ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


በዚህ ቻናል ዲ/ዮርዳኖስ የሚያስተምራቸው ወቅታዊ እና የነገረ ቅዱሳን (ዝክረ ቅዱሳን ትምህርቶችን ከእርሱ በመቀበል እናስተላልፋለን):: "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


"" ምኲራብ "" (ዮሐ. ፪:፲፪)

"የዐቢይ ጾም ትምህርት" (ክፍል ፭/5)

(የካቲት 28 - 2017)






16:17-18

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)


Memhir Esuendale:
#Feasts of #Megabit_3

✞✞✞On this day we commemorate the departure of our father Saint Cosmas the 58th Archbishop of Alexandria✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞Saint Cosmas the Archbishop✞✞✞
=>The word bishop has the meaning father, leader or shepherd. And according to the teachings of the Church, in the New Testament, there are generally 3 spiritual ranks of authority. And they are deacon, priest and bishop. They in-turn have, in total, 9 subdivisions. And from these, the highest rank is that of the bishop. 

✞Being a bishop means protecting Christ’s flock as He did. This authority, on earth, is “a burden, a debt” but in heaven, it is “glory”. Thence, no one wants the episcopate unless he wishes to be severe unto his flesh.

✞Taking what St. Paul has said, “If a man desire the office of a bishop, he desireth a good work” 1Tim. 3:1 at face value and saying “Ordain me” is a hard choice that will get one thrown into an un-quenching fire. And that is because a Christian will be asked for his/her sins however a priest will be asked for his and his spiritual children’s. Nonetheless, the highest accountability is that of the bishop’s.

✞Even if one bishop fasts and prays, it will not be enough for his salvation. This is because He [God] has put him on the See to keep his flock and not himself [alone]. As the Lord had said, “the good shepherd giveth his life for the sheep” (John 10:11). Therefore, the priesthood, being a bishop, is an apostolic commission which comes with a huge responsibility.

✞Our fathers, the Apostles and their disciples, established great bishopric Sees, and passed their teachings with the cathedrae.  And from these Sees of the Bishops, 4 are elevated.

✞They are - St. Peter’s the See of Rome, St. John’s the See of Antioch, St. Mark’s the See of Alexandria and St. Paul’s the See of Ephesus.

✞These Sees have stayed together after the ascension of Christ until the Council of Chalcedon in the year 443 E.C. (451 A.D.) but then they separated. And from them, the Alexandrian (Egypt’s) and the Antiochian (Syria’s) Sees are intact to this day with their Miaphysite (Tewahedo) faith.

✞And as our Church is also an Apostolic one, It remembers and commemorates, the bishops that rose and were like the Apostles in their deeds on their respective feast days.  

✞We, particularly, honor many fathers from Alexandria and Antioch. And that is because they have endured with gratitude for the upright faith and the flock many trials. And one of these fathers whom we commemorate is St. Cosmas who was the 58th Archbishop of Alexandria (Egypt). He was enthroned when Islam flourished in the country (Egypt) and being appointed a bishop at that time was not like a participation in a wedding banquet seen these days (in Ethiopia). Rather, it was a decision to endure afflictions of fire and the sword from the apostates.

✞The Church, after the 6th century A.D, has a special place for the Copts (Egyptians) from the Archbishops that rose in the world.  And the reason is because they have received their share from the chalice of brutality of the Caliphs of Egypt. And one of those fathers was St. Cosmas who departed on this day and who loved our Lady amply.

✞✞✞ May the God of the Holy Fathers/Scholars keep us and the Church by their prayers from wicked enemies.

✞✞✞Annual feasts celebrated on the 3rd of Megabit
1. St. Abba Cosmas (the 58th Archbishop of Alexandria)
2. The Honored Abba Porphyry (Porphorius)

✞✞✞ Monthly Feasts
1. The Entrance of our Lady the Virgin Saint Mary the God-bearer into the Temple
2. Sts. Joachim and Anna
3. Sts. The Arch-Priests (Zacharias and Simeon)
4. Abba Libanos of Mata
5. Abune Zena Markos
6. Abune Medhanine Egzi of Debre Benkol

✞✞✞ “Now I beseech you, brethren, mark them which cause divisions and offences contrary to the doctrine which ye have learned; and avoid them. For they that are such serve not our Lord Jesus Christ, but their own belly; and by good words and fair speeches deceive the hearts of the simple.”✞✞✞Rom.




††† እንኳን ለአባታችን ቅዱስ ቆዝሞስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ቆዝሞስ ሊቀ ጳጳሳት †††

††† "ጳጳስ" ማለት "አባት - መሪ - እረኛ" ማለት ነው:: በቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ በሐዲስ ኪዳን የመንፈሳዊ ስልጣን ደረጃዎች በጥቅሉ 3 ናቸው:: እነሱም ዲቁና: ቅስና: ጵጵስና ሲሆኑ በሥራቸው ወደ 9 ያህል ክፍሎች አላቸው:: ከእነዚህም ከፍተኛው ስልጣን ጵጵስና ነው::

ጵጵስና ማለት የክርስቶስን መንጋ እንደ ባለቤቱ አድርጐ መጠበቅ ማለት ነው:: ሥልጣኑ በምድር "ሸክም: ዕዳ" ሲሆን በሰማይ ግን "ክብር" ነው:: ማንም በሥጋው ላይ ካልጨከነ በቀር ጵጵስናን አይመኝም::

ቅዱስ ጳውሎስ "ሠናየ ግብረ ፈተወ - ማንም ጵጵስናን ቢመኝ መልካም ሥራን ተመኘ" (1ጢሞ. 3:1) ማለቱን ይዞ "ሹሙኝ" ማለት ወደ ማይጠፋ እሳት የሚያስጥል ከባድ ውሳኔ ነው:: ምክንያቱም አንድ ክርስቲያን የሚጠየቅ በራሱ ኃጢአት ሲሆን አንድ ካህን ደግሞ ስለ ልጆቹ ይጠየቃል:: የከፋው ግን የጳጳሱ ነው::

አንድ ጳጳስ ቢጾም ቢጸልይም እንኳ ለድኅነቱ በቂ አይደለም:: ምክንያቱም በመንበሩ ላይ ያስቀመጠው መንጋውን እንጂ ራሱን እንዲያድን አይደለምና:: ጌታ እንዳለ መልካም እረኛ "ይሜጡ ነፍሶ ቤዛ አባግኢሁ - መልካሙ እረኛ ስለ በጐቹ ቤዛ ራሱን አሳልፎ የሚሰጥ ነው::" (ዮሐ. 10) ስለዚህም ክህነት ( ጵጵስና) ሐዋርያዊ አገልግሎት ከባድም ኃላፊነት ነው::

አባቶቻችን ሐዋርያትና ተከታዮቻቸው ሐዋርያውያን ታላላቅ የጵጵስና መንበሮችን መሥርተው: ትምሕርቱን ከነ ወንበሩ አስተላልፈዋል:: ከእነዚህ መንበረ ጵጵስናዎች አራቱ የበላይ ናቸው::

እነዚህም የቅዱስ ጴጥሮሱ የሮም: የቅዱስ ዮሐንሱ የአንጾኪያ: የቅዱስ ማርቆሱ የእስክንድርያና የቅዱስ ጳውሎሱ የኤፌሶን መናብርት ናቸው::

እነዚህ መንበሮችም ከክርስቶስ ዕርገት እስከ 443 (451) ዓ/ም: ጉባኤ ኬልቄዶን ድረስ በአንድነት ቆይተው ተለያይተዋል:: ከእነዚህ መናብርት መካከል የእስክንድርያው (የግብጹ) እና የአንጾኪያው (የሶርያው) ዛሬም ድረስ በተዋሕዶ እምነት የጸኑ ናቸው::

የእኛ ቤተ ክርስቲያንም ሐዋርያዊት እንደ መሆኗ ሐዋርያትን መስለው: ሐዋርያትን አህለው የተነሱ አበው ጳጳሳትን በየጊዜው በበዓላት ታስባለች: ታከብራለች::

በተለይ ደግሞ የእስክንድርያና የአንጾኪያ በርካታ አባቶችን እናከብራለን:: እነርሱ ለቀናች ሃይማኖትና ለመንጋው ሲሉ ብዙ መከራን በአኮቴት ተቀብለዋልና:: ከእነዚህም መካከል አንዱ ቅዱስ ቆዝሞስ የእስክንድርያ (የግብጽ) 58ኛ ሊቀ ጳጳሳት የነበረ አባት ነው:: ዘመኑ እስልምና የሰለጠነበት ነበርና በዚያ ጊዜ እረኝነት (ጵጵስና) መመረጥ እንደ ዛሬው ዘመን ሠርግና ምላሽ አልነበረም:: በከሃዲዎች እሳትና ስለት መከራን ለመቀበል መወሰን እንጂ::

ከ6ኛው መቶ ክ/ዘመን በኋላ በዓለማችን ከተነሱ ሊቃነ ጳጳሳት ለግብጻውያኑ ቤተ ክርስቲያን ልዩ ቦታ አላት:: ምክንያቱም በወቅቱ በጎቻቸውን (ምዕመናንን) ለመጠበቅ ከግብጽ ከሊፋዎች የግፍ ጽዋዕን ጠጥተዋልና:: ከነዚህም አንዱ የእመቤታችን ፍቅር የበዛለትና በዚህ ቀን ያረፈው ቅዱስ ቆዝሞስ ነው::

††† አምላከ ቅዱሳን ሊቃውንት በጸሎታቸው እኛንም: ቤተ ክርስቲያናችንንም ከክፉ ጠላት ይጠብቅልን::

††† መጋቢት 3 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ አባ ቆዝሞስ (የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት)
2.አባ በርፎንዮስ ክቡር

††† ወርኀዊ በዓላት
1.በዓታ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ
2.ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
3.ቅዱሳን ሊቃነ ካህናት አበው (ዘካርያስና ስምዖን)
4.አባ ሊባኖስ ዘመጣዕ
5.አቡነ ዜና ማርቆስ
6.አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ዘደብረ በንኮል

††† "ነገር ግን ወንድሞች ሆይ! እናንተ የተማራችሁትን ትምህርት የሚቃወሙትን: መለያየትንና ማሰናከያን የሚያደርጉትን ሰዎች እንድትመለከቱ እለምናቹሃለሁ:: ከእነርሱ ዘንድ ፈቀቅ በሉ:: እንዲህ ያሉት ለገዛ ሆዳቸው እንጂ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ አይገዙምና:: በመልካምና በሚያቆላምጥ ንግግርም ተንኮል የሌለባቸውን ሰዎች ልብ ያታልላሉ::" †††
(ሮሜ ፲፮፥፲፯)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††


✝እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ መጋቢት ቡሩክ፥ አመ ፪

✝ጾም ዐቢይ ዘመድኅን ክርስቶስ (አምላክነ)

✞ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦

✿መከራዊ ሰማዕት ዘኒቅዮስ (አረጋዊ ኤጲስ ቆጶስ)
✿ጎርጎርዮስ ጻድቅ ዘገዳመ ሮሃ (ፍቁራ ለእግዝእትነ ማርያም)
❀መክፈልተ ማርያም ጻድቅ (ዘአበርገሌ-ምድረ አገው)

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://t.me/zikirekdusn


""  ገንዘብን አለመውደድ "" (ሉቃ. ፲፯:፲)

"የዐቢይ ጾም ትምህርት" (ክፍል ፬/4)

☞አርዕስተ ምግባራት

(የካቲት 26 - 2017)

https://t.me/zikirekdusn


ዝክረቅዱሳን (ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት)

" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/

🛑በዩቲብለመከታተል👉https://www.youtube.com/@ZikereKedusan

🛑በቴሌግራም👉
https://t.me/zikirekdusn






4. St. Abel the Righteous
5. St. Abba Paul the Hermit (the Great)
6. St. Severus of Antioch
7. Abba Heryakos of Behensa✞✞✞ “This is a faithful saying, and worthy of all acceptation, that Christ Jesus came into the world to save sinners; of whom I am chief. Howbeit for this cause I obtained mercy, that in me first Jesus Christ might shew forth all longsuffering, for a pattern to them which should hereafter believe on him to life everlasting.”✞✞✞
1Tim. 1:15-16

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)


Memhir Esuendale:
#Feasts of #Megabit_2

✞✞✞On this day we commemorate the departure of Saint Gregory the Seer of Heavenly Mysteries✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞Saint Gregory the Seer of Heavenly Mysteries✞✞✞
=>St. Gregory is from Roha (around Syria, Edessa) and is known as “Reaye Hibuat” - “Seer of the Hidden/Heavenly Mysteries”. If asked how that name came to be, it was as follows.

✞In the place where the Saint was born and grew up, he was a sinner to the fullest sense. Though he was a grave sinner, he used to love our Lady, the Virgin St. Mary, with all his heart. And she enabled him to repent on a day of salvation, by a call to penance.

✞And starting that day, he became a holy man of God, a pure sacrifice of the Church and a firm pillar in the desert. And our Lady, the Virgin, took him up in the flesh to heaven and showed him paradise and hell. She also presented him to Adam, Noah, Abraham, Moses, King David and saints of such status and revealed to him many mysteries that cannot be uttered by a mortal tongue and brought him back to earth.

✞During his stay/visit in/to paradise, he saw and was amazed by the glory of the saints. Particularly, he saw male and female saints that had kept their purity and were virgins living with the Theotokos, the Queen of Heaven and Earth, our Lady, the Virgin Saint Mary.

✞He stated, “The vestments which were worn by them were indescribable through the tongue of a created being.” And added that the faces of the virgins shone 7 times brighter than the sun and that their majesty instilled reverence.

✞While he was still in heaven, he also saw this. One elder, who had a long beard, came wearing a cope of light. And while that elder was surrounded front and back, left and right by angels, he started praising God.

✞And when he said, “O Lord our Lord, how excellent is thy name in all the earth!” (Ps.8:1/9) the angels started to sing with him as well and a great tremor took place at that moment. Then the virgins took the elder’s blessing.

✞This praising elder was the righteous, the meek, the one who was after God’s own heart, the King of Israel, David. If asked how that was known, he was identified because of the harp that he had and also because Gregory had heard our Lady call him, “My father David!”

✞Finally, St. Gregory saw our Lady in great honor and majesty and was delighted. And the Mother of Light honored St. Gregory saying, “You are a beloved and pure person”. She also sent a message through him to this world. It said;

✞”My children! Why have you chosen darkness over light, evil over goodness, sin over righteousness . . . ? I live everyday beseeching for you. Please repent so you will not go to hades!”

✞Then, after she had told the Saint this, being followed by St. David and surrounded by angels entered into the tabernacle which had fiery veils. And there she was exalted.
 
✞That’s why the scholar Abba Giorgis of Gasicha praised her saying, “The Angels venerate Mary within the veil saying, ‘Salutation to you, Mary, His young calf.’”

✞After his return from heaven, St. Gregory wrote down what he had seen and gave it to the fathers. And so he is called ‘”The Seer of Hidden/Heavenly Mysteries”. The Saint completed the rest of his life with spiritual strife and departed on this day.

✞✞✞ May the Mother of Light, the Virgin, the Lady of the Saint, multiply in us the tang of her love.

✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 2nd of Megabit
1. St. Gregory the Seer of Heavenly Mysteries (of Roha)
2. The Righteous Abune Mekfelte Maryam (Ethiopian)
3. Abba Macrobius (Makrawy) of Nikiu (Nakiyos) (Elder, Righteous, Bishop and Martyr)

✞✞✞Monthly Feasts
1. St. John the Baptist
2. St. Thaddeus the Apostle (One of the 12)
3. The Righteous and Longsuffering St. Job




††† እንኳን ለጻድቁ አባታችን ቅዱስ ጐርጐርዮስ ረዓዬ ኅቡዓት ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ቅዱስ ጐርጐርዮስ ረዓዬ ኅቡዓት †††

††† ቅዱስ ጐርጐርዮስ ሃገሩ ሮሃ (ሶርያ አካባቢ) ሲሆን ረዓዬ ኅቡዓት (ምሥጢራትን የተመለከተ) ይባላል::
ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
ቅዱሱ ተወልዶ ባደገባት ሃገር ይህ ቀረው የማይባል ኃጢአተኛ ሰው ነበር:: ታዲያ ምንም ኃጢአተኛ ሰው ቢሆን እመቤታችን ድንግል ማርያምን በፍፁም ልቡ ይወዳት ነበርና በመዳን ቀን ጥሪ ለንስሐ አበቃችው::

ከዚያች ዕለት ጀምሮም ቅዱስ የእግዚአብሔር ሰው : ንጹሕ የቤተ ክርስቲያን መስዋዕት : ጽኑዕ የበርሃ ምሰሶ ሆነ:: ድንግል እመቤታችንም ከነሥጋው ወደ ሰማያት ወስዳ ገነትና ሲዖልን አሳይታ : ከአዳም : ኖኅ : አብርሃም : ሙሴ : ዳዊትን ከመሰሉ ቅዱሳን ጋር አስተዋውቃ : ከዚህም በላይ የሆነና በሰብአዊ አንደበት የማይነገር ብዙ ምሥጢር አሳይታ ወደ ምድር መልሳዋለች::

ቅዱስ ጐርጐርዮስ በሰማይ (በገነት) በነበረው ቆይታ ክብረ ቅዱሳንን ተመልክቶ አድንቋል:: በተለይ በፍጹምነት ድንግልናቸውን የጠበቁ ቅዱሳንና ቅዱሳት ደናግል አኗኗራቸው ከአምላክ እናት : ከሰማይ ንግሥት : ከእመቤታችን ከድንግል ማርያም ጋር መሆኑን አይቷል::

"የለበሱት ልብስም በፍጡር አንደበት ተከናውኖ ሊነገር የሚቻል አይደለም" ይላል:: የደናግል ፊታቸው ከፀሐይ 7 እጅ ያበራልና ግርማቸው ያስፈራል::

ቅዱሱ ሰው በዚያው በሰማይ ሳለ ደግሞ ይህንን ተመለከተ:: አንድ አረጋዊ : ጽሕሙ ተንዠርግጐ : የብርሃን ካባ ላንቃ ለብሶ ይመጣል:: ቅዱሳን መላእክት በፊት በኋላ : በቀኝ በግራ ከበውት ሳለ እግዚአብሔርን ሊያመሰግን ጀመረ::

"እግዚኦ እግዚእነ : ጥቀ ተሰብሐ ስምከ በዲበ ምድር (አቤቱ ጌታችን : በምድር ሁሉ ስምህ የተመሰገነ ሆነ)" ሲል . . . መላእክቱ በዝማሬ አጀቡት:: በዚህ ጊዜም ታላቅ መናወጥ ሆነ:: ደናግሉም የቅዱሱን ሽማግሌ በረከቱን ተሳተፉ::

ይህ አመስጋኝ ሽማግሌ ልበ-አምላክ : ጻድቅ : የዋህና የእሥራኤል ንጉሥ የሆነው ዳዊት ነበር:: በምን ታወቀ ቢሉ :- በበገናው:: አንድም እመቤታችን "አባቴ ዳዊት!" ብላ ስትጠራው ጐርጐርዮስ ሰምቷልና::

በመጨረሻም እመቤታችንን በፍጹም ክብርና ግርማ ተመልክቷት ሐሴትን አድርጓል:: እመ-ብርሃንም "ተወዳጅና ንጹሕ ሰው ነህ" ስትል ቅዱስ ጐርጐርዮስን አመስግናዋለች:: ስለዚህ ዓለምም እንዲህ የሚል መልእክትን ልካለች::

"ልጆቼ ሆይ! ከብርሃን ጨለማን : ከደግነት ክፋትን : ከጽድቅ ይልቅ ኃጢአትን . . . ምነው መምረጣችሁ? እኔ ስለ እናንተ በየቀኑ እየለመንሁ እነሆ አለሁ:: ወደ ጨለማ ገሃነም እንዳትወርዱ እባካችሁ ንስሐ ግቡ!"

ቅድስት ድንግል ማርያም ይህንን ለቅዱሱ ሰው ነግራው : ቅዱስ ዳዊትን አስከትላ : በግሩማን መላእክት ታጅባ ወደ ውሳጤ መንጦላዕት (የእሳት መጋረጃዎች ወደ ተተከሉበት ድንኳን) ገባች:: በዚያም ተመሰገነች::

ለዛም አይደል ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ:-
"ይዌድስዋ መላእክት ለማርያም በውስተ ውሳጤ መንጦላዕት : ወይብልዋ : በሐኪ ማርያም ሐዳስዩ ጣዕዋ::" ሲል ያመሰገናት::

ቅዱስ ጐርጐርዮስም ከሰማይ ቆይታ መልስ ያየውን ሁሉ ጽፎ ለአበው ሰጥቷል:: ስለዚህም ረዓዬ ኅቡዓት (ምሥጢራትን ያየ) ይሰኛል:: ቅዱሱ ተረፈ ዘመኑን በተጋድሎ ፈጽሞ በዚህች ቀን አርፏል::

††† የቅዱሱ እመቤት ድንግል እመ ብርሃን መዓዛ ፍቅሯን ታብዛልን::

††† መጋቢት 2 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ረዓዬ ኅቡዓት (ዘሃገረ ሮሃ)
2.አቡነ መክፈልተ ማርያም ጻድቅ (ኢትዮጵያዊ)
3.አባ መከራዊ ዘሃገረ ኒቅዮስ (አረጋዊ: ጻድቅ: ጳጳስና ሰማዕት)

††† ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት
2.ቅዱስ ታዴዎስ ሐዋርያ
3.ቅዱስ ኢዮብ ጻድቅ ተአጋሲ
4.ቅዱስ አቤል ጻድቅ
5.ቅዱስ አባ ጳውሊ ገዳማዊ (ታላቁ)
6.ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ
7.አባ ሕርያቆስ ዘሃገረ ብሕንሳ

††† "ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው:: ከኃጢአተኞችም ዋና እኔ ነኝ:: ስለዚህ ግን የዘላለምን ሕይወት ለማግኘት በእርሱ ያምኑ ዘንድ ላላቸው ሰዎች ምሳሌ እንድሆን ኢየሱስ ክርስቶስ ዋና በምሆን በእኔ ላይ ትዕግስቱን ሁሉ ያሳይ ዘንድ ምሕረትን አገኘሁ::" †††
(፩ጢሞ. ፩፥፲፭)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††


✝እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ መጋቢት ቡሩክ፥ አመ ፩

✝ጾም ዐቢይ ዘመድኅን ክርስቶስ (አምላክነ)

❖ሠረቀ ወርኀ መጋቢት ቡሩክ (በሰላመ እግዚአብሔር)

✞ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦

✿ማቱሳላ ጻድቅ (ወልደ ሄኖክ ወእድና)
✿በርኪሶስ አረጋዊ (ዘኢየሩሳሌም)
❀እለእስክንድሮስ ሰማዕት (ዘሮሜ)
❀መርቆሬዎስ ጳጳስ (ዘብሔረ ግብጽ)

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://t.me/zikirekdusn




ዝክረቅዱሳን (ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት)

" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/

🛑በዩቲብለመከታተል👉https://www.youtube.com/@ZikereKedusan

🛑በቴሌግራም👉
https://t.me/zikirekdusn



Показано 20 последних публикаций.