🙏ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🙏


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Эзотерика


ገና እንዘምራለን እንደ መላእክቱ
ብርሃንን ለብሰን ገና እንዘምራለን
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርሰቲያን አሰተምሮ ና ሰርአት የጠበቁ
✥👉መንፈሳዊ ትምህርቶች
✥👉መንፈሳዊ መዝሙሮች
✥👉መንፈሳዊ ንግሰ እናሳዉቃለን
✥👉መንፈሳዊ ምክር ነክ ፁሁፍ
✥👉መንፈሳዊ ታሪኮች

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Эзотерика
Статистика
Фильтр публикаций


✝️የእናታችን_የአማላጃችን_የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ከፅንሰት እስከ ትንሣኤዋ ያሉት እውነታዎች:- ✝️
-  ነሐሴ ፯ ተፀነሰች ።
-  ግንቦት ፩ ተወለደች ።
-  ታህሣስ ፫ ወደ ቤተመቅደስ ገባች።
-  መጋቢት ፳፱ ቀን አምላክን በድንግልና ፀነሰች ።
-  ታህሣስ ፳፱ ቀን አምላክን በድንግልና ወለደች ።
-  የካቲት ፲፮ ቀን ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከአምላካችን ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ የምህረት ቃል ኪዳን ተቀበለች (ኪዳነ - ምህረት)
-  ጥር ፳፩ ቀን በክብር አረፈች ።
-  ነሐሴ ፲፬ ቀን በክብር ተቀበረች ።
-  ነሐሴ ፲፮ ቀን እንደ ልጅዋ ትንሣኤ ተነስታ በክብር አረገች ።

ክብር ምስጋና ለቅድስት ድንግል ማርያም

እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )


✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️

✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


🗓 #ነገ ማለትም
#ዕለት:- ረቡዕ
      #ቀን:- ጥር ፳፩ ፳፻፲፯(21/5/17) ዓ.ም
በቅድስት ቤተክርስቲያናችን

እመቤታችን በዓለ ረፍት✅
ነቢዩ ኢዩኤል፣ አቡነበትረ ማርያም፣ ቅድስት ሔራኒ፣ ጻድቁ ቆጵርያኖስ


አክብረን እና አስበን እንውላለን:

እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )


✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️

✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


✝️የኔ መሃሪ ✝️

የኔ መሀሪ ሁሉን መርሻዬ
ሁሉን መርሻዬ
እንደ ህልም አልፏል ትናንትናዬ
ባንተ ጌታዬ...(2)

አዝ.....
      አዳፋው ልብሴ ከነፃ
      ከእዳ ከፈታኝ በነፃ
      የፅድቁ ባሪያው ሆኛለው
      ሳገለግለው ኖራለው።
                የእንባ ዘለላን ያቀፈው
                አይኔም እልልታ ተረፈው
                ደልዳዩ መዳፍ ደርሶሎኝ
                ተራራው ሜዳ ሆነልኝ።
አዝ.....
     አይኖቼን ከጉድ ጋርዶልኝ
     ክንዶቼን በእጁ ይዞልኝ
     ከእግሬ በታች ነው ወጀቡ
     አሁን ታይቶኛል ወደቡ።
                   ሰላም ይነፍሳል ዙሪያዬ
                   እረፍት ሆኖልኝ ጌታዬ
                   የባረከኝን ባርኬ
                   ተለወጠልኝ ታሪኬ።
አዝ.....
   ብርሃንህ ገፏል ድቅድቁን
   በልቤ ተክሏል ሰንደቁን
   ተቆጣጥሮኛል መውደዱ
   መንገዴ ሆኗል መንገዱ።
                    ያበቃው ነገር ቀጥሏል
                   ጭንቄ በሞቱ ተሰቅሏል
                    የእየሱስ ሆኜ ምን አጣሁ
                    ሁሉን በስሙ ተወጣሁ።
አዝ.....
       እንደኔ ማንን ታግሷል
       ይቅርታ ፍቅሩን አልብሷል
      ማይገባኝን አድርጎ
       ያሳለፈልኝ ሸሽጎ።
               መልካም ነው ለኔስ መልካም
               ፀጋው ያገዘኝ ስደክም
               ሞትኩኝ ስል ምህረት ደርቦ
               አቆመኝ በህይወት አስዉቦ።

✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️

✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


የአባ ዝሑራ ፣ የአባ ባሱራ እና የእናታቸው የኔራ ሥጋ ለመጀመርያ ግዜ ያገኘው ማነው?
Опрос
  •   ሀ. የኮሞል ንጉሥ
  •   ለ. የንጉሱ ወታደር
  •   ሐ. የቄሱ ሚስት
  •   መ. ሁሉም
20 голосов


✝️ይተካል እግዚአብሔር✝️

ይተካል እግዚአብሔር አገልጋይ ለቤቱ
ከዛሬው የሚልቅ የማይዝል ጉልበቱ
አይሰስትምና ፀጋን በማካፈል
ብርቱ ውን ያስነሳል ከትውልዱ መሃል (፪)

የሙሴ በረከት ደርሶዋል ለኢያሱ
አምላክ በቃ ብሎ ሊጣራው ወደርሱ
ኢያሱን አቆመው በበረታ ጸጋ
የነገስታት ንጉሥ አልፋና ኦሜጋ (፪)

መጎናጸፊያውን ለኤልሳ ትቶለት
ኤሊያስ ቢኤድም ቢነጠቅ በእሳት
እጥፍ ድርብ ጸጋ ከሁሉ የሚልቅ
አምላክ ስለ ሰጠው ፈጽሞዋል ድንቃድንቅ (፪)

እኔ ብቻ በቀር ማነው ያለው ሌላ
ትጉን አገልግሎት ዝናሩ ያላላ
እንዲ አትበሉ እግዚአብሔር ዘገየ
ይሾማል ለቤቱ ጠላት ዓይኑ እያየ (፪)

ቀድሰን ዘምረን ወንጌሉን መስክረን
ወደ ሰማዩ ቤት ደሞ እኔዳለን
እግዚአብሔር ያስነሳል ዳግም እንደገና
ዘመኑ የዋጀ እጅጉን የጸና (፪)


ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ

✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️

✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


🗓🌹ወር በገባ ነገ በ17 ቅዱስ እስጢፋኖስ ❤️

"እስጢፋኖስ ማለት የግሪክ ቋንቋ ሲሆን ትርጓሜውም «አክሊል»ማለት ነው።ቅዱስ እስጢፋኖስ በግሪክ ሀገር እንደተወለደ የሚነገርለትና ከክርስቶስ እርገት በኋላም አስራ ሁለቱም ሐዋርያት በጋራ ተሰብስበውና ለአገለግሎት ከመረጡዋቸው ሰባት ዲያቆናት አንዱና ዋነኛው ነበር። ሕዝቡን በማዕድ ያገለግሉ ዘንድ ሰባት ዲያቆናት ተመርጠዋል።


        🌿❤️ ከእነዚህ መካከል ቅዱስ

እስጢፋኖስ አንዱ ሲሆን ለስድስቱ ዲያቆናት ደግሞ አለቃ ሊቀ ዲያቆን ሆኖ ተሹሟል። ቅዱስ እስጢፋኖስ በማዕድ አገልግሎት ሕዝቡን ከማገልገሉ በተጨማሪ ወንጌልን ይሰብክ ነበር ። ተዐምራትን የማድረግ ጸጋም ተሰጥቶት ነበር በዚህም አገልግሎቱ ብዙዎችን ወደ ክርስትና መልሷል።

        🌿❤❤️ በዚህም አይሁድ በቅናት ተነሳስተው በሐሰት ከሰሱት ከከተማውም ወደ ውጭ አውጥተው ቄዳር በተባለ ቦታ በድንጋይ ወገሩት በሚወግሩትም ጊዜ ሰማያት ተከፍተው ምሥጢረ ሥላሴን እግዚአብሔርን በሦስትነቱ ተመለከተ።


