ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


በዚህ ቻናል ዲ/ዮርዳኖስ የሚያስተምራቸው ወቅታዊ እና የነገረ ቅዱሳን (ዝክረ ቅዱሳን ትምህርቶችን ከእርሱ በመቀበል እናስተላልፋለን):: "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


"" ጦሬም አያድነኝም! "" (መዝ. ፵፫:፮)

"ዝክረ ቅዱስ ዳዊት - ዘወርኀ የካቲት"

(የካቲት 23 - 2017)

https://t.me/zikirekdusn


✝ ቅዱስነታቸው አቡነ ቄርሎስ ፮ኛ እና ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ✝

☞116ኛው የእስክንድርያ ፓትርያርክ፡፡
☞13ኛው ሐዋርያ (በግብጻውያን አበው አጠራር)፡፡
☞የቅዱስ ሚናስ ወዳጅና፡፡
☞ድንቅ አድራጊው አባት ያረፉት የካቲት 30, 1971 (1963) ነበር፡፡

(እንዳጋጣሚ ዛሬ አንድ ሰው የላከልኝን መጽሐፍ ስመለከት ስለርሳቸው ነው፡፡ በNabil Adly በዐረቢኛ ተጽፎ፤ በSamuel Bishara ወደ እንግሊዝኛ የተተረጎመ ነው፡፡ The Gate of Heaven ይላል፡፡ ከጀርባው ላይ ደግሞ የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ፫ኛ አስተያየት አለበት)

"" በረከታቸው ይደርብን፡፡ ""

ዝክረቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት

"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር
በዩቲብለመከታተል👉https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
በቴሌግራም👉
https://t.me/zikirekdusn


>

=>ቸሩ አምላካችን እግዚአብሔር ባለፉት 6 ወራት (180 ቀናት) ምንም እንኩዋ ኃጢአታችን ቢበዛ : ሰውነታችንም ቢከፋ ያጠፋን ዘንድ አልወደደም::

=>እስኪ ለዛሬ እንዲህ ብለን ራሳችን እንጠይቅ?

=>ባለፉት 6 ወራት (180 ቀናት) ምን በጐ ሥራ ሠራን?

=>ምንስ መልካም ፍሬ አፈራን?

=>ስንት ጊዜስ ንስሃ ገባን?

=>አሁንስ ለቀጣዮቹ 6 ወራት ምን አሰብን?

=>ቸሩ አምላካችን ተረፈ ዘመኑን የፍቅር : የበረከትና የንስሃ ያድርግልን::

=>+"+ ከእንግዲህ ወዲህ በሥጋ ልትኖሩ በቀረላችሁ ዘመን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንጂ እንደ ሰው ምኞት እንዳትኖሩ . . . የአህዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት . . . ያለፈው ዘመን ይበቃልና . . . ዳሩ ግን የነገር ሁሉ መጨረሻ ቀርቧል:: እንግዲህ እንደ ባለ አእምሮ አስቡ . . . +"+ (1ዼጥ. 4:2-7)



ዝክረቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት

"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር
በዩቲብለመከታተል👉https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
በቴሌግራም👉
https://t.me/zikirekdusn


"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::
(ማቴ ፫:፫
ሰላም ለሙሴ ዘተሰብሐ ገጹ፤
ወተለዓለ ድምጹ፤
ወዘሠነየ ምርዋጹ!


ብፁዕ አባ አቡነ ተክለሃይማኖት ዘኤለ ገዳማተ እምኀበ እግዚኡ ይነሣእ እሴተ ቦአ ሀገረ ደብረ ሊባኖስ በፍሥሐ ወበሰላም።

ማኅደረ ሰላምነ ቅድስት ደብተራ እሞሙ ለሰማዕት ወእኅቶሙ ለመላእክት ንዑ ንስግድ ኵልነ ኀበ ማርያም እምነ።

ልብኪ የዋህ ዘኢየአምር ተበቊሎ ለኃጥእ እምተኃጒሎ፡፡ ተሣሀልኒ ድንግል ዘልማድኪ ተሣሕሎ ምንተ እነግረኪ ዉስተ ልብየ ዘሀሎ፡፡ እስመ አንቲ ተአምሪ ኀዘንየ ኩሎ፡፡"

ብጹእ አንተ ወሠናይ ለከ ብእሴ እግዚአብሔር መርቆሬዎስ ሰማዕት ሰላመ ጸሊ ለርኁቃን ወዳኅና ለቅሩባን ሰአል ወጸሊ በእንቲአነ::

ሰላም ለክሙ እንጦንስ ወመቃርስ፤
አቢብ ሲኖዳ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፤
ለባርኮትነ ንዑ ውስተ ጽርሐ ዛቲ መቅደስ፤
ተክለ ሃይማኖት አኖሬዎስ ኤዎስጣቴዎስ፤
ሳሙኤል ተክለ አልፋ በብኑዳ ኪሮስ፡፡

✝ 5 ነገሮችን በደንብ ያዙ።
    1, 🛑አላማ

    2 ,🛑እምነት

   3,🛑ጥረት

   4 🛑ጥንቃቄ
     5🛑ጽናት
=>እነዚህን ያዟቸው ተጠቀሙባቸዉ ኑሯቸው።
@9ኙ የቅድስና መንገዶች

፩👉ሃይማኖት
፪👉ጾም
፫👉ጸሎት
፬👉ስግደት
፭👉ምጽዋት
፮👉ፍቅር
፯👉ትህትና
፰👉ትዕግስት
፱👉የዋህነት

ንስሐ የተጣመመውን ያቀናል።በኃጥያት የቆሸሸውን ያነጻል፤ንስሐ ለሚገቡ ሁሉ የመላዕክት ንጹሕ ልብስ ይሰጣችኃል

ዝክረቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት

"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር
በዩቲብለመከታተል👉https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
በቴሌግራም👉
https://t.me/zikirekdusn




This was because he was a hermit whose stamina was upright, whose beard came down like woven silk, whose hair was as dark as a raven, and who had an appearance that was complete and had an impression that triggered fear.✞He then immediately preached to the people to repent and baptized many unto repentance. And after six months in this ministry, our Lord came to him. St. John was alarmed when the Creator, Who holds heaven and earth with everything in them in His hands, came saying, “Baptize Me.” He [St. John] did not know where to go.

✞He said, “No my Lord! You baptize me.” However, the Lord responded with, “I have permitted it [for you St. John to baptize Me].” So, he baptized Him. And for this, he will always be called, “Metmeqe Melekot” (The Baptist). Finally, St. John rebuked Herod (Antipas). And the king led by a grudge imprisoned him for 7 days. 

✞And when Herod celebrated his birthday, the daughter of Herodias trapped him with music and persuaded him to make a vow. And he gave her the head of the great prophet in a charger, after decapitating him. The scholars say, “it was better for him if he had swallowed up [have not honored] his vow.” Then, while the decapitated head of St. John flew away, his disciples buried his body (Matt. 3:.1/ Mark 6:14/ Luke 3:1/ John 1:6).

✞The head of John the Baptist flew with wings of grace after the cursed Herod beheaded him and it bowed down before the Lord at Mt. Olive, where he was. The Holy Apostles astounded by what they saw, gave salutations to the Saint’s head.

✞After this, our Lord Jesus Christ, gave authority to St. John’s head to preach and sent it forth. Thence, it spent 15 years preaching all over the world and on this day it rested in Arabia.

+++ Names of St. John the Baptist +++
1. Prophet
2. Apostle
3. Martyr
4. Righteous
5. Priest
6. Hermit/Ascetic
7. Baptist [Metmeqe Melekot]
8. Forerunner
9. Virgin
10. Bridge (that joins the Old and the New)
11. Herald (The voice that crieth)
12. Teacher and Rebuker
13. Greater from All

✞✞✞May our Lord, the Holy Savior, in remembrance of St. John the Baptist forgive us. And may He indwell in us his grace, blessing and glory.

✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 30th of Yekatit
1. St. John the Baptist (After the Great Prophet and Priest St. John the Baptist was brutally beheaded with a sword by the order of Herod, his head travelled and preached for 15 years and rested. And on this day is commemorated the day it was found in a clay vessel. And the feast is called “Terekbote Re’su” – “The Finding/Appearance of His Head.”)
2. Abba Minas the Archbishop

✞✞✞ Monthly Feasts
1. St. Mark the Apostle
2. Abba Shalusi the Honorable
3. St. Gregory the Theologian
4. St. Sophia Martyr

✞✞✞ “. . . Jesus began to say unto the multitudes concerning John . . . But what went ye out for to see? A prophet? Yea, I say unto you, and more than a prophet. . . Verily I say unto you, Among them that are born of women there hath not risen a greater than John the Baptist . . . For all the prophets and the law prophesied until John. And if ye will receive it, this is Elias, which was for to come. He that hath ears to hear, let him hear.”✞✞✞
Matt. 11:7-15

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)


Memhir Esuendale:
#Feasts of #Yekatit_30

✞✞✞On this day we commemorate the annual feast of the Great Prophet and Martyr Saint John the Baptist✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞Saint John the Baptist✞✞✞

=>It is difficult to say that there is someone whose honor was mentioned as much as the family of Zacharias in the Gospel, except our Lady. St. Luke started his Gospel with this family and the Holy Spirit inspired him to write the following. “And they were both righteous before God, walking in all the commandments and ordinances of the Lord blameless.”(Luke 1:6)

✞ Let us leave ‘before mankind’, but how transcendent is it to live blameless before God? And to this, awe is appropriate!

✞These holy husband and wife, because they were barren, most of their days/ages were spent without bearing a child. And according to the Tradition of the Church, the age of Elisabeth was 90 and Zacharias had reached 100.

✞However, the Lord who saw their patience, sent the angel of annunciation, St. Gabriel, to give them [annunciate the birth of] a great prophet, who was greater than men and about whom a prophecy was foretold (Isa. 40:3/ Mal. 3:1).

✞St. Zacharias, because he was a human and argued from joy, was made dumb. But Saint Elisabeth conceived the great man on Meskerem 26 (October 6) and concealed herself for 6 months. And on the sixth month, when the Lord of all creation was conceived (assumed flesh [human nature]), the Queen of Heaven, our Lady the Virgin Saint Mary, came to Elisabeth through the hill country. The two Saints were daughters of sisters (cousins).

✞And when the Theotokos (Mother of God) reached and saluted them, the Holy Spirit descended upon the mother and child; hence Elisabeth praised and John, while in the womb, leaped (prostrated) with joy. Then, he was born on Sene 30 (July 7) and Zacharias, his father, was able to speak when he named him “John.” 

✞When St. John was 2 years and 6 months old, because the wise men came, Herod the ‘Great’ slaughtered the children that were found in Israel. Later, the Jews told Herod about St. John. They said, “Because there is a child who had shut his father’s mouth [before he was conceived] and opened it when he was born [miraculously]. Kill him as well.”

✞Thence, when St. Elisabeth, his mother, took him and fled, soldiers killed the priest Zacharias in the middle of the Temple. And the old woman, Elisabeth, raised the child and stayed in the Desert of Zifata for 3 (5) years. And when St. John was 5(7) years old, his mother passed away in the desert. Thus, Zacharias and Simeon descended from heaven and buried her.

✞And when the child John cried, the Virgin Mary heard him from far away as she was also in exile. She then went with the Lord upon a cloud and comforted him. Thereafter, she asked the Lord, “Shall we take him?” To which our Lord answered, “Until I call him for ministry, let him stay here.” After that she blessed, consoled St. John and they departed.

✞Afterwards, St. John, in that desert, lived in asceticism wearing a raiment of camel's hair and a leathern girdle about his loins. And for 25 (23) years, while living in purity, he did not see anyone except beasts of the field and heavenly hosts. He as well did not know the tang of this rebellious world.

✞Then, when he became 30, God spoke to him from heaven. And because the prophets had prophesized about it, He said to him, “Go! Pave the way for My Son” (Isa. 40:3/Mal. 3:1). Also Zacharias, his father, had said, “And thou, child, shalt be called the prophet of the Highest: for thou shalt go before the face of the Lord to prepare his ways” about his forerunning (Luke 1:76).

✞Hence, at that time, St. John, filled with the Power of the Holy Spirit, came hurriedly to Judea from the desert. And all those that saw him feared and respected him.




††† እንኳን ለታላቁ ነቢይና ሰማዕት ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!†††

††† ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ †††

††† ቅዱስ ወንጌል ላይ ከእመቤታችን ቀጥሎ የነ ዘካርያስን ቤተሰብ ያህል ክብሩ የተገለጠለት ፍጡር ይኖራል ብሎ መናገሩ ይከብዳል:: ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን የጀመረው በዚህ ቅዱስ ቤተሰብ ነውና መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ሲል አጽፎታል::
"ዘካርያስ ካህኑና ቅድስት ኤልሳቤጥ በሰውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ" ይላቸዋል:: (ሉቃ. 1:6)

*የሰውን እንተወውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ መኖር ምን ይረቅ? ለዚህ አንክሮ (አድናቆት) ይገባል!
እሊህ ቅዱሳን ባልና ሚስት ግን መካኖች በመሆናቸው ልጅ ሳይወልዱ ዘመናቸው አልፎ ነበር:: እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ዕድሜአቸው የኤልሳቤጥ 90 የዘካርያስ ደግሞ 100 ደርሶ ነበር::

*ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ ግን በስተ እርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ: ትንቢት ለብቻው የተነገረለት (ኢሳ. 40:3, ሚል. 3:1) ታላቅ ነቢይን ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው::

*ቅዱስ ዘካርያስ ሰው ነውና ከደስታ ብዛት በመከራከሩ ድዳ ሆነ:: ቅድስቲቷ ግን መስከረም 26 ቀን ታላቁን ሰው ጸንሳ ለ6 ወራት ራሷን ሠወረች:: በ6ኛው ወር የፍጥረት ሁሉ ጌታ በተጸነሰ ጊዜ የአርያም ንግሥት ድንግል እመቤታችን ደጋ ደጋውን ወደ ኤልሳቤጥ መጣች:: ሁለቱ ቅዱሳት የእህትማማች ልጆች ናቸው::

*የአምላክ እናቱ ስትደርስና "ሰላም" ስትላቸው መንፈስ ቅዱስ በእናትና ልጅ ወርዶ ኤልሳቤጥ በምስጋና: ዮሐንስ ደግሞ ገና በማሕጸን ሳለ በደስታ ዘለለ (ሰገደ):: ከዚህ በሁዋላ ሰኔ 30 ተወልዶ: አባቱ ዘካርያስ "ዮሐንስ" ሲለው አንደበቱ ተፈትቶለታል::

*ቅዱስ ዮሐንስ ከተወለደ 2 ዓመት ከ6 ወር በሆነው ጊዜ ሰብአ ሰገል በመምጣታቸው በእሥራኤል ምድር የሚገኙ ሕጻናትን ሔሮድስ ቁዝ አስፈጀ:: ትንሽ ቆይቶም አይሁድ ለሔሮድስ ስለ ቅዱሱ ሕጻን ነገሩት:: "ሲጸነስ የአባቱን አንደበት የዘጋ: ሲወለድ ደግሞ የከፈተ 'ዮሐንስ' የሚባል ሕጻን አለና እሱንም ግደል" አሉ::

*እናቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ ይዛው ስትሸሽ ካህኑን ዘካርያስን ግን በቤተ መቅደስ መካከል ገድለውታል:: አረጋይት ኤልሳቤጥም ሕጻኑን እያሳደገች በገዳመ ዚፋታ ለ3 (5) ዓመታት ቆይታለች:: ቅዱስ ዮሐንስ 5 (7) ዓመት ሲሞላው ግን እዚያው በበርሃ እናቱ ዐረፈች:: ከሰማይ ዘካርያስና ስምዖን ወርደው ቀበሯት::

*ሕጻኑ ዮሐንስ ሲያለቅስ ድንግል ማርያም ስንት አገር አልፋ ሰማችው:: እርሷም ስደት ላይ ነበረችና:: ከጌታ ጋር በደመና ሒደው ድንግል አቅፋ አጽናናችው:: ጌታንም "እንውሰደው ይሆን?" አለችው:: ጌታችን ግን "ለአገልግሎት እስክጠራው እዚህ ይቆይ" አላት:: ባርካው: አጽናንታውም ተለያዩ::

*ቅዱስ ዮሐንስ ከዚህ በሁዋላ በዚያ ቆላ የግመል ጠጉር ለብሶ: ጠፍር ታጥቆ ተባሕትዎውን ቀጠለ:: ለ25 (23) ዓመታትም በንጽሕና ሲኖር ከምድር አራዊትና ከሰማይ መላእክት በቀር ማንንም አላየም:: ይሕችን ዐመጸኛ ዓለምም አልቀመሳትም::

*ከዚህ በሁዋላ 30 ዘመን ሲሞላው እግዚአብሔር ከሰማይ ተናገረው:: "ሒድ! የልጄን ጐዳና ጥረግ" አለው:: ነቢያት ስለዚህ ነገር ተናግረው ነበርና:: (ኢሳ. 40:3, ሚል. 3:1) አባቱ ዘካርያስም "ወአንተኒ ሕጻን ነቢየ ልዑል ትሰመይ: እስመ ተሐውር ቅድመ እግዚአብሔር ከመ ትጺሕ ፍኖቶ" (ሉቃ. 1:76) ብሎ መንገድ ጠራጊነቱን ተናግሮ ነበርና::

*ቅዱስ ዮሐንስ በዚያ ጊዜ በኃይለ መንፈስ ቅዱስ እየገሰገሰ ከበርሃ ወደ ይሁዳ መጣ:: ያዩት ሁሉ ፈሩት: አከበሩት:: ቁመቱ ቀጥ ያለ: ጽሕሙ እንደ ተፈተለ ሐር የወረደ: ጸጉሩ የቁራ ያህል የጠቆረ: መልኩ የተሟላ: ግርማው የሚያስፈራ ገዳማዊ ነውና::

*ፈጥኖም ሕዝቡን ለንስሃ ሰበከ: ለንስሃም በርካቶችን አጠመቃቸው:: በዚህ አገልግሎት ለ6 ወራት ቆይቶ ጌታችን ወደ እርሱ ዘንድ መጣ:: ዮሐንስ ሰማይን ከነግሱ: ምድርን ከነልብሱ የያዘ ፈጣሪ "አጥምቀኝ" ብሎ ሲመጣ ደነገጠ:: የሚገባበትም ጠፋው::

*"እንቢ ጌታየ! አንተ አጥምቀኝ" አለው:: ጌታ ግን "ፈቅጄልሃለሁ" አለው: አጠመቀው:: በዚህ ምክንያት ይሔው እስከ ዛሬም "መጥምቀ መለኮት" ሲባል ይኖራል:: ቅዱስ ዮሐንስ በመጨረሻ ሔሮድስን ገሰጸው:: ንጉሡም ተቀይሞ ለ7 ቀናት አሠረው::

*ልደቱን ባከበረ ጊዜ ወለተ ሔሮድያዳ በዘፈን አጥምዳ አስማለችው:: እርሱም የታላቁን ነቢይ ራስ አስቆርጦ በወጪት አድርጐ ሰጣት:: አበው "እምሔሶ ለሔሮድስ ይብላዕ መሐላሁ - ሔሮድስ መሐላውን በበላ በተሻለው ነበር" ይላሉ:: የቅዱስ ዮሐንስ ራሱ በርራ ስትሔድ አካሉን ግን ደቀ መዛሙርቱ ቀብረውታል:: (ማቴ. 3:1, ማር. 6:14, ሉቃ. 3:1, ዮሐ. 1:6)*ርጉም ሔሮድስ አንገቱን ካስቆረጠው በሁዋላ የመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ራሱ የጸጋ ክንፍ ተሰጥቷት ጌታችን ወዳለበት ደብረ ዘይት ሔዳ በፊቱ ሰገደች:: ቅዱሳን ሐዋርያት በአዩት ነገር ተገርመው ራሱን እጅ ነሷት::

*ከዚሕ በሁዋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱስ ዮሐንስ ራስ የማስተማር ስልጣን ሰጥቶ አሰናበታት:: በመላው ዓለም ለ15 ዓመታት ስትሰብክ ኑራ ዓረቢያ ውስጥ ዓርፋለች::

††† አስማተ-ዮሐንስ መጥምቅ (የመጥምቁ ዮሐንስ ስሞች)
1.ነቢይ
2.ሐዋርያ
3.ሰማዕት
4.ጻድቅ
5.ካሕን
6.ባሕታዊ/ገዳማዊ
7.መጥምቀ መለኮት
8.ጸያሔ ፍኖት (መንገድ ጠራጊ)
9.ድንግል
10.ተንከተም (የብሉይና የሐዲስ መገናኛ ድልድይ)
11.ቃለ አዋዲ (አዋጅ ነጋሪ)
12.መምሕር ወመገሥጽ
13.ዘየዐቢ እምኩሉ (ከሁሉ የሚበልጥ)

††† ጌታችን መድኃኔ ዓለም መጥምቁ ዮሐንስን አስቦ ይቅር ይበለን:: ጸጋውን: በረከቱንና ክብሩንም ያሳድርብን::

††† የካቲት 30 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት
(ታላቁ ነቢይና ካህን መጥምቁ ዮሐንስ ሔሮድስ በግፍ አንገቱን ካስቆረጠው በሁዋላ ቅድስት ራሱ ለ15 ዓመታት ዙራ አስተምራ አርፋለች:: በዚህ ዕለትም በልሑክት (በሸክላ ዕቃ) የተገኘችበት በዓል ይከበራል:: በዓሉም "ተረክቦተ ርዕሱ" በመባል ይታወቃል:: )
2.አባ ሚናስ ሊቀ ዻዻሳት

††† ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ማርቆስ ዘአንበሳ (ሐዋርያ)
2.አባ ሣሉሲ ክቡር
3.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት
4.ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት

††† "ጌታ ኢየሱስ ለሕዝቡ ስለ ዮሐንስ ሊናገር ጀመረ . . . ምን ልታዩ ወጣችሁ? ነቢይን? አዎን እላችሁአለሁ ከነቢይም የሚበልጠውን . . . እውነት እላቹሃለሁ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሳም . . . ነቢያት ሁሉና ሕጉ እስከ ዮሐንስ ድረስ ትንቢት ተናገሩ:: ልትቀበሉትስ ብትወዱ ይመጣ ዘንድ ያለው ኤልያስ ይሕ ነው::
የሚሰማ ጀሮ ያለው ይስማ::" †††
(ማቴ. 11:7-15)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††


✝እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ የካቲት ቡሩክ፥ አመ ፳ወ፱

✝ጾም ዐቢይ ዘመድኅን ክርስቶስ (አምላክነ)
✝ወተዝካረ በዓሉ ለክርስቶስ እግዚእነ (ስቡሕ ወውዱስ)

✞ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦

✿ፍቅርተ ክርስቶስ/እማ ምዑዝ (ጻድቅት፥ ወሰማዕት)
✿ደናግል ንጹሐት (ማኅበራኒሃ)
❀ዘርዓ ክርስቶስ ሰማዕት (ምታ)
❀ገብርኤል መነኮስ
❀ዘመለኮት ጳጳስ
✿ቢላካርዮስ አረጋዊ (ጳጳስ ወሰማዕት)

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://t.me/zikirekdusn




✞”Be joyous, for I have prepared for you an everlasting Kingdom.” And St. Fikerte Kirstos pleaded Him so that He would make a covenant with her. Hence, He vowed, “Let it all be according to your word. As My name is added to yours (notice Kirstos), anyone who gives alms to your church, or is sent for the church/ for service/, or is buried in its compound, or comes and gives salutations to your church, I will forgive for 12 generations. I gave this pledge of mercy to you.”

✞”And may my blessing dwell in his/her house, indwell in his/her children and upon his/her money/wealth. And where your hagiography is placed demons will not come near. And when they invoke your name during harvest, may it be blessed. And whoever pleads through your name, may he/she be of good health.”

✞”He/she who truly invokes your name is honored. And he/she that writes your accounts or have it written or reads or translates or listens to it in faith or gives in your name a cup of cold water with an upright faith and without any doubt, his/her sins will be forgiven. For your toil and for your virtue I have given you 7 crowns and all these promises. And if I will not forgive him/her, I will not let a person set foot into your monastery.” And after saying these things to her, He ascended to heaven.

✞And the next day, she fell a bit ill and called the virgins and the monks and told them that her day of departure has arrived. And she said farewell to them after appointing one of them to be the Abbot of the monastery. And as she prayed the Psalm of David on Yekatit 29 (March 8), the day of the monthly commemoration of the Lord, she fell asleep (her soul departed from her body).

✞Our Lord came with His mother and the saints and took her soul to paradise. And the saints and the angels ululating accompanied her into paradise. And light was seen shining upon the tomb of St. Fikerte Kirstos for 40 days.

✞Her feasts are celebrated on Tahisas 16 (December 25) the day of the consecration of her church and on Yekatit 29 (March 8) the day of her departure in the Coenobitic Monastery of Eme Me’uz Kidane Miheret and Fikerte Kirstos which is found in the diocese of Northern Wollo, district of Meket, locality of Tiba Maryam in a place called Mintamer which was established in the 17th century by the her, the Ethiopian martyr and righteous mother St. Fikerte Kirstos.

✞✞✞ May the God of the Saint grant us from her grace and blessing.

✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 29th of Yekatit
1. St. Fikerte Kirstos the Ethiopian mother
2. St. Zera Kirstos (Her husband, righteous and martyr)
3. The holy child (The son of Fikerte Kirstos – Cyriacus the Second)
4. St. Polycarp, Bishop of Smyrna (Elder, author, righteous and martyr)

✞✞✞ Monthly Feasts
1. The Birth of our Lord and God Jesus Christ
2. St. Arsema (Arbsima/Repsima/Hripsime) the Virgin
3. St. Peter the Seal of the Martyrs
4. St. Mark of Tormak

✞✞✞“Many daughters have done virtuously, but thou excellest them all. Favour is deceitful, and beauty is vain: but a woman that feareth the Lord, she shall be praised. Give her of the fruit of her hands; and let her own works praise her in the gates.”✞✞✞
Prov. 31:29-31

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)


✞And after allocating for them some servants, she went to Jerusalem and dwelt there for 7 years. And when she went to hold the feast of our Lady in Egypt, she entered and prayed in one church on her way and there our Lady appeared to her from her icon and told her that her place was in Ethiopia and instructed her by pointing, “Go to Ethiopia”.

✞Being led by a pillar of light and St. Michael, she reached to the now monastery which she is famous for, the Cenobitic Monastery of Eme Me’uz Kidane Miheret and Fikerte Kirstos.

✞And when she reached the place, because the greenery of the area was so beautiful she exclaimed, “How beautiful is this place?!” (‘Min-tamer’ = how beautiful) And it to this day is called as Min-tamer.

✞And there at Mintamer, where she rested with her servants, the pillar of light that had led her reached to the heavens. And because the angel told her, “This is your place”, she settled there.

✞And when the landlord of the area instructed her, “Leave my place”, she replied, “This is my place which God has given me”. Hence, he went to Gonder to charge her, where Emperor Fasil had taken up the throne as Susenyos I had died. And when he asked for a ruling, because the Emperor new her by fame, gave a verdict saying, “If a church has not been built on it, let her vacate it for you and if it has, then you shall be given another land.”

✞And while he returned, St. Michael reached to her first and told her, “Build a church fast, as a verdict of such matter has been delivered.” And so after the morning prayers of Tahisas 14 (December 23) she built in a day an enclosed church whose walls were made of the plants Sensel (Adhatoda schimperiana) and Simiza (Justicia schimperiana), and Cissampelos (Cissampelos mucronata) which was used as a support. And on Tahisas 16 (December 25) on Sunday, she had the Ark-tablet of Kidane Miheret (The Covenant of Mercy of St. Mary – The Queen-ship of Mary) placed in it and the Divine Liturgy was celebrated.

✞And when the Liturgy was concluded, our Lord on His throne and with His mother, our Lady, appeared before them all. And when He came down from His throne and blessed the place, the church made of the plant Simiza bowed down to its Creator on all four sides.

✞The earth shook. And St. Fikerte Kirstos asked, “Did You come to abolish us? And are You going to demolish my church?” To which the Lord answered, “This, your church that is made of Sensel will not be destroyed until My second coming. It will be preserved and not even be renewed. And no apostate or heretic will set foot inside it until the end of the world. And all who partake of the Eucharist in it, their sins will be forgiven and My mercy and blessing will always be with them.” And then He disappeared from those that had gathered.

✞Afterwards, hearing her accounts, many monks and nuns came from different parts to St. Fikerte Kirstos. And after St. Fikerte Kirstos had taught, advised and showed them with example how they should finish their struggles by the Power of God and they had lived for many years, she separated the monks from the nuns so that they will not be afflicted by demons [of lust].

✞And through the prayers of St. Fikerte Kirstos an angel of the Lord used to always keep them from seeing one another. And when the time of her departure came near, two angels came and took her to Debre Nebat (Realm of the Living) with a chariot of light, there, they gave her from the Holy Eucharist and returned her to her abode.

✞And the angel said to her, “Your time to depart from this world, from suffering, fatigue, nakedness, hunger, thirst, strife and weeping has come.” And on Yekatit 27 (March 6) she stretched her hands while she prayed facing East in the church and light together with a pleasant smell filled the place.

✞Then, the Lord with a multitude of His angels and saints came to her. And our mother, St. Fikerte Kirstos, bowed down, knelt and lamented much. Raising her from where she fell, our Lord said to her, “I have not come here to do away with you, rather I am here to glorify you.”


✞After all those years passed, by the will of God, the Archangel St. Michael appeared and told both of them that they would have a son. However, both said, “How could this be?” then fasted, and prayed diligently for 40 days. Thereafter, the angel appeared to them again and said, “This is the will of God and both of you will not lose your purity.”

✞Hence, they bore a son. And when he became 7 years old St. Michael took him up and showed him paradise for 7 days and when he brought him back to earth, the child pleaded the angel saying, “I beg you for the sake of the God of my mother and father, do not return me to this wicked world.” Thence, St. Michael asked God and placed the child in the Realm of the Blessed as the leader of the children there. And he was named Cyriacus the Second.

✞Sts. Fikerte Kirstos and Zera Kirstos lived preserved in holiness and purity after they had their son. Later on, they witnessed about their Tewahedo (Miaphysite) Faith without fear by going to Emperor Susenyos I , the Emperor of their time, and before him when they heard that he had changed his faith and, “Because he had accepted Catholicism which confesses Dyophysitism (two natures in Christ), he is killing Christians.”

✞Hence, the Emperor put them under much affliction. And they converted back many of the followers and soldiers of the Monarch by enduring the trials. Around 60,000 Christians received martyrdom.

✞And the Emperor had the Saints beheaded because they had become nuances to him by converting many back to the Upright Faith. And when they were beheaded, blood and milk came forth from both their necks.

✞In those days, Abba Amde Selassie of Mahibere Selassie, Abba Mereawi of Goregor Maryam, Amma Wetet of Messi Kidane Mehiret were among the Christians that received trials and martyrdom with the previously mentioned 60,000 Christians.

✞Nonetheless, God raised back St. Fikerte Kirstos by reconnecting her severed head with her body as if waking up a sleeping person. Then, she received the rites of monasticism and was made a nun by Abune Markos and served in the Monastery of Waldiba.

✞Then, with more than 500 monks and nuns that followed her, she went to Rama Kidane Miheret Coenobitic Monastery which was established by the Saint Abba Guba, one of the Nine Saints of the 7th century, which had been abandoned and was found in northern Wollo, the district of Qobo. There, she re-established the monastery, made rites for the men and women separately, demarcated the place, placed around 500 monks and nuns, and started a journey to Jerusalem.

✞On her way, the Saint reached a place where the inhabitants ate humans and there the people took out her eyes and that of 60 of her followers and placed them in a dark room for 4 months. And after four months, when they took them out to feast upon them, the inhabitants found them shining like the sun and asked the Saint, “O woman, what are you?”

✞Hence, she told them that they were Christians and that they should not eat human beings which are the temples of the Holy Trinity. Then, the people asked her, “What should we eat?” And as she had made her servants carry some seeds from Rama Kidane Miheret, she took a bit of the wheat and sowed it. It grew, was harvested, was dried, grounded and it was ready for consumption miraculously in a day.

✞Then, she tasted and gave it to the people that ate men and they had it happily as it tasted like honey and milk. After which, she taught them to work in such manner and eat, then she made them receive baptism and founded for them more than 6 churches.


#Feasts of #Yekatit_29

✞✞✞On this day we commemorate the departure of the Ethiopian Female Martyr Saint Fikerte Kirstos✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞Eme Me’uz (Fragrant Mother) Saint Fikerte Kirstos ✞✞✞
=>The Ethiopian Martyr and Righteous St. Fikerte Kirstos (Eme Me’uz) is one of the mothers who have received a covenant from God and are commemorated on the 29th of each month in the Church. Who is Fikerte Kirstos (Eme Me’uz)? What covenant did she receive? Let us see her strife a bit.

✞”. . . he that receiveth a righteous man in the name of a righteous man shall receive a righteous man's reward.” Matt. 10:41✞

=>In the diocese of Northern Wollo, district of Meket, locality of Tiba Maryam in a place called Mintamer there is a coenobitic monastery, the Monastery of Eme Me’uz Kidane Miheret and Fikerte Kirstos, which was established in the 17th century by the Ethiopian martyr and righteous mother St. Fikerte Kirstos.

✞You will find this great and wondrous monastery, the Monastery of Eme Me’uz Kidane Miheret and Fikerte Kirstos, which was built in a single day by Saint Fikerte Kirstos and that bowed on all its four corners for the Lord and which was established more than 370 years ago after you have traveled 665kms from Addis Ababa through Dessie and stopping at the town called Gerager (Filakit) and journeying on foot for 2hrs and 30 minutes.

✞The founder of this monastery, the Ethiopian martyr and righteous woman, St. Fikerte Kirstos was conceived on Miyazia 04 (April 12) and was born on the day of the commemoration of the Nativity of the Lord, Tahisas 29 (January 7) in Southern Gonder, the district of Anbesa Meda at a place called Keteta Maryam, which is adjacent to the Monastery of Abune Hara Dingel.

✞The Saint’s father was called Laba and her mother Wengelawit and they were compassionate people that loved God and kept His commandments. However, as they were barren and did not have any children, they diligently prayed to God and He gave them a daughter like St. Fikerte Kirstos who is a blessing through her prayers for the country and her kinsfolk.

✞When the Saint was 80 days old, they took her to be baptized and when she was given the Body of the Lord, she miraculously praised the Lord saying, “Glory be to You my God Who have given me Your life giving Holy Body and Glorious Blood.” Her baptismal name was Maryam Tsedale and her formal one was Muzit. Fikerte Kirstos is her monastic name.

✞Our mother, St. Fikerte Kirstos, grew up learning the Scriptures from a father named Abba Daniel. And when she was old enough, her parents wanted to give her hand in marriage and wedded her to Zera Kirstos a man from a kind family.

✞During the night, when the newlyweds entered their chamber, St. Fikerte Kirstos said to Zera Kirstos, “My brother! I did this so that I would fulfill the wishes of my parents and not because I want to be a wife. Rather my wish is to be a bride of God.” And the Righteous Zera Kirstos who was filled with the grace of God replied, “I also did this to honor the wishes of my mother and father but I do not have any carnal desires.”

✞Then, they lived before their families and the countrymen as husband and wife for 40 years but kept their purity and were virgins.


አድዋ (ኃይለ ዐቢያተ).m4a


"" ታላቅ ሥራን ሠርቶልኛል! "" (ሉቃ. ፩:፵፱)

❖የአድዋ ድል በዓል (መታሰቢያ)

(የካቲት 23 - 2017)






+ከዚያም የተወሰኑ አገልጋዮችን አስቀምጣላቸው ወደ
ኢየሩሳሌም በመሄድ ለ7 ዓመታት በአየሩሳሌም ከኖረች
በኋላ የእመቤታችን በዓል ለማክበር ወደ ግብፅ በመሄድ
ላይ ሳለች በመንገድ አንድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ገብታ
ስትፀልይ እመቤታችን በስዕሏ ላይ ተገልጣ: ቦታዋ
በኢትዮጵያ መሆኑን ነግራ: እጇን ዘርግታ "ወደ ኢትዮጵያ
ሂጂ" ብላ ነገረቻት::

+በኋላ በብርሃን አምድና በቅዱስ ሚካኤል እየተመራች
አሁን ወደ ምትታወቅበትና የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ ወደ
ተገለፀበት እመ ምዑዝ ኪዳነ ምህረት ቅድስት ፍቅርተ
ክርስቶስ አንድነት ገዳም ደርሳለች፡፡
+በቦታው ስትደርስ የቦታው ልምላሜ የሚያስደስት ነበርና
"ይህች ቦታ ምን ታምር!" ብላለች፡፡ ቦታውም እስከ አሁን
ድረስ ምንታምር በመባል ይጠራል፡፡

+ምንታምር ላይ ከአገልጋዮቿ ጋር በመሆን አርፋ ሳለ
ከኢየሩሳሌም መርቶ ያመጣት የብርሃን አምድ በዚያ ቦታ
ላይ በስፋት ረቦ (ከምድር እስከ ሰማ ተተክሎ) ብታየው:
መልአኩም "ቦታሽ ይሄ ነው" ብሎ ቢነግራት በዚያው
ተቀምጣለች፡፡

+የቦታው ባለ አባት "ይህን ቦታ ልቀቂ" ቢሎ ቢጠይቃት
"እግዚአብሔር የሰጠኝ ቦታዬ ነው" ብላዋለች፡፡ እርሱም
ለክስ ወደ ጎንደር በመሄድ አፄ ሱስንዮስ አርፈው አፄ
ፋሲል ነግሰው ነበርና እሳቸውን ፍርድ ቢጠይቃቸው በዝና
ያውቋት ነበርና "ቤተ ክርስቲያን ካልተሰራ ትልቀቅልህ:
ከተሠራ ግን ሌላ ቦታ ይሰጥሃል" የሚል ፍርድ አስፈርዶ
ነበር::

+ሲመለስ ቅዱስ ሚካኤል ቀድሞ "ቶሎ ቤተ ክርስቲያን
ስሪ እንዲህ የሚል ፍርድ ተፈርዷል ብሎ ነግሯት ‹‹ታህሳስ
14 ቀን ከነግህ ፀሎት በኋላ በሰንሰልና በስሚዛ
ግድግዳዋን: በአይጥ ሀረግ ማገር አድርጋ: የግድግዳ
ቤተ መቅደስ በዕለተ አርብ: በአንድ ቀን ሰርታ ታህሳስ 16
ቀን እሁድ ታቦተ ኪዳነ ምህረትን አስገብታ ቅዳሴ
አስቀድሳለች::››

+ቅዳሴውም ከተፈፀመ በኋላ ጌታችን ከቅዱስ መንበሩ
ላይ እንዳለ ሆኖ ከእናቱ ከእመቤታችን ጋራ ታያቸው፡፡
ከመንበሩ ወርዶም ይህን ቦታ በባረከው ጊዜ የስሚዛው
ቤተ መቅደስ በአራቱም አቅጣጫ ለፈጣሪው ሰገደ፡፡

+የመሬት መናወጥም ሆነ:: ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስም
"ልታጠፋን መጣህን? ቤተ ክርሰቲያኔንስ ልታፈርሳት
ነው?" ብላ ብትጠይቀው "ይህ የሰንሰል ቤተ መቅደስሽ
ዳግም እስከምመጣ ድረስ ሳይፈርስ: ሳይታደስ ፀንቶ
ይኖራል፣ በውስጡም እስከ ዓለም ፍፃሜ ድረስ
የክሀድያንና ፣ መናፍቃን እግር አይገባበትም፣ በውስጧ
ቁርባንን የተቀበሉ ሁለ ኃጢያታቸው ይሰረይላቸዋል፣
ዘወትር ምህረቴ በረከቴ ከእነርሱ ጋር ይኖራል" በማለት
ተናግሮ ተሰወራቸው፡፡

+ከዚያም በኋላ መነኮሳትና መነኮሳይያት የቅድስት ፍቅርተ
ክርስቶስን የትሩፋት ዜናዋን ሰምተው ከየአቅጣጫው
ተሰበሰቡ፡፡ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስም በአምላክ ሀይል
ተጋድሎአቸውን ይፈፅሙ ዘንድ ታስተምራቸው ፣
ትመክራቸው፣ በተግባርም እያሳየቻቸው ለብዙ ዘመናት
ከኖሩ በኋላ በገዳሙ ላይ የአጋንንት ፆር እንዳይነሳ
ወንዶቹን ለብቻ ሴቶቹን ለብቻ አደረገች፡፡

+ዘወትርም እንዳይተያዩ የእግዚአብሔር መልዐክ
በቅድስተ ፍቅርተ ክርሰቶስ ፀሎት ይጠብቃቸው ነበር፡፡
ከዚህ በኋላ እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ከዚህ
ኃላፊ ዓለም መለየቷ በቀረበ ጊዜ ሁለት መላዕክት ወደ
እርሷ መጥተው በብርሃን ሰረገላ ጭነው ወደ ደብረ ነባት
(ወደ ብሔረ- ህያዋን) ወስደው በዚያ ቅዱስ ቁርባንን
አቀብለው ወደ ቦታዎ መለሷት፡፡

+መልዐኩም "ከጻማ: ከድካም: ከመታረዝ: ከረሐብ
ከጥም: ከመትጋት: ከእንባ: ከዚህ ዓለም የምትለይበት
ጊዜ እነሆ ደረሰ" አላት፡፡ የካቲት 27 ቀንም ወደ ምስራቅ
እጇን ዘርግታ ቆማ ስትጸልይ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ
ከደስታ ብርሀን ጋር ያማረ ሽታ መላ::

+ጌታችን ከአዕላፋት መላዕክትና ቅዱሳን ጋር ወደ እርሷ
መጣ፡፡ እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስም ሰገደች፡
ተንበረከከች: እጅግም አለቀሰች፡፡ ከወደቀችበት ቦታ
አንስቶ ‹‹ላጠፋሽ አልመጣሁም ወዳጄ ላከብርሽ ነው
እንጂ›› አላት፡፡

+"የዘለአለም መንግስት አዘጋጅቼልሻለሁና ደስ ይበልሽ"፡፡
ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስም ቃል ኪዳን እንዲገባላት
ተማጸነችው:: ጌታችንም ‹‹ሁሉም እንደ ቃልሽ ይሁንልሽ::
በስምሽ ስሜ ተጨምሯልና ለቤተ ክርስቲያንሽ መባ
የሰጠ፣ የተላከ ፣የተቀበረ፣ ቤተ መቅደስሽ መጥቶ
የተሳለመ ፣ እስከ 12 ትውልድ የምህረት ቃል ኪዳን
ሰጠሁሽ::

+በረከቴም በቤቱና በልጆቹ በገንዘቡም ላይ ይደር::
የገድልሽ መጽሐፍ ባለበት አጋንንት (ሰይጣናት)
አይቀርቡም:: በአዝመራ ስምሽን በጠሩት ጊዜ የለመለመ
ይሁን:: በጸሎትሽ የተማጸነ ሁሉ ባለጤና ይሁን::

+ስምሽን በእውነት የሚጠራ የከበረ ነው፡፡ ያለመጠራጠር
በቀናች ሐይማኖት የገድልሽን መጽሐፍ የጻፈ: ያጻፈ:
ያነበበ: የተረጎመ በሐይማኖት የሰማ: እስከ ቀዝቃዛ ውሃ
ድረስ የሰጠ ኃጢያቱ ይሰረይለታል::
ስለ ድካምሽ ስለ ትሩፋትሽ 7 አክሊሎችን እና ይህን ሁሉ
ቃል ኪዳን ሰጠሁሽ፡፡ ላልምረው ቦታሽን
አላስረግጠውም›› ብሏት ወደ ሰማይ አረገ፡፡

+በማግስቱ ትንሽ ህመም ታመመች ደናግል መነኮሳትን
ጠርታ የእረፍት ቀኗ መድረሱን ነገረቻቸው:: ከመካከላቸው
አንዷን ለገዳሙ አስተዳዳሪነት መርጣ በፍቅር ስም
ተሰናበተቻቸው፡፡ የዳዊት መዝሙርንም ስትጸልይ የካቲት
29 ቀን እሁድ አጥቢያ ጠዋት በጌታ በዓል አንቀላፋች
(ነፍሷ ከስጋዋ ተለየች)፡፡

+ጌታችንም ከእናቱ: ከቅዱሳኑ ጋር መጥቶ ነፍሷን
ተቀብሎ ወደ ዘለዓለም ገነት ወሰዳት፡፡ ቅዱሳንም
ከመላእክት ጋር እልል እያሉ እያመሰገኑ ወደ ዘለዓለም
ቦታ ገነት አስገቧት፡፡ ከቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ መቃብር
ላይ 40 ቀናት ብርሃን ሲበራበት ታይቷል፡፡

+በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት: በመቂት ወረዳ ጥባ
ማርያም ቀበሌ ውስጥ ምን ታምር በመትባል ቦታ ላይ
በ16ኛው መቶ ክ/ዘመን በኢትዮጵያዊቷ ሰማዕትና ጻድቅ
ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ የተመሰረተቸው እመ ምዑዝ
ኪዳነ ምህት ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ አንድት ገዳምም
በዓላቶቿ የሚከበሩት ታህሳስ 16 የቅዳሴ ቤቷ እንዲሁም
የካቲት 29 ቀን በዓለ እረፍቷ ይከበራል፡፡

††† ከቅድስት እናታችን በረከት አምላክ አይለየን::

††† የካቲት 29 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ኢትዮዽያዊት
2.ቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ (ጻድቅና ሰማዕት)
3.ቅዱሱ ሕፃን (የፍቅርተ ክርስቶስ ልጅ)
4.ቅዱስ ቢላካርዮስ ዘሃገረ አርሞኒ (አረጋዊ: ደራሲ: ጻድቅና ሰማዕት)

††† ወርኀዊ በዓላት
1.የፈጣሪያችንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት
2.ቅድስት አርሴማ ድንግል
3.ቅዱስ ዼጥሮስ ተፍጻሜተ ሰማዕት
4.ቅዱስ ማርቆስ ዘቶርማቅ

††† "መልካም ያደረጉ ብዙ ሴቶች አሉ:: አንቺ ግን ከሁሉ ትበልጫለሽ::
ውበት ሐሰት ነው:: ደም ግባትም ከንቱ ነው::
እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርስዋ ትመሰገናለች:: ከእጇ ፍሬ ስጧት:: ሥራዎቿም በሸንጐ ያመስግኗት::" †††
(ምሳሌ. 31:29)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††


†✝† እንኳን ለኢትዮዽያዊቷ እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †✝†

†✝† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †✝†

†✝† እመ ምዑዝ (እም ምዑዝ) †✝†

††† ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ሐዋርያዊት: ጻድቅትና ሰማዕት ናት::
ይህስ እንደምን ነው ቢሉ:-
=>ወር በገባ በ29 በቤተክርስቲያናችን ታስበው
ከሚውሉት እግዚአብሔር አምላክ ቃል ኪዳን ከገባላቸው
(ከሰጣቸው) እናቶች ኢትዮጵያዊቷ ሰማዕትና ጻድቅት
ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ (እመ ምዑዝ) ትገኛለች::
ፍቅርተ ክርስቶስ (እመ ምዑዝ) ማን ናት? ምን ቃል ኪዳን
ተሰጣት? ያደረገችውን ተጋድሎ በጥቂቱ እንመልከት:-
✞✞ ጻድቅን በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ
ይወስዳል፡፡ (ማቴ. 10፡40) ✞✞

=>በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት በመቂት ወረዳ ጥባ
ማርያም ቀበሌ ውስጥ ምን ታምር በመትባል ቦታ ላይ
በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በኢትዮጵያዊቷ ሰማዕትና
ጻድቅ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ የተመሰረተቸው እመ
ምዑዝ ኪዳነ ምህት ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ አንድት
ገዳም ትገኛለች፡፡

+ይህች ገዳም ከአዲስ አበባ በደሴ ወደ ጎንደር
በሚወስደው መንገድ 665 ኪሎ ሜትር ከተጓዙ በኋላ
ገራገር (ፍላቂት) ከምትባለው ከተማ በመውረድ በእግር
2፡30 እንደተጓዙ ከ370 ዓመት ባለይ ያስቆጠረችውን
እመ ምዑዝ ኪዳነምህት ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ በአንድ
ቀን የሠራቻትና ለጌታ በአራቱም አቅጣጫ የሰገደችውን
ታላቅና ድንቅ ቤተመቅደስ ያገኛሉ፡፡

+የዚህች ታላቅ ገዳም መስራች ኢትጵያዊት ሰማዕትና
ጻድቅ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ በደቡብ ጎንደር ደራ ፎገራ
አንበሳሜ ወረዳ ልዩ ስሙ አቡነ ሐራ ገዳም አዋሳኝ ከተታ
ማርያም ተብሎ በሚጠራ ቦታ በሚያዚያ 4 ቀን ተፀንሳ
ታህሳስ 29 በጌታ ልደት ቀን ተወለደች፡፡

+አባቷ ላባ እናትዋ ወንጌላዊት የተባሉ እግዚዘብሔርን
የሚወዱ ትዕዛዙን የሚከብሩ ደጋግ ሰዎች ነበሩ፡፡
መሀን ሆነው ልጅ ባመውለዳቸው እያዘኑ ተግተው ወደ
እግዚአብሔር በመፀለያቸው ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስን
የመሰለች ልጅ: በፀሎትዋ ለሀገር ለወገን የምትበቃ
ሰጥቷቸዋል፡፡

+ከዚያም 80 ሲሆናት ለልጅነት ጥምቀት ወደ ቤተ
መቅደስ በወሰዷት ጊዜ ከጥምቀት በኋላ ስጋ አምላክ
ስትቀበል (ስትቆርብ) "ሕይወት የሆነውን ቅዱስ ስጋህን
ክቡር ደምህን የሰጠኸኝ አምላኬ ክብር ምስጋና ይግባህ"
ብላ አመስግናለች፡፡ ስመ ክርስትናዋ ማርያም ፀዳለ
ሲሆን የአለም ስሟ 'ሙዚት' ነው፡፡ ፍቅርተ ክርስቶስ
የምንኩስና (የቆብ) ስሟ ነው፡፡

+እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ አባ ዳንኤል ከሚባል
አባት መፅሐፍን እየተማረች ካደገች በኋላ ለአቅመ ሄዋን
ስትደርስ እናትና አባቷ ሊድሯት በመፈለጋቸው ዘርዓ
ክርስቶስ ለሚባል ከደጋግ ሰዎች ወገን ለሆነ ሰው
አጋቧት፡፡

+ማታ እንደ ሙሽሮች ደምብ ወደ ጫጉላ ቤት ሲገቡ
ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ዘርዓ ክርስቶስን "ወንድሜ ሆይ!
እኔ የእናት አባቴን ፍቃድ ለመፈፀም ነው እንጂ ስጋዊ
ሙሽራ መሆን አልፈልግም ፡፡ ፍላጎቴ የእግዚአብሔር
ሙሽራ መሆን ነው" በማለት ብታማክረው ቅዱስ ዘርዓ
ክርስቶስም ፀጋ እግዚአብሔር የበዛለት ሰው ነበርና "እኔም
እናት አባቴን ላክበር ፈቃዳቸውን ለመፈፀም ነው እንጂ
የስጋ ፈቃድ የለኝም በማለት ተነጋገሩ::

+በኋላ በአንድ ቤት ውስጥ ለቤተሰቦቻቸው: ለአገሬው
እንደ ባልና ሚስት ግን በንፅህና ለ40 ዓመት ሁለቱም
በድንግልና ኖረዋል፡፡

+ከዚያም በኋላ በእግዚአብሔር ፈቃድ ቅዱስ ሚካኤል
መጥቶ ወንድ ልጅ እንደሚወልዱ ቢግራቸውም ሁለቱም
"ይህስ አይሆንም" ብለው ለ40 ቀን በጾም: ፀሎት:
በትጋት ጸልየዋል፡፡ መልአኩ ተገልጦ "ይህ የእግዚአብሔር
ፈቃድ ነው ሁለታችሁም ድንግልናችሁ አይፈርስም ብሎ
ነግሮአቸዋል፡፡

+ከዚያም ወንድ ልጅ ወልደዋል:: ህፃኑ በተወለደ በ7
ዓመቱ በቅዱስ ሚካኤል እቅፍ ገነትን ለ7 ቀናት ከጎበኛት
በኋላ ወደ ምድር ሲመልሰው "በእናት አባቴ አምላክ
ይዤሃለሁ ወደዚች ወደ ከፋች ዓለም አትመልሰኝ" ብሎ
ቢለምነው ቅዱስ ሚካኤልም ከአምላክ ጠይቆ በብሔረ
ህያዋን የህፃናት አለቃ ተብሎ እንዲቀመጥ አድርጎታል፡፡
ስሙም ዳግማዊ ቂርቆስ ተብሏል፡፡

+ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶና ቅዱስ ዘርዓ ክርስቶስም ልጅ
ከወለዱ በኋላ እንደ ቀደሞው በቅድስና: በንፀህና ፀንተው
ኑረዋል፡፡ በዘመናቸው በኢትዮጵያ ነግሶ የነበረው አፄ
ሱስንዮስ ሃይማኖቱን ለውጦ 'ሁለት ባህርይ የሚሉ
ካቶሊኮችን በመቀበሉ ክርስቲያኖችን እየገደለ ነው' የሚል
ወሬ ሰምተው ወደ ንጉሱ በመሄድ ሳይፈሩ ስለ ተዋህዶ
ሃማኖታቸው በንጉሱ ፊት መስክረዋል፡፡

+ንጉሱም በጣም የበዛ መከራን አድርሶባቸዋል፡፡ መከራ
በበዛ ቁጥር እነርሱም እየፀኑ ተከታዮቻቸውንና የንጉሱን
ሠራዎቶች ሳይቀር አሳመኑ:: 60,000 ክርስቲያኖችም
ሰማዕትነትን ተቀብለዋል፡፡

+ንጉሱም በጣም የበዛ መከራ አድርሶባቸዋል፡፡ መከራ
በበዛ ቁጥር እነርሱም እየጸኑ ተከታዮቻቸውንና የንጉሱን
ሰራዊቶች እያሳመኑ ቢያስቸግሩ በሰማዕትነት አንገታቸውን
አስቆርቷቸዋል፡፡ አንገታቸውም ሲቆረጥ ከሁለቱም ደም
ውሃ ወተት ፈሷዋል፡፡

+በዚያን ዘመን ከእነ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ጋር
ሰማዕትነት ከተቀበሉት ውስጥ የማህበረ ስላሴው ጻድቁ
አምደ ስላሴ: የጎረጉር ማርያም አባ መርአዊ: የመሲ
ኪዳነ ምህረት እመ ወተት እና ከ60 ሺ በላይ ክርስቲያኖች
ሰማዕትነት ተቀብለዋል፡፡

+ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ አንገቷ ከተቆረጠና ሰማእትነት
ከተቀበለች በኋላ ወደ ምድር መልሶ አንገቷን ከቀሪው
የሰውነቷ ክፍል ጋር አዋህዶ ከአንቅልፍ አንደሚነቃ ሰው
ቀስቅሶ አስነስቷቷል፡፡
ከዚያም ከአቡነ ማርቆስ ስርዓተ ምንኩስናን በመቀበል
ዋልድባ ገዳም ለ4 ዓመት አገልግላለች፡፡

+ከዚህም ከ500 የሚበልጡ ተከታዮችዋን መነኮሳትን
አስከትላ በሰሜን ወሎ ቆቦ ወረዳ ወደምትገኘውና በፃድቁ
በአባ ጉባ ተመስርታ ጠፍታ ወደ ነበረችው ራማ ኪደና
ምህረት አንድነት ገዳም በመሄድ ገዳሟን አቅንታ: የወንድ
የሴት ብላ ስርዓት ሰርታ: ገዳሟን አስተካክላ: 500
የሚሆኑ አገልጋች መነኮሳትን አኑራ ወደ ኢየሩሳሌም ጉዞ
ጀምራለች፡፡

+በመንገዷም ላይ ሰውን የሚበሉ ወደ ሚኖሩበት አካባቢ
በመድረስ እነርሱም እርሷንና 60 የሚሆኑ አገልጋዮችዋን
ዓይኖቻቸውን በጉጠት በማውጣት ለ4 ወራት በጨለማ
ቤት ውስጥ ዘግተውባቸዋል፡፡ ከአራት ወር በኋላም በዓል
አድገው ለመብላት ከቤት ቢያወጧቸው መልካቸው እንደ
ፀሐይ የሚያበራ ቢሆንባቸው "አንቺ ሴት ምንድን ናችሁ?"
ብለው ጠይቀዋታል፡፡

+እርሷም ክርሰቲያን መሆናቸውንና እነሱ የስላሴ ሕንፃ
የሆነውን የሰውን ልጅ መብላት እንደሌለባቸው
ብትመክራቸው "ምን አንብላ?" ብለዋታል፡፡ እርሷም
ከራማ ኪዳነ ምህረት ስትነሳ የእህል ዘርን በአገልጋዮቿ
አሲዛ ነበርና ስንዴውን በአንድ ቀን ዘርታ: በቅሎ: ታጭዶ:
ደርቆ: ተፈጭቶ ለምግብነት በቅቷል፡፡

+እርሷ ቀምሳ ብታቀምሳቸው እንደማር እንደ ወተት
የሚጣፍጥ ሆኖላቸው በደስታ ተመግበውታል፡፡ ከዚያም
እንደዚህ እያደረጉ እየሰሩ እንዲበሉ አስተምራ: አስጠምቃ
ከ6 የሚበልጡ አብያተ ክርስቲያናትን አስተክላላቸዋለች፡፡

Показано 20 последних публикаций.