ሌዋንዶዎስኪ"ጦርነት ከየትኛውም ስፖርት በተቃራኒ የሚቆም ነገር ነው" ሲል ተናገረ
የባየር ሙኒኩ ፖላንዳዊ ኢንተርናሽናል አጥቂ ሮበርት ሌዋንዶዎስኪ ከሰሞኑ ሩሲያ በዩክሬን ላይ የከፈተችውን ጦርነት ተከትሎ "ጦርነት ከየትኛውም ስፖርት በተቃራኒ የሚቆም ነገር ነው" ሲል ተናገረ።
ጦርነቱ በቶሎ እንዲቆምም ሁሉም አካላት የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ጥሪውን አቅርቧል።
ሁለቱ ሀገራት ባለፋት ጥቂት ሳምንታት ከፍተኛ የፖለቲካ ውጥረት ውስጥ መቆየታቸው የሚታወስ ሲሆን በስተመጨረሻም ወደ ጦርነት ለማምራት ተገደዋል።
በሌላ በኩል የማንቺስተር ሲቲው አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ዩክሬናዊው የቡድኑ የክንፍ ተጫዋች ዚንቼንኮ የሩሲያውን ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አስመልክቶ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ካሰፈረው አነጋጋሪ ጽሁፍ ጋር ተያይዞ ተቃውሞ እንደሌለው አስታውቆ ተጫዋቹ በዚያ ቤተሰብ ያለው መሆኑን ተከትሎ እንዲህ ያለው አስተያየት መስጠቱ እንዳላስገረመው ተናግሯል።
የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ሩሲያ በዩክሬን ላይ የከፈተችውን ጦርነት ተከትሎ በዚህ አመት በሴንት ፒተርስበርግ ሊካሄድ የነበረውን የሻምፒየንስ ሊግ ፍጻሜ ጨዋታ በትላንትናው እለት በጠራው አስቸኳይ ስብስባ ወደ ፓርክ ደ ፕሪንስ መቀየሩን ማስታወቁ ይታወሳል።
@ETHIO_BAYERN_MUNICHET@ETHIO_BAYERN_MUNICHET