣቱ አማካይ የእግር ኳስ ተጨዋች አለልኝ አዘነ የሚለብሰው የማሊያ ቁጥር በክብር እንዲቀመጥ መወሰኑን ክለቡ ይፋ አድርጓል።

የጣና ሞገዶቹ ተጫዋቾች በኮከብ ተጫዋቻቸው ህልፈተ ህይወት የተሰማቸዉን ሀዘን በትዉልድ ስፍራው በመገኘት እንደተሰናበቱ ለማወቅ ተችሏል።

አለልኝ አዘነ በባህር ዳር ከነማ ስፖርት ክለብ ይለብሰዉ የነበረው የማልያ ቁጥር 23 ከዚህ በኋላ ማንም የክለቡ ተጫዋች የማይለብው ሆኖ በክብር እንዲቀመጥ የባህርዳር ከነማ ስፖርት ክለብ ወስኗል።

#ዳጉ_ጆርናል


የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በድጋሚ የሚያገረሽበት ዕድል ዝግ ነው ሲሉ አቶ ጌታቸው ረዳ ተናገሩ

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ ፣ የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በድጋሚ የሚያገረሽበት ዕድል ዝግ ነው በማለት ትናንት ከቻይናው ሲጂቲኤን ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ተናግረዋል።

ያለፈው ጦርነት የትግራይ ሕዝብ ፍላጎት አልነበረም ያሉት ጌታቸው ፣ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደርና የትግራይ ሕዝብ ድጋሚ ጦርነት እንዳያገረሽ የተቻላቸውን ጥረት ኹሉ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።

ጌታቸው ይህን ያሉት ፣ በአላማጣ አቅራቢያ በትግራይ ኃይሎች እና ባካባቢው ሚሊሻዎች መካከል የተኩስ ልውውጥ በተደረገ ማግስት ነው መባሉን ዳጉ ጆርናል ከዋዜማ ዘገባ ተመልክቷል።

አቶ ጌታቸዉ ይህንን ይበሉ እንጂ አብን፣ ሕወሃት ለአዲስ ዙር ጦርነት ቅስቀሳ እያደረገ ነው ሲል ትናንት ምሽት ባወጣው መግለጫ ከሷል። ፓርቲው፣ በግጭት ማቆም ስምምነቱ መሠረት የሕወሃት ተዋጊዎች ሙሉ በሙሉ ትጥቅ ሳይፈቱና መከላከያ ሠራዊት በትግራይ ክልል ጸጥታ ለማስከበር ሳይሠማራ ሕወሃት ለሌላ ዙር ጦርነት ፕሮፓጋንዳ በመለፈፍ ተጠምዷል ብሏል።

የፌደራሉና የአማራ ክልል መንግሥታት የሕወሃትን የጠባጫሪነት ቅስቀሳ በትኩረት እንዲከታተሉና በአማራ ክልል የሚካሄደው ግጭት "በንግግር" እና "ድርድር" እንዲፈታም አብን ጠይቋል። የአማራ ሕዝብ ሕወሃት ሊያደርስበት የሚችለውን ጥቃት ለመከላከል በአንድነት እንዲቆም የጠየቀው ፓርቲው፣ የትግራይ ሕዝብም ራሱን ከሕወሃት ቀንበር እንዲያላቅቅ ጥሪ አድርጓል።

#ዳጉ_ጆርናል


‹‹ አብን ትናንት ምሽት ያወጣዉ መግለጫ የግለሰቦች እንጂ የፓርቲዉ አቋም አይደለም ›› - ከፍተኛ አመራር እና የምክር ቤት አባል

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ረቡዕ ምሽት ያወጣው መግለጫ እንደማይወክላቸዉ  የምክርቤት  አባላቱና ስማቸዉ እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ አንድ ከፍተኛ የቀድሞ አመራር ለአሻም ነግረዋታል፡፡

የቀድሞው ከፍተኛ አመራር ይህን ያሉበትን ሲያሥረዱ ‹‹ ከ9 ስራ አስፈጻሚ አባላት 6ቱ በሌሉበትና የምክርቤት አባላት የሆኑ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላቱን ጭምር ሰብስቦ ባላወያየበት በጣት በሚቆጠሩ ግለሰቦች ፍላጎትና ሀሳብ ተጠናቅሮ በፓርቲዉ ስም የተሰጠ መግለጫ  ነዉ ›› ሲሉ ነቅፈውታል፡፡

እኚሁ አመራር አስከትለዉም ‹‹ ፓርቲዉ ለእውነት የቆመ ቢሆን  የስራ አስፈጻሚ፣ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላቱን ጠርቶ በማወያየት ማህበራዊ መሠረቴ ነው፤ እቆምልታለሁ ለሚለዉ ህዝብ፣ ለታሰሩና ለጠፉ አባላቶቹ መግለጫ ያወጣ ነበር ሲሉ ፓርቲያቸዉን ›› ተችተዋል፡፡