         🌿❤️ ኢየሱስ ክርስቶስንም በአብ

ቀኝ ተቀምጦ አየ ። ለሚወግሩትም ሰዎች ከአምላኩ እንዲህ በማለት ምሕረትን ለመነ «ጌታ ሆይ ይህንን ኃጢአት አትቁጠርባቸው» በመጨረሻም «ጌታ ኢየሱስ ሆይ ነፍሴን ተቀበል»ብሎ ነፍሱን ሰጠ


           🌿❤️ ከከተማም ወደ
ውጭ
አውጥተው ወገሩት። ምስክሮችም ልብሳቸውን ሳውል በሚሉት በአንድ ጎበዝ እግር አጠገብ አኖሩ። እስጢፋኖስም። ጌታ ኢየሱስ ሆይ፥ ነፍሴን ተቀበል ብሎ ሲጠራ ይወግሩት ነበር። ተንበርክኮም። ጌታ ሆይ፥ ይህን ኃጢአት አትቍጠርባቸው ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህንም ብሎ አንቀላፋ። ሳውልም በእርሱ መገደል ተስማምቶ ነበር። 《የሐ ሥራ 7፥58

—60》

🌿✨ የቅዱስ እስጢፋኖስ ረድኤት በረከትና ምልጃው አይለየን ለዘለዓለሙ አሜን🙏✝️


✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️

✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


🗓✞ ተመስገን

ተመስገን /3/ ለምስጋና ስላሰባሰብከን
እግዚአብሔር ተመስገን /2/


ሁሉን ስሰጠን ያለ ዋጋ ነው
ግን ምንዘምረው ተደርጎልን ነው
በነፃ አይደለም የምናዜምልህ
ተቀብለን ነው ወስደን ነው ከእጅህ
ተመስገን ነው የአንተ እጅ ሲሰጥ
ተመስገን ነው ሰቶ እንዳልነበር ነው
ተመስገን ነው የዃላን አይሰፍርም
ተመስገን ነው ወስዶ ነበር አይልም

አዝ----------------

ለሁሉም ፀሐይ ቀን የምታወጣ
ድሃን አትንቅም ገንዘብ ስላጣ
ባይኖረው እንኳን በአንተ ይኖራል
ቆርሰህ ስሰጠው ተመስገን ይላል
ተመስገን ነው ክብርህ አይጓደል
ተመስገን ነው በሰማይ በምድር
ተመስገን ነው የድሃ አደጉ አባት
ተመስገን ነው ደጉ እግዚአብሔር

አዝ----------------

ውጊያን ለራስህ ለእኛ ድል ሰተህ
ከክብር ሰገነት ታኖረናለህ
ጠላት እያየ ዘይት የምትቀባ
ፅኑ ግንብ ነህ መጠጊያ አንባ
ተመስገን ነው በመልካምነትህ
ተመስገን ነው ያላሰብከው ማነው
ተመስገን ነው ከአንተ ያገኘነውን
ተመስገን ነው ቆጥረን አንጨርሰው

አዝ----------------

በስደት ሀገር ወተን እርቀን
አንተን ለመማር ሰበሰብከን
የእኛ የምንለው ባይኖረን እኛ
አንተ አለኸን ብርቱ መፅናኛ
ተመስገን ነው በማለዳ አውጥተህ
ተመስገን ነው ሰርክ የምትመልስ
ተመስገን ነው መልካም እረኛነህ
ተመስገን ነው ኢየሱስ ክርስቶስ

አዝ----------------

በጌታ ድጋፍ የቆመ ሰው
ምድር ገፍትራ ጠልፋ አትጥለው
የሺውን ታሪክ በቀን ይሰራል
ሁሉን በሚችል ሁሉን ይችላል
ተመስገን ነው ሌላ ምን ይባላል
ተመስገን ነው ለአንተ ምን ይሰጣል
ተመስገን ነው ሁሉን አሳለፍከው
ተመስገን ነው አዲስ አደረከው

                  መዝሙር   
       ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ


✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️

✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


🗓 ነገ ማለትም
ዕለት:- ረቡዕ
#ቀን:- ጥር ፲፬ ፳፻፲፯ ዓ.ም
በቅድስት ቤተክርስቲያናችን


አቡነ አረጋዊ (አመታዊ)
አባ ጳኩሚስ ፣ ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ፣ አቡነ ተስፋ ጽዮን ፣ ሰማዕቱ አብሮኮሮስ ፣ አባ ዘሚካኤል ፣ ሙሴ ጸሊም