ይሁን እንጂ በእነዚህ ግለሰቦች በፓርቲዉ ስም የወጣዉ ዳግም ግጭት ቀስቃሽ  መግለጫ ጨምሮ  በትግራይና አማራ ክልልና የፌደራሉ መንግስት  በኩል ጉዳዩን  በእርጋታ በመመልከት  ህዝቡን  ከሰብዓዊና ቁሳዊ ዉድመቶች መታደግ ተገቢ ነዉ ሲሉ  የግል አቋማቸዉን አንጸባርቀዋል፡፡

በተመሳሳይ  ፓርቲዉን ወክለዉ የ2013 ምርጫ በተወዳደሩበት ስፍራ አሸንፈው የፌደራል የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አባል የሆኑት አበባዉ ደሳለዉ በበኩላቸው መግለጫዉ የስራ አስፈጻሚ አባላት ከግማሽ በላይ ያልተሟሉበትና ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ተሰብስበዉ ያልተወያዩበት በመሆኑ መግለጫዉ የፓርቲዉ ነዉ ለማለት እንቸገራለን ሲሉ ለአሻም ነግረዋታል፡፡

አሻም በጉዳዩ ላይ የፓርቲዉን ሊቀመበር በለጠ ሞላን(ዶ/ር) ጨምሮ ቀሪ የስራ አስፈጻሚ አባላቱን ለማነጋገር ብትሞክርም ፍቃደኛ ባለመሆናቸው በዘገባው ሊካተቱ አልቻሉም፡፡

Via አሻም
#ዳጉ_ጆርናል




በመላው የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጡ ተገለፀ

ዛሬ ከቀኑ 9 ሠዓት 46 ጀምሮ ከባህርዳርና አካባቢው በስተቀር በመላው ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉ መቋረጡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል።

ሲስተም ላይ በገጠመ ችግር ኃይል የተቋረጠ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን÷ ለጊዜው የችግሩን ምክንያት ለማወቅ ጥረት እየተደረገ ነው ተብሏል።

የተቋረጠውን ኤሌክትሪክ መልሶ የማገናኘት ሥራ የተጀመረ  መሆኑም ተመላክቷል፡፡

እስከዛ ድረስ ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠብቁ  ተቋሙ ጠይቋል፡፡

#ዳጉ_ጆርናል


በአምቦ ወረዳ የ90 ዓመት አዛውንት አስገድዶ የደፈረው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ

በምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ወረዳ ኢላሙ ጎሮሙጢ የተባለ አካባቢ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈጸመው ግለሰብ በእስራት መቀጣጡት የምዕራብ  ሸዋ ዞን  ከፍተኛ ፍርድ ቤት አስታውቋል ፡፡ 

የምዕራብ ሸዋ ዞን የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት  በተለይም ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን የላከእ መረጃ እንደሚያመላክተው ተከሳሽ ለቴራ ቀና የተባለው ግለሰብ  መጋቢት 7 ቀን 2016 ዓ.ም ከሌሊቱ 7 ሰዓት ላይ የ90 ዓመት ኣዛውንት  በመኖሪያ ቤታቸው  ተኝተው  ባሉበት  ቤታቸውን ሰብሮ በመግባት አስገድዶ የመድፈር ወንጀል እንደፈጸመ በማስረጃ ተረጋግጧል፡፡

ተከሳሽ  በእድሜ  የደከሙ ራሳቸውን መከላከል  የማይችሉ  አዛውንትን  በጉልበት  አስገድዶ  መድፈሩ ፖሊስ በህክምና ማስረጃ ያረጋገጠ እና የምርመራ መዝገቡን አጠናክሮ ለ ዓቃቢህግ መላኩን ብስራት ተመልክቷል ፡፡

በዚኅም  ዓቃቢ ህግ  ከፖሊስ የተላከውን የምርመራ መዝገብ ተመልከቶ  በወንጀለኛ  መቅጫ ህግ መሰረት ክስ መስርቷል፡፡  ክሱን ሲመለከት የነበረው የምዕራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት  መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም  በዋለው ችሎት ተከሳሽ ለቴራ  ቀና በስምንት  ዓመት እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ  የተላለፈበት መሆኑን  የምዕራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት  ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት  ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን የላከው መረጃ  ያመላክታል ፡፡

በኤደን ሽመልስ
#ዳጉ_ጆርናል


ህጋዊ የስፖርት ውርርድ ድርጅቶች ስራቸው በመቋረጡ የተነሳ ለሰራተኞቻቸው ደሞዝ መክፈል ሊያቆሙ መሆኑን አስታወቁ

የቫሞስ እና የሀበሻ የስፖርት ውርርድ ድርጅቶች እንዳስታወቁት ከታህሳስ ወር ጀምሮ በአዲስ አበባ ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ግብረ ሐይል በማቋቋም እንዲዘጋ መደረጉን ተናግረዋል፡፡የቫሞስ ኢንተርቴይመንት ስራ አስኪያጅ አቶ የኔብልህ ባንታየው እና የሀበሻ ስፖርት ውርርድ ስራ አስኪያጅ አቶ መርሻ ቡዛየሁ ለብስራት ሬድዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት ከ5 ዓመት በፊት በብሄራዊ ሎተሪ ፍቃድ የተሰጠው ዘርፍ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ሁለቱ ተቋማት በሀገር ውስጥ 156 እና 166 ቅርንጫፎች እንዳሏቸው እና ከ1ሺ በላይ ለሚሆኑ ሰዎችም የስራ እድል የፈጠረ ዘርፍ መሆኑን ተናግረዋል ፡፡የሀበሻ ስፖርት ውርርድ ስራ አስኪያጅ አቶ መርሻ ቡዛየው ከታህሳስ ወር ጀምሮ ድርጅቶቹ መዘጋታቸውን እና ያለምንም ስራ ለሰራተኞቻቸው እንዲሁም ለቤት ኪራይ እየከፈሉ እንደቆዩም ገልፀዋል፡፡

የስፖርት ውርርድ ተቋማቱ በብሄራዊ ሎተሪ መመሪያ መሰረት ከ21 ዓመት በታች እና ተማሪዎች እንዳይገቡ የሚለውን መመሪያ መፈፀማቸውን እና ለዚህም ብለው ከ340 በላይ የጥበቃ ሰራተኞች ቀጥረው እንዳይገቡ ይከለክሉ እንደነበርም ተናግረዋል፡፡

የቫሞስ ኢንተርቴይመንት ስራ አስኪያጅ አቶ የኔብልህ ባንታየሁ አክለውም በስፖርት ውድድር ዘርፍ ውስጥ 8 መቶ ድርጅቶች ህጋዊ መሆናቸው ተነግሮናል፤ ሌሎቹ 3ሺ የሚሆኑት ግን በህገወጥ ስራ የተሰማሩ መሆናቸው ከተለየ የህጋዊነት አግባብ ያለን ድርጅቶች ወደ ስራችን እንድንመለስ መልስ ይሰጠን ሲሉ ጠይቀዋል፡

መልስ በመጠበቅ አራት ወራት እንደቆዩ ለሰራተኞቻቸው ሲከፍሉት የነበረውን ወርሀዊ ደሞዝ ከዚህ በላይ መክፈል የማይችሉበት ከባድ ሁኔታ ውስጥ መሆናቸውን አቶ የኔብልህ ባንታየሁ እና አቶ መርሻ ብዙአየሁ ጨምረው ለብስራት ሬድዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።በቅሬታ አቅራቢዎቹ ዘንድ ህጋዊ የስፖርት ቤቶች ይከፈትልን የሚሉ አቤታታዎች ቢኖሩም ዘርፉ መዝጋቱ የሚደግፉና ቁጥጥሩ የላላ በመሆኑ ታዳጊዎች ላልተገባ ሱሱ ተዳርገዋል ሲሉ የሚደመጡም አሉ።

በምህረት ታደሰ
#ዳጉ_ጆርናል


ከእህቱ ሞት ጋር በተያያዘ በመንፈስ ተወግታ ነው በሚል ወሬ ተነሳስቶ የግድያ ወንጀል የፈፀመዉ ተከሳሽ በእስራት ተቀጣ

በኢሊባቡር ዞን በያዮ ወረዳ አጨቦ ቀበሌ ልዩ ቦታው ብርቂቱ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ከእህቱ ሞት ጋር በተያያዘ በመንፈስ ተወግታ ነው በሚል ወሬ ተነሳስቶ አንድ ግለሰብን የገደለ ተከሳሽ በእስራት ተቀጥቷል ።

የ29 ዓመት እድሜ ያለው ምትኩ በቀለ የተባለ ግለሰብ ኑሮው ከቤተሰቦቹ ጋር አድርጎ ነበር ። ታላቅ እህቱ በተደጋጋሚ በመታመሟ የተነሳ የአዕምሮ መታወክ ይገጥማታል ። ሆኖም ከገጠማት የአዕምሮ መታወክ በህክምና ስትረዳ ከቆየች በኋላ በመስከረም ወር 2016 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ትለያለች ።

ሞቷ በቤተሰቦቿ ላይ ከፍተኛ ሀዘን ያስከተለ ከመኖኑ ባሻገር ከአማሟቷ ጋር በተያያዘ የሚወራው ወሬ መላ ቤተሰቡን ያስከፋ ሲሆን በተለይም ደግሞ ምትኩን አስደንግጧል ። ወሬውም ሟች ህይወቷ ያለፈው በአካባቢው በምትገኝ ጫልቱ ተረፈ በተባለች ግለሰብ መንፈስ ተወግታ ነው ይባላል ።

ይህ ወሬ በመጨረሻም የምትኩን ልብ ለበቀል ያነሳሳል ። ጫልቱ በበኩሏ የሚወራው ችላ በማለት የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴዋን ትቀጥላለች ። በዚህም ጥቅምት 27 ቀን 2016 ዓ.ም  ዓመታዊውን የመድኃኒዓለም ክብረ በዓል አክብራ ስትመለስ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ምትኩ በቀለ በመንገድ ጠብቆ በገጀራ ጭንቅላቷ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የኢሉባቡር ዞን ፖሊስ ኮሚኒኬሽን ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ገልጿል ።

በወቅቱ ተጎጅዋን በመረባረብ ወደ መቱ ካርል ሪፈራል ሆስፒታል ተወስዳ እርዳታ ቢደረግላትም ህይወቷ መትረፍ ሳይችል ይቀራል ። ፖሊስ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር አውሎ የምርመራ መዝገቡን አጣርቶ ለዓቃቤ ህግ ይልካል ።

ዓቃቤ ህግ በደረሰው ማስረጃ ተመስርቶ በኢሊባቡር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ክስ ይመሰርታል ። ፍርድ  ቤቱ ዓቃቤ ህግ የመሠረተውን ክስ ሲመለከት ቆይቶ ተከሳሽ ምትኩ በቀለን ጥፋተኛ በማለት በ11 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል ።

በአበረ ስሜነህ
#ዳጉ_ጆርናል




የቻይናው ግዙፍ የስማርትፎን ኩባንያ ዢኦሚ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ለገበያ ማቅረብ ሊጀምር ነው

የቻይናው የስማርት ስልክ አምራች ዢኦሚ የመጀመሪያውን የኤሌትሪክ ተሽከርካሪ (ኢቪ) ለገበያ ለማቅረብ የተዘጋጀ ሲሆን ሀሙስ እለት ትእዛዝ መቀበል ጀምሯል። ዋና ስራ አስፈፃሚው ሌይ ጁን በዚህ ሳምንት እንደተናገሩት ስፒድ አልትራ 7 (SU7) ከ500,000 ዩዋን ወይም በ69 ሺ186 የአሜሪካን ዶላር ዋጋ እንደሚሸጥ ተናግረዋል። እርምጃው የቴክኖሎጂ ግዙፉ እንደ ቴስላ እና ቢዋይዲ ካሉ ተቀናቃኞቹ ጋር ያለውን ፉክክር ያጠናክራል።

የዢኦሚ ወደ ኤሌክትሪክ መኪና ገበያ መግባቱ በአለም አቀፍ ደረጃ የሽያጭ እድገት በመቀነሱ የዋጋ ጦርነትን አስነስቷል። ኩባንያው የ SU7 የጋራ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ከስልኮች፣ ላፕቶፖች እና ሌሎች ምርቶቹ ተጠቃሚ ከሆነ ነባር ደንበኞችን ይስባልኛል ሲል ተስፋ አድርጓል።

ዢኦሚ በዓለም አቀፍ ደረጃ በሶስተኛ ስፍራ ላይ የተቀመጠ የስማርት ስልኮች አቅራቢ ሲሆን 12 በመቶው የገበያ ድርሻ እንዳለው ካውንተር ፖይንት የተባለው የምርምር ድርጅት ገልጿል። ዢኦሚ ካለፈው አመት ጀምሮ ፍተሻ ሲያደርግበት የነበረው SU7 ከፖርሽ ታይካን እና ፓናሜራ የስፖርት መኪና ሞዴሎች ጋር ንፅፅር ተደርጎበታል። በዓመት እስከ 200 ሺ የሚደርሱ ተሽከርካሪዎችን ማምረት በሚችል በቤጂንግ በሚገኝ ፋብሪካ በመንግስት ባለቤትነት በተያዘው የመኪና አምራች ዩኒት ይሠራል።

እስከዚህ ድረስ መድረስ በራሱ ትልቅ ስኬት ቢሆንም የመጨረሻው ስኬት ዢኦሚ የሸማቾች ገበያ ላይ ተፈላጊነቱን ማሳየት ነው ሲሉ ኩባንያው አስታውቋል። የኤሌክትሪክ መኪና ለመሥራት የሚፈልጉ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የሚያጋጥሟቸውን ፈተናዎች ለማመልከት የአይፎን አምራች አፕል ባለፈው ወር ተሽከርካሪዎችን የመሥራት ዕቅዱን መሰረዙ ይታወሳል።


ዢኦሚ በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ውስጥ በተሽከርካሪ ንግዱ 10 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስት አደርጋለሁ ብሏል። በቢሊየነሩ ኤሎን ማስክ የሚመራው ቴስላ በቅርብ ወራት ውስጥ በቻይና ያለውን ድርሻ በሀገር ውስጥ ተቀናቃኝ በሆነው ቢዋይዲ ተነጥቋል።የዋጋ ቅናሽ በማድረጉ ቴስላ ፉክክሩን መቋቋም አልቻለም።

በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል




አል አይን አማርኛ በአፍሪካ ስለሚገኙ አየር መንገዶች እና አውሮፕላኖች ቁጥር ያቀረበው አሳሳች መረጃ....

አል አይን አማርኛ በትናንትናው እለት 'በርካታ አውሮፕላኖች ያሏቸውን ሀገራት ዝርዝር' በማለት አንድ መረጃ አጋርቶ ነበር፣ ለዚህም የፕሌን ስፖተርስ ድረ-ገጽ መረጃን መሰረት አድርጓል።

በዚህ መረጃ መሰረት ደቡብ አፍሪካ በ195 አውሮፕላኖች አንደኛ፣ ኬንያ በ177 አውሮፕላኖች ሁለተኛ፣ ግብፅ በ166 አውሮፕላኖች ሶስተኛ፣ እንዲሁም ኢትዮጵያ በ142 አውሮፕላኖች አራተኛ ደረጃን እንደያዙ ዘገባው ይጠቁማል (ስክሪን ቅጂው ተያይዟል)።

ይህ የአል አልይን ዘገባ በመግቢያው በአፍሪካ ስለሚገኙ አየር መንገዶች ሀተታ ስላቀረበ ያቀረበው ቁጥርም ስለነዚህ አየር መንገዶች እንደሆነ ያመላክታል።

ይሁንና በአቪዬሽን ዘርፍ በሚሰራቸው ዘገባዎች የሚታወቀው ሲምፕል ፍላይንግ (Simple Flying) የዛሬ ሁለት ወር ገደማ ባወጣው ሪፖርት በአፍሪካ ከሚገኙ አየር መንገዶች የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ133 አውሮፕላኖች ቀዳሚው፣ የግብፅ አየር መንገድ በ82 አውሮፕላኖች ሁለተኛ፣ የአልጄርያ አየር መንገድ በ55 አውሮፕላኖች ሶስተኛ፣ የሞሮኮ አየር መንገድ በ51 አውሮፕላኖች አራተኛ እንዲሁም የኬንያ አየር መንገድ በ32 አውሮፕላኖች አምስተኛ እንደሆነ ዘግቧል (https://simpleflying.com/largest-airlines-africa/)

ይህን የሚያረጋግጠው ሌላው መረጃ ለምሳሌ የግብፅ አየር መንገድ በራሱ ድረ-ገፅ የአውሮፕላኖቹ ቁጥር 80 ገደማ እንደሆነ አስቀምጧል። በኪሳራ ላይ የሚገኘው የደቡብ አፍሪካ አየር መንገድ ደግሞ አሁን ላይ ያሉት አውሮፕላኖች 13 ብቻ እንደሆኑ በድረ-ገፁ ላይ ይታያል።

የአል አይን ዘገባ በአጠቃላይ በተጠቀሱት ሀገራት ውስጥ ስለሚገኙ አውሮፕላኖች ቢሆን ምናልባት ትክክል ሊሆን እንደሚችል የጠቆሙን አንድ የአቪዬሽን ባለሙያ፣ እንደ ኢትዮጵያ አንድ ግዙፍ አየር መንገድ እና ጥቂት የግል የቻርተር በረራ የሚሰጡ ድርጅቶች ሳይሆኑ በርካታ የግል አየር መንገዶች እና የግል አውሮፕላኖች ያሉባቸው ሀገራት እንዳሉ ጠቁመዋል። ስለዚህ ብዙ አውሮፕላኖች ያሏቸው ሳይሆን ያሉባቸው ሀገራት ተብሎ መቅረብ እንደነበረበት ባለሙያው አስረድተዋል።

ይሁንና የዜናው ቅኝት በአየር መንገዶች ዙርያ ስለሆነ መረጃውን አሳሳች ያደርገዋል።

Via Ethiopia Check
#ዳጉ_ጆርናል




ተቀጥሮ በሚሰራበት ቤት ዉስጥ በእንቅልፍ ላይ  የነበረችን የ6 ዓመት ህፃን ለመድፈር ሙከራ ያደረገው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስራቅ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ  በ6 ዓመት ህፃን ላይ የመድፈር ሙከራ አድርጓል የተባለ  ተከሳሽ  በ15  ዓመት ፅኑ እስራት  እንዲቀጣ የተወሰነበት መሆኑ   የወረዳዉ ፖሊስ ገልጿል።

በሶዶ ወረዳ ጢያ 01 ቀበሌ ነዋሪ የሆነው ተከሳሽ ተመስገን ከበደ በእስራት ሊቀጣ የቻለዉ ጥር 19 ቀን 2016 ዓ.ም ከለሊቱ 6:00 ሰዓት ላይ ወንጀሉን የፈጸመው።

የክልሉ ፖሊስ የሚዲያ ክፍል ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ታጁ ነጋሽ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት ተቀጥሮ በሚሰራበት  ቤት ዉስጥ በእንቅልፍ ላይ  የነበረችን  የ6 ዓመት ህፃን ለመድፈር በሙከራ ሲያደርግ  የታዳጊዋ እናት ድንገት ደርሳ  እጅ ከፍንጅ መያዙን ገልጿል።

የሶዶ ወረዳ ፖሊስ በተከሳሹ ላይ ያጣራዉን የምርመራ መዝገብ  ተቀብሎ ዐቃቤህግ የመሰረተዉ ክስ የተመለከተዉ የወረዳዉ ፍርድቤት ተከሳሹ  ወንጀሉን መፈፀሙን በቀረበለት የሰዉና የሰነድ ማስረጃ  በማረጋገጡ ተከሳሹን ጥፋተኛ ሲል ብይን ሰጥቷል።

የሶዶ ወረዳ ፍርድ ቤት መጋቢት 17 ቀን 2016 ዓ.ም በዋለው የወንጀል ችሎች ተከሳሽ በ15 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ የተወሰነበት መሆኑን  ምክትል ኮማንደር ታጁ ነጋሽ ጨምረው ለብስራት ሬድዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

በሳምራዊት ስዩም
#ዳጉ_ጆርናል


የአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት “ዲሞግራፊ ለመቀየር” የሚካሄድ አይደለም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስተባበሉ

በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወነ የሚገኘው የመንገድ እና አካባቢ ልማት ፕሮጀክት፤ “ዲሞግራፊ ለመቀየር” አሊያም “ኦሮሞዎችን ወደ ከተማ ለመመለስ ነው” የሚሉ ወገኖችን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተቹ።

አዲስ አበባ ውስጥ “ከበቂ በላይ” የኦሮሞ እና የሌሎች ብሔር ተወላጆች መኖራቸውን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “የሌለ ሰው ኖሮ፤ ሰው ለማምጣት የምንቸገርበት አይደለም” ሲሉም አስተባብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ይህን ያሉት የአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደር ልማት ስራን ከሚያስፈጽሙ አመራሮች እና የስራ ኃላፊዎች ጋር ትላንት ረቡዕ መጋቢት 18፤ 2016 ባደረጉት ውይይት መሆኑን ዳጉ ጆርናል ከኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘገባ ተመልክቷል። እርሳቸው የሚመሩት መንግስት ከዚህ ቀደም ባከናወናቸው የግንባታ ስራዎች “ብዙ ስሞታዎች ነበሩ” ያሉት አብይ፤ ለዚህም የምኒልክ ቤተ መንግስት እና የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት እድሳትን በምሳሌነት አንስተዋል።

“ይሄ ግቢ ሲቀየር ሀገራዊ ፖለቲካ ነበር። የእዚህን ግቢ እድሳትን እና ዩኒቲ ፓርክን ለመቃወም ሰዎች በጣም ብዙ ደክመዋል። በኋላ [የአዲስ አበባ ከተማ] ማዘጋጃ ቤት ሲጠናቀቅ፤ ‘ለምን ተሰራ’ ተብሎ ብዙ ተብሏል። አሁንም ብዙ አሉባልታዎች፤ ብዙ ወሬዎች ይሰማሉ። ‘ዲሞግራፊ ለመቀየር ነው’፤ ‘ኦሮሞዎች ለመመለስ ነው’ [የሚሉ] የተለያዩ ስሞች ይሰጣሉ” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

Via Ethiopia Insider
#ዳጉ_ጆርናል


የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ፤ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በተወሰኑ የክልሉ አካባቢዎች ላይ ትንኮሳ ጀምሯል ሲል ከሰሰ

የአማራ ብሔራዊ ክልል መንግሥት ከሰሞኑ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ያወጣውን መግለጫ ተከትሎ ምላሽ ሰጥቷል። ሙሉ መግለጫዉ እንደሚከተለው ቀርቧል...

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም የአማራ ክልል ተማሪዎች መማሪያ መጻህፍትን እንደሰበብ ተመርኩዞ ያወጣውን የዛቻ እና የጠብ አጫሪነት መግለጫ ተመልክተናል፡፡ ጊዜያዊ አስተዳደሩ የአማራ ክልል የትምህርት ሥርዓትን በማጣቀስ የተሳሳተ ካርታ ተሰርቷል ሲል ያወጣው መግለጫ በተሳሳተ ካርታ ወደ አማራ ክልል ተካተዋል ያላቸውን አካባቢ ሕዝቦች ታሪካዊ እውነታን፣ ተጨባጭ ማስረጃዎችን እና ነባራዊ ሐቅን የካደ፣ አሳሳች እና የጠብ አጫሪነት ፍላጎትን የተሸከመ መግለጫ በመሆኑ እና በትናንትናው እለት ማለትም መጋቢት 18 ቀን 2016 ዓ.ም ደግሞ ከነበረበት አካባቢ በመንቀሳቀስ የራያ አላማጣ ወረዳ ቀበሌዎችን በመያዝ ነዋሪዎችን በመግደል እና በማሰቃየት ላይ ይገኛል፡፡

ጊዜያዊ አስተዳደሩ የአማራ ክልል የተማሪዎች የመማሪያ መጻሕፍ ውስጥ የተሳሳተ ካርታ ተሰርቷል ሲል ባወጣው መግለጫ ሊያመላክታቸው የተፈለጉት አካባቢዎች ካለፉት 30 ዓመታት በፊት ጀምሮ የወልቃይት ጠገዴ፣ ጠለምት እንዲሁም የወፍላ ወረዳዎች እና የራያ የማንነት ጥያቄ ያሉባቸው ወረዳዎች የማንነት እና ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄዎችን ሲያቀርቡባቸው በነበሩ ቦታዎች ላይ መኾኑ ግልጽ ነው፡፡

አሁን በሥራ ላይ የሚገኘው የሀገሪቱ ሕገ መንግሥት ከመጽደቁ በፊት በተስተዋሉት የአስተዳደራዊ መዋቅሮች እና አደረጃጀት ቅመራ ጅማሬ አንስቶ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በሰሜን ዕዝ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ላይ አሰቃቂ ጥቃት በመፈጸሙ ምክንያት ጦርነት እስከተቀሰቀሰበት ግዜ ድረስ የወልቃይት ጠገዴ፤ ጠለምት እንዲሁም የወፍላ ወረዳዎች እና የራያ የማንነት ጥያቄ ያለባቸው ወረዳዎች በወቅቱ ለነበረው መንግስት የማንነትና ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄዎችን በማንሳት መብቶቻቸው እንዲከበሩላቸው ሲጠይቁ የነበሩ መሆኑን በበርካታ ታሪካዊ ሁነቶችና ተጨባጭ ማስረጃዎች የተረጋገጠ ጉዳይ ነው፡፡

ይሁን እንጂ እነዚህ የማንነትና ራስን በራስ የማስተዳደር መብቶቻቸው እንዲከበሩላቸው ሲጠይቁ የነበሩ ሕዝቦች እና አካባቢዎችን ለበርካታ ዘመናት በኃይል ሲገዛ የነበው የቀድሞው የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የወልቃይት ጠገዴ፤ ጠለምት እንዲሁም የወፍላ ወረዳዎች እና የራያ የማንነት ጥያቄ ያለባቸው ወረዳዎች ላነሱት ታሪካዊና ሕጋዊ ጥያቄዎች ሕጋዊ አሰራርን የተከተለ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ የአካባበው ተወላጆችን፣ የሀገር ሽማግሌዎችን፣ የማንነትና የአስተዳደር ጥያቄ አስተባባሪዎችን በማሰር፣ በማሰደድ እና በመግደል የሕዝቡ ጥያቄ ምላሽ ሳያገኝ እስከ ሰሜኑ የህግ ማስከበር ጊዜ ድረስ እንዲገፋ አድርጎታል ማለቱን ዳጉ ጆርናል ከመግለጫው ተመልክቷል፡፡

የማንነት እና የአስተዳደር መብት ዙሪያ ላነሳቸው ጥቄዎች የወልቃይት ጠገዴ፣ ጠለምት እንዲሁም የወፍላ ወረዳዎች እና የራያ የማንነት ጥያቄ ያለባቸው ወረዳዎች ትግል በተፋፋመበትና ከፍተኛ መስዋዕትነት ጭምር እየከፈለ በሚገኝበት ወቅት ህወሓት የሠሜን ዕዝ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊትን አሰቃቂ ጥቃት መሰንዘሩን ተከትሎ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ መንግስት ሁሉንም ኢትዮጵያዊያንን በማቀናጀት ለሁለት ዓመታት የቆየ የሕግ ማስከበር እርምጃ ለመውሰድ የተገደደበት ሁኔታ መፈጠሩ ይታወሳል፡፡

የማንነትና የአስተዳደር ጥያቄዎቹ ለዘመናት የታፈኑበት ሕዝብም ከማዕከላዊው መንግስት ጎን ተሰልፎ በህ.ወ.ሓ.ት የክህደት ተግባር በኢትዮጵያ ሕልውና እና ሉአላዊነትት ላይ የተጋረጠውን ግልጽ አደጋ እንዲቀለበስ የበኩሉን አስተዋጽዖ ከማበርከቱ ባሻገር በሂደቱ ህወሓት በኃይል ተገፍፎባቸው የነበረውን የማንነትና ጥያቄና ራስን በራስ የማስተዳደር ነጻነት የተቀዳጁበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡

በዚህም ምክንያት የወልቃይት ጠገዴ፣ ጠለምት እንዲሁም የወፍላ ወረዳዎች እና የራያ የማንነት ጥያቄ ያለባቸው ወረዳዎች ህዝብ እንደማንኛውም የሀገሪቱ ሕዝብ ሁሉ የልማቱ ተሳታፊና ተጠቃሚነት መብቱ ሊቀለበስ የማይችል በመሆኑ በቀድሞው የህ.ወ.ኃ.ት እና በኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግስት መካከል የፕሪቶሪያው ስምምነት ከመፈረሙ በፊት ጀምሮ የአማራ ክልል እንደሌሎቹ ዞኖችና የልማት ትሩፋቶች ሁሉ የአካባቢው ሕዝብም በትምህርቱም መስክ ተጠቃሚ እንዲሆኑ አድርጓል፡፡

አካባቢዎቹን በተመለከተ የነበረው፣ ያለው እና የሚኖረው እውነታ ይሄ ሆኖ ሳለ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ/ም ከፕሪቶሪያው ስምምነት ከመፈረሙ በፊት በስራ ላይ የዋሉ የአማራ ክልል ተማሪዎች እንደሌሎቹ አካባቢዎች የነዚህ አካባቢ ህፃናትም የመማራ መብታቸው እንዲከበር የአማራ ክልል መንግስት ግዴታውን መወጣቱን ሰበብ በማድረግ በአማራ ክልል ላይ ጥቃት ከመፈጸም የማይመለስ መሆኑን የሚገልጽ የጠብ አጫሪ መግለጫ ማውጣቱ ካለፉት ድርብርብ ውድቀቶች ትምህርት አለመውሰድን ከማሳየት የዘለለ ፋይዳ አይኖረውም፡፡

የተፈጠሩ ችግሮችን በህግ አግባብ እንዲፈታ እተደረገ ያለውን ጥረት የአማራ ክልል መንግስት የራሱን ድርሻ እየተወጣ ባለበት ሁኔታ በህዝብ መጎሳቆልና በወጣቶች እልቂት ትምህርት አለመወሰዱና የተለመደ ትንኮሳ በማድረግ ላይ መሆኑ እጅጉን አሳዝኖናል፡፡

ስለሆነም የትግራይ ክልል ግዜያዊ አስተዳደር ለሀገሪቱ ቋሚ ቀውስ ምንጭ ከሚያደርጉት ተግባራት እንዲታቀብ፣ ሀገራችንንና ሁለቱን ክልሎች ወደ ቀውስ ከሚያስገቡ ተግባራት በመቆጠብ ከለመደው አጓጉል የካርታ ፖለቲካ ጨዋታ እንዲወጣና የህዝብን ፍላጎት ማዕከል ባደረጉ ውይይቶች ላይ እንዲያተኩር እንዲሁም አንድ ሀገር ለመገንባት ለሚፈለገው ዘላቂ ሠላም እና ለሕዝቦች አንድነት መጽናት በሚበጅ ሐሳብና ተግባር ላይ እንዲያተኩር እንመክራለን ሲል መግለጫውን አጠናቅቋል፡፡

#ዳጉ_ጆርናል




የኮንዶሚኒየም ቤት እጣ ጠባቂዎች ላልተፈለገ እንግልት እንዳትዳረጉ ተብላችኋል

ከሰሞኑ በማህበራዊ ሚዲያ በተለይም በቲክቶክ በተለቀቀ የተሳሳተ መረጃ የጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝግባችሁ እየተጠባበቃችሁ ያላችሁ ብቁ መሆን አለመሆናችሁን ባምቢስ በሚገኘው የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ 5ኛ ፎቅ መታችሁ እንድታዩ በሚል የተለቀቀው መረጃ የተሳሳተ መሆኑን ዳጉ ጆርናል ከአዲስአበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ሰምቷል። በዛሬዉ እለትም ይህን መረጃ የሰሙ በርካታ ሰዎች ወደ ባንቢስ አቅንተዉ ወረፋ መያዛቸዉን ዳጉ ሰምቷል።

የአዲስአበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ፤ ተመዝግባችሁ እየተጠባበቃችሁ የምትገኙ ሰዎች ላተፈለገ እንግልት እንዳትዳረጉ ሲል አሳስቧል፡፡

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ እና ኮርፖሬሽኑ ነዋሪውን በተለይም ተመዝግቦ የሚጠባበቀውን የቤት ባለቤት ለማድረግ የተለያዩ የቤት ልማት አማራጮችን ተግባራዊ በማድረግ ከምንጊዜውም  በተሻለ መልኩ እየሰሩ እንደሚገኝ የገለጸም ሲሆን ተመዝጋቢዎችም ሆነ ሌሎች ነዋሪዎች የተቋሙ ባልሆኑ ማህበራዊ ሚዲያዎችም ሆነ ግለሰቦች በሚያናፍሱት ወሬ እንዳትታለሉ አስገንዝቧል።

#ዳጉ_ጆርናል

Показано 20 последних публикаций.