አክብረን እና አስበን እንውላለን

እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )


✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️

✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


ቅዱስ አባት እድራኒቆስ ለእስክንድርያ ስንተኛ ሊቀ ጳጳስ ነበሩ?
Опрос
  •   ሀ. 15
  •   ለ. 31
  •   ሐ. 37
  •   መ. 25


📣✝️እግዚኡ መርሐ✝️📣

እግዚኡ መርሐ ዮርዳኖስ አብጽሐ
/2/
ወበ ህየ ዮሐንስ ወበህየ ፍጹመ ተፈሥሐ /2/

ጌታውን መራና ዮርዳኖስ አደረሰው /2/

በዚያችም ዕለት ዮሐንስ በዚያችም ዕለት ፍጹም ደስ አለው /2/

✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️

✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


🗓ዮሐንስኒ

ዮሐንስኒ ያጠምቅ/4/
በሄኖን /4/ በማዕዶተ ዮርዳኖስ
አዝ

እዩት ትህትናውን     ያጠምቅ
ፅድቁን ተመልከቱ    ያጠምቅ
በባሪያው እጅ ሆኖ   ያጠምቅ
የጌታ ጥምቀቱ         ያጠምቅ
አዝ

አንተ መናኙ ሰው    ያጠምቅ
ቅዱስ ባህታዊ        ያጠምቅ
በእጅህ ተጠምቆ    ያጠምቅ
ኢየሱስ ናዝራዊ      ያጠምቅ
አዝ

ተሰውሮ ሳለ            ያጠምቅ
ከዓለም ተለይቶ       ያጠምቅ
አዋጁን ስሙ አለ    ያጠምቅ
በጉን አሳይቶ           ያጠምቅ
አዝ

ንስሀ እየገቡ                 ያጠምቅ
እየተናዘዙ                    ያጠምቅ
በዮሐንስ ስብከት         ያጠምቅ
ለእግዚአብሔር ተገዙ  ያጠምቅ
አዝ

የሰማዩን ጌታ                    ያጠምቅ
ምድራዊ ሲያጠምቀው   ያጠምቅ
ምሥጢር ተገለጠ            ያጠምቅ
ዓለም ሁሉ አወቀው         ያጠምቅ

ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን

✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️

✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨

10k 1 122 103

    ዘላለም  ሥላሴ   

📣✝️  እንኩዋን ለአጋእዝተ ዓለም ሥላሴ  ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ  ✝️📣


❝ በሥላሴ ገመድ ፍጹም ታስረናል ፤ ከልባችን በማይነቀል በቅንዋተ ፍቅሩ ተቸንክረናል ፣ እርሱ ወዶናል አይጠላንም። እኛም በእምነት ይዘነዋል አንተወውም። ❞

     [  አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ  ]

❝ እምነታችንም እንዲህ በባሕርይ በመለኮት አንድ ፤ በአካል ፤ በገጽ ሦስት ብለን ነው፡፡ እነዚህ በቅድምና የነበሩ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ናቸው፡፡ አስቀድመን መላልሰን እንደ ተናገርን ቀዳማዊ ወልድ ሰው ስለ መሆኑና ስለ ቅድስት ሥላሴ የምናምነው እምነት ይህ ነው ፤ ከተማሩ ከሚያስተምሩ ተስፋን ከሚያስረዱ ቅዱሳን ሊቃውንት ለምዕመናን ሁሉ ገልጠን የምናስተምረው ፤ እውነተኛ ሃይማኖትን ከሚያስተምሩ የሰማይ አምላክ ከሾማቸው ከሐዋርያትም ሲያያዝ የመጣልን እጅ ያደረግነው እምነት ነው፡፡ በንጹሕ ልቡና በአፋችንም በልባችንም በዚህ ሃይማኖት እንመን ፤ ያለ ጥርጥርም በበጎ ግብር በቅን ሕሊና እናስተውል ፤ በዚህ እንድንድን መንግሥተ ሰማያትንም እንድንወርስ እንረዳለን፡፡ ❞

[    ሃይማኖተ አበው   ]


ጥር ፯ [ 7 ]

ሕንጻ ሰናዖርን ማፍረሳቸውና ቅዳሴ ቤታቸው በዓል ይከበራል።

የሰናዖርን ሕንጻ ያፈረሱ ሥላሴ : የኃጢአታችንን ሕንጻም በቸርነታቸው ያፍርሱልን አሜን በእውነት !


✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️

✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


🗓ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ

ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ /2/
ተጠምቀ ሰማያዊ በእደ መሬታዊ /2/

አምላክ ሆይ ሕዝቦችህ ዳኑ በጥምቀትህ
አምላክ ሆይ ሕዝቦችህ ዳኑ በልደትህ

አምላክ ሆይ ሕዝቦችህ ዳኑ በልደትህ
አምላክ ሆይ ሕዝቦችህ ዳኑ በጥምቀትህ

#ለባለ ማህተቦች ሼር ያድርጉ ↗️
📣📣📣📣📣📣📣
#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ
📣📣📣📣📣📣📣


​​
እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ከዘጠኙ ንዑሳን በዓላት አንዱ እና የመጀመሪያው የሆነው ለበዓለ ግዝረት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን

                          
 
✝️"በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
                       
                   ጥር 6
  ❤️  
              
በዚች ቀን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ። ክርስቶስ በሥጋው ወደ ቤተ ግዝረት በመግባት የኦሪትን ሕግ ፈጸመ ልሳነ ዕረፍት ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "ጌታ ክርስቶስ በሥጋው ግዝረትን ተቀበለ ለአባቶች የተሰጠውን ቃል ኪዳን ይፈጽም ዘንድ" ብሎ እንደተናገረ። ለብዙዎችም ጌታችን ወደ ቤተ ግዝረት እንዳልገባና እንዳልተገረዘ ይመስላቸው ነበር እነርሱ እንዳሰቡት ሁኖ ቢሆን ኑሮ አይሁድ ታላቅ ምክንያትን የሚያገኙ በሆኑ ነበር ጌታችን ግን ግዝረትን ሕግ ፈጸመ ለእኛ በግዝረት ፈንታ የክርስትና ጥምቀትን ሰጠን የፋሲካውንም ቂጣ በላ በእርሱም ፈንታ ሥጋውንና ደሙን ሰጠን።

የከበረ ወንጌል "ስምንተኛው ቀን በተፈጸመ ጊዜም ሕፃኑን ሊገዝሩት ወሰዱት ሳትፀንሰው መልአኩ እንዳወጣለት ስሙን ኢየሱስ አሉት" እንዳለ ንጽሕት ድንግል እመቤታችን ማርያም ጻድቅ አረጋዊ ዮሴፍን "እንደ ሕጉ ልጄን እንዲገርዘውና ስሙንም እንድንሰይመው ብልህ የሆነ ገራዥ ሰው አምጣልኝ" አለችው። ዮሴፍም ሔዶ የሚገርዝ ባለሙያ አመጣ ያ ባለሙያም ሕፃኑን ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስ በእናቱ በንጽሕት ድንግል ማርያም ክንድ ላይ አየው "እንድገርዘው ሕፃኑን በጥንቃቆ ያዙት" አላቸው። ሕፃን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ መልሶ እንዲህ አለው "ባለሙያ ገራዥ ሆይ ደሜ ሳይፈስ ትገርዘኝ ዘንድ ትችላለህን በዚያች ዕለት ካልሆነ በቀር ደሜ አይፈስምና ጐኔን በጦር ሲወጉኝ ያን ጊዜ ውኃና ደም ይፈሳል ለአዳምና ለሚያምኑ ልጆች መድኃኒት ይሆናል"።

የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረውን ያ ባለሙያ በሰማ ጊዜ አደነቀ ዕቃውንም ሰብስቦ ተነሥቶ ከሕፃኑ ጌታ እግር በታች ሰገደ ያንጊዜም ምላጮቹ በእጆቹ ላይ ቀልጠው እንደ ውኃ ሆኑ የከበረች ድንግል እመቤታችን ማርያም "ከሴቶች ተለይተሽ አንቺ የተባረክሽ ነሽ የማሕፀንሽ ፍሬ የተባረከ ነው ይህ ልጅሽ ስለርሱ ነቢያት ትንቢት የተናገሩለት የሕያው አምላክ ልጅ ነው" አላት።

ሕፃኑም ለዚያ ባለሙያ ዳግመኛ መልሶ እንዲህ አለው "እኔ ነኝ ትገዝረኛለህ ወይስ ተውክ ወይም ያባቶቼ አባቶች እንዳደረጉ እኔ ላድርግ" ያም ባለሙያ "የአባቶችህ አባቶች እነማን ናቸው?" አለው ሕፃን ጌታችንም "አብርሃም፣ይስሐቅ ያዕቆብ የሕዝቡ ሁሉ አባቶች የሆኑ ናቸው ለእነርሱም ይህ ግዝረት አስቀድሞ ከአባቴ ዘንድ ተሰጣቸው" ባለሙያውም "እኔ ከአንተ ጋር እናገር ዘንድ አልችልም በአንተ ህልውና መንፈስ ቅዱስ አለና" አለው። በዚያንም ጊዜ ሕፃኑ ጌታችን ዐይኖቹን ወደ ሰማይ አቅንቶ "አባት ሆይ ለአብርሃም፣ለይስሐቅ ለያዕቆብ አስቀድሞ ግዝረትን የሰጠሃቸው ያቺን ግዝረት ዛሬ ለእኔ ስጠኝ" አለ። ያን ጊዜ ያለ ሰው እጅ በሕፃኑ ሥጋ ላይ ግዝረት ተገለጠች።

ድንግልናዋ ሳይለወጥ ከድንግል ማሕፀን እንደ መውጣቱ የጌታችን ግዝረቱ የማይመረመር ሆነ እንዲሁ ወደ ሐዋርያት በተዘጋ አዳራሽ መግባቱና መውጣቱ እንደማይመረመር እንዲሁ እንደ ፈቀደ ከረቀቀ ጥበቡ ችሎታውን በመገረዝ ከሥጋው ምንም ምን ሳይቆረጥ ገለጠ። አዳምንና ልጆቹን ያድናቸው ዘንድ በፈቃዱ ከጐኑ በመስቀል ላይ የሚፈሰው ደምና ውኃ ካልሆነ በቀር ብዙም ሆነ ጥቂት ሊሆን አይችልም እርሱ በፈቃዱ ሕጉ እንዲፈጸም አስቀድሞ አዘዘ እንጂ።

ያም ባለሙያው ገራዥ ይህን ተአምር ባየ ጊዜ የሕፃኑንም ነገር በሰማ ጊዜ እጅግ አደነቀ የክብር ባለቤት ከሆነ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እግር በታች ሦስት ጊዜ ሰገደና "በእውነት አንተ የእግዚአብሔር ልጅ የእስራኤልም ንጉሥ ነህ" አለው። ከዚህም በኋላ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተአምራቱ ያየውንና የሰማውን እየተናገረ ወደ ቦታው ሔደ።

ለእርሱም ለጌታችን ከቸር አባቱ ጋራ ማሕየዊ ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ጋራ ክብር ምስጋና ስግደትም ይሁን ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን። 🙏❤️

ዳግመኛም ጥር ስድስት
የቅዱስ ኤልያስ በእሳት ሰረገላ ያረገበት
የቅዱስ ኖኅ በዓለ ዕረፍቱ
የቅዱስ ባስልዮስም በዓለ ዕረፍቱ ነው።

የቅዱሳን አምላክ በቅዱሳኖቹ አማላጅነት ይማረን ይቅርም ይበለን🙏❤️

ምንጭ፡- የጥር 6 ስንክሳር

                         
✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️

✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


🗓ጥር ፭ /5/

በዚች ቀን በከሀዲው ዑልያኖስ ዘመን የከበረ አውስግንዮስ ምስክር ሁኖ ሞተ።

ይህም ቅዱስ አውስግንዮስ እድሜው መቶ ዐሥር ዐመት እስከ ሆነው ከቈስጠንጢኖስና ከልጆቹ ዘመነ መንግሥት በኋላ እስከ ከሀዲው ዑልያኖስ ዘመን ኖረ።

በአንዲት ዕለትም በአንጾኪያ ከተማ በአደባባይ ውስጥ ወዲያ ወዲህ ሲመላለስ ሁለት ሰዎች እርስ በርሳቸው ሲጣሉ አግኝቷቸው ሊአስታርቃቸውና በመካከላቸው ሰላም ሊያአደርግ ወዶ አስታረቃቸው በመታረቃቸውም ደስታ አደረጉ እርሱ የከበረ አረጋዊ ሰው ነውና።

ከዚያም አንድ ክፉ ሰው ወደ ንጉሥ ዑልያኖስ ሒዶ ነገር ሠራበት እንዲህም አለው አውስግንዮስ በራሱ ፈቃድ ገዥና ፈራጅ ዳኛ ሆነ። ንጉሥም ይህን ቅዱስ ወደርሱ አቅርቦ ገሠጸው ገዥና ፈራጅ ዳኛ አድርጎ የሾመህ ማነው አለው።

የከበረ አውስግንዮስ መልሶ ነፍስህ በእጁ የተያዘች የእግዚአብሔርን አምልኮት ትተህ አንተ ለረከሱ ጣዖታት ለምን ሰገድክ ከአንተ በፊት የነበሩ ነገሥታትን ለምን አልተከተልካቸውም እኔም እንዳንተ ወታደር ሁኜ ከቈስጠንጢኖስ ጋር ሃያ ዓመት ኖርኩ ከልጆቹም ጋር ነበርኩ ከእነርሱ ውስጥ እንዳንተ ያለ ጠባየ ክፉ የለም አለው።

ዑልያኖስም በቅዱስ አውስግንዮስ ላይ እጅግ ተቆጣ ይሰቅሉት ዘንድ በጐኖቹም ውስጥ መብራቶችን አስገብተው እንዲለበልቡት አዘዘ እርሱም ስለ ክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይህን ሁሉ ታገሠ።

ማሠቃየቱንም በሰለቸ ጊዜ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ወታደሮችም ሊቆርጡት በመጡ ጊዜ እስኪጸልይ ይታገሡት ዘንድ ለመናቸው ጸሎቱንም ሲፈጽም የከበረች ራሱን ቆረጡት የምስክርነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር

 ✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️
✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


'' መልአኩም እንዲህ አላቸው፦ እነሆ፥ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤  ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።'' - ሉቃስ 2÷10

እንኳን ለጌታችን እና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ🙏


🗓" |አዳም ከመሬት ተወለደ፤ ሔዋን ከአዳም
ጎን ተወለደች፤ ቃየል ከአዳምና ሔዋን ተወለደ። ሦስቱ አልጠቀሙኝም። #እኔ_የተጠቀምኩት_ክርስቶስ_ከድንግል_በመወለዱ ነው። "


#አባ_ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ |(1357-1417)
             #መልካም ገና /ጌና

ታኅሳስ 28/2017 ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጲያ

 ✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️
✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


🗓✞ ፍቁረ እግዚእ ዮሐንስ

ፍቁረ እግዚእ ዮሐንስ (2)
ምስክሩ ነህ የኢየሱስ
ባማረው ቃልህ ልቤን አድስ


ጌታ የሚወደው ትሁት ወንጌላዊ
ምድራዊ አይደለ ክብሩ ሰማያዊ
በወንጌል የተካ የአሣውን መረብ
አደገ በፊቱ ተሞልቶ በጥበብ

አዝ----------------

ወንጌል ናት ሕይወቱ የተሰወረባት
በርሷ እየነደደ ለአለም ያበራባት
ተነጥፎ ያነባ በአምላኩ ፍቅር
ሳለው በውስጣችን የወንጌልን ክብር

አዝ----------------

የአይሁድ ጭካኔ ቢወራ ቢነገር
ከእራት ብቻ አይደለም ቀራንዮም ነበር
ፊቱን አላዞረም በዚያች የጭንቅ ቀን
ዮሐንስ አልቻለም በጌታው መጨከን

አዝ----------------

አምደ ቀራንዮ ከአስራ ሁለቱ አንዱ
አስራ አንዱ ሸሽተው በመንገድ ሲሄዱ
ዮሐንስ ነው ስሙ ጅራፍ ያላሸሸው
የክርስቶስ ፍቅር ውስጡን ያሸነፈው

አዝ----------------

ከአይሁድ ዛቻ ይልቅ ፍቅሩ ይሰማዋል
ገዳዮቹን ሊያድን ለሚሞተው አዝኗል
እንዲህ ያለ ፍቅር ለማንም የለውም
አለና ጻፈለት ብዕር ባይችለውም

ዘማሪት ቅድስት ምትኩ

 ✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️
✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


🗓❤ከዕለቱ መዝሙር

#መዝሙረ ዳዊት 69

  አቤቱ፥ እኔን ለማዳን ተመልከት፤ አቤቱ፥ እኔን ለመርዳት ፍጠን።
  ነፍሴን የሚሹአት ይፈሩ ይጐስቍሉም፥ ክፉንም የሚመክሩብኝ ወደ ኋላቸው ይመለሱ ይፈሩም።
  እንኳ እንኳ የሚሉኝ አፍረው ወዲያው ወደ ኋላቸው ይመለሱ።
  የሚሹህ ሁሉ በአንተ ሐሤት ያድርጉ ደስ ይበላቸው፤ ማዳንህን የሚወድዱ ሁልጊዜ፦ እግዚአብሔር ታላቅ ነው ይበሉ።
  እኔ ችግረኛና ምስኪን ነኝ፤ አቤቱ፥ እርዳኝ፤ ረዳቴ ታዳጊዬም አንተ ነህ፤ አቤቱ፥ አትዘግይ።

          እንኳን ለጻድቁ፣ለየዋሁ፣ለደጉ፣ለብእሴ #እግዚአብሔር ለቅዱስ #ዳዊት በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሳችሁ!!!የቅዱስ #ዳዊት በረከቱ ይደርብን!!!

        


 ✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️
✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


🗓✞ ወደ አንቺ የመጣው ✞

ወደ አንቺ የመጣው በብሩህ ደመና
ከሦስቱ አካል አንዱ ክርስቶስ ነውና
የጠፋ በግ አዳም ታደሰ በጌታ
በአንቺ ተፈጸመ የሰው ልጆች ደስታ(፪)


        አዝ

በደይን የተጣለች ሔዋን ተደሰተች
የደስታ መፍለቂያ አንቺን ስላገኘች
የበረከት ፍሬ ከአንቺ ተገኘልን
የወይን ቦታ ነሽ ድንግል እናታችን

        አዝ

ወልድም ባሕርይሽን ባሕርይ አድርጎት
ለፍጥረታት ጌታ መዓዛሽ ተስማምቶት
ከአንቺ ይወለድ ዘንድ ፍጹም ሊላላክሽ
በጥቂት አደገ ተልኮና ታዞሽ

        አዝ

ከድንግልና ጋር አንድ የኾነ ሐሊብ
በሩካቤ ሳይሆን በብሥራት እንደ ንብ
ከሆድ መጥበብ ጋር የመለኮት ስፋት
አንቺ ኾነሽ ሳለ ታናሿ ሙሽሪት

        አዝ

በፍጡር ሕሊና የማይመረመር
ዕጹብ ነው ድንቅ ነው የመፅነሷ ነገር
እሳተ ነበልባል በሆድሽ ውስጥ ሲያድር
ነደ ነበልባሉ አልፈጀሽም ነበር

             መዝሙር|
        የአእላፋት ዝማሬ


የአእላፋት ዝማሬ መዝሙር ጥናት
ለሁሉም ሼር በማድረግ አዳርሱ
!

✝️ለባለ ማህተቦችሼር ያድርጉ↗️
✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨

Показано 20 последних публикаций